2 013
Subscribers
No data24 hours
-87 days
-1430 days
Data loading in progress...
Similar Channels
Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
December '24
December '24
+2
in 0 channels
November '24
+11
in 0 channels
Get PRO
October '24
+8
in 0 channels
Get PRO
September '24
+2 057
in 0 channels
| Date | Subscriber Growth | Mentions | Channels | |
| 21 December | 0 | |||
| 20 December | 0 | |||
| 19 December | 0 | |||
| 18 December | 0 | |||
| 17 December | +1 | |||
| 16 December | 0 | |||
| 15 December | 0 | |||
| 14 December | 0 | |||
| 13 December | 0 | |||
| 12 December | 0 | |||
| 11 December | 0 | |||
| 10 December | 0 | |||
| 09 December | 0 | |||
| 08 December | 0 | |||
| 07 December | 0 | |||
| 06 December | 0 | |||
| 05 December | 0 | |||
| 04 December | +1 | |||
| 03 December | 0 | |||
| 02 December | 0 | |||
| 01 December | 0 |
Channel Posts
የ12ኛ ክፍል የውጤት መግለጫ አድራሻ!የ2016 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (12ኛ ክፍል) ፈተና ውጤት እና የውጤት መግለጫ አድራሻ ይፋ ሆነ፡፡ የ2016 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ተፈታኞች ውጤታቸውን በሚከተሉት የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የውጤት መግለጫ አማራጮች ከጳጉሜ 4 ቀን ከሌሊቱ 6፡00 ሰዓት ጀምሮ ማወቅ ይችላሉ። በዚህ መሰረት 1. ፖርታል፡- https://result.eaes.et 2. በቴሌግራም ቦት (Telegram Bot):- https://t.me/EAESbot 3. በአጭር የጽሑፍ መልዕክት (SMS)፡- 6284 ላይ ‘R’ን በማስቀደም የመለያ ቁጥር በማስገባት (ምሳሌ R1234567) መልዕክት በመላክ ውጤትዎን ማወቅ ይችላሉ፡፡ ይህ አማራጭ ኢትዮ ቴሌኮም የሚያስከፍለው መደበኛ የSMS ክፍያ ይኖረዋል። ከውጤት መግለጫ ፖርታልና ቴሌግራም ቦት ላይ ጊዜያዊ ሰርቲፊኬት ማውረድና ማታም ይችላሉ፡፡ ውጤቱን ለምትጠብቁ በሙሉ መልካም እድል ተመኝተናል፡፡
| 2 | ውድ የአዲስ 1879 ቤተሰቦች አዲስ ዓመት እየመጣ በመሆኑ እነሆ ቀደም ያሉ የበአልና የተለያዩ ቸብቸቦችዎችን የምትሰሙበት ቻናል ከፍተናል፡፡አዲሱን ቻናል እንደተለመደው ቤተሰብ እንድትሆኑ እንጋብዛለን፡፡
https://www.youtube.com/@1879Music-w5f
ስለቤተሰብነታችሁ ከልብ እናመሰግናለን፡፡ | 390 |
| 3 | የ12ኛ ክፍል ውጤት!
✍️የፈተናው ውጤት ለሊት 6 ሰዓት ላይ ይፋ ይደረጋል።
✍️አጠቃላይ ፈተናውን ያለፉ ተማሪዎች 5.4 በመቶ ናቸው።
✍️አዲስ አበባ 10,690 ተማሪዎች በማሳለፍ ከፍተኛውን ስፍራ ይዟል። ይህ ማለት አዲስ አበባ ካስፈተናቸው ተማሪዎች በመቶኛ ሲሰላ 21.4 በመቶ አሳልፏል።
✍️በሀገር ከፍተኛ ውጤት የተመዘገበው በትግራይ ነው።በትግራይ ፈተናው ከ700 ነው የተሰጠው። በወንድ ተማሪ ከቀላሚኖ 675 ከፍተኛ ውጤት ተመዝግቧል፡፡ ይህም በኢትዮጵያ ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው ተብሏል።
✍️በሀገር ደረጃ ከ600 ከተፈተኑት ውስጥ 575 ከተፈጥሮ ሳይንስ እንዲሁም ከማህበራዊ ሳይንስ ደግሞ 538 ከፍተኛ ውጤት ተመዝግቧል። በተፈጥሮም በማህበራዊ ሳይንስም ትልቅ ውጤት የመጣው በሴቶች ነው። | 338 |
| 4 | የ12ኛ ክፍል ውጤት!
✍️የማህበራዊ ሳይንስ የትምህርት ዘርፍ ፈተናውን ከወሰዱት 353, 287 ተፈታኞች የማለፊያ ውጤት ያስመዘገቡት 2 በመቶ ብቻ ነው፡፡
✍️በአጠቃላይ ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች 1,221 ናቸው፡፡
✍️የዘንድሮውን ፈተና ካስፈተኑ ትምህርት ቤቶች መካከል1,363 የትምህርት ቤቶች “አንድም ተማሪ አለማሳለፋቸውን” የትምህርት ሚኒስቴሩ አስታውቋል።
✍️በፈተናው የማለፊያ ውጤት ካስመዘገቡ ተማሪዎች መካከል 1 ሺህ 220 የሚሆኑት ከ500 በላይ ማምጣታቸውን ገልፀዋል።
✍️በኢትዮጵያ ያሉ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ብዛት 3,792 ነው። | 274 |
| 5 | የ12ኛ ክፍል ውጤት!
✍️ዛሬ ሰኞ ጷጉሜ 4፤ 2016 ዓ.ም ትምህርት ሚኒስቴር ይፋ ባደረገው መግለጫ የዘንድሮውን 12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተናን ከወሰዱ 674,823 ተፈታኞች ውስጥ ከ50 በመቶ በላይ ውጤት ያስመዘገቡት ተማሪዎች 5.4 በመቶ ብቻ ናቸው።
✍️ተማሪዎችን ካስፈተኑ ትምህርቶች ቤቶች መካከል 1,363 የሚሆኑት አንድም ተማሪ አላሳለፉም።
✍️ለ3ተኛ ጊዜ በመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ውስጥ እንዲሰጥ የተደረገውን ይህን ሀገር አቀፍ ፈተና ከወሰዱት ተማሪዎች ውስጥ፤ 8 በመቶ ያህል የሚሆኑት በይነ መረብን ተጠቅመው የተፈተኑ ናቸው።
✍️የዘንድሮውን ሀገር አቀፍ ፈተናውን ለመውሰድ ከተቀመጡት ተማሪዋች መካከል፤ ከፍተኛ ውጤት የተመዘገበው በተፈጥሮ ሳይንስ የትምህርት ዘርፍ ነው።
✍️ከተፈጥሮ ሳይንስ ዘርፍ ፈተናውን ከወሰዱ 321,536 ተማሪዎች መካከል፤ ከ50 በመቶ በላይ ውጤት ያመጡት 9 በመቶው ናቸው። | 322 |
| 6 | ደብረ ታቦር – እድሜ ጠገቧ ባለታሪክ ከተማ!
ጥንታዊቷ እና ታሪካዊቷ ደብረ ታቦር ስያሜዋን ያገኘችው በ1327 ዓ.ም በአጼ ሰይፈ አርዕድ ዘመነ መንግሥት ነው።
ከስያሜው ጋር በተያያዘ ወደ መካከለኛው ምሥራቅ በተለይም ለመንፈሳዊ ተልእኮ ወደ እየሩሳሌም ይመላለሱ በነበሩ አባቶች በእየሩሳሌም ይገኝ ከነበረው የታቦር ተራራ ወይም ደብረታቦር ጋር በነበረው የተፈጥሮ የአቀማመጥ መመሳሰል ምክንያት እና በሌሎች መንፈሳዊ ጉዳዮች ደብር ኢየሱስ በሚለው ላይ ታቦር የሚለውን በማካተት ደብረታቦር ኢየሱስ ቤተክርስቲያን በሚል መጠራት ሲጀመር በዙሪያው ለተመሰረተው የመኖሪያ አካባቢም ደብረታቦር የሚለው አሁን ድረስ የከተማዋ መጠሪያ ሁኖ እንዲዘልቅ ምክንያት ሁኗል።
ደብረታቦር ማለት የቃሉ ትርጉሙም ደብረ ማለት ተራራ ሲሆን ታቦር ደግሞ ብርሃን በጥቅሉም የብርሃን ተራራ ማለት ነው። የደብረታቦር ከተማ ከ13ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ ለነገሥታት መቀመጫነት ተመራጭ ካደረጓት ዋነኛ ጉዳዮች ውስጥ ከተማዋ እና አካባቢው የነበራቸው ፓለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ወሳኝ ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታዎች ይጠቀሳሉ። በሀገሪቱ ታሪክ ወታደራዊ እና አሥተዳደራዊ ጉዳዮች ላይ ታሪካዊ ድርሻ እንድታበረክትም አስችሏታል።
ለከተማዋ መሰረት ከጣሉት አጼ ሰይፈ አርዕድ ዘመን ጀምሮ በመካከለኛው ዘመን የኢትዮጵያ ታሪክ በዋና የሀገር መዲናነት ተመራጭ የነበረች ከተማ ናት።በተለይ በአካባቢው ለጤና ተስማሚ የአየር ንብረት መኖር በአጼ ሱስኒዮስ ዘመነ መንግሥትም ተመራጭ እንድትሆን አድርጓታል። በመሆኑም በደብረታቦር ከተማ አካባቢ አሪንጎ በሚባል ስፍራ በአጼ ሱስንዮስ የተጀመረው አሥተዳደራዊ ማእከልነት ትልቅ የሥልጣኔ አሻራ የተጣለበት ነበር።
የደብረታቦር ከተማ በኢትዮጵያ ታሪክ ዘመነ መሳፍንት በመባል በሚታወቀው ከ18ኛው ክፍለ ዘመን ሰባዎቹእስከ 19ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ ድረስ ለተመሰረተው እና በወቅቱ የፓለቲካ እና ወታደራዊ የበላይነት ለነበረው አሥተዳደር ዋነኛ ተመራጭ ከተማ ነበረች። በዚህ የታሪክ ወቅት የደብረታቦር ከተማ ምንም እንኳን የተጠናከረ ማእከላዊ መንግሥት በመላ ሀገሪቱ ባይኖርም መቀመጫቸውን በከተማዋ ያደረጉት መሳፍንቶች ጠንካራ አሥተዳደራዊ ሥርዓት የነበራቸው ናቸው።
ከ19ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ ጀምሮ በኢትዮጵያ ታሪክ በዘመኑ ከፍተኛ ድርሻ የነበራቸው ወሳኝ ታሪካዊ ክንዋኔዎችን በማስተናገዱ በኩል የደብረታቦር ከተማ ቅድሚያውን ትወስዳለች። ለዚህም በኢትዮጵያ ዘመነ መሳፍንት ሲያከትም እና ወደ ማዕከላዊ መንግሥት ምስረታ ሽግግር ታሪካዊ ሂደት ቀዳሚ ጉዞውን ሲጀምር ደብረታቦር መንደርደሪያ ነበረች። ይህ የሽግግሯ ታሪካዊ ጉዞ በሁለት ዋነኛ ታላላቅ ተግባራት ሲንፀባረቅ መነሻው ደብረታቦር ከተማ ነበረች። እነዚህም በአጼ ቴዎድሮስ መሪነት የተካሄዱት አንደኛው የማዕከላዊ መንግሥት ዳግም ምስረታ ታሪካዊ ድል ሲሆን ሌላው እና ሁለተኛው በኢትዮጵያ ታሪክ ግንባር ቀደም የሆነው እና በደብረታቦር አካባቢ ጋፋት ላይ ተመስርቶ የነበረው የኢንዱስትሪ መንደር ተጠቃሽ ነው።
የደብረታቦር ከተማ በዘመኑ ለነበረው የሀገሪቱ ግዛት ክልል የማዕከላዊነት ድርሻዋ በወቅቱ ይካሄድ ለነበረው ወታደራዊ ዘመቻዎች መነሻ እና መንደርደሪያ በመሆን ከየትኛውም የሀገሪቱ አካባቢ የጎላ ሚና ነበራት። ከአጼ ቴዎድሮስ በኃላም የመጡት አጼ ዮሐንስ አራተኛ በአብዛኛው የማዕከላዊ መንግሥት ምስረታ እና ሌሎች ዘመቻዎችን ለማካሄድ ለአሥተዳደራዊ አመራራቸው የመረጧት እና ቤተ-መንግሥታቸውን በመሥራት መቀመጫቸውን ያደረጉት ደብረታቦር ከተማ ነበር።
በወቅቱ በጌምድር በመባል በሚታወቀው ሰፊ አሥተዳደር አካባቢ በበላይነት የተቀመጡት አሥተዳዳሪ ራስ ጉግሳ መቀመጫቸው በደብረታቦር ከተማ የነበረ ሲሆን ራስ ጉግሳ እና ደብረታቦር በዘመኑ ማዕከላዊ መንግሥት በበላይነት ለመቆጣጠር በነበረው የራሶች እና ባላባቶች ሽኩቻ ዋነኛ ዕእከል የነበሩ መሆናቸው ይታወቃል።
በደብረታቦር ከተማ የሀገር ጎብኝዎችን ትኩረት የሚስቡ በርካታ ታሪካዊ ቋሚ እና ተንቀሳቃሽ መስህብ ሀብቶች ይገኛሉ። ከእነዚህም በታሪካዊ ቅደም ተከተል በ1327 ዓ.ም የተመሰረተው የደብረታቦር ኢየሱስ ቤተክርስትያን ልዩ ጥበብ የሚስተዋልበት፣ በርካታ ቅርሶችም የሚገኙበት ነው።
ከከተማዋ አቅራቢያ የሚገኘው እና በ17ኛው ክፍለ ዘመን እንደተመሰረተ የሚነገርለት የአጼ ሱስንዮስ ቤተ መንግሥት ሕንፃ ቅሪት፣ በዚሁ ዘመናት በአካባቢው የተተከሉት የተለያዩ ጥንታዊ አብያተ ክርስቲያናት፣ ጋፋት የኢንዱስትሪ መንደር የነበረው እና አጼ ቴዎድሮስ ሴባስቶፓልን ያሠሩበት ታሪካዊ ስፍራ፣ የአጼ ዮሐንስ አራተኛ ቤተ-መንግሥት የነበረው ሕንፃ ቅሪትን ያሠሩት የኅሩይ ጊዮርጊስ ቤተክርስትያን ከእነ ቅርሶቹ፣ በወቅቱ አጼ ዮሐንስ ይጠቀሙበት የነበረው የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ፣ ወንበራቸው፣ የገብርዬ ጦር እና የመሳሰሉት ይገኙበታል። በከተማዋ በኢትዮጵያ ብቸኛው የተክሌ አቋቋም የዜማ ማስመስከሪያ ዩኒቨርስቲ ይገኛል።
ከላይ ጉና ከታች ጣና የከተማዋን የአየር ንብረት የተመቻቸ አድርገውታል። በአጠቃላይ የደብረታቦር ከተማ ለወደፊቱ ለከተማዋ እድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከት የሚችሉ የታሪካዊ መስህብ ባለቤት ናት። መረጃው የደብረታቦር ኮሙኒኬሽን ነው።
#አዲስ1879 #addis1879
ዩቱዩብ ላይ አለን፡፡ መግቢያው https://www.youtube.com/@Addis_1879 | 682 |
| 7 | No text... | 547 |
| 8 | ደብረ ታቦር
ሊቀ ካህናት መርዓዊ ተበጀ (ዶ/ር) ቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌም በተሰኘው መጽሐፋቸው እንዳብራሩት፣ በስድስተኛው ክፍለ ዘመን የተነሳው ኢትዮጵያው ሊቅ ቅዱስ ያሬድ፣ ስሙን ‹‹ደብረ ታቦር›› ብሎ በመጥራት ‹‹አማን በአማን ተሰብሐ በደብረ ታቦር›› – እውነት በእውነት በደብረ ታቦር ተመሰገነ በማለት ዘምሮለታል፡፡ ለዜማ፣ ለከበሮና ለጸናጽል እንዲስማማ አድርጎ ለበዓለ ደብረ ታቦር /ነሐሴ 13 ቀን ቡሔ/ አዘጋጅቶታል፡፡ በግዕዙ ‹‹ደብር ርጉዕ ወደብር ጥሉል›› ተረጋግቶ የተንጣለለ ተራራ ነው፡፡
ስለ ቡሔ ትውፊት የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ባዘጋጀው እትም እንደተገለጸው፣ ሰማይ ከጭጋጋማነት ወደ ብሩህነት የሚለወጥበት የመሸጋገሪያ ወቅት ነው፡፡
እንኳን ለደብረ ታቦር (ቡሄ) በዓል አደረሳችሁ!
መልካም በዓል! | 535 |
| 9 | ደብረ ታቦር
‹‹ነሐሴ የተስፋ ምልክት፣ የምሥራች ዋዜማ፣ የብርሃን ተምሳሌት ናት፡፡ እሸት አዝላ፣ አበባ ታቅፋ፣ ብቅ ስለምትል ለገበሬው የተስፋ ምልክቱ ናት፡፡ ነሐሴ ደግሞ በቡሔዋ ትለያለች፤ እንዲሁም በፍልሰታ፡፡›› ይሉናል መምህራኑ፡፡በቤተ ክርስቲያን ባሕረ ሐሳብ የደስታ ብርሃን የሚንፀባረቅባቸው የበዓላት ቀኖች ናቸው የነሐሴ 13ቱ ቡሔ እና የነሐሴ 16ቱ ፍልሰታ፡፡
ቡሔ ማለት የብርሃን መገለጥ፣ የብርሃን መታየት፣ መጉላት ብሩህ መሆን ማለት ነው፡፡ ‹‹ቡሔ የበዓል ስምም ነው፡፡ ስሙም ከግብሩ ተገኝቷል፣ በደብረ ታቦር ቧ ብሎ የተገለጸውን የጌታችንን የፊቱን ብርሃን ጸዳል ያስረዳል፤›› ሲል መዝገበ ቃላት ዘደስታ ተክለ ወልድ ያብራራዋል፡፡
ደብረ ታቦር ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሦስት ደቀመዛሙርቱን ጴጥሮስንና ያዕቆብን ወንድሙንም ዮሐንስን ይዞ እሑድ ነሐሴ 13 ቀን 33 ዓ.ም. ወደ ተራራው የወጣበትና ፊቱ እንደ ፀሐይ የበራበት ልብሱም እንደ ብርሃን ነጭ የሆነበት ቦታ ነው፡፡ በማቴዎስ ወንጌል እንደተጻፈው ኢየሱስ ከሙሴና ኤልያስ ጋር ሲነጋገሩ ታዩአቸው። | 438 |
| 10 | https://youtu.be/rRyxLiw7m1k | 469 |
| 11 | ወሬ በድርበቡ
አሁን ላይ እንደቀላል የምንሰማቸው ነገሮች በጣሙን የሚገርሙ ናቸው፡፡የዋቻሞ ዩንቨርስቲ አመራሮች የነበሩት አቃቤ ህግ ለፍርድ ቤት ባቀረበው ማስረጃ ላይ እንደተመለከተው የሀገር ሚሊዮን ብሮች እንዴት እንደባከኑ የሚያሳይ ነው፡፡እስቲ እንመልከተው፡፡
#በከባድ_የሙስና_ወንጀል የተጠረጠሩት የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንትና ምክትል ፕሬዚዳንትን ጨምሮ በአጠቃላይ በ6 ግለሰቦች ላይ የተመሰረተው የዐቃቤ ሕግ የክስ መዝገብ እንዲህ ይላል፡፡
➡️ ተጠርጣሪዎች በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ፣ ለንግስት ኢሌኒ መታሰቢያ ሆስፒታል የኦክስጂን ማምረቻ ለማስገንባት መቀመጫውና ዋናው መ/ቤቱን ካናዳ ቶሮንቶ ካደረገ " ኤ. ኤ. ኤምዲ. ቴክኖሎጂ ኢንካ " ለተባለ ድርጅት የመንግስትን የግዢ መመሪያው ባልጠበቀ መንገድ በ5 አመት አፈጻጸሙ እየታየ መከፈል የሚገባውን አሰራሩን በመተላለፍ በውል ላይ የተዘረዘሩ ስራዎች ሙሉ በሙሉ ባልተሰሩበት ሁኔታ ለድርጅቱ የ57 ሚሊየን 383 ሺህ 956 ብር ከ72 ሳንቲም ለታለመለት አላማ ሳይውል በመክፈል ጉዳት እንዲደርስ አድርገዋል።
የውል ማስከበሪያ የውሉን ጠቅላላ ዋጋ 10 ከመቶ ማለትም 117 ሚሊየን 10 ሺህ 859 ብር ከ60 ሳንቲም የውል ማስከበሪያ ሳይቀርብ እና ስራውም በውል ላይ በተገለጸው ጊዜ ሳይጠናቀቅ በመቅረቱ ይህ የውል ማስከበሪያ ዋስትና ቀርቦ ቢሆን ኖሮ ለመንግስት ገቢ መደረግ የነበረበትን ጥቅም አሳጥተዋል።
➡️ " ደሳለኝ አስረደ የግንባታ ስራዎች ተቋራጭ " የመምህራን መኖሪያ ቤት ሁለት (2) ህንጻ ግንባታ ስራ ግንቦት 2013 ዓ/ም እና ጥር 2016 ዓ/ም ላይ በተገባው ውል መሰረት ለዚሁ ህንፃ ተቋራጭ በተጋነነ ዋጋ በመስጠት 272 ሚሊየን 170 ሺህ 210 ብር ከ60 ሳንቲም ያለአግባብ ለተጨማሪ የግንባታ ወጪ መደረጉ ፤ ክፍያ በመፈጸም በዚህ ልክ በመንግስት ላይ ጉዳት በማድረስና ለውለታ 26 ሚሊዮን ብር ጥቅም ማስገኘትና ማግኘት።
➡️ በዝምድና እንዲሁም በትውውቅ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ባለቤት እህት እና ሌሎች 2 ሰራተኞች ባልሰሩት ስራ በአበል መልክ የዩኒቨርሲቲውን ገንዘብ ያለአግባብ በመመዝበር ከ6 ሚሊየን ብር በላይ ጉዳት ደርሷል።
➡️ ተጠርጣሪዎቹ ከሌሎች እስካሁን ድረስ እጃቸው ለጊዜው ካልተያዙ ተጠርጣሪዎች ጋር በመመሳጠር በመንግስት ላይ 487 ሚሊየን 333 ሺህ 912 ብር ከ78 ሳንቲም ጉዳት እንዲደርስና ለሌሎች ያልተገባ ጥቅም እንዲያገኙ ተደርጓል።
እንቁርቁሪት፡- ኤፍ ቢ ሲ
ዩቱዩብ ላይ አለን፡፡ መግቢያው https://www.youtube.com/@Addis_1879 | 541 |
| 12 | የዝንጀሮ ፈንጣጣ ምንድን ነው?
በሽታው የሚከሰው መንኪፖክስ በተባለ ቫይረስ ነው።ለፈንጣጣ (ስሞልፖክስ) ከሚያጋልጠው ቫይረስ ጋር ዝርያው ይቀራረባል።
የዝንጀሮ ፈንጣጣ ቫይረስ ከፈንጣጣ ጋር ሲነጻጸር የሚሰራጭበት ፍጥነት አናሳ ከመሆኑም በላይ ሕመሙም አይበረታም።በመካከለኛውና ምዕራብ አፍሪካ አገራት በገጠራማ አካባቢዎች ነው በብዛት የሚከሰተው። በተለይም በጥቅጥቅ ደን (ሬንፎረስት) አቅራቢያ ያጋጥማል።
ቫይረሱ ሁለት ዓይነት ዝርያ ያለው ሲሆን፣ አንደኛው የምዕራብ አፍሪካ ሁለተኛው ደግሞ የማዕከላዊ አፍሪካ የሚባሉ ናቸው።የምዕራብ አፍሪካው ለከፋ ሕመም አያጋልጥም፡፡
ምልክቶቹ ምንድን ናቸው?
በዝንጀሮ ፈንጣጣ የተያዙ ሰዎች መጀመሪያ ላይ ሙቀት፣ ራስ ምታት፣ የጀርባ ሕመም፣ የጡንቻ ሕመም፣ የሰውነት እዚህም እዚያም ማበጥ እና በማንኛውም ነገር ላይ ፍላጎት ማጣት ይታይባቸዋል።
ሙቀቱ ጋብ ሲል ሰውነት ከፊት ጀምሮ ማሳከክ ይጀምራል። መላው ሰውነትን ቢያሳክክም ክንድና እግር የበለጠ ያሳክካሉ።የሚከሰተው እከክ በጣም የሚያምና በተለያየ ደረጃ የሚያልፍ ነው።
ቆዳ ላይ የሚከሰተው እብጠት ኋላ ላይ ቆዳ እንዲቆስልና እንዲረግፍም ያደርል። ጠባሳ ጥሎም ሊያልፍ ይችላል።ሕመሙ በራሱ ጊዜ የሚጠፋ ሲሆን ከ14 እስከ 21 ቀናት ይወስድበታል፡፡
በሽታው እንዴት ይይዛል?
በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር የቅርብ ንክኪ ያላቸው ሰዎች ተጋላጭ ናቸው።በቆዳችን ክፍተቶች በኩል፣ በዓይን፣ በአፍንጫ ወይም በአፍ በኩል ቫይረሱ ወደ ሰውነታች ይገባል።
በወሲብ ወቅት ባለ ንክኪም ቫይረሱ ይተላለፋል።በቫይረሱ ከተያዙ ዝንጀሮዎች፣ አይጦች ወይም ሌሎች እንስሳት ጋር ንክኪ ከተደረገ ቫይረሱ ወደ ሰው ይተላለፋል።ቫይረሱ በልብስ ወይም በሌሎችም ንክኪ ባላቸው ጨርቆች በኩልም ይተላለፋል።
ምን ያህል አስጊ ነው?
አብዛኞቹ በቫይረሱ የሚያዙ ሰዎች ለከፋ ሕመም አይዳረጉም።ልክ እንደ ፈንጣጣ በተወሰኑ ሳምንታት ውስጥ ይጠፋል። ሆኖም ግን በሽታው ከፍተኛ ደረጃ ሊደርስም ይችላል።በምዕራብ አፍሪካ በበሽታው ሳቢያ የሞቱ ሰዎች አሉ።
በቫይረሱ ከተያዘ ሰው ጋር ወሲብን ጨምሮ ማንኛውም ዓይነት ንክኪ ሲኖር የበሽታው የመተላለፍ ዕድል አለው፡፡
ቫይረሱ ለመጀመሪያ ጊዜ የታየው በማቆያ ውስጥ ባለ ዝንጀሮ ላይ ነበር።እአአ ከ1970 ወዲህ በ10 የአፍሪካ አገራት በሽታው ተከስቷል።በ2003 በአሜሪካ ሲከሰት ከአፍሪካ ውጪ የመጀመሪያ ጊዜው ነበር። ወደ አገሪቱ ከገቡ እንስሳት ላይ አንድ ውሻ በቫይረሱ ተይዞ ነበር ሕመሙ የተነሳው።81 ሰዎች በቫይረሱ ቢያዙም የሞተ ሰው አልነበረም።
በ2017 በናይጄሪያ ቫይረሱ በከፍተኛ ደረጃ ተሰራጭቶ 172 ሰዎች መያዛቸው ይታወሳል።75 በመቶ ታማሚዎች ከ21 እስከ 40 ዓመት የሆናቸው ወንዶች ናቸው።
ሕክምና አለው?
ለዝንጀሮ ፈንጣጣ ሕክምና የለውም።ነገር ግን ስርጭቱን መቆጣጠር ይቻላል።ክትባቱ በሽታውን በመከላከል ረገድ 85 በመቶ ውጤታማ ሆኖ ተገኝቷል።
በዩናትድ ኪንግደም የጤና ደኅንነት ተቋም የሚሠሩት ፕሮፌሰር ጆናታን ባል እንደሚሉት፣ በአገሪቱ ለመጀመሪያ ጊዜ ቫይረሱ ከተገኘበት ሰው ጋር ግንኙነት ከነበራቸው 50 ሰዎች አንዱ ብቻ በቫይረሱ መያዙ፣ የቫይረሱ የስርጭት መጠን ውስን መሆኑን ያሳያል።
እንቁርቁሪት፡- ቢቢሲ
#አዲስ1879 #addis1879
ዩቱዩብ ላይ አለን፡፡ መግቢያው https://www.youtube.com/@Addis_1879 | 545 |
| 13 | ወሬ በድርበቡ
በኢትዮጵያ እስከ አሁን ድረስ በዝንጀሮ ፈንጣጣ የተያዘ ሰው አለመኖሩን ጤና ሚኒስቴር እወቁልኝ ብሏል፡፡
ጤና ሚኒስቴርና የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን በቅርበት ክትትል እያደረጉ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን÷ እስከ አሁንም በኢትዮጵያ በበሽታው የተያዘ ሰው አለመኖሩ ተረጋግጧል፡፡
በቅርቡ በሽታው ወደ ከተከሰተባቸው ሀገሮች የጉዞ ታሪክ ያለው ሰው በአቅራቢያው ወደሚገኝ የጤና ተቋም በመሄድ አስፈላጊውን ምርመራና እንክብካቤ ማግኘት እንዳለበት ሚኒስቴሩ አሳስቧል፡፡
#አዲስ1879 #addis1879
ዩቱዩብ ላይ አለን፡፡ መግቢያው https://www.youtube.com/@Addis_1879 | 513 |
| 14 | ወሬ በድርበቡ
ትናንት ነሐሴ 7 ቀን 2016 ዓ.ም. 1,671 የንግድ ድርጅቶች የታሸጉ መሆናቸውን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር አስታውቋል፡፡በተመሳሳይ እስካሁን ታሽገው ከነበሩ 18,789 ድርጅቶች የውል ስምምነት እየፈጸሙ እሸጋው ተነስቶላቸዋል፡፡
በተመሳሳይ በትናንትናው ዕለት የታሰሩት 82 ነጋዴዎችን ጨምሮ እስካሁን በድምሩ 628 ነጋዴዎች በእስር ላይ ሲሆኑ ከዚህ ውስጥ 182 ነጋዴዎች ከእስራት መፈታታቸው ተነግሯል፡፡
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ነሐሴ 6 ቀን 2016 ዓ.ም. ባወጣው መረጃ በዚሁ ቀን በአገር ደረጃ እየተደረገ ባለ የሕገወጥ የንግድ እንቅስቃሴ የክትትልና ቁጥጥር ሥራ 1,126 የንግድ ተቋማት መታሸጋቸውን አስታውቋል፡፡ ሚኒስቴሩ በመግለጫው 53 ምርት የደበቁ የንግድ ተቋማት መታሸጋለውን ገልጾ የ22 ተቋማት ደግሞ ፈቃዳቸው መሰረዙን ተናግሮ ነበር።
#አዲስ1879 #addis1879
ዩቱዩብ ላይ አለን፡፡ መግቢያው https://www.youtube.com/@Addis_1879 | 408 |
| 15 | ″የኔሞ″ ሥርዓት በሽናሻ ብሔረሰብ
የቦሮ ሺናሻ ሕዝብ የራሱ የሆነ ባህላዊ የዳኝነት ተቋም ‹‹ኔሞ›› ተብሎ ይጠራል፡፡ ‹‹የኔሞ›› ተቋም ሦስት የዳኝነት ደረጃዎች ያሉት ሲሆን፣ እነሱም ‹‹ቡራ›› ‹‹ኔማ›› እና ‹‹ቴራ/ጼራ/›› ተብለው ይጠራሉ፡፡ ለእነዚህ የዳኝነት ደረጃዎች የሚበቁና የዳኝነት ሥራዎች የሚሠሩ ከኅብረተሰቡ ውስጥ በዕድሜ የበሰሉ፣ ብልህና የአካባቢውን ወግና ልማድ ጠንቅቀው የሚያውቁ፣ በአስተዳደር ጥበብ የተሻሉ ከብሔረሰቡ ″ከዶዋ″፣ ″ኢኖሮ″፣ እና ″ኢንዲ″ ከሚባሉ ተመርጠው፣ ተመርቀውና ፍትሐዊ አገልግሎት እንዲሰጡ አደራ ተሰጥቷዋቸው ይሾማሉ፡፡
‹‹ቡራ›› እንደ ብሔረሰቡ የዳኝነት ሥርዓት ወንጀለኛን ከመቅጣት በፊት በዳኝነት ደረጃዎች የማጣራት ሥራ ይሠራል፡፡ ‹‹ቡራ›› የሚባለው በአንድ ታዋቂ ሽማግሌ የሚመራና ጉዳዩ የሚታይበት፣ የሚመረመርበት የመጀመሪያ የዳኝነት ደረጃ ነው፡፡ በዚህ ደረጃ እንደ ጉዳዩ ክብደትና ቅለት ውሳኔ ሊያገኝ ወይም ወደሚቀጥለው የዳኝነት ደረጃ ሊሻገር የሚችል ሲሆን፣ ውሳኔውም በብሔረሰቡ ቋንቋ ‹‹ቡሪ ናይር ቆራ›› ይባላል፡፡ ትርጉሙም የመጀመሪያ ደረጃ ዳኛ ውሳኔ ማለት ነው፡፡
‹‹ኔማ›› ሁለተኛው የዳኝነት ሥርዓት ሲሆን፣ በዚህ የዳኝነት ሥርዓት ውስጥ በቡራ የዳኝት እርከን የተሰጠውን በመመርመርና ባለ ጉዳዮችን በማነጋገር ባገኙት ጭብጥ በመነሳት ‹‹የቡራን›› ውሳኔ በማፅደቅ፣ ወይም በማሻሻል ወይም በመሻር ውሳኔ የሚሰጥበት የዳኝነት ደረጃ ነው፡፡ በዚህ ደረጃ ″በኔሞ″ የሽምግልና አካል በተሰጠው ውሳኔ ያልረካ ከሳሽ ወይም ተከሳሽ ወደ ሚቀጥለው የዳኘነት እርከን ይግባኝ ጥያቄውን ያቀርባል፡፡ የመጨረሻውና ይግባኝ የማይጠየቅበት የዳኝነት እርከን ‹‹ቴራ/ጼራ›› ይባላል፡፡ ይህ የዳኝነት ሒደት በአንድ ሰው የሚፈጸም ሲሆን፣ የሁለቱን የዳኝነት እርከኖች ውሳኔ ከፈተሸና ከመረመረ በኋላ በኅብረተሰብ ውስጥ ተቀባይነት ያለው የመጨረሻ ውሳኔ የሚሰጥበት የዳኝነት እርከን ነው፡፡
እንቁርቁሪት፡- ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ፣ መስከረም 2016 ዓ.ም. | 506 |
| 16 | ወሬ በድርበቡ
በፓሪስ 2024 ኦሎምፒክ ለተሳተፉ እና ውጤት ላስመዘገቡ የልዑካን ቡድን አባላት በነገው ዕለት ከጠዋቱ 12 ሰዓት በቦሌ ዓለም አቀፍ አየር መንገድ አቀባበል እንደሚደረግ የባህል እና ስፖርት ሚኒስቴር አስታወቋል፡፡
በዕለቱ ከሰዓት በኋላ በብሔራዊ ቤተ-መንግስት ፕሬዚዳንት ሳህለ ወርቅ ዘውዴ በተገኙበት የክብር ሽልማት፣ የማበረታቻ እና የእራት ግብዣ መርኃ-ግብር የሚካሄድ መሆኑንም ሚኒስቴሩ ገልጿል፡፡
ኢትዮጵያ በ33ኛው የፓሪስ ኦሊምፒክ 1 የወርቅ እና 3 የብር በአጠቃላይ 4 ሜዳሊያዎችን በመሰብሰብ ከዓለም 47ኛ ከአፍሪካ ደግሞ 4ኛ ደረጃን ይዛ ማጠናቀቋ ይታወቃል፡፡
#አዲስ1879 #addis1879
ዩቱዩብ ላይ አለን፡፡ መግቢያው https://www.youtube.com/@Addis_1879 | 500 |
| 17 | የሴቶቾ ማራቶን
ፘጭ ትዕግስት አሰፋ በሴቶች ኦሎምፒክ ማራቶን ውድድር ከፋጡማ ሮባ ፣ ቲኪ ገላና እና ማሬ ዲባባ በመቀጠል ሜዳልያ ያስገኘች አራተኛዋ ኢትዮጵያዊት ሴት ፘጭ ሆናለች።
የዛሬው ማራቶን እስከ መጨረሻው ድረስ ትልቅ ፍልሚያ የነበረበት ነው። በታሪክም ከምርጦቹ አንዱ ማራቶን ተብሏል።
ሌላኛዋ ከፍተኛ ፉክክር ያደረገችው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮናዋ ፘጫችን አማኔ በሪሶ 5ኛ ደረጃ ይዛ አጠናቃለች።
#ጀግኖቻችን እናመሰግናለን🙏 | 665 |
| 18 | የማራቶን ጅማሮ ታሪክ
ከክርስቶስ ልደት በፊት በአምስተኛው ምዕት ዓመት በ490 ዓመት፣ በግሪክ በምትገኘው ማራቶን ውጊያ ተደረገ፡፡ ግሪኮች ፋርሶችን አሸነፉ፡፡ አንድ አቴናዊ የዚህን አኩሪ ድል ዜና በተቻለ ፍጥነት ለወገኖቹ ለማድረስ ከማራቶን እስከ አቴና ያለውን ርቀት በሩጫ አቋረጠው፡፡ ወደ ከተማው እምብርት እየሮጠ መሄድ ‹‹አቴናውያን! ድሉ የእኛ ስለሆነ ፈንጥዙ!›› የሚል የምሥራች ካበሰረ በኋላ ወዲያውኑ ሕይወቱ አለፈች፡፡
በኦሊምፒክ መድረክ የማራቶን 42 ኪሎ ሜትር ሩጫ ለዚህ የጀግንነት ተግባር መታሰቢያነት በየአራት ዓመቱ እየተከበረ ነው የሚለን የጥንት የዓለም ታሪክ የተሰኘው መጽሐፍ ነው፡፡ የታሪክ መጽሐፉ ስለ ድሉ አብሳሪ ማንነት ባይገልጽም በሌሎች መጻሕፍት ስሙ ፊዲፒዲስ እንደሆነ ተጠቅሷል፡፡ፊዲፒዲስ ለድል ብሥራት አቴንስ ድረስ ከሰላሳ ኪሎ ሜትር በላይ ሮጠ ‹‹የሕይወት ውድድርን ፈጸመ›› በኦሊምፒክ የታወቀውን ታሪክ አቆመ፡፡
ይህ የማራቶን ታሪካዊ ገድል ነው በፈረንሣዊው ሚሸል ብሬአል ህሊና ውስጥ ትውስታን ቀርፆ፣ የኦሊምፒክ ጨዋታዎች እ.ኤ.አ. በ1896 እንዲጀመሩ በተወሰነበት የ1894ቱ ኢንተርናሽናል ጉባዔ ማብቂያ ላይ፣ ‹‹የማራቶን መታሰቢያ – የፊዲፒዲስ ማስታወሻ›› የሩጫ ውድድር መኖር እንደሚገባው፣ ለወዳጃቸው የዘመናዊ ኦሊምፒክ አባት ባሮን ደ. ኩበርቲን ማስታወሻ የጻፉት፡፡‹‹ከሩጫዎች ሁሉ በርዝማኔ ብልጫ ያለውና በታሪካዊነቱም የታወቀ አገር አቋራጭ ውድድር በዘመናዊ ኦሊምፒክ ውስጥ ቢኖር ተጨማሪ ውበት፣ ጉጉትና አድናቆት ሊፈጥር ይችላል›› በማለት ነበር የሚሸል ጽሑፍ የገለጸው፡፡
ይህን መዘክራዊ ሐሳብ መነሻ በማድረግ ኢንኦኮ (ኢንተርናሽናል ኦሊምፒክ ኮሚቴ) የውድድሩ ርቀት 42 ኪሜ. የሆነ ሩጫ ‹‹ማራቶን›› የሚል ስያሜ በ1ኛው ኦሊምፒያድ አቴንስ ላይ እንዲጀመር አደርጓል፡፡
ኢትዮጵያ ለመጀመርያ ጊዜ በኦሊምፒክ ከተወዳደረችባቸው ስፖርቶች አንዱ የአትሌቲክሱ ማራቶን ነበር፡፡ በውድድሩም ባሻዬ ፈለቀና ገብሬ ብርቄ ነበሩ፡፡ ባሻዬ 29ኛ፣ ገብሬ 32ኛ ሆነው ማጠናቀቃቸው እ.ኤ.አ. የ1956 ሜልቦርን ኦሊምፒክ ሰነድ ያወሳል፡፡
#አዲስ1879 #addis1879
ዩቱዩብ ላይ አለን፡፡ መግቢያው https://www.youtube.com/@Addis_1879 | 507 |
| 19 | የማራቶን ባለድሎቻችን!
ዛሬ በተገኘው የማራቶን ድል የተነሳ ኢትዮጵያ በኦሎምፒክ የማራቶን ሩጫ ውድድር ታሪክ 5 ጊዜ በማሸነፍ በሁለት የወርቅ ሜዳልያ ብልጫ ከዓለም ቀዳሚዋ ሀገር ሆናለች። ኬንያ እና አሜሪካ 3 ወርቅ በማምጣት በሁለተኛነት ይከተላሉ።
🇪🇹አትሌት አበበ ቢቂላ (1960ና 1964)፣ 🇪🇹ማሞ ወልዴ (1968)፣ 🇪🇹ገዛኸኝ አበራ (2000) እና 🇪🇹ታምራታ ቶላ (2024) ለኢትዮጵያ የኦሎምፒክ ማራቶን ወርቅ በማምጣት ስማቸውን በወርቅ ቀለም አስጽፈዋል። የሀገራቸውንም ሰንደቅ ከፍ አስድርገዋል።
ባለድሎቻችን ሁሌም እናመሰግናችኋለን!!
#አዲስ1879 #addis1879
ዩቱዩብ ላይ አለን፡፡ መግቢያው https://www.youtube.com/@Addis_1879 | 611 |
| 20 | የታምራት ቶላ ደስታ ከፓሪስ
በፓሪስ ኦሎምፒክ ውድድር ለኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የወርቅ ሜዳልያ በወንዶች ማራቶን ያስገኘው አትሌት ታምራት ቶላ ባስመዘገበው ድል እጅግ መደሰቱን ተናግሯል።
" እኔ የምለው ነገር የለኝም " ያለው ሯጭ ታምራት ቶላ " እኔን የረዳኝ እግዚአብሔር ነው ፤ እግዚአብሔር ይመስገን " ሲል በእምባ ታጅቦ ከድሉ በኋላ አስተያየቱን ሰጥቷል።
" ውድድሩን በማሸነፌ እና የወርቅ ሜዳልያው ለሀገሬ ኢትዮጵያ በማስገኘቴ በጣም በጣም ተደስቻለሁ " ሯጭ ታምራት ቶላ
ሯጭ ታምራት ቶላ በውድድሩ በ2:06:26 በሆነ ሰዓት በመግባት በወንዶች ማራቶን የኦሎምፒክ ሪከርድ ባለቤት በመሆን ለኢትዮጵያም የመጀመሪያውን ወርቅ አስገኝቷል።
#አዲስ1879 #addis1879
ዩቱዩብ ላይ አለን፡፡ መግቢያው https://www.youtube.com/@Addis_1879 | 329 |
