2 633
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
2 633
“ሰው በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን እንጂ፣ ሕግን በመጠበቅ እንደማይጸድቅ እናውቃለን። ስለዚህ ሕግን በመጠበቅ ሳይሆን፣ በክርስቶስ በማመን እንጸድቅ ዘንድ እኛም ደግሞ በክርስቶስ ኢየሱስ አምነናል፤ ሕግን በመጠበቅ ማንም አይጸድቅምና።”
— ገላትያ 2፥16 (አዲሱ መ.ት)
2 633
Watch "የታምራት ሆኑዋል New Gosple rap (lyrics video) Bush bright son" on YouTube
https://youtu.be/1ZXnOvUMJQA
2 633
2 633
KEMI channel’s Live stream started.
https://live.vidogram.org/ZdLKfLh7Uj7kPX8Fq8XbsE
Vidogram users can watch quality live stream via the icon on the top of the page. Otherwise you can view the live stream by clicking on the below image.
You can download vidogram from the links below.
Website: http://www.vidogram.org
Google Play Link: https://play.google.com/store/apps/details?id=org.vidogram.messenger&hl=en
2 633
ድርሻህን ተወጣ ❤
አንተ የምታስበውን ሌላው ቢያስበውስ?
ከዛሬ ሶስቶር በፊት አንድ ጥያቄ ጠይቄ ነበር እርሱም ንባብን የሚወዱ 300 ሰዎች ካሉ 100 ብር እንዲያዋጡ ጠይቄ 10 ሰው ብቻ አዋጣ ለምን አሰር ሰው ብቻ ብዬ አሰብኩና ገርሞኝ ዝም አልኩ ግን በግዜው አስር ሰዎች ለምንፈልገው ነገር የሚሆን ብር ሰጠውናል ለዚህም ትልቁን 11,000 የሰጠችን ወዳጃችን ለሚ እና 5500 ደግሞ ኤልቢ የተቀሩት 8 ሰዎች 1500 - 100 በመስጠት ላሰብነው አላማ ሆኖልናል እጅግ እግዚአብሔር ይባርክልን በጠቅላላ 21ሺ ብር አገኘን ግን ለምን ሌሎችስ ብለን ነበር? እና አሁን ደግሞ አድማስ ለማስፋት ፈልገን 100 ለሚሆኑ ሰዎች ቴክስት በማድረግ ፔጃችንም ላይ ፖስት በማድረግ ገንዘብ እንድትለግሱ ብንጠይቅም ያገኘነው ምላሽ እስካሁን 4 ሰው ብቻ ነው አሁንም ለምን አላማችን አልገባቸውም ይሆን? ስራችን ቢሮ ተከራይተን በነፃ ትውልድ መፅሐፍ እንዲያነብ ማድረግ ነው ይህ ደግሞ ሊደገፍ ሊበረታታ የተገባ ነው ታዲያ ለምን ወዳጆቻችን ዝም አሉን 100 ክብር ማኪያቶ ስንጠጣ የሚያልቅ ብር ነው ታዲያስ ለምን አዋጡ ስንል ለምን ዝም አሉን ዛሬም 100 ብር ብትልኩ ሁላችሁም የአመት የቤት ክራይ ይከፍላል ወር ጠብቃችሁ ብትደግሙ ብዙ ቦታ ይከፈታል አንባቢ ሲበዛ ደግሞ አገር ሰላም ትሆናለች በሀሳብ የበላይነት የሚያምን ትውልድ ይፈጠራል አገር ስልጡን ትሆናለች ታዲያ ለምን ለዚህ አላማ ለመተባበር ዘገዩ? ይኸው እንግዲህ "❤ አንድ ንጉስ ሰርግ ድግስ ደገሰና መልካም ብፌ አዘጋጅቶ እንግዶችን ጠራ እና እያንዳንዱ እንግዳ ግን ሲመጣ በገንቦ ጠጅ ይዞ እንዲመጣ እና በማጀት ባለው በርሜል እንዲገለብጥ ተነገረው አንዱ ሰው እንዲህ አሰበ ሁሉም ጠጅ ይዘው ከመጡ እኔ ውሀ ብወስድ አይታወቅም ብሎ በገንቦ ውሀ ይዞ ወደ ድግሱ ይሄዳል እንደተባለው በበርሜል ላይ ውሃውን ይጨምራል እራቱ ተዘጋጅቶ ከበርሜል ሲቀዳ ውሃ ሆነ ለካ ሁሉ እንደሱ አስበው በገንቦ ውሃ ነበር ያመጡት እኔ ባደርግም ባላደርግም ለውጥ የለም እንዳልከው ሌላውም እንደሚል አስብና አንተ አንቺ እኔ ለውጥ አምጪ እንደሆንን ተረድተን ድርሻችንን በአግባብ እንወጣ እላለሁ።" ዛሬም ለልህቀት 100 ጀምረው በመለገስ ያለማንበብን ጨለማ ተባብረን ገፈን እንጣለው ቁጥር ሁለት ለመክፈት በሃያት አካባቢ ያሰብነውን እናሳካ ከተባበርን በየስፍራው እንከፍታለን በሉ ከ100 ጀምረው ይለግሱ ሞባይል ባንኪንግ ይጠቀሙ። ተባብረን አለማንበብን ተራራ እንናደው እንገዳደረው እኛ ከነቀነቅነው ልጆቻችን ይጥሉታል። ዛሬ በዚህ በጎ ስራ ላይ ተሳትፈው ቀንዎን ያሳምሩ።
መልካም ቀን ❤
