486
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
📩ውድ ወላጆች📨
✍የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል የቅዳሜ ማጠናከርያ ትምህርት ነገ መጋቢት 7/2016 ዓ.ም የሚቀጥል ይሆናል።
📌 ለ ተፈታኝ ተማሪዎች የቅዳሜ የማጠናከረያ ትምህርት መማር ግደታ መሆኑን እናሳስባለን።
ት/ቤቱ
ውድ ወላጆች
የስራ ዘመኑን በጨረሰው ወ.ተ.መ.ሕ (ወላጅ ተማሪ መምህር ሕብረት) ምትክ ምርጫ ለማድረግ ባደረግነው ጥሪ መሠረት ቅዳሜ ፣የካቲት 9/2016 ዓ.ም ምልዐተ ጉባዔ ባለመሟላቱ ሳይካሄድ በመቅረቱ፣ለሁለተኛ ጊዜ ቅዳሜ የካቲት 30/2016 ዓ.ም ምርጫው የሚካሔድ መሆኑ፣በገለጽንላችሁ መሠረት በቦሌ ክ/ከተማ በቪዥን አካዳሚ ከቅድመ 1ኛ ደረጃ፣ በመጀመሪያ ደረጃና በሁለተኛ ደረጃ ልጆቻችሁን የምታስተምሩ ወላጆች በዋናው ግቢ ከ2:30 ጀምሮ የሚካሔድ መሆኑን ልናስታውሳቸው እንወዳለን።
ት/ቤቱ!
ውድ ወላጆች
የስራ ዘመኑን በጨረሰው ወ.ተ.መ.ሕ (ወላጅ ተማሪ መምህር ሕብረት) ምትክ ምርጫ ለማድረግ ባደረግነው ጥሪ መሠረት ቅዳሜ ፣የካቲት 9/2016 ዓ.ም ምልዐተ ጉባዔ ባለመሟላቱ ምክንያት ምርጫውን ማካሔድ አልተቻለም።
ለሁለተኛ ጊዜ ቅዳሜ የካቲት 30/2016ዓ.ም ምርጫው የሚካሔድ በመሆኑ፣ በቦሌ ክ/ከተማ በቪዥን አካዳሚ
👉በቅድመ 1ኛ ደረጃ
👉በመጀመሪያ ደረጃና
👉በሁለተኛ ደረጃ ልጆቻችሁን የምታስተምሩ ወላጆች
👉በዋናው ግቢ
👉ከ2:30 ጀምሮ እንድትገኙ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
ት/ቤቱ!
📩ውድ የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ወላጆች እና ተማሪዎች📨
ነገ በአድዋ ድል በዓል ምክንያት የቅዳሜ ማጠናከሪያ ትምህርት የማይኖር መሆኑን እንገልፃለን::
ት/ቤቱ
✅በአዲስ አበባ የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል የ2016 ዓ.ም ከተማ አቀፍ ፈተና‼️
✍️" ፈተናው በሰኔ ወር መጀመሪያ ይሰጣል " - የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ
በአዲስ አበባ የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች የ2016 ዓ.ም ከተማ አቀፍ ፈተና በሰኔ ወር መጀመሪያ ይሰጣል፡፡
ከተማ አቀፍ የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ፈተና ትምህርት ሚኒስቴር በሚሰጠው አቅጣጫ መሰረት በዚህ ዓመት በሰኔ ወር መጀመሪያ ላይ እንደሚሰጥ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ገልጿል።
በዚህም በአዲስ አበባ ለ6ኛ ክፍል 86,691 ተማሪዎች እንዲሁም ለ8ኛ ክፍል 88,028 ተማሪዎች በከተማ አቀፍ ፈተናው ይቀመጣሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ አሳውቋል። #ኢዜአ
📩ውድ ወላጆች📨
የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል የቅዳሜ ማጠናከርያ ትምህርት ነገ የካቲት 16/2016 ዓ.ም የሚቀጥል ሲሆን ተማረዎች ሙሉ የት/ቤቱን የደንብ ልብስ ለብሰው ጧት 2:00🕰 መገኘት ይገባቸዋል። ለ ተፈታኝ ተማረዎች የቅዳሜ የማጠናከረያ ትምህርት መማር ግደታ መሆኑን እናሳስባለን።
ት/ቤቱ
ውድ ወላጆች
የወ.ተ.መ.ህ ምርጫ ለማድረግ ባደረግነው ጥሪ መሠረት ቅዳሜ ፣የካቲት 9/2016 ዓ.ም ምልዐተ ጉባዔ ባለመሟላቱ ምክንያት ምርጫው ሳይካሔድ በመቅረቱ፣
ለሁለተኛ ጊዜ ቅዳሜ የካቲት 16/2016 ሊካሔድ የታሠበው ሥብሰባ የተላለፈ መሆኑን እየገለጽን፣ አመቺ ጊዜ ፈልገን በቅርቡ የምናሳውቃችሁ ይሆናል፡፡
ት/ቤቱ!
ውድ የቪዥን አካዳሚ ወላጆች
ዐርብ የካቲት 15/2016 ዓ.ም ከ2:30-9:00 የ2ኛ ተርም ውጤት የሚሰጥበትና ስለ ልጅዎ የትምህርትና የስነ ምግባር ሁኔታ ውይይት የሚደረግበት ዕለት ስለሆነ በሰዓቱ ልጅዎ በሚማርበት/በምትማርበት ግቢ ተገኝተው ልጅዎን በተመለከተ በውይይቱ እንዲሳተፉ በአክብሮት ጠርተኖታል።
የት/ቤቱ አስተዳደር
#አስቸኳይ!!
ውድ የቪዥን ዋና ግቢ ወላጆች
ልጆቻችሁ በ2016 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና እና የ8ኛ ክፍል የአንደኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና (ሚኒስትሪ) ተፈታኝ ከሆኑ:-
የልጆቻችሁን መረጃ በአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ የፈተና ማስተዳደሪያ (Exam Management System) ላይ የጫንን ስለሆነ ዛሬ ለልጆቻችሁ በምንልከው መለያ ቁጥር እና የመጀመሪያ ስማቸውን (Registration Number and First Name) በማስገባትና በማየት ስህተት ካለ ለትምህርት ቤቱ አስተዳደር በአስቸኳይ እንድታሳውቁ እንጠይቃለን።
ለ6ኛ ክፍል ተማሪዎች በዚህ ማስፈንጠሪያ በመግባት ማረጋገጥ ይቻላል።
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://aa6.ministry.et/#/result
ለ8ኛ ክፍል ተማሪዎች በዚህ ማስፈንጠሪያ በመግባት ማረጋገጥ ይቻላል።
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://aa.ministry.et/#/result
የተፈታኞች ሙሉ ስም፣ ፎቶ፣ ጾታ፣ እድሜ እና ሌሎች መረጃዎች ትክክለኛ መሆናቸውን በማየት ስህተት ካለ በቀጣይ ቀን መረጃ በ 👉👉👉👉@Yoeeeeeeeeessss
በሚለው Telegram Link 🔗 እንድትልኩልን ስንል በአክብሮት እናሳስባለን።
የት/ቤቱ አስተዳደር
📩ውድ ወላጆች📨
የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል የቅዳሜ ማጠናከርያ ትምህርት ነገ የካቲት 09/2016 ዓ.ም የሚቀጥል ሲሆን ተማረዎች ሙሉ የት/ቤቱን የደንብ ልብስ ለብሰው ጧት 2:00🕰 መገኘት ይገባቸዋል። ለ ተፈታኝ ተማረዎች የቅዳሜ የማጠናከረያ ትምህርት መማር ግደታ መሆኑን እሳስባለን።
ት/ቤቱ
ውድ ወላጆች
በቦሌ ክ/ከተማ በቪዥን አካዳሚ
👉 በቅድመ 1ኛ ደረጃ
👉 በመጀመሪያ ደረጃና
👉 ሁለተኛ ደረጃ ልጆቻችሁን ለምታስተምሩ
ወላጆች
የስራ ዘመኑን በጨረሰው ወ.ተ.መ.ሕ (ወላጅ ተማሪ መምህር ሕብረት) ምትክ ምርጫ የምናካሂድ መሆኑን የካቲት 4/2016ዓ.ም በላክነው ደብዳቤ መሠረት ነገ ፣ቅዳሜ ፣የካቲት 9/2016ዓ.ም
👉በዋናው ግቢ
👉ከ2:30 ጀምሮ የሚካሄድ መሆኑን ልናስታውሳችሁ እንወዳለን።
ት/ቤቱ!
📩ለቪዥን አካዳሚ ወላጆችና ተማሪዎች📩
ነገ ሰኞ፥ የካቲት 04 ፥2016 ዓም የ2016 ት/ት ዘመን የ3ኛዉ ሩብ ዓመት እንደምጀመር እየገለጽን ተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት በሚመጡበት ወቅት
👔 የደንብ ልብስ /uniform/ አሟልተው መልበስ ይኖርባቸዋል፡፡
🏫 🕰 ትምህርት ከጠዋቱ 2 ሰአት ላይ ስለሚጀመር ቀደም ብለው መገኘት ይኖርባቸዋል፡፡
💇♂ ወንድ ተማሪዎች እግረ ጠባብ ሱሪ /በተለምዶ እስኪኒ/፣ በተጨማሪ ፀጉርን አሳድጎ ወይም በዲዛይን ተቆርጦ መምጣት፣ እንዲሁም ጥፍርን አሳድጎ ወደ ትምህርት ቤት መምጣት ፈፅሞ የተከለከለ ነው፡፡ ተማሪዎች በዚህ አይነት ሆነው ከመጡ ወዲያውኑ ወደ ቤት እንዲመለሱ ይደረጋል።
👩🦰 ሴት ተማሪዎች ፀጉርን መልቀቅ፤ አርቴፊሻል ፀጉር መቀጠል፤ ቀለም ወይም ሂና መቀባት፣ የጥፍር ቀለም መቀባት፤ ማንኛውም ጌጣጌጥ ማድረግ፣ ሱሪና የሰውነት ቅርፅ የሚያሳይ የደንብ ልብስ ማድረግ ፈፅሞ የተከለከለ ነው፡፡
📵ማንኛውንም ኤሌክትሮኒክስ ይዞ ወደ ትምህርት ቤት መምጣት ፈፅሞ የተከለከለ ነው፡፡
🦺👚 ምንም አይነት ልብስ ዩኒፎርም ላይ ደርቦ መልበስ የተከለከለ ነው።
🍱🥖በቁርስ እና ምሳ ሰአት ላይ ተማሪዎች የራሳቸውን ምግብ እና ውሃ ይዞ በመምጣት መመገብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
ት/ት ቤቱ።
ውድ የቪዥን ወላጆች
የተቋማችን የ3ኛ ሩብ ዓመት የትምህርት አገልግሎት ክፍያ ቀድማችሁ የፈፀማችሁትን ወላጆች እያመሰገንን ላልከፈላችሁት ግን የክፍያ ጊዜ ከጥር 30 እስከ የካቲት 15/2016ዓ.ም እንደሆነ ልናስታውሳችሁ እንወዳለን፡፡
የት/ቤቱ አስተዳደር!
📩ውድ ወላጆች📨
በሴሚስተር ዕረፍት ምክንያት ከሰኞ፣ ጥር 27 እስከ አርብ፣ የካትቲ 01፣ 2016 ከኬጂ እስከ አንደኛ ደረጃ ያሉ ተማሪዎች በቤታቸው ይቆያሉ። 3ኛዉ ሩብ ዓመት ሰኞ፣ የካትቲ 04፣ 2016 ይጀመራል።
ትምህርት ቤቱ.
📩ውድ ወላጆች📨
ነገ አርብ ጥር 24/2016 ዓ.ም ለተማሪዎች የፈተና ግብረ መልስ የሚሠጥ ሲሆን ተማሪዎች የትምህርት ቤቱን የደንብ ልብስ ለብሰው በመምጣት እስከ 🕰6:00 የሚቆዩ ይሆናል።
ማሳሰቢያ: የፈተና ወረቀት ለ ተማሪ ብቻ የምንሰጥ መሆኑን እናሳውቃለን።
📩ለ ዋና ግቢ የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች እና ወላጆች📨
ይህን ስሊፕ በተማሪዎች በኩል ዛሬ ረቡዕ ጥር 22/2016 ዓ.ም የላክን መሆኑን እያሳወቅን የሚጠይቀውን መረጃ በትክክል ሞልተው ነገ ሐሙስ 23/2016 ዓ.ም ይላኩልን።
✍️ መረጃው የሚሞላው ለ 6ኛ ክፍል በ አማርኛ ሲሆን ለ 8ኛ ደግሞ በእንግሊዝኛ መሆኑን እናሳውቃለን።
📝ነገ ሐሙስ 23/2016 ዓ.ም የ6ኛ እና 8ኛ የከተማ አቀፍ ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎች በበይነ መረብ ለሚደረገው የተፈታኞች ምዝገባ ፎቶ ለመነሳት ት/ቤት ሲመጡ ሙሉ የት/ቤቱን የደንብ ልብስ መልበስ ይጠበቅባቸዋል። ተማሪዎች ጧት ⏰2:00 ት/ቤት ጊቢ ተገኝተው 5:00 ላይ ወደቤታቸው የምመለሱ ይሆናል።
ማሳሰቢያ: ተፈታኝ ተማሪ ፎቶ ባለመነሳቱ ለምፈጠረው ችግር ት/ቤቱ ሃላፊነት እንደማይወሰዲ በመረዳት ልጅዎን በተጠቀሰው ሰአት ት/ቤት ያድርሱ።
ለሁልጊዜ ትብብሮ ከልብ እናመስግናለን🙏።
ት/ቤቱ
📩ውድ ወላጆች📨
የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል የቅዳሜ ማጠናከርያ ጥር 18/2016 ዓ.ም የማይኖር መሆኑን እናሳስባለን።
ት/ቤቱ
📩ዉድ ወላጆች📨
📌የ 2ኛ ሩብ አመት የማጠቃለያ ፈተና ነገ ሐሙስ ፣ጥር 16፣ 2016 እንደሚጀምር ይታወቃል። ፈተናዉን በተሳካ ሁኔታ ለማስኬድ ይረዳን ዘንድ ቀጥሎ የተዘረዘሩትን ማሳሰቢያዎች ልብ ይበሉ።
⚠️በፈተና ቀናት ተማሪዎች ደብተር ፣ መጽሐፍ፣ እና የግንኙነት ደብተር(Communication book) ይዞ መምጣት በጥብቅ የተከለከለ ነው::
📝ተማሪዎች እርሳሰ ፣ ላጲስ ፣ መቅረጫ እና ብዕር (ለ 7ኛ ክፍል ተማሪዎች ብቻ) መያዝ ይጠበቅባቸዋል።
✍️በዕለቱ ተማሪዎች ሙሉ የደንብ ልብስ መልበስ ይጠበቅባቸዋል።
🍽የፈተና ቀናት ግማሽ ቀን ስለሆነ በእረፍት ሰአት ልጆች የሚመገቡትን ቁርስ ብቻ አስይዘው ይላኩ።
⏰መዉጫ ሰአት 5:45 መሆኑን በመረዳት ልጆችዎን በጊዜ በመውሰድ ለቀጣይ ፈተና እንዲዘጋጁ ያድርጉ።
ት/ቤቱ
