en
Feedback
አንድ ጥምቀት አንድ ሐይማኖት

አንድ ጥምቀት አንድ ሐይማኖት

Closed channel
3 156
Subscribers
No data24 hours
-87 days
-5330 days
Posts Archive
አሜሪካ በኢትዮጵያ ላይ የምታደርገውን ያልተገባ ጫናና ጣልቃ ገብነት የሚቃወም ሰልፍ በዋሺንግተን ዲሲ ዋይት ሃውስ ፊት ለፊት ተካሄደ። ባሕር ዳር፡ ሕዳር 20/2014 ዓ.ም (አሚኮ) "የበቃ ወይም #NoMore" ዘመቻ አካል በሆነው ሰላማዊ ሰልፍ በዋሺንግተን ዲሲ፣ ሜሪላንድና ቨርጂንያ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን፣ ትውልደ ኢትዮጵያውያን፣ ኤርትራውያንና የኢትዮጵያ ወዳጆች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡ ሰልፈኞቹ የባይደን አስተዳደር በኢትዮጵያና ኤርትራ ላይ እየተከተለ ያለውን የተሳተተ የውጪ ጉዳይ ፖሊሲ እንዲያስተካክልና ጣልቃ ገብነቱን እንዲያቆም ጥሪ የሚያደርጉ መልዕክቶች አስተላልፈዋል። ሰልፈኞቹ በአሸባሪው የሕወሓት ቡድን በኢትዮጵያ ላይ የከፈተውን ጥቃት የሚያወግዙና ለኢትዮጵያ አጋርነታቸውን የሚያሳዩባቸው መፈክሮችም አሰምተዋል። በሰላማዊ ሰልፉ ላይ የዳያስፖራ ማኅበረሰብና የሲቪክ ተቋማት ተወካዮች፣ የአሜሪካ ዜግነት ያላቸው አፍሪካውያንና ሌሎች የኢትዮጵያ ወዳጆች ንግግር አድርገዋል፡፡ የባይደን አስተዳደር በኢትዮጵያ ላይ የሚከተለውን የውጪ ጉዳይ ፖሊሲ እንዲያስተካልና ጣልቃ ገብነቱን እንዲያቆም ጫና ለማድረግ ሰላማዊ ሰልፉ በዋሺንግተን ዲሲ በቋሚነት በየሳምንቱ እንደሚካሄድ ተገልጿል። በአሜሪካ ዋሺንግተን ዲሲ እየተካሄደ ያለው ሰላማዊ ሰልፍ ሰላምና አንድነት ማኅበር የዋሺንግተን ዲሲ ግብረ ኀይል ከ "በቃ ወይም #NoMore" ዘመቻ አስተባባሪዎች፣ ከተለያዩ ተቋሞችና አገር ወዳዶች ጋር በመተባባር ያዘጋጁት ነው። አሜሪካን ጨምሮ ምዕራባውያን አገራት በኢትዮጵያ ላይ የምታደርገውን ጫና የሚቃወም ሰላማዊ ሰልፍ በተለያዩ ሀገራት ከተሞች እየተካሄደ መሆኑ ይታወቃል። #ተነሳ!! #መሪህን ተከተል!! #ሀገርህን አድን!! #ነፃነትህን አትስጥ !! #አካባቢህን ጠብቅ!!

ከጥንት እስከ ዛሬ የድል አብሪ ኮከቦች – ኢትዮጵያውያን https://www.amharaweb.com/ከጥንት-እስከ-ዛሬ-የድል-አብሪ-ኮከቦች-ኢት/ ባሕር ዳር፡ ሕዳር 19/2014 ዓ.ም (አሚኮ) ኢትዮጵያ ከቅድመ ክርስቶስ ልደት በፊት በቀጣናው ገናን እና ከግብጽ ደቡባዊ ግዛት እስከ ህንድ ውቅያኖስ የሚደርስ ማንነት እና ግዛት የነበራት ታላቅ ሀገር እንደነበረች የታሪክ መዛግብት ያሳያሉ፡፡ የተወሰኑትን እንኳን ብንጠቅስ ከክርስቶስ ልደት በፊት 1 ሺህ አንድ መቶ ዓመታት በላይ የነበረው ዳዊት በመዝሙሩ ኢትዮጵያ ብሎ የሚጠቅሳት ሀገር ጠንካራ እና የተደራጀ ሥዓርተ መንግሥት [...]

“ትልቁ ጉዳይ ሀገራችን” የተሰኘ የባለሀብቶች ኮሚቴ ለወገን ጦር ከ4 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ድጋፍ አደረገ። ሕዳር 10/2014 ዓ.ም (አሚኮ) መሠረቱን ወሎ ያደረገው “ትልቁ ጉዳይ ሀገራችን” የተሰኘ የባለሀብቶች ኮሚቴ በወሎ ግንባር ሽብርተኛውን የትግራይ ወራሪ ኃይል እየደመሰሰ ለሚገኘው የወገን ጦር ከ4 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የምግብ ድጋፍ አድርጓል። ድጋፉን ያስረከቡት የኮሚቴው ሰብሳቢ ቤንቤላ አብዱልቃድር በዚህ ወቅት ከምንም በላይ የሐሳብ አንድነት እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል፡፡ ኹሉም የህልውና ዘመቻውን እንዲደግፍ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ የባለሀብቶቹ ቡድን ከ4 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ቴምር፣ ብስኩት እና ሌሎች ድጋፎችን ያካተተ መሆኑን አስታውቀዋል። ባለሃብቶቹ ወደፊትም የተጠናከረ ድጋፍ እንደሚያደርጉ ቃል ገብተዋል፡፡ ድጋፉን የተረከቡት የደቡብ ወሎ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የግንባሩ የሎጀስቲክስ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ተስፋ ዳኘው ወሎን የወረረውን ሽብርተኛው የትግራይ ወራሪ ኃይልን ለመደምሰስ እየተደረገ ባለው ትግል የአካባቢው ባለሀብቶች ጠንካራ ድጋፍ እያደረጉ መሆናቸውን ገልጸዋል። የወሎና አካባቢው ባለሀብቶች ያደረጉት ድጋፍ የመጀመሪያው አለመሆኑንም አስታውቀዋል። አሸባሪው የትግራይ ወራሪ ኃይል ከምድረ ገጽ እስኪጠፋ ሁሉም ተሳትፎውን አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል፡፡ ዘጋቢ :- ታርቆ ክንዴ ወራሪውን ጠላት ደምስስ! የጀግንነት ታሪክህን ዳግም አድስ! ያለ መስዋእትነት ድል አይገኝም! ነፃነትህን አትስጥ! ተዋርዶ ከመኖር በክብር መሞት ይሻላል! ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡ ዩቱዩብ https://bit.ly

ሸዋ አሸባሪው የትግራይ ወራሪ ኃይልን ፍም ሆኖ እየለበለበው ነው https://www.amharaweb.com/ሸዋ-አሸባሪው-የትግራይ-ወራሪ-ኃይልን-ፍም/ ባሕር ዳር: ሕዳር 05/2014 ዓ.ም (አሚኮ) አሸባሪው የትግራይ ወራሪ ኃይል ወደ ሰሜን ሸዋ ምድር ዘልቆ የመግባት ህልሙ እንደጉም እየበነነ ነው። የክልሉን መንግሥት የክተት ጥሪ ተቀብለው ወደ ግንባር ከዘመቱት የአማራ ሕዝባዊ ሠራዊት መካከል የኤፍራታና ግድም ወረዳ እና የአጣዬ ሚሊሺያዎች ከጀግናው የሀገር መከላከያ ሠራዊት ጋር በመሆን ከፍተኛ ጀብዱ እየፈፀሙ ነው። ወጣት ሃብታሙ ሲሳይ የክተት ጥሪውን ተቀብሎ ዘመቻውን [...]

"ከአማራ አብራክ የወጣችሁ ደም መላሾች የውትድርና ሳይንስን በመላበስ አማራ ከገጠመው የሕልውና አደጋ እንደምታወጡ አልጠራጠርም" ርእሰ መሥተዳድር ዶክተር ይልቃል ከፋለ ሁመራ፡ ሕዳር 04/2014 ዓ.ም (አሚኮ) የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሌጅ በወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሑመራ ዞን የባእከር ጊዜያዊ የፖሊስ ማሰልጠኛ ለ9ኛ ዙር ያሰለጠናቸውን የአማራ ልዩ ኀይል አባላት አስመርቋል። የአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳድር ይልቃል ከፋለ (ዶክተር) እንዳሉት አሸባሪው የትግራይ ወራሪ ኃይል በአማራና በአፋር ክልሎች ወረራ በመፈጸም ንጹሐንን እየገደለ፣ እየደፈረ፣ እያፈናቀለና እየዘረፈ ነው፡፡ ጠላት እያደረሰ ያለው ሰቆቃ የአማራ ሕዝብ ‘ሆ’ ብሎ እንዲነሳ አድርጎታል ብለዋል። "የዛሬ የልዩ ኀይል ተመራቂዎች የአማራ ሕዝብ ለሕልውናው የማይደራደር መኾኑን ማሳያ ትኾናላችሁ ብለን እናምናለን" ነው ያሉት ዶክተር ይልቃል፡፡ ተመራቂ የልዩ ኀይል አባላት ባገኙት የወታደራዊ ሳይንስ ስልጠና ማንኛውንም ችግር በመቋቋም፣ በዓላማ በመጽናት ጠላትን መደምሰስ እንደሚጠብቅባቸው ነው ዶክተር ይልቃል ያሳሰቡት። ርእሰ መሥተዳድሩ "ከአማራ አብራክ የወጣችሁ ደም መላሾች የውትድርና ሳይንስን በመላበስ አማራ ከገጠመው የህልውና አደጋ እንደምታወጡ አልጠራጠርም" ብለዋል። የሚደረገው ትግል የመኖርና ያለመኖር ስለኾነ ብቸኛው መፍትሔ አሸባሪውን ኃይል ማጥፋት ብቻ ነው ያሉት ርእሰ መሥተዳድሩ ከሕዝብ የተሠጣቸውን አደራ ለተመራቂ የልዩ ኀይል አባላት ማስተላለፋቸውን ተናግረዋል፡፡ አሸባሪውን እና ወራሪውን የትግራይ ኀይል በያዛችሁት ትጥቅ በልበ ሙሉነት፣ በጀግንነት እና በወኔ በመደምሰስ ለአማራ ሕዝብ የድል ብስራት እንደሚያሰሙ ጥርጥር እንደሌላቸው ገልጸዋል፡፡ ዶክተር ይልቃል እንዳሉት የአማራ ሕዝብ በጠላት እየተጎሳቆለ፣ እየተገደለ፣ እየተደፈረና እየተዘረፈ በመኾኑ ጠላትን ለማጥፋት ጊዜ መውሰድ እንደማያስፈልግ ተናግረዋል። ተመራቂ የልዩ ኀይል አባላት በጽናት አስፈላጊውን ኹሉ መስዋእትነት በመክፈል እንደ አባቶቻቸው ኹሉ ጠላትን በመቅበር በታሪክ ሊመዘገቡ እንደሚገባ ገልጸዋል። በጽናት፣ በወኔ፣ በአንድነት እና በጀግንነት መንፈስ ጠላትን በአማራ ምድር መቀበር አለበት ብለዋል። ለዚህም መንግሥት በሚችለው አቅም ኹሉ ድጋፍ እንደሚያደርግ አመላክተዋል። ተመራቂዎች በዓላማ ጸንተው ከወገን ኃይል ጎን በመሰለፍ በሚደረገው አውደ ውጊያ ድል በማድረግ የአማራንና የኢትዮጵያን ሕዝብ ታሪክ ማደስ እንደሚገባ አሳስበዋል። ዘጋቢ:- ቡሩክ ተሾመ- ከሑመራ ባእከር ወራሪውን ጠላት ደምስስ! የጀግንነት ታሪክህን ዳግም አድስ! ነፃነትህን አትስጥ! ተዋርዶ ከመኖር በክብር መሞት ይሻላል! ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡ ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq በዌብሳይት amharaweb.com ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m

በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በጭና እና ቦዛ በአሸባሪው የትግራይ ወራሪ ኃይል ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች ድጋፍ አደረጉ፡፡ ደባርቅ: ሕዳር 03/2014 ዓ.ም (አሚኮ) በአሜሪካ የሚኖሩት የደባርቅ አካባቢ ተወላጁ አቶ ሙሉነህ ዮሐንስ በአሜሪካ፣ አውሮፓ፣ አውስትራሊያ እና ካናዳ የሚኖሩ ጓደኞቻቸውን በማስተባበር በአሸባሪው የትግራይ ወራሪ ኀይል ጉዳት ለደረሰባቸው የጭናና ቦዛ ነዋሪዎች ከ200 ሺህ ብር በላይ ወጭ የተደረገበት የምግብና አልባሳት ድጋፍ አድርገዋል፡፡ ድጋፉን ለተጎጂዎች ያደረሱት አቶ እሸቱ ፍስሃ በአሜሪካ የሚኖሩት የደባርቅ አካባቢ ተወላጁ አቶ ሙሉነህ ዮሐንስ ከዚህ በፊትም ጓደኞቻቸውን በማስተባበር ለሠራዊቱና ለተፈናቀሉ ወገኖች ድጋፍ ሲያደርጉ መቆየታቸውን ጠቁመዋል፡፡ በዕለቱ ድጋፍ የተደረገላቸው የቦዛ ቀበሌ ነዋሪ አቶ ወንዜ ንጉሤ አሸባሪው የትግራይ ወራሪ ኀይል በደባርቅና ዳባት ወረዳ ወረራ በፈጸመበት ወቅት በአውደ ውጊያው ተሳትፈው መቁሰላቸውን ተናግረዋል፡፡ አቶ ወንዜ ወራሪው ኀይል ከፈጸመው ግድያ ባሻገር በቀበሌው የሚኖሩ አርሶ አደሮችን ሀብትና ንብረት በመዝረፉና በማውደሙ በወቅቱ ከፍተኛ ችግር ውስጥ እንደነበሩ ነው ያስረዱት፡፡ አሁን ላይ በባለሀብቶችና በውጭ የሚኖሩ ወገኖች ድጋፍ እየተደረገላቸው መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ሌላኛዋ ድጋፍ የተደረገላቸው ወይዘሮ አስቴር ዋካ የሽብር ኃይሉ በከባድ መሣሪያ ቤታቸውን ሙሉ በሙሉ ከጥቅም ውጭ እንዳደረገው ተናግረዋል፡፡ ወይዘሮ አስቴር “ጠላት በጭካኔ ቤታችንና ንብረታችንን ቢያወድምብንም በወገኖቻችን ድጋፍ በሕይወት መቆየት ችለናል” ነው ያሉት፡፡ ድጋፍ የተደረገላቸው ተጎጅ ወገኖች ራሳቸውን እስኪችሉ ድረስ መንግሥት ቋሚ የኾነ ድጋፍ እንዲያደርግላቸውም ጠይቀዋል፡፡ ዘጋቢ፡- አድኖ ማርቆስ-ከደባርቅ ወራሪውን ጠላት ደምስስ! የጀግንነት ታሪክህን ዳግም አድስ! ነፃነትህን አትስጥ! ተዋርዶ ከመኖር በክብር መሞት ይሻላል! ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡ ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq በዌብሳይት amharaweb.com ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m

ከህልውና ዘመቻ በተጓዳኝ ኢኮኖሚውን ለማጠናከር የባሕር ዳር ኢንዱስትሪ ፓርክ የመጀመሪያ የጨርቃ ጨርቅ እና አልባሳት ምርቱን ለውጭ ገበያ ማቅረብ ጀመረ፡፡ ባሕር ዳር: ሕዳር 01/2014 ዓ.ም (አሚኮ) የአማራ ክልል መንግሥት በአሸባሪው የትግራይ ወራሪ ኃይል የተፈጸመውን ወረራ ለመቀልበስ እያከናወነ ካለው የህልውና ዘመቻ ባለፈ ምጣኔ ሃብታዊ እንቅስቃሴ እንዳይቀዛቀዝ እየሠራ ይገኛል። ከዚህም መካከል የባሕር ዳር ኢንዱስትሪ ፓርክ የምርት አገልግሎት እንዳይስተጓጎል የጸጥታና ሌሎች ድጋፎችን እያደረገ ነው። በፌዴራል የኢንዱስትሪ ፓርኮች ኮርፖሬሽን ከተቋቋሙት 13 የኢንዱስትሪ ፓርኮች አንዱ ነው የባሕር ዳር ኢንዱስትሪ ፓርክ፡፡ ኢንዱስትሪ ፓርኩ ባለፈው ዓመት ተመርቆ ወደ ሥራ የገባ ሲሆን እስካሁን ለ1 ሺህ 300 ዜጎች ቋሚ እና ጊዜያዊ የሥራ ዕድል ፈጥሯል፡፡ የባሕር ዳር ኢንዱስትሪ ፓርክ የመጀመሪያ የጨርቃ ጨርቅ እና አልባሳት ምርቱን ለውጭ ገበያ ማቅረብ ጀምሯል፡፡ ይህም የክልሉን ብሎም የሀገሪቱን ምጣኔ ሃብት በወቅታዊ ችግር ምክንያት እንዳይጎዳ ያግዛል ተብሏል። በባሕር ዳር ኢንዱስትሪ ፓርክ የማምረቻ ሼድ ወስደው በጨርቃጨርቅ እና አልባሳት ሥራዎች ምርት ከጀመሩ ድርጅቶች መካከል አንዱ (ሆፕ ሉን አፓረን ኢትዮጵያ ፒ.ኤል.ሲ) አንዱ ነው፡፡ ድርጅቱ በጨርቃጨርቅ ምርት ዘርፎች ልብሶችን አምርቶ ለመጀመሪያ ጊዜ ዛሬ ወደ ውጭ ገበያ አቅርቧል፡፡ በሆፕ ሉን አፓረን ኢትዮጵያ ፒ.ኤል.ሲ ከፍተኛ የሰው ሃብት ልማት ሥራ አስኪያጅ አቶ ቡልቲ ሙህየ ድርጅቱ ያመረታቸውን 75 ሺህ ያህል አልባሳት ዛሬ ወደ አሜሪካ እንደሚልክ ገልጸዋል፡፡ ከ570 ሺህ ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሬ እንደሚያስገኝም ነው የተናገሩት፡፡ ድርጅቱ ዛሬ ለውጭ ገበያ ያቀረበው ምርት ላለፉት ስምንት ወራት ሠራተኞቹን ሲያሰለጥን ቆይቶ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ያመረተውን እንደሆነም አቶ ቡልቲ ጠቁመዋል፡፡ በድርጅቱ ውስጥ በቋሚ እና ጊዜያዊነት ተቀጥረው ከሚሠሩት ሠራተኞች መካከል ከ95 በመቶው በላይ ሴቶች መሆናቸውን ነው ሥራ አስኪያጁ የነገሩን፡፡ ኢንዱስትሪ ፓርኩ በሥራ ዕድል ፈጠራ ዙሪያ ያለው አቅም ገና ያልተነካ መሆኑንም አንስተዋል፡፡ በዕውቀት እና በቴክኖሎጂ ሽግግር እንዲሁም በሥራ ፈጠራ ረገድ ባለፉት ወራት አመርቂ ውጤቶች ተገኝተዋል ብለዋል፡፡ በኢትዮጵያ የሚስተዋለውን የውጭ ምንዛሬ እጥረት ለመቅረፍ ፓርኩ አዎንታዊ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ያሉት በኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ኮርፖሬሽን የባሕር ዳር ኢንዱስትሪ ፓርክ ዋና ሥራ አስኪያጅ ወይዘሮ ጥሩየ ቁሜ ናቸው፡፡ የመጀመሪያ ምርቱን ወደ ውጭ መላኩ ለፓርኩ ሠራተኞች ከፍተኛ መነቃቃትን ፈጥሯልም ብለዋል፡፡ ኢንዱስትሪ ፓርኩ በሙሉ አቅሙ ወደ ሥራ ሲገባ ፋይዳው የጎላ ይሆናል ያሉት ዋና ሥራ አስኪያጇ የሥራ ዕድል ፈጠራ፣ የክህሎት ሽግግር እና የውጭ ምንዛሬ ችግሮችን መቅረፍ የኢንዱስትሪ ፓርኩ ተቀዳሚ ዓላማዎች መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡ ወቅታዊው የፀጥታ ሁኔታ በተለይም በውጭ ባለሃብቶች ላይ ተጽዕኖ ፈጥሮ እንደነበር የጠቆሙት ሥራ አስኪያጇ የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር፣ የክልሉ እና የፌዴራል መንግሥት ያደረጉት ድጋፍ የሚበረታታ ነበር ብለዋል፡፡ በቀጣይም የውጭ ባለሃብቶችን በመሳብ የልምድ፣ የዕውቀት እና የክህሎት ሽግግር ለማድረግ ይሠራል ተብሏል፡፡ ኢትዮጵያ በ2009 ዓ.ም ከጨርቃጨርቅ እና አልባሳት ኢንዱስትሪው 90 ሚሊየን ዶላር ገቢ አግኝታ ነበር፡፡ ከ2010 ዓ.ም እስከ 2013 ዓ.ም ባሉት አራት ተከታታይ ዓመታትም 578 ሚሊየን ዶላር ገቢ መገኘቱን መረጃዎች ያመላክታሉ፡፡ በ2014 ዓ.ም የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ከዘርፉ የተገኘው ገቢ 45 ሚሊየን ዶላር ሲሆን በ10 ዓመቱ የልማት እቅድ ከዘርፉ የሚገኘውን ገቢ 3 ቢሊየን ዶላር ለማግኘት መታቀዱን መረጃዎች ያመላክታሉ፡፡ ዘጋቢ፡- ታዘብ አራጋው ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡ ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq በዌብሳይት amharaweb.com ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m

ባለሀብቶቹ 100 የእርድ ሰንጋዎችን ለወገን ጦር አስረከቡ። ሕዳር 01/2014 ዓ.ም (አሚኮ) የአማራ ባለሀብቶች 100 የእርድ ሰንጋዎችን በጋሸና ግንባር ለተሰለፈው የወገን ጦር አስረክበዋል። ድጋፉ ከ 2 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ተደርጎበታል። ድጋፉን በደቡብ ጎንደር የሎጂስቲክ አስተባባሪ ኮሚቴ አማካኝነት ለመከላከያ ሠራዊት፣ ለአማራ ልዩ ኀይል፣ ፋኖ እና ለሚሊሻ አባላት አስረክበዋል። ድጋፉን ያስረከቡት የደቡብ ጎንደር ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የግንባሩ የሎጅስቲክ አስተባባሪ ኮሚቴ ሰብሳቢ ጥላሁን ደጀኔ የአማራ ባለሀብቶች ተደጋጋሚ ድጋፍ እያደረጉ መሆኑን ተናግረዋል። ከባለሀብቶች ባለፈ ልዩ ልዩ የኀብረተሰብ ክፍሎችም ድጋፍ እያደረጉ መሆኑንም ጠቅሰዋል። የሚደረገውን ድጋፍ እያንዳንዱ ምሽግ ድረስ እንዲደርስ መደረጉንም ነው ያስረዱት። አሸባሪውን የትግራይ ወራሪ ኀይል እየተፋለመ የሚገኘውን የወገን ጦር ሕዝቡ እየደገፈው መሆኑን በመከላከያ ሠራዊት የግንባሩ የሎጂስቲክስ አስተባባሪ ተናግረዋል። የአካባቢው ሕዝብ እና የመንግሥት አካላትም እንጀራ እና ወጥ በማዘጋጀት ምሽግ ድረስ እያቀረቡ ነው ብለዋል። ሕዝቡ ከሚያደርገው ድጋፍ ባለፈ ወጣቱ ግንባር ድረስ በመሰለፍ የሕይወት መስዋእትነት እየከፈለ እንደሆነም ጠቅሰዋል። ይህም ለሠራዊቱ ትልቅ ትርጉም አለው ነው ያሉት። ትግል ማለት ጥይት ተኩሶ ጠላትን መግደል ብቻ አይደለም ያሉት የሎጂስቲክስ ኀላፊው ሀብታቸውን ለሠራዊቱ በመስጠት እየታገሉ ላሉ ባለሀብቶች ምስጋና አቅርበዋል። ሠራዊቱ የሽብር ቡድኑን የመጨረሻ መቃብር በማፋጠን ሕዝቡ ወደ መደበኛ የልማት ሥራው እንዲመለስ እየሠራ ነው ብለዋል። ያለ መስዋእትነት ድል አይገኝምና እየተደረገ ያለው ሁለንተናዊ ድጋፍ ተጠናክሮ እንዲቀጥልም ጠይቀዋል። ሌሎች የኅብረተሰብ ክፍሎችም የአማራ ባለሀብቶችን ፈለግ እንዲከተሉ ነው የጠየቁት፡፡ ግንባር ከተሰማራው ሕዝባዊ ሠራዊት አንጻር የሚደረገው ድጋፍ በቂ እንዳልሆነ ተመላክቷል፤ ተጨማሪ ድጋፍ እንዲደረግም አስተባባሪዎቹ ጥሪ አቅርበዋል። ዘጋቢ፡-ደጀኔ በቀለ-ከጋሸና ግንባር ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡ ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq በዌብሳይት amharaweb.com ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m

በአዲስ አበባ የሚኖሩ የአማራ ወጣቶች አሸባሪውን የትግራይ ወራሪ ኀይል ለመፋለም ዝግጁነታቸውን ገለጹ። ጥቅምት 30/2014 ዓ.ም (አሚኮ) ለህልውና ዘመቻው በሙያቸው ከማገልገል ባለፈ አሸባሪውን የትግራይ ወራሪ ኀይል በግንባር ለመፋለም ዝግጁ መኾናቸውን በአዲስ አበባ የሚኖሩ የአማራ ወጣቶች ገልጸዋል፡፡ በአዲስ አበባ የዳግማዊ ምኒልክ ሆስፒታል የአማራ ጤና ባለሙያዎች ማኅበር ተወካይ ደሳለኝ መልካሙ እንደተናገረው የጤና ባለሙያዎች በሕልውና ዘመቻው በግንባር ከሕዝባዊ ሠራዊቱ ጎን ተሰልፈው የማገልገል ታሪካዊ ግዴታ አለባቸው፡፡ በዚህም የአማራን ብሎም የኢትዮጵያውያንን ሕልውና ለማስቀጠል የሚዋደቀውን ሕዝባዊ ሠራዊት ሕይወት የመታደግ ኀላፊነታቸውን ለመወጣት ወደ ግንባር ማቅናታቸውን ነው ያነሳው፡፡ ሌሎች ወጣቶችም ግንባር በመሰለፍ ከመፋለም ባለፈ በሙያቸው ማገልገል እንዳለባቸው ገልጸዋል፡፡ የአዲስ አበባ ጤና ባለሙያዎች ማኅበር አባል የኾነው ጌታነህ ብርሃኔ እንደገለጸው የአዲስ አበባ የአማራ ጤና ባለሙያዎች በሙያቸው ለመዝመት ወስነዋል፡፡ ይህ ጦርነት የሕልውና ዘመቻ እንደመኾኑ የታጠቀው አካል ብቻ ሳይሆን ማንኛውም አካል በሙያው ማገልግል እንደሚገባውም ገልጿል፡፡ በአዲስ አበበ የየካ ክፍለ ከተማ የወጣቶች ማኅበር ዋና ጸሐፊ ክንድዬ ፈቃዱ አሁን ላይ ወጣቶች በአንድነት ተሰልፈው በሕልውናቸው ላይ የተቃጣውን አደጋ የሚመክቱበት ወሳኝ ወቅት በመኾኑ ትግሉን ለመቀላቀል መወሰኑን ነው የተናገረው፡፡ በግንባርም የሚሰጠውን ግዳጅ ተቀብሎ በድል ለመወጣት ቁርጠኛ እንደሆነም አንስቷል፡፡ ከዚህ በፊትም ሌሎች በአዲስ አበባ የሚኖሩ የአማራ ወጣቶች አሸባሪውን ኃይል ለመፋለም ግንባር ድረስ መዝመታቸውን ነው ያብራራው፡፡ ❝አሸባሪውን የትግራይ ወራሪ ኃይል ለመደምሰስ በሚደረገው ተጋድሎ በግንባር ተሰልፈን ለመፋለም ተነስተናል❞ ብሏል ወጣት ክንድዬ። አማራ በሕልውናው የመጣን ማንኛውንም ኀይል እንደማይታገስ ያነሳው ወጣቱ ለዚህ ደግሞ መሪዎች የሚሉትን ወጣቱ በማዳመጥ፣ አንድነቱን በማጠናከር፣ በመሰልጠን እና በመታጠቅ አማራ ጠል የሆነውን ቡድን መፋለም እንደሚገባው ነው የገለጸው፡፡ አሸባሪውን እና ወራሪውን ኀይል ለመፋለም ወደ ግንባር ከተንቀሳቀሱት ውስጥ አንዱ የኾነው ወጣት አብርሃም ተሾመ በአዲስ አበባ የአማራ ወጣቶች ከዚህ በፊትም በጸጥታ መዋቅሩ በመቀላቀል ግንባር ላይ እየተፋለሙ እንደሚገኙ አስረድቷል፡፡ ዘጋቢ፡- ዳግማዊ ተሠራ ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡ ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq በዌብሳይት amharaweb.com ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m

❝ሁሉም ሀገሩን ለማስቀጠል የአርበኝነት ተጋድሎ ማድረግ ይጠበቅበታል❞ አቶ ክርስቲያን ታደለ ጥቅምት 30/2014 ዓ.ም (አሚኮ) ኢትዮጵያ ከውስጥም ኾነ ከውጭ የተቃጣባትን የህልውና አደጋ ለመመከትና ሀገርን ለማስቀጠል እያንዳንዱ ዜጋ የአርበኝነት ተጋድሎ ማድረግ ይጠበቅበታል ሲሉ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የፖለቲካ ጉዳዮች ኃላፊ አቶ ክርስቲያን ታደለ ገለጹ። የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የፖለቲካ ጉዳዮች ኃላፊና የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል አቶ ክርስቲያን ታደለ እንደተናገሩት፤ አሸባሪው ትህነግ ከምስረታው ጀምሮ ኢትዮጵያን ለማጥፋት የተፈጠረ ቡድን በመሆኑ ኢትዮጵያ እንድትቀጥል የሚፈልግ ዜጋ ኹሉ ይህንን አሸባሪ ቡድን ግንባር ድረስ ሄዶ ሊፋለመው ይገባል። አቶ ክርስቲያን ለኢፕድ እንደተናገሩት፤ ከአሸባሪው ትህነግ ውጪ በዓለም ታሪክ የመራትን ሀገር ለማጥፋት አልሞ የተነሳ የፖለቲካ ፓርቲ የለም። አሸባሪው የትህነግ ቡድን በገሀድ ሀገርን የማፍረስ ዓላማን አንግቦ ኢትዮጵያን በማፈራረስ ወደ ትናንሽ መንደርነት የመቀየር ፍላጎት አለው። አሸባሪ ኃይሉ ለሕጻናት፣ አረጋውያንና ለደከሙት እንዲሁም ለእንስሳትም ጭምር የማይራራ መሆኑን ገልጸዋል። አሸባሪውን ኃይል ማስወገድ ለነገ የማይባል ተግባር መሆኑንም ተናግረዋል። ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡ ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq በዌብሳይት amharaweb.com Z ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m

በአማራ ክልል የሰብዓዊ ድጋፍ ለማድረስ እንደሚሠራ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብዓዊ ድጋፍ አስተባባሪ የኢትዮጵያ ዳይሬክተር ዶክተር ካትሪን ሱዚ ገለጹ። https://www.amharaweb.com/በአማራ-ክልል-የሰብዓዊ-ድጋፍ-ለማድረስ-እ/ በአማራ ክልል የሰብዓዊ ድጋፍ ለማድረስ እንደሚሠራ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብዓዊ ድጋፍ አስተባባሪ የኢትዮጵያ ዳይሬክተር ዶክተር ካትሪን ሱዚ ገለጹ። ባሕር ዳር: ጥቅምት 28/2014 ዓ.ም (አሚኮ) አሸባሪው የትግራይ ወራሪ ኃይል በአማራ ክልል በከፈተው ወረራ በርካታ ሰብዓዊ እና ቁሳዊ ውድመቶችን ፈጽሟል፤ እየፈጸመም ይገኛል፡፡ ንጹሐን የጦርነቱ ሰለባ ሆነዋል፣ ሕጻናት ሴቶች እና አረጋውያን ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው ለከፋ ጉዳት ተዳርገዋል፡፡ ፆታዊ [...]

❝በአንድነት ስንቆም የትኛውንም ነገር መሻገር እንችላለን❞ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) አዲስ አበባ: ጥቅምት 28/2014 ዓ.ም (አሚኮ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) በትዊተር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ውበታችን አንድነታችን ነው ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ❝በአንድነት ስንቆም የትኛውንም ነገር መሻገር እንችላለን❞ ነው ያሉት። እኛ የቆምነው ታላቅ መስዋእትነት በከፈሉ አያቶቻችን ትከሻ ላይ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ እኛም ለመጪው ትውልድ ጠንካራ መሰረት ለመጣል በቁርጠኝነት ቆመናል ሲሉ ገልጸዋል። ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡ ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq በዌብሳይት amharaweb.com QpiZ ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m

ጀብደኞቹ ለድል ብስራት ቃል ገብተዋል! https://www.amharaweb.com/ጀብደኞቹ-ለድል-ብስራት-ቃል-ገብተዋል/ ጥቅምት 27/2014 ዓ.ም (አሚኮ) አሸባሪውን የትግራይ ወራሪ ኀይል በአጭር ጊዜ በማጽዳት ለሀገራቸው እና ለሕዝባቸው የድል ብስራት እንደሚያሰሙ በጋሸና ግንባር ተሰልፈው ጀብድ የፈጸሙ የሠራዊት አባላት ተናግረዋል፡፡ በግንባሩ የተሰማራው የሀገር መከላከያ ሠራዊት ከአማራ ልዩ ኀይል፣ ፋኖ እና ሚሊሻ ጋር በቅንጅት በፈጸመው ጀብድ አሸባሪውን ኀይል ድባቅ በመምታት ቀቢጸ ተስፋውን መና አስቀርቷል፡፡ አሸባሪው የትግራይ ወራሪ ኀይል ከጦርነት ሕግ ባፈነገጠ [...]

"ሀገርን ሊወር እና የወገንን አንገት ሊያስደፋ የመጣውን አሸባሪ ኀይል ለማጥፋት ቆርጠው መነሳታቸውን የባሕር ዳር ዘማቾች ገለጹ። ባሕር ዳር፡ ጥቅምት 27/2014 ዓ.ም (አሚኮ) ባሕር ዳር ዘማቾቿን ዛሬ ወደ ግንባር ሸኝታለች፡፡ መንግሥት ያስተላለፈውን የክተት ጥሪ ተቀብለው ወደ ግንባር የዘመቱት አቶ ሲሳይ ወርቁ ሀገርን ሊወር እና የወገንን አንገት ሊያስደፋ የመጣውን አሸባሪ ኀይል ለማጥፋት ቆርጠው መነሳታቸውን ነው የተናገሩት፡፡ መዝመት የሚችለው በግንባር ቀደም በመሰለፍ የአባቶቹን የጀግንነት ታሪክ ሊደግም ይገባል ያሉት አቶ ሲሳይ መዝመት ያልቻለው ኅብረተሰብ አካባቢውን ከሰርጎ ገቦች እና የጥፋት ኀይሎች በንቃት እንዲጠብቅ ጠይቀዋል፡፡ ሌላው ዘማች ወጣት ከድር ማሩ በጊዜያዊ ጥቅም ሳንገደብ ኢትዮጵያ ተገዳ የገባችበትን ጦርነት በድል ለማጠናቀቅ በአንድነት መነሳት አለብን ብሏል፡፡ የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ድረስ ሳህሉ (ዶክተር) አሸባሪው የትግራይ ወራሪ ኀይል እየፈጸመ ያለውን የንጹሃን ግድያ፣ የሀብት ዘረፋና ውድመት ለማስቆም ለተላለፈው የክተት ጥሪ ሕዝቡ ፈጣን ምላሽ መስጠቱን በምስጋና ገልጸዋል። በሽኝት መርሃ ግብሩ የከተማ አስተዳደሩ የሥራ ኀላፊዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎች እና የሃይማኖት አባቶች እንዲሁም የዘማች ቤተሰቦች ተገኝተው ዘማቾችን በድል እንዲመለሱ መርቀው ሸኝተዋል፡፡ ዘጋቢ:–ባለ አለምየ ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡ ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq በዌብሳይት amharaweb.com ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m

የጋይንት ወይዛዝርት ማዕዳችሁ አይጉደል! ደብረታቦር፡ ጥቅምት 27/2014 ዓ.ም (አሚኮ) በነፋስ መውጫ ከተማ የሚገኙ እድሮች ሕብረት ፈጥረው በጋሸና ግንባር ለተሰለፈው የወገን ጦር በየዕለቱ እንጀራ እያቀረቡ ነው። በከተማዋ 40 እድሮች አሉ፡፡ ከነዚህ ውስጥ አምስት እድሮች በየቀኑ እስከ 5 ሺህ እንጀራ በማሰባሰብ በአስተባባሪዎቻቸው አማካኝነት ምሽግ ድረስ ማቅረብ ከጀመሩ 15 ቀናት አልፏቸዋል። የከተማዋ ነዋሪዎች በሁለት ዙር ከ60 ሺህ በላይ እንጀራ እና 10 ኩንታል ሹሮ አድርሰዋል፡፡ ድጋፉ በገንዘብ ሲተመንም ከ 700 ሺህ ብር በላይ እንደኾነ ማወቅ ተችሏል። አሸበሪው የትግራይ ወራሪ ኀይል በከተማዋ ከፍተኛ ውድመት ማድረሱ ይታወቃል። የከተማዋ ሕዝብም ጦርነቱ በአሸናፊነት እንዲጠናቀቅ በየዕለቱ እንጀራ እያዋጣ ለወገን ጦር ድጋፍ እያደረገ ነው። የነፋስ መውጫ ከተማ እድሮች ሕብረት አስተባባሪዎች ‹ከእናንተ በፊት እኛ እንሞታለን› ብለው መስዋእትነት እየከፈሉ ለሚገኙት የቁርጥ ቀን ልጆቻችን ከምንበላው እየቀነስን እናጎርሳለን፤ የምናደርገው ድጋፍም ሀገር ነጻ እስክትሆን ድረስ ይቀጥላል ብለዋል። የነፋስ መውጫ ከተማ ከንቲባ ጽሕፈት ቤት ኀላፊና የእድሮች ሕብረት አስተባባሪ በለጠ አስራቴ የከተማዋ ሕዝብ ለመከላከያ ሠራዊት፣ ለአማራ ልዩ ኀይል፣ ለፋኖ እና ሚሊሻ አባላት ጠንካራ ደጀን መኾኑን ጠቅሰዋል። እድሮች ከሚያደርጉት ድጋፍ ባለፈ እንጀራ፣ አጥሚት፣ ሹሮ፣ በርበሬ፣ እሽግ ውኃ፣ ጁስ፣ ወተት፣ አልባሳት እና ሌሎች ድጋፎች እየተደረጉ እንደሆነም ነው የተናገሩት። ባለፉት 15 ቀናት የከተማዋ ነዋሪዎች ከ1 ሚሊዮን 270 ሺህ ብር በላይ የሚገመት ድጋፍ ያደረጉ ሲኾን ቁስለኞችን መደገፍ እና መንከባከብ የሕዝቡ የዕለት ከዕለት ተግባር እንደሆነም ነው ያስረዱት። በአሁኑ ወቅት ከፍተኛ ቁጥር ያለው ዘማች ወደ ግንባር እየዘመተ ነው፤ ለዘማች ኀይል በቂ ምግብ ማቅረብ ደግሞ ነጻነትን የሚፈልግ ዜጋ ሁሉ ግዴታ መሆን አለበት ብለዋል፡፡ ዘጋቢ፡- ደጀኔ በቀለ-ከጋይንት ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡ ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq በዌብሳይት amharaweb.co ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m

"አሸባሪውን ኀይል ለመደምሰስ ተዘጋጅተናል" ወደ ግንባር ያቀኑ የምእራብ ጎጃም ዞን ዘማቾች ጥቅምት 27/2014 ዓ.ም (አሚኮ) አሸባሪው የትግራይ ወራሪ ኀይል በተለያዩ የአማራ ክልልና የአፋር ክልል አካባቢዎች ወረራ በመፈጸም የንጹሃንን ሕይወት ቀጥፏል፣ መሰረተ ልማቶችን አውድሟል፣ ሀብትና ንብረት ዘርፏል። ከሶስት ዓመታት በፊት በሕዝብ ተቃውሞ የተወገደው ይህ ወራሪ ኀይል ''እኔ ያልመራኋት ኢትዮጵያ ትፈርሳለች'' በሚል ቀቢጸ ተስፋ እየሠራ ስለመሆኑ በሽብር ኀይሉ አፈቀላጤዎች አንደበት ሲነገር ይሰማል። ይህን ሀገር የማፍረስ እኩይ ተግባሩን ለመፈጸም የኢትዮጵያን መዳከም ከሚመኙ ሀገራትና ተቋማት ጋር ተቀናጅቶ እየሠራም ይገኛል። የአሸባሪው ኀይል ድርጊትም ኢትዮጵያዊያንን አስቆጥቷል። የአማራ ሕዝብም የክልሉ መንግሥት ላደረገው የክተት ጥሪ ምላሽ እየሰጠ ይገኛል። የክተት ጥሪውን የተቀበሉ የምእራብ ጎጃም ዞን ዘማቾች አሸኛኘት ተደርጎላቸዋል። አቶ አብየ ተረፈ አሸባሪው የትግራይ ወራሪ ኀይል አሰቃቂ ተግባራትን በአማራ ሕዝብ ላይ መፈጸሙ እጅጉን እንዳሳመማቸው ነግረውናል፡፡ አቶ አብየ "እድሜየ ሳይገድበኝ ጠላትን ድባቅ ለመምታት ለመዝመት ወስኛለሁ" ብለዋል። አሸባሪው እና ወራሪው ኀይል የሃይማኖት አባቶችን በመግደልና ሴቶችን በመድፈር በአማራ ሕዝብ ላይ ሰይጣናዊ ተግባራትን ፈጽሟል የሚሉት አቶ አብየ ለመፋለም እና ወገናቸውን ለመታደግ በቁርጠኝነት መነሳታቸውን ነግረውናል። "እናት አይኗ እያየ ልጇን እስከ መግደል የጭካኔ ተግባር በአማራ ሕዝብ ሲፈጸም እያየሁ ቤቴ አልቀመጥም"ያለው ዘማች ወጣት አለሰው ወራሪ ኀይሉን ለመደምሰስ ሁሉም መነሳት እንዳለበት ገልጿል። ሌላው የዱርቤቴ ከተማ ኗሪ አርሶአደር መኩሪያ "ሀገሬ ጥሪ ስታደርግልኝ ጥሪዋን ተቀብየ መጥቻለሁ "ነው ያሉት። የሰሜን አቸፈር ወረዳ የማዘጋጃ ቤት ኀላፊ አቶ አለሰው መንገሻ "ሀገር ተወረረች እየተባለ ባለበት ወቅት እንቅልፍ የሚተኛ ወጣት መኖር የለበትም" ነው ያሉት። "ጤናማ የሆነ ማንኛውም ወጣት ይሄን ወራሪ ለመደምሰስ መነሳት አለበት" ብለዋል። በሽኝት መርሃ ግብሩ ከፍተኛ የክልሉ የሥራ ኀላፊዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎች ተገኝተዋል። ዘጋቢ፡- ፈረደ ሽታ ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡ ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq በዌብሳይት amharaweb.com ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m

"የዋርካዎች መሰብሰብ ደኑን የማይደፈር እያደረገው ነው" ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ባሕር ዳር፡ ጥቅምት 27/2014 ዓ.ም (አሚኮ) በዚህ ፈታኝ ጊዜ የኢትዮጵያ ልጆች ከጫፍ እስከ ጫፍ ተነስተዋል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው እንደገለጹት የመጨረሻው ከባዱ ምጥ ልጁ የሚወለድበት ነው፤ ይህ ፈታኝ ጊዜም ጀግኖች የሚወለዱበት ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ ልጆች ከጫፍ እስከ ጫፍ ተነሥተዋል፤ ፈተናዎቹ አጠንክረውናል፤ ፈታኞቻችን ሌሎች መንገዶችን አሳይተውናል ሲሉ መልዕክታቸውን አጋርተዋል። ፊታቸውን ካዞሩብን ወዳጆች እጥፍ የቁርጥ ቀን ወዳጆች አግኝተናልም ነው ያሉት። የቅጠሎች መሰብሰብ ዋርካ አያደርጋቸውም፤ የዋርካዎች መሰብሰብ ግን ደኑን የማይደፈር እያደረገው ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚከፈል መሥዋእትነት አለ፤ ያ መሥዋእትነት ግን ኢትዮጵያን ዋጅቶ በአለት ላይ ይተክላታል ብለዋል። ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡ ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq በዌብሳይት amharaweb.com በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m

ከአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጅ መምሪያ ዕዝ የተሰጠ መግለጫ https://www.amharaweb.com/ከአስቸኳይ-ጊዜ-ዐዋጅ-መምሪያ-ዕዝ-የተሰጠ/ የአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጅ መምሪያ ዕዝ በአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጅ ቁጥር 5/2014 መሠረት፣ ዛሬ ሥራውን ጀምሯል። ዕዙ በልዩ ልዩ ጉዳዮች ላይ ከተነጋገረ በኋላ የሚከተሉትን የመጀመሪያ ውሳኔዎች አስተላልፏል። 1. በአማራና በኦሮሚያ ክልሎች፤ እንዲሁም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የነዋሪነት መታወቂያ በሕገ ወጥ መንገድ እየተሰጠ መሆኑን የአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጅ መምሪያ ዕዝ አረጋግጧል። በመሆኑም ከዛሬ ጀምሮ በየትኛውም የክልልና የከተማ አስተዳደር የነዋሪነት [...]

የጎንደር ከተማ ነዋሪዎች በግንባር ከመሰለፍ ባለፈ ለሕልውና ዘመቻው የሚውል ስንቅ እያዘጋጁ ነው። ጎንደር፡ ጥቅምት 26/2014 ዓ.ም (አሚኮ) የጎንደር ከተማ ነዋሪዎች አሸባሪውን የትግራይ ወራሪ ኀይል ለመደምሰስ እየተካሄደ ላለው የህልውና ዘመቻ ስንቅ እያዘጋጁ ነው። ነዋሪዎች ለሕዝባዊ ሠራዊቱ የኋላ ደጀንነት ሚናቸውን ለመወጣት በግንባር ከመሰለፍ እስከ ስንቅ ማዘጋጀት ድረስ በተግባር እያስመሰከሩ ይገኛሉ። የስንቅ ዝግጅቱ በተለያዩ አደረጃጀቶች አስተባባሪነት እየተካሄደ እንደሚገኝ ተገልጿል፡፡ በሥራው ላይ በየክፍለ ከተማው ሥር በሚገኙ የቀበሌ ነዋሪዎች፣ የበጎ ፈቃደኛ ሴት አደረጃጀቶች እና የመንግሥት ሠራተኞች እየተሳተፉ ነው፡፡ በሥንቅ ዝግጅቱ ላይ እየተሳተፉ የሚገኙት ወይዘሮ አንሻ ሐሰን እና ወይዘሮ ሳድያ ወንድሙ ለሕዝባዊ ሠራዊቱ ስንቅ የማዘጋጀት ሥራውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል። ከሠራዊቱ ጎን ተሰልፈው ለመፋለም ዝግጁ እንደሆኑም ነው የተናገሩት፡፡ የአራዳ ክፍለ ከተማ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ግዛቸው አስናቀው ለሕዝባዊ ሠራዊቱ የሚካሄደው የስንቅ ዝግጅት ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡ በክፍለ ከተማው ለማዘጋጀት ከታቀደው ሥንቅ ውስጥ እስካሁን ግማሽ ያህሉ መፈጸሙን ነው የጠቆሙት፡፡ የስንቅ ዝግጅቱን ሂደት የጎንደር ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ዘውዱ ማለደ ተዘዋውረው ተመልክተዋል፡፡ ከንቲባው የአሸባሪውን የትግራይ ኀይል ወረራ ለመቀልበስ እየተከናወነ ካለው ሕዝባዊ ዘመቻ ጎን ለጎን የስንቅ ዝግጅቱ ተጠናክሮ መቀጠሉንና ይህም ቀጣይነት እንዳለው ገልጸዋል፡፡ ነዋሪው ጸጉረ ልውጦችን በመከታተልና ለመንግሥት የጸጥታ አካላት ጥቆማ በመስጠት እያደረገ ያለውን ድጋፍም ማስቀጠል እንደሚገባውም አሳስበዋል፡፡ የዘማች ቤተሰቦችን ለመደገፍ እየተከናወነ ያለው ተግባር ምተጠናክሮ ይቀጥላል ነው ያሉት፡፡ መረጃው የጎንደር ከተማ የመንግሥት ኮምዩኒኬሽን መምሪያ ነው። ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡ ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq በዌብሳይት amharaweb.com ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m