ትንሽ ፅሁፏ ብትረዝምም ሳትሰለቹ አንብቡት ቁም ነገር ነው 🙏🙏🙏
ያገባኛል ይመለከተኛል ለሚል ሁሉ!
ኡለሞች የነብያት ምትክ መሆናቸውን ለሚያውቅ ሁሉ!
የኡለሞች መኖር በረካ በዱንያ አስተማሪ ብሎ በለአ ተከላካይ በዱአ ሀገር የሚያቆሙ በነሱ ሰበብ እንጂ እንደ ስራችንማ እንደ አድና ሰሙድ ህዝቦች ድሮ ነበር ጠፊነታችን።
ኡለሞች ባለውለታዎቻችን ናቸው ለሀገርም ዋርካ ናቸው ህዝበ ሙስሊሙ ንቃተ ህሊናውና አመለካከቱ የተስተካከለ ቢሆን ዛሬ ሀገራችን ላይ አንድም የእውቀት ባልተቤት በዱንያ ችግር ተታሎ መስመር የሳተ አመለካከት ውስጥ ባልገባ ነበር።ቅኖች ሆነን የኡለማን ጥቅም ብንረዳ ኖሮ አንድም ኡለማ በድህነት አረንቋ ውስጥ ባልተገኘ ነበር።የኡለማ መኖር የሀገር መኖር መሆኑን ብናውቅ ኖሮ እኛ እያለን ኡለማ የህክምና ባላጣ ነበር።የኡለማ መቀመጥ መጠበቅ ያለው በረካ ቢገባን ኖሮ አንድም ኡለማ በማይመች ቤት ባልኖረ ነበር።ኡለማ ለጀነት እንደሚያበቃን ብናቅ ኖሮ አንድም ኡለማ በመንግስት ቤት ባልኖረ ነበር በትራንስፖርት ባልተንከራተተ ነበር።
የሆነው ሆኖ የኡለማ መኖር የነገ ልጆቼ መኖር የቤቴ የሀገሬ የዲኔ መኖር ነው ለሚል ለሚመለከተው ሁሉ አንድ ሀሳብ ላጋራ አሰብኩ፤
ሀገራችን ኢትዮጵያ ለአያሌ አመታት ጉምቱ ኡለሞችን ስታፈራ ቆይታለች ከኢማም አህመድ እስከ ሙፍቲ ዳውድ ከዳንዩል አወል እስከ ሼህ ኢሳ ቃጥባሬ ከሼህ አሊ ጎንደር እስከ የአናጂናው ኮከብ ሼህ ኑር ሁሴን ባሌ ከጫልይ እስከ ሰይድ አበራሙዝ (አብሬትዬወች) ከሼህ መሀመድ ራፊ እስከ ሀጂ መሀመድ ሳኒ ከሀጂ ዘይኑ እስከ ሀጂ ሙሳ ከሼህ ፈድሉ እስከ ሼህ ሰይድ ሁሴን ከሀጂ መሀመድ ሰብዩ እስከ ተቀዳሚ ሙፍቲ ድረስ አረ ሌሎች አያሌ ኡለሞችም ስንት አሉ። ይሄ ሁሉ የተከበረ ኡለማ አንዱም ደልቶት አይደለም በስነስረአቱ ሳይቸገረ የኖረ አልነበረም ሀበሻን ሀበሻ አድርገው ያቆዩ አያሌ ኡለሞች በጣሙኑ ተፈትነዋል አስቡት እስቲ እነዚህ ሁሉ ኡለሞች ፓኪስታን ውስጥ ቢሆኑ ? አረብ ሀገራት ላይ ቢሆኑ ? አውሮፓ ውስጥ ቢሆኑ ? ሀበሻ የታደለች ሀገር ሆነችና እዝህ ሆኑ አለመታደላቸው ሆነና ከኛ መሀል ሆኑ።
ዛሬም ድረስ ስለ ኡለሞቻችን መንገላታት እንሰማለን አንድ ትልቅ ኢማም ታላቅ መሻይኽ ሀፊዝ ሙፈሲር ዝርያቸው ሁሉ ኡለማ የሆኑ በከፍተኛ ሁኔታ ታመው ነበር ከገፍላ መሀል አንዳንድ ኸይረኞች አሉና ህክምናቸውን ሸፈኑ፤ የገባው ማለት ይህ ነው።ዛሬም ታላቁ ሼሀችን የኑር መስጂድ ኑር የሆኑት ታላቁ አሊም ሀጂ መሀመድ ሰብዩ ቤታቸው ለሀገራዊ ልማት ሊፈርስ እንደሆነና 40 አመት አያሌ ትውልድን ካነፁበት መስጂድ ርቀው ወደ ቃሊቲ ሊሄዱ እንደሆነ ሰማን ይሄን ጉዳይ እንደ ሀገር ዋርካነታቸው መንግስት የሆነ ነገር ማድረግ አለበት! እንደ ሙስሊም ለማይከፈል ውለታቸው ደሞ እኛ ሙስሊሞች የሆነ ነገር ማድረግ አለብን!
ቢሆን ቢሆን እሳቸውም ሆነ ህዝበ ሙስሊሙ ልማት ወዳድ ከመሆናቸው በላይ ለልማት ቀናኢ መሆናቸው አለም ያወቀው ፀሀይ የሞቀው ነው ከመሆኑም ጋር ሰውን ለአመታት ላለሙ ጉምቱ ታላላቅ አባቶች በልማቱ መሀል ታሳቢ ቢደረጉና እንደ ሀገር ሀብት ጥበቃ ቢደረግላቸው መልካም ነበር።
ያ አልሆነም ስለዚህ ይሄ ወጣት ትውልድ በወሬ ሳይሆን በተግባር ኡለማ መውደዱን ማሳየት አለበት እስቲ ዛሬ ተግባራዊ እንሁን 50 ሎሚ ለ50 ሰው ጌጡ ነው ና ተባብረን ታላቁ አባታችንን እንኻድም የተወሰኑ ትልልቅ ባለሀብቶች አረ እንደውም አንድ ባለሀብት የሚሸፍነው ነገር እኮ ነው።ጥሩ ቤት ለሀጂ መሀመድ ሰብዩ ገዝተን እንስጥ ዱአ እንቀበል በረካም አጅርም አለው ታሪክም እንሰራለን ፍቅራችንን በተግባር አባትነታቸውን በኺድማ ልጅነታችንን በመስጋና እንግለፅ።
ኡለማ በሀያት እያሉ ሊካደሙ ይገባል! ኡለሞቻችን ማብራት የአይን ብሌኖቻችን ናቸው ለብሌኖቻችን ደሞ ጥበቃ ማድረግ ግዴታች ነው።