en
Feedback
አንድ ጥምቀት አንድ ሐይማኖት

አንድ ጥምቀት አንድ ሐይማኖት

Closed channel
3 156
Subscribers
No data24 hours
-87 days
-5330 days
Posts Archive
Hyundai Avante 2016 Automatic transmission Original left hand drive 2B5 ka talalafe Only 65,000km drived Almost new car really Accident free Original paint Full options Super and super excellent Condition Price 2,380,000birr you should payable 2%com Mobile no 0955333271 0901104014

Hyundai Avante 2016 Automatic transmission Original left hand drive 2B5 ka talalafe Only 65,000km drived Almost new car really Accident free Original paint Full options Super and super excellent Condition Price 2,380,000birr N.B:- መኪናዎን ለመሸጥ፣ለመለወጥ አልያም ለመግዛት አ ስ በዋል እንግዲያው ይህንን ሊንክ በመጫን በ ውስጥ ያናግሩኝ 24 ሰአት ክፍት ነው inbox 👇👇👇 @Rodassuprbroker To see more photo and details of car.click here and see the all you want👇👇👇 https://t.me/Rode22anycarsellbuyandexchange you should payable 2%com Mobile no 0955333271 0901104014

ዝግጅት ! ነገ ምን እንደሚያመጣ አታውቅምና ባለህ ነገር አትመካ ፤ ምንም ነገር ቢመጣ ሊያሳልፍህ በሚችለው ፈጣሪህ ተመካ ። ዛሬን እየኖርክ ለነገ ተዘጋጅ ነገ የዛሬ ውጤት እንጂ ሌላ አይደለም በደጉ ጊዜ ፍቅርህን ፣ ስራህን እምነትህን አጠንክር ነገ የምትመነዝረው የዛሬን ስራህን ነው ። ያማረ ቅዳሜ ተመኘን 🙏

ባሕር ዳር/ጎምባት --:-- የሚሸጥ ቤት ከካራታ እና ከፕላን ጋር ማዞር የሚቻል 500 ካሬ ያለው ለጎንደር-ባሕር ዳር አስፓልት 50 ሜትር ከመሀል ከተማ/ጊዮርጊስ 17 ኪሎሜትር ርቀት ጣና አቀርራቢያ የመሸጫ ዋጋ 750000 ድርድር ያለው ለበለጠ መረጃ ቀጥታ ለሻጭ በመደወል ዋጋ ይደራደሩ የሻጭ ስልክ 0911760949

መለወጥ አለብህ! ህልምህን ከመኖር በላይ የአይምሮ ሰላም የሚሰጥህ ነገር የለም፤ ወደምትፈልገው መንገድ መጓዝ የምትጀምረው መቼ ነው? ሰው እንዴት ወደ ምስራቅ መጓዝ እያለበት ወደ ምዕራብ ይሄዳል? ከማይጠቅሙህ ሰዎች ጋር መሆን የምታቆመው መቼ ነው? ጊዜህን በዋዛ ፈዛዛ የሚያባክኑ ነገሮችን ከህይወትህ ቆርጠህ የምታወጣው መቼ ነው? ስኬትና የህይወት እርካታ ዋጋ ያስከፍላሉ፤ በነፃ አይገኙም። አንተ ደግሞ እንኳን ለሚጠቅምህ ለማይጠቅምህም ነገር ዋጋ ከፍለህ ታውቃለህ፤ አሁን ሰዓቱ ራስህን እስከ መጨረሻው ስለ መቀየር የምናወራበት ነው! ወዳጄ አሁን የሚያስደስትህን ሰው ስለመሆን በማሰብ ጀምር፤ ከዛ ወደ ተግባር ግባ! አለቀ ዋጋ መክፈል ይሄ ነው! እመነኝ መለወጥ አለብህ! ቆሞ መቅረት የለም!

አትጓጓ! ለነገሮች በጣም የምትጓጓ ከሆነ ያ ነገር እንዳይሳካ መንገድ እየከፈትክ ነው፤ ቢሳካ ራሱ እንደጠበከው አትደሰትም። በጓጓህ ቁጥር አይምሮህ ውስጥ የዛ ነገር ምስል አለመጠን ይገዝፍና የተግባር ሰው መሆን ይከብድሀል። ለህይወት ጣዕም እንድታጣ ያደረገህ መጓጓት ነው፤ አሁንም እየጓጓህ የሀሳብ ሰማይ ላይ መንሳፈፍ ካላቆምክ ብዙ ነገር ታጣለህ! ወዳጄ አጥብቀህ ፈልግ ግን አትጓጓ አለዚያ ስህተትህ በዝቶ ከመንገድ ትቀራለህ!

እኔ እችላለሁ💪 ለራስህ እንዲህ ብለህ ንገረው አይምሮህ መሬት ነው የዘራህበትን ነው የሚያበቅለው። 1. እኔ ልዩ ነኝ! እኔ ድንቅ ነኝ! 2. እኔ እችላለሁ! 3. በጎ አሳቢ አይምሮ አለኝ! 4. የጀመርኩትን የህይወትና ጉዞ በድል እጨርሳለሁ! 5. ስኬታማም፤ ደስተኛም፤ መንፈሳዊም ነኝ! ይሄኝ ለራስህ መንገር ወይ ድምፅ አውጥተህ ማንበብ ብቻ ስሜትህን ይቀይረዋል፤ ቀንህን ስለ ድክመትህ፣ ስለ ጭንቀትህ፣ ስለ ችግርህ በማሰብ አትጀምር! ምክንያቱም ጭንቀትና ችገር ከዘራህ ጭንቀትና ችግር ነው ምታጭደው፤ አይምሮህ ውስጥ አሪፍ ነገር ዝራ ወዳጄ!

ሰበር ዜና የኢትዮጵያ የጸጥታ ኃይሎች ጥምረት የወልዲያ ከተማን ሙሉ በሙሉ ተቆጣጠረ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት እንዳስታወቀው የኢትዮጵያ የጸጥታ ኃይሎች ጥምረት፣ በዘመቻ ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት ከተማዋን ተቆጣጥሯል። (ኢትዮ ኤፍ ኤም)

❝እንኳን ደስ አለን! ድሉ የመላ ኢትዮጵያውያን ድል ነው❞ ርእሰ መሥተዳድር ይልቃል ከፋለ (ዶ.ር) https://www.amharaweb.com/❝እንኳን-ደስ-አለን-ድሉ-የመላ-ኢትዮጵያው/ ታኅሣሥ 09/2014 ዓ.ም (አሚኮ) የአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳድር ይልቃል ከፋለ (ዶ.ር) በወገን ጦር የተገኘው ድል አስመልክቶ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። ርእሰ መሥተዳድሩ ያስተላለፉት መልዕክት ቀጥሎ ቀርቧል:- የተገኘው ድል የሚያሳየን የኢትዮጵያን አንድነት ማጽናት በትውልድ ቅብብሎሽ የነበረ፣ ያለና ወደፊትም የሚኖር የጀግኖቻችን መስዋእትነት ውጤት መሆኑን ነው። የአሁኑ ትውልድም ልክ እንደቀደምት ጀግኖች ኢትዮጵያውያን የገጠመውን ወደር በሌለው ጥላቻና ምቀኝነት [...]

ኤርትራዊው ለታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የ2 ሺህ ዶላር ቦንድ ገዛ፡፡ ታኅሣሥ 06/2014 ዓ.ም(አሚኮ) ኤርትራዊው ሀብቱ አድሃኖም ይባላል፡፡ ነዋሪነቱ በስዊዘርላንድ ፍሪበርግ ነው፡፡ ኤርትራዊው ለታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግንባታ ድጋፍ ይሆን ዘንድ 2 ሺህ የአሜሪካ ዶላር በማውጣት የቦንድ ግዢ ፈጽሟል፡፡ የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኢትዮጵያውያን ብቻም ሳይሆን አፍሪካውያን ምልክት ነው፡፡ እናም የሁሉንም አፍሪካውያን ድጋፍ ይሻል ብሏል፡፡ ግድቡ አፍሪካ ተስፋ የጣለችበት መሆኑን እንደገለጸ ከውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘ መረጃ ያመላክታል፡፡ በደጀኔ በቀለ ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡ ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq በዌብሳይት amharaweb.com በቴሌግራም https://bit.ly/2wdQpiZ ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m ቲክቶክ tiktok.com @amharamediacorporation

ትውልደ ኢትዮጵያዊው ኦባላ ኦባላ አሸባሪው የትግራይ ወራሪ ቡድን የፈጸመውን እና እየፈጸመ ያለውን ግፍ ለአሜሪካው ፕሬዚዳንት ባይደን ማስረዳቱን ገለጸ፡፡ https://www.amharaweb.com/ትውልደ-ኢትዮጵያዊው-ኦባላ-ኦባላ-አሸባሪ/ ባሕር ዳር፡ ሕዳር 23/2014 ዓ.ም (አሚኮ) ትውልደ ኢትዮጵያዊው ኦባላ ኦባላ ለአሜሪካው ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን አሸባሪው የትግራይ ወራሪ ቡድን በኢትዮጵያ በቀሰቀሰው ግጭት በርካታ ዜጎችን ለከፋ ችግር መዳረጉን በአገኘው አጋጣሚ አብራርቶላቸዋል። በጋምቤላ ክልል የተወለደውና በአሜሪካ ሚኔሶታ ኦስቲን የምክር ቤት አባል የሆነው ኦባላ ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን በመሰረተ ልማት ጉዳዮች ላይ ባተኮረው ስብሰባ ንግግር አድርገው ሲወጡ በአካል አግኝቶ አነጋግሯቸዋል። [...]

በኩዌት የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ በአሸባሪው የትግራይ ወራሪ ኀይል ለተፈናቀሉ ወገኖች ከ315 ሺህ ብር በላይ ድጋፍ አደረጉ። ባሕርዳር፡ ሕዳር 20/2014 ዓ.ም (አሚኮ) በኩዌት የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ በአሸባሪው የትግራይ ወራሪ ኀይል ለተፈናቀሉ ወገኖች መርጃ በተከፈተው የድጋፍ ማስባስቢያ የባንክ አካውንት ከ315 ሺህ ብር በላይ ገቢ መደረጉ ተገልጿል። በኩዌት የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ በርክክቡ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት ማኅበራቸው እያደረገ ያለውን ድጋፍ እጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸው፣ ሁሉም ኢትዮጵያዊ በያለበት ሀገራዊ ኀላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ ማቅረባቸውን የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ኤጀንሲ በማኅበራዊ ትስስር ገጹ ገልጿል። #ተነሳ!! #መሪህን ተከተል!! #ሀገርህን አድን!! #ነፃነትህን አትስጥ !! #አካባቢህን ጠብቅ!!

"የሀገር መከላከያ ሠራዊት እኛ እንዳንጠፋ፣ ላሞቻችንና በሬዎቻችን በሽብርተኛው የትግራይ ወራሪ ቡድን እንዳይታረዱብንም ታድጎናል" የዳባት ከተማ ነዋሪዎች ደባርቅ፡ ሕዳር 20/2014 ዓ.ም (አሚኮ) የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት አሸባሪው የትግራይ ወራሪ ቡድንን በገባበት እያሳደደ መደምሰሱ በኢትዮጵያውያን ዘንድ ታላቅ ከበሬታን ተችሮታል። አሸባሪው የትግራይ ወራሪ ቡድን አጥፊና አውዳሚ ተልዕኮውን እንዳያሳካ መከላከያ ሠራዊቱ እያደረገ ያለውን ተጋድሎ ለመደገፍ በርካታ ወጣቶች ከጫፍ እስከ ጫፍ በመነሳት እየተቀላቀሉት ይገኛሉ። በሰሜን ጎንደር ዞን የዳባት ከተማ አስተዳደር ነዋሪዎች አሸባሪው የትግራይ ወራሪ ቡድን አካባቢያቸውን ለመውረር ሙከራ ባደረገበት ወቅት የሀገር መከላከያ ሠራዊት ከማኅበረሰቡ ጋር በመኾን ባደረገው ተጋድሎ ጠላትን እንደ ቅጠል ሲያረግፈው በዐይናቸው ተመልክተዋል። ነዋሪዎቹ ስለ የሀገር መከላከያ ሠራዊት ጀብድ ከእነሱ በላይ ማንም ሊነግራቸው እንደማይችልም ተናግረዋል። ምክትል 10 አለቃ ደረበ ባዬ እንዳሉት ሽብርተኛው የትግራይ ወራሪ ቡድን አካባቢያቸውን ለመውረር ቢሞክርም ሕዝቡ በቁርጠኝነት ከሀገር መከላከያ ሠራዊት ጎን በመሰለፉ ቅዠቱ እውን ሳይሆን ቀርቷል። የሀገር መከላከያ ሠራዊት አባላት ሀገር አፍራሹን እና ሽብርተኛውን የትግራይ ወራሪ ቡድን እየደመሰሱት ስለኾነ ክብር እንደሚገባቸው ነዋሪው አስረድተዋል። አስተያየት ሰጪው "ከጥፋት ቡድኑ ለታደጉን የወገን ኀይሎች ኹሉ ክብርና ምሥጋናዬን ላቀርብ እወዳለሁ። ኹሉም የወገን ጦር በአንድነት ጭና ላይ ጀብድ ፈጽሟል" ነው ያሉት። ሌላኛው አስተያየት ሰጪ አርሶ አደር ዋለ ታከለ "የሀገር መከላከያ ሠራዊት እኛ እንዳንጠፋ፣ ላሞቻችንና በሬዎቻችን በሽብርተኛው የትግራይ ወራሪ ቡድን እንዳይታረዱብንም ታድጎናል" ብለዋል። ጠላት ከምድረ ገጽ እስኪጠፋ ድረስ ከሀገር መከላከያ ሠራዊት ጎን በመሰለፍ ትግላቸውን አፋፍመው እንደሚቀጥሉም አርሶ አደሩ አረጋግጠዋል። ወጣት መኳንንት አድን ወረራ ለመፈጸም ሙከራ ሲያደርግ የነበረውን አሸባሪ የትግራይ ወራሪ ቡድንን በመጣበት እንደቀበሩት ተናግሯል። በወቅቱ የሀገር መከላከያ ሠራዊት ያደረገውን ተጋድሎ ለመግለጽ ቃላት ያጥሩኛል ነው ያለው። "የሀገር መከላከያ ሠራዊት ፊት ለፊት ጠላትን በመደምሰስ ነበር ዱቄት ያደረገው" ያለው ወጣቱ እሱም የሀገር መከላከያ ሠራዊትን ለመቀላቀል ዝግጁ መኾኑን ተናግሯል። አለባቸው ደሴ የተባሉ የደባርቅ ከተማ ነዋሪም ኹሉም በአንድነት ከሀገር መከላከያ ሠራዊት ጎን በመሰለፍ አሸባሪውን የትግራይ ወራሪ ቡድን ጭቃ እንዳደረጉት አስታውሰዋል። "አካባቢያችንን ነፃ ማውጣት ብቻ ሳይኾን ሽብርተኛው የትግራይ ወራሪ ቡድን ሙሉ በሙሉ እስኪጠፋ ድረስ ጠንክረን እንታገላለን፤ ከሀገር መከላከያ ሠራዊት ጎንም እንሰለፋለን" ብለዋል። ዘጋቢ:- ቡሩክ ተሾመ #ተነሳ!! #መሪህን ተከተል!! #ሀገርህን አድን!! #ነፃነትህን አትስጥ !! #አካባቢህን ጠብቅ!! ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡ ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq በዌብሳይት amharaweb.com ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m ቲክቶክ tiktok.com @amharamediacorporation

ኢትዮጵያውያንና ትውልደ-ኢትዮጵያውያን የምዕራባውያን ሀገራት ጫና የሚቃወም ሰልፍ በፕሪቶሪያ እያካሄዱ ነው። ባሕር ዳር፡ ሕዳር 20/2014 ዓ.ም (አሚኮ) አንዳንድ የምዕራባውያን ሀገራት በአፍሪካ ላይ የሚያደርጉትን ጫና የሚቃወም ሰልፍ በደቡብ አፍሪካ በፕሪቶሪያ ከተማ እየተካሄደ ነው። ሰልፈኞቹ በፕሪቶሪያ ከተማ በሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ተቃውሟቸውን ያሰሙ ሲሆን ለኤምባሲውም ደብዳቤ አስገብተዋል። በተመሳሳይም ፕሪቶሪያ በሚገኘው የአውሮፓ ሕብረት መስሪያ ቤት ተቃውሟቸውን እንደሚያሰሙና ደብዳቤ እንደሚያስገቡ ተገልጿል። በሰልፉ ላይ በደቡብ አፍሪካ ዘጠኝ ግዛቶች የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ-ኢትዮጵያውያን፣ ደቡብ አፍሪካውያንን ጨምሮ በሀገሪቷ የሚኖሩ የተለያዩ አፍሪካ ሀገራት ዜጎችና የፓን አፍሪካኒዝም አቀንቃኞች እየተሳተፉ መሆኑ ታውቋል፡፡ በሰልፉ ላይ ምዕራባውያን ሀገራት ኢትዮጵያን ጨምሮ በአፍሪካ ላይ ለመጫን የሚፈልጉትን ዘመናዊ የቅኝ ግዛት አስተሳሰብ የሚቃወሙ መልዕክቶች እየተላለፉ ነው። ሰላማዊ ሰልፉ አፍሪካውያን ከኢትዮጵያ ጎን እንደሚቆሙ የሚያሳዩበት እንደሆነ ኢዜአ ዘግቧል፡፡ ሰላማዊ ሰልፉን ያዘጋጁት የተባበሩት የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ ማኅበር በደቡብ አፍሪካ እና የአፍሪካ ዳያስፖራ ፎረም ናቸው። #ተነሳ!! #መሪህን ተከተል!! #ሀገርህን አድን!! #ነፃነትህን አትስጥ !! #አካባቢህን ጠብቅ!! ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡ ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq በዌብሳይት amharaweb.com ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m ቲክቶክ tiktok.com @amharamediacorporation

በአሜሪካ የሚኖሩ የደባርቅና የዳባት ተወላጆች ለደባርቅና ዳባት ሆስፒታሎች የቁሳቁስ ድጋፍ አደረጉ፡፡ ደባርቅ፡ ሕዳር 20/2014 ዓ.ም (አሚኮ) በአሜሪካ የሚኖሩ የደባርቅና የዳባት ተወላጆች ለደባርቅ ጠቅላላ ሆስፒታልና ለዳባት አንደኛ ደረጃ ሆስፒታል 23 ሚሊዬን ብር የሚገመት የሕክምና ቁሳቁስና ድጋፍ አድርገዋል፡፡ ሆስፒታሎቹ እያንዳንዳቸው 50 ደረጃቸውን የጠበቁ አልጋዎችን እና ፍራሾችን በድጋፉ እንዳገኙ ነው የተገለጸው፡፡ ድጋፉን በውክልና ያስረከቡት የሂውማን ብሪጅ ሪጅናል ዳይሬክተር አዳሙ አንለይ (ዶክተር) ድጋፉ በውጭ የሚኖሩ የአካባቢው ተወላጆች እንደ ዜጋ ኀላፊነታቸውን ለመወጣትና ከሠራዊቱ ጎን መሆናቸውን ለመግለፅ ያደረጉት ድጋፍ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ የአካባቢው ተወላጅ ያልሆኑ ትውልደ ኢትዮጵያዊያንም አስተዋፅኦ ማድረጋቸውን ጠቁመዋል፡፡ የተደረገው ድጋፍ በሰሜን ጎንደር ዞን ካለው ወቅታዊ ሁኔታ አንፃር ለአካባቢው ኅብረተሰብና ለሆስፒታሉ ትልቅ አቅምን የሚፈጥር ነውም ብለዋል፡፡ የደባርቅ ጠቅላላ ሆስፒታል ሥራ አሥኪያጅ መኩሪያው አማረ ሆስፒታሉ መደበኛ ሕክም የሚከታተሉ ታካሚዎችን አገልግሎት ለመስጠት የአልጋና መሰል ቁሳቁስ ክፍተት ነበረበት ብለዋል፡፡ ድጋፉ ሆስፒታሉ የነበረበትን ክፍተት የሞላና ለማኅበረሰቡ ተገቢ አገልግሎት እንዲሰጥ የሚያስችለው ነው ብለዋል፡፡ የዳባት አንደኛ ደረጃ ሆስፒታል ሥራ አሥኪያጅ አቶ ሙሉጌታ መለሰ በበኩላቸው ሆስፒታሉ በቅርቡ ወደ ሥራ የገባ ከመሆኑ ጋር ተያይዞና ሀገሪቱ ከምትገኝበት ወቅታዊ ሁኔታ አንፃር ቁሳቁስን ለማሟላት ለመንግሥት ከባድ ነው፡፡ በውጭ የሚኖሩ የአካባቢው ተወላጆችም ይህን ታሳቢ በማድረግ ለሆስፒታሉ ጠንከር ያለ ድጋፍ አድርገዋል ነው ያሉት፡፡ አቶ ሙሉጌታ የዳባት አንደኛ ደረጃ ሆስፒታል ሊሟሉለት የሚገቡ የሕክምና ቁሳቁስ መኖራቸውን ጠቁመው ሌሎች ኢትዮጵያዊያንም ድጋፋቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ አሳስበዋል፡፡ ዘጋቢ፡- አድኖ ማርቆስ-ከደባርቅ #ተነሳ!! #መሪህን ተከተል!! #ሀገርህን አድን!! #ነፃነትህን አትስጥ !! #አካባቢህን ጠብቅ!! ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡ ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m ቲክቶክ tiktok.com @amharamediacorporation

"ወጣቱ መከላከያንና ልዩ ኀይልን በመቀላቀል ጠላትን መደምሰስ አለበት" ረዳት ፕሮፌሰር ገብሬ ሙሉዓለም ገንዳ ውኃ፡ ሕዳር 20/2014 ዓ.ም (አሚኮ) በምዕራብ ጎንደር ዞን መተማ ወረዳ የዩኒቨርሲቲ ሙህራንን ጨምሮ የዞንና የወረዳ የሥራ ኃላፊዎች የህልውና ዘመቻውን አስመልክቶ ከወጣቶች ጋር መክረዋል። መከላከያንና ልዩ ኀይልን ለመቀላቀል የተመዘገቡት ወጣቶች እኛ እያለን ሀገር በባንዳዎች አትፈርስም፤ ተቀምጠን ለባርነት እጃችን አንሰጥም፤ ጠላትን ከገባበት ጉድጓድ ለመቅበርም ዝግጁ ነን ብለዋል። አሸባሪውና ሀገር አፍራሹ የትግራይ ወራሪ ቡድን በአማራ እና በአፋር ክልል የተለያዩ ቦታዎች ከህጻናት እስከ አዛውንት በማሰለፍ የጭካኔ ድርጊት መፈጸሙን ያስታወሱት ወጣቶቹ ህዝባዊ ማዕበል በማድረግ ጦርነት የከፈተውን ወራሪ ቡድን በህዝባዊ ማዕበል ምላሽ ለመስጠት ወጣቱ መደራጀት፣ መሰልጠን፣ በሥነ ልቦና መታጠቅና መዝመት እንዳለበትም ነው የገለጹት። የህልውና ዘመቻውን ለመደገፍ በምክክር መድረኩ የተገኙት የአማራ ሙህራን መማክርት አባልና የጎንደር ዩኒቨርሲቲ መምህሩ ረዳት ፕሮፌሰር ገብሬ ሙሉዓለም ወጣቱ ህልውናውንና ነጻነቱን በክንዱ ሊያረጋግጥ እንደሚገባ ገልጸዋል። አሸባሪው የትግራይ ወራሪ ቡድን ኢትዮጵያን ለማፍረስ ዓልሞ ሲነሳ በብሔር ከመከፋፈል ባሻገር አማራን በኢኮኖሚና በሰው ኃይል ማዳከም የመጀመሪያ ሴራው ነውና ወጣቱ በዚህ መጠን ተረድቶ መከላከያን እና ልዩ ኃይልን በመቀላቀል የሀገሩን ዳር ደንበር ሊያስከብር ይገባል ብለዋል። የውጊያ ዓላማችን ለነጻነት ነው፤ አማራጫችን ደግሞ ማሸነፍ ነው፤ ስናሸንፍ አርአያችን ዓድዋ ተልዕኳችን ሀገር መገንባት ይሆናልም ብለዋል ረዳት ፕሮፌሰሩ። በዘመን አጋጣሚ የታሪክ ባላደራ የሆነው ወጣቱ መከላከያና ልዩ ኃይልን በመቀላቀል ሀገርና ህዝብን ሊያጠፋ የመጣውን የወያኔ ወራሪ ቡድን ሊፋለም እንደሚገባ የገለጹት ደግሞ የመተማ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ኃላፊ አቶ ማሩ ሙሉጌታ ናቸው። ጦርነቱን በስኬት ማሸነፍ የሚቻለው መዝመት የማይችለው ሎጅስቲክስ በማሰባሰብ፣ ስንቅ ማዘጋጀት፣ በማስተባበርና መረጃ በመስጠት ሀገሪዊ ኃላፊነትን ሲወጣ መሆኑን አስገንዝበዋል። ሰርጎ ገብችንና ጸጉረ ልውጦችን መከታተልና መቆጣጠር የህልውና ዘመቻው አንድ አካል በመሆኑ ወጣቱ በተደራጀ አግባብ በቀንና በማታ አካባቢውን በንቃት መጠበቅ እንዳለበትም በምክክር መድረኩ ተገልጿል። ዘጋቢ:– ቴዎድሮስ ደሴ— ከመተማ #ተነሳ!! #መሪህን ተከተል!! #ሀገርህን አድን!! #ነፃነትህን አትስጥ !! #አካባቢህን ጠብቅ!! ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡ ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq በዌብሳይት amharaweb.com ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m ቲክቶክ tiktok.com @amh

"አንድነት ለመላው አማራ" የደባርቅና አካባቢው ተወላጆች መረዳጃ ማኅበር በደባርቅ ወረዳ ለወደሙ ትምህርት ቤቶች ድጋፍ አደረገ፡፡ ደባርቅ፡ ሕዳር 20/2014 ዓ.ም (አሚኮ) ማኅበሩ ከዚህ ቀደም በደባርቅ ወረዳ በትግራይ ወራሪ ቡድን ለተጎዱ 65 ቤተሰቦች ለእያንዳንዳቸው 5 ሺህ ብርና ለወረዳው ተማሪዎች 85 ሺህ ብር የሚገመት 5 መቶ ደርዘን ደብተርና እስክርቢቶ አበርክቷል፡፡ አሁን ደግሞ በወረዳው በአሸባሪው የትግራይ ወራሪ ኀይል ለወደሙ ትምህርት ቤቶች ግብዓት የሚሆን 29 ሺህ ብር የሚገመት 45 የጥቁር ሠሌዳ ድጋፍ አድርጓል፡፡ በደባርቅ ከተማ የማኅበሩ አባል ወጣት አየነው መንግሥቴ በውጭ ሀገር የሚኖሩ የማኅበሩ አባላት ካላቸው ቀንሰው በደባርቅ ወረዳ ጉዳት የደረሰባቸውን ቤተሰቦችና ተቋማት ለማገዝ ጥረት እያደረጉ መሆናቸውንና ይህም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ቃል መግባታቸውንም ተናግሯል፡፡ የደባርቅ ወረዳ ትምህርት ጽሕፈት ቤት ኀላፊ አቶ አገናኘው ማሙዬ የትግራይ ወራሪ ኀይል በወረዳው ማኅበረሰብም ሆነ በትምህርት ተቋማት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱን ገልፀዋል፡፡ ማኅበሩ ለመማር ማስተማር ሥራው ማነቆ ለሆኑ ጉዳዮች ወቅቱን የጠበቀ ድጋፎችን እያደረገ እንደሚገኝም አረጋግጠዋል፡፡ ዘጋቢ:–አድኖ ማርቆስ–ከደባርቅ #ተነሳ!! #መሪህን ተከተል!! #ሀገርህን አድን!! #ነፃነትህን አትስጥ !! #አካባቢህን ጠብቅ!! ተጨማሪ መረጃዎችን ከአሚኮ የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡ ዩቱዩብ https://bit.ly/2RnNHCq በዌብሳይት amharaweb.com ትዊተር https://bit.ly/37m6a4m ቲክቶክ tiktok.com @amharamediacorporation