FLY
#share በማድረግ እና በመዝናናት አብራቹን እንደምቶኑ እናምናለን መግኘት የምትችሉት ነገር #Art #ቀልድ #music cover #music ሌላ ነገር እንድንለቅ ከፈለጋችሁ ሀሳብ መስጠት ይቻላል @fikerbuna #join #share @Flyforever1
Show moreThe country is not specifiedThe language is not specifiedThe category is not specified
200
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
- Subscribers
- Post coverage
- ER - engagement ratio
Data loading in progress...
Subscriber growth rate
Data loading in progress...
ዝክረ_ሰመአታት_የካቲት_12 💚💛❤️
🇪🇹 የካቲት 12 1929 ዓ.ም በመዲናችን አዲስ አበባ ከ30 ሺህ በላይ ነዋሪዎቿ ሰማአትነት የተቀበሉባት ታሪካዊ ቀን ነች።
📍የዛሬ 83 ዓመት አብርሃም ሞገስ እና ስምዖን የተባሉ ኢትዮጵያዉያን አርበኞች በግራዚያኒ ላይ ባቀናበሩት የግድያ ወጥመድ ፋሺስት ጣልያን በገዛ አገራችን ላይ ህዝቡን አሸባሪ ብለዉ ከፍተኛ ጭፍጨፋ አድርገዉ ነበረ።
🇪🇹 ታሪክን ወደኋላ ⬇️
🇪🇹 አብርሃም ደቦጭ እና ሞገስ አስገዶም ከሐማሴን አና አካለጉዛይ (ማለትም ከአሁኗ ኤርትራ) በፋሺሽት ጣሊያን የሚፈፀመዉን በደል ግፍ እና ግድያን በመቃወም የወደቀችውን ሀገራቸውን ነፃ ለማዉጣት የኢትዮጵያ አርበኞች ቡድንን ተቀላቀሉ። ልክ እንደነሱ ሁሉ በሀገሩ ጉዳይ ይንተከተክ የነበረውን ስምዖን በዛው ተዋወቁት።
📍ስምዖን አደፍርስ ገና የከተማ መልክ አየያዘች በነበረችው አዲስ አበባ ውስጥ በመኪናዉ የታክሲ ሥራ የሚሰራ አርበኛ ነበር።
📍በስራው ላይ እያለ አያሌ የፋሺሽት ጣልያኖችን ግፍ ፣ በደል እና የሃገሩ የወደፊት እጣ ሲያስበው ንዴት፣ውርደት እና አልገዛም ባይነት አንድ ላይ ተደባልቀው ውስጡን ያናዉጡት ነበር።
📍ይህንን የታመቀ ስሜት ይዞ ነበር የሀገር ፍቅር ያንገበገባቸውን የነበረዉን ሁለቱን ወጣቶች አብርሃም እና ሞገስን የተዋወቃቸዉ።
📍ስምዖን ሁሌ ''በመናደድ ብቻ መቆም የለብንም አንድ ወሳኝ የሆነ ሥራ መስራት አለብን '' ይላቸው ነበር።
📍ታዲያ የካቲት 12 ቀን የጣሊያኑ ሹመኛ ግራዝያን'' የጣሊያኑን ኔፕልስ ልእልት ወለደች በማለት የደስታ ድግስ አዘጋጅቶ ህዝቡን ኑኑ ተሰብሰቡ ቸርነቴን ተመልከቱ ላብላችሁ ላጠጣችሁ ብሎ በዛሬዉ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ 6 ኪሎ ካምፓስ በያኔው የአፄ ሀይለስላሴ ቤተመንግስት ግቢ ውስጥ ኢትዮጵያዉን በተሰበሰቡት እብሪት የተሞላበት የግራዝያኒ ንግግር ተጀመረ።
📍ግራዚያኒ በንቀት ያየው ሕዝብ ላይ ስለ ''ታላቂቱ ጣልያን'' መደስኮር ጀመረ። ነገር ግን ብዙም አልቆየም አብርሃም እና ሞገስ ተከታትለዉ ሕዝቡን ጥሰው በመግባት ሰባት ቦንቦችን አከታትለው ወረወሩበት ግራዝያን ቆሰለ ነገር ግን አልሞተም የአየር ኃይሉ ኃላፊ ግን ተገደለ።
📍 አብርሃም እና ሞገስ ጥቃቱን ካደረሱ ቡሀላ በቅዱስ ማርቆስ ቤተክርስትያን በኩል ባለው የቤተመንግስቱ አጥር ዘለው ወጡ እና መኪና ይዞ ወደ ሚጠብቃቸው ስምዖን ገሰገሱ።
📍ስምዖንም ወደ መኪናው አስገብቷቸዉ ወጣቶቹን ይዞ ነጎደ። እንጦጦ ተራራ ላይ ውጥተው ቁልቁል አዲስ አበባን አይዋት ግራዝያን አዋጅ አውጆ የአዲስ አበባ ህዝብ ወንድ ከሴት ሕፃን ከአዋቂ ሳይባል የተገኘዉን ሀበሻ ሁሉ በጥይት በአካፋ እና በዶማ በአሰቃቂ ሁኔታ እያሰቃዩ ገደሉ የነዋሪዎቹን ቤቶች አቃጠሉ አፈረሱት።
📍የካቲት 12 1929 እንደዛሬ እንዲህ ባልሰፋችዉ በትንሿ አዲስ አበባ ከ30 ሺህ በላይ ነዋሪዎች ሰማዕትነት ተቀበሉ።
📍ሶስቱ ወጣቶች ተቃቅፈው ተላቀሱ ጊዜው እስኪመሽ ጠበቁ እና ስምዖን አብርሃምን እና ሞገስን ይዞ ለሰሜን ሸዋ ቅርብ ወደ ሆነችው ደብረ ሊባኖስ ወሰዳቸዉ እዛም የአርበኛው የራስ አበበ አረጋይን ጦር ተቀላቀሉ።
📍ስምዖን ደብረ ሊባኖስ ካደረሳቸዉ ቡሀላ በደም ወደ ጨቀየችዉ አዲስ አበባ ተመለሰ ብዙም አልቆየ በፋሽስቱ ጥቁር ለባሾች ተይዞ በብዙ መከራ እና ስቃይ ተገደለ። ስምዖን የእጁም ሆነ የእግሩ ጥፍር በጉጠት እየተነቀለ ጣቶቹን እየሰባበሩ አሰቃይተው ነበር የገደሉት።
📍አብርሃም ደቦጭ እና ሞገስ አስገዶም ከራስ አበበ አረጋይ የአርበኞች ጦር ጋር ከተቀላቀሉ ቡሀላ ልዩ እንክብካቤ እንዲያገኙ ተደረገላቸው።
📍ትንሽ ቆይተው ግን የነበራቸውን የትምርት ደረጃ በመረዳት ከሀገር ውጭ ወጥተው ቢማሩ ለሀገራቸው ይጠቅማሉ ብለው በማሰብ ከስንቅ እና ገንዘብ ጋር ወደ ሱዳን እንዲሄዱ መከሯቸው።
📍ሆኖም ግን በጉዞአቸው ላይ ሱዳን ሊገቡ ትንሽ ሲቀራቸው ፎቶዋቸው በገጠር ባሉ የፋሺሽት ወታደሮች ሁሉ ተበትኖ ስለነበር በፋሺሽቶች ተይዘው በስቅላት ሰማዕትነት ተቀበሉ።
📍ያኔ አፄ ኃይለሰላሴ በሱዳን በኩል ጣልያንን ከእንግሊዝ ሰራዊት ጋር ሆነው ድል ካደረጉ ቡሃላ የአብርሃም እና የሞገስ አስከሬን ወጥቶ በቅድስት ስላሴ አርበኞች ሃውልት ስር እንዲያርፍ ተደረገ።
🇪🇹 ክብር ለታላቆቹ ለሰማዕታት ህይወታቸውን ሰጥተው ሀገርን በነፃነት ላስከበሩን።
🇪🇹 ተከፍሎ የማያልቀዉን የአባቶቻችንን ዉለታ መቼም ቢሆን መዘንጋት የለብንም።
💚💚💚💚💚💚
💛💛💛💛💛💛
❤️❤️❤️❤️❤️❤️
@Flyforever1
Photo unavailableShow in Telegram
ታላቅ የምስራች ለስዕል አፍቃሪዎች እና መሳል ለምትፈልጉ !!!
ማድረግ የሚጠበቅባቹ ውድድሩን ማሸነፍ ብቻ ነው ፡፡
ውድድሩ ፎቶ channel ላይ post ተደርጎ ብዙ like ያገኘ የላከውን ፎቶ ስለን እናበረክታለን
photo ለመላክ 👇👇👇
@fikerbuna
ውደድሩ እስከ እሁድ ይቆያል
join የሚለው በመጫን ውድድሩን ተቀላቀሉ
join
Photo unavailableShow in Telegram
ታላቅ የምስራች ለስዕል አፍቃሪዎች እና መሳል ለምትፈልጉ ማድረግ የሚጠበቅባቹ ውድድሩን ማሸነፍ ብቻ ነው ፡፡
ውድድሩ ፎቶ channel ላይ post ተደርጎ ለመለ
like ያገኘ የላከውን ፎቶ ስለነ እናበረክታለን
photo ለመላክ 👇👇👇
@fikerbuna
join የሚለው በመጫን ውድድሩን ተቀላቀሉ
Join
Are u helping by sharing
anonymous poll
No – 1
👍👍👍👍👍👍👍 100%
Yes
▫️ 0%
👥 1 person voted so far.
Yes
No – 1
Are u sharing?
public poll
Yes – 1
👍👍👍👍👍👍👍 50%
@fikerbuna
No – 1
👍👍👍👍👍👍👍 50%
@kidasman
👥 2 people voted so far.
Yes – 1
No – 1
Pencil sketch
And other Art works of
@fikerbuna
Masal mifelg
Contact me
@fikerbuna
https://t.me/fkr_art
Fiker arts 🎨
Pencil sketch And other Art works of @fikerbuna Masal mifelg Contact me @fikerbuna
Choose a Different Plan
Your current plan allows analytics for only 5 channels. To get more, please choose a different plan.