486
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
ለ3ኛ እና 4ኛ ክፍል ተማሪ ወላጆች
ሐሙስ፣ ታህሳስ፣ 14/2014ዓ.ም ከ8፡30 ጀምሮ/ልጆቻችሁን ለመውሰድ በምትመጡበት ሰዓት/ በመማር-ማስተማር ሂደቱና በልጆች አያያዝ ላይ የጋራ ውይይት ስለምናደርግ በሰዓቱ በመገኘት በውይይቱ ላይ እንድትሳተፉ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡
የሰሚት ግቢ ወላጆችን አይመለከትም
ቅድሚያ ለልጆች!
ውድ ወላጆች
ት/ቤታችን የሁለተኛ ሩብ ዓመት ትምህርት ከመጀመሩ በፊት የፀረ ተሀዋሲያን ኬሚካል ርጭት ቅዳሜና እሁድ/ታህሳስ 9 እና 10/ ያደርጋል፡፡
በዚህ ምክንያት ሰኞ ት/ት የማይኖር መሆኑን እየገለፅን፣ የሁለተኛው ሩብ ዓመት ትምህርት ማክሰኞ ታህሳስ 12/2014 የሚጀመር መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
የት/ቤቱ አስተዳደር
ውድ ወላጆች
የ2ኛ ሩብ ዓመት የትምህርት አገልግሎት ክፍያ እንድትከፍሉ ባሳሰብናችሁ መሠረት ክፍያውን የፈፀማችሁትን ወላጆች እያመሰገንን ያልከፈላችሁ ወላጆች የመጨረሻው የመክፈያ ቀን ታህሳስ 10/2014 መሆኑን ልናስታውሳችሁ እንወዳለን፡፡
ለክፍያ ስትመጡ
የልጅዎ መታወቂያ ላይ ያለውን መለያ ቁጥር በመያዝ በተመቻችሁ የአቢሲኒያ ባንክ ቅርንጫፎች በመሄድ
በአካውንት ቁጥር 5208599 ገቢ እንድታደርጉ እናሳስባለን፡፡
የቪዥን አካዳሚ አስተዳደር
ውድ ወላጆች
የ1ኛው ሩብ አመት ማጠቃለያ ፈተና ከረቡዕ ታህሳስ 06 እስከ አርብ ታህሳስ 08 2014 ዓ.ም በግማሽ ቀን መርሀ ግብር ይሰጣል፡፡በመሆኑም፡
👉ከአፀደ ሕፃናት እስከ 7ኛ ክፍል 6፡00
👉ከ8-12ኛ ክፍል ተማሪዎች ከ7፡00 ሰአት ጀምሮ ወደቤት የሚሄዱ መሆኑን አውቃችሁ በሰአቱ እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡
ውድ ወላጆች
በሀገራችን ለ12ኛ ጊዜ፣በአለም አቀፍ ደረጃ ለ24ኛ ጊዜ የሚከበረውን የመቻቻል እና የብሄር ብሄረሰቦች ቀን በት/ቤታችን ነገ ህዳር 29/2014 ዓ.ም. ስለሚከበር የሚከተሉትን ጉዳዮች ትኩሩት እንድትሰጡ እናሳስባለን፦
👉ተማሪዎች የመጀመሪያዎቹን 4 ክፍለጊዜዎች መማሪያ ደብተርና ሌሎች አስፈላጊ የትምህርት ቁሳቁሶችን ይዘው ይመጣሉ።
👉ተማሪዎች የተለያዩ ባህላዊ አልባሳትን ወይም ዩኒፎርም ለብሰው ይመጣሉ።
👉ተማሪዎች ሙሉ ቀን ት/ቤት ስለሚቆዩ ወደ ቤት መውጫ ሰአት የተለመደው ሰአት መሆኑን እንገልጻለን።
ቀን 25/03/2014 ዓ.ም
ቪዥን አካዳሚ
ለተማሪ ወላጆች
የ2ኛ ሩብ ዓመት የትምህርት አገልግሎት ክፍያ ከታህሳስ 1-10/2014 ዓ.ም ድረስ መጠናቀቅ እንዳለበትና ክፍያው ከዚህ ጊዜ ካለፈ ቅጣት እንዲሚያስከትል በቴሌግራምና በማስታወሻ ማሳወቃችን ይታወቃል፡፡ስለሆነም በተገለፀው የክፍያ ወቅት ግዴታዎን እንዲወጡ ደግመን እያሳሰብን ባሉበት አካባቢ ሆነው የልጅዎን ስም፣ የክፍል ደረጃና መለያ ቁጥር በመያዝ በተመቻችሁ የአቢሲንያ ባንክ ቅርንጫፎች በA/C 5208599 መክፈል የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡
ት/ቤቱ
ማሳሰቢያ ለወላጆች
ለልጅዎ የሚያስፈልጉ ነገሮችን አስይዘው እንዲልኩ እያሳሰብን ለተማሪዎች ገንዘብ ይዘው ትምህርት ቤት መምጣት የተከለከለ መሆኑን እንገልፃለን፡፡
