en
Feedback
Admas

Admas

Open in Telegram

......@@በየቀኑ አስገራሚ እና የተለየያዩ(social Media) ፅሁፎች የምታገኙበት channel ነው.....@@

Show more
614
Subscribers
No data24 hours
-17 days
-1230 days
Posts Archive
ሰላም ሲያምራችሁ ይቅር! (አሌክስ አብርሃም) ቤተሰቦቻችሁ ጋር ፣ ጎረቤቶቻችሁና ጓደኞቻችሁ ጋር ተጨዋቱ ቡና ጠጡ ፣የታመመ ጠይቁ፣ የሚያገባን እልል ብላችሁ ዳሩ ፣የሞተ ቅበሩ! እድር ዕቁብ መሀበር ግቡ! በቂ እንቅልፍ ተኙ ቤት ያፈራውን በወጉ ብሉ፣ ቤት ካላፈራ ተካፈሉ፣ በየዕምነታችሁ ፀልዩ ! ሮጥ ሮጥ ማለትም ጥሩ ነው! " ዓለም የመሰከረለት ማህበራዊ ፈውስ እውነተኛ ምንጩ ይሄ ነው! ማህበራዊ ህይዎት! ዮጋ ፣ ሜዲቴሽን መነጠል መገንጠል " ከሚሉት ኮተታም የብቸኝነት ቁዘማ ራቁ! ለምንም አይጠቅማችሁም! ከቻይና ህንድና አጠቃላይ ሩቅ ምስራቅ ምርታቸውን እንጅ መንፈሳዊ ስንክሳራቸው ይቅርባችሁ! እነሱ ራሳቸው እግራቸውን አጣጥፈውና ዓይናቸውን ጨፍነው ተቀምጠው "ተመሰጥን ተነጠቅን" እያሉ በተጃጃሉበት ዘመን ምዕራቡ ዓለም ትቷቸው የትና የት ደረሰ!(ቁሳዊ ቢሆንም) የእነሱ ዮጋና ሜዲቴሽን ምሳጤና ምናምን ስንዝር አላራመዳቸውም! ዘግናኝ ርሀብ ነው የቆላቸው! ለማኝ ነበር ያደረጋቸው ! ስደተኛ ነበር የሆኑት! እስካሁንም ቅንጫሬው ገና አለቀቃቸውም! እንኳን ውስጣዊ ሰላም ሊያገኙ ከዛ አካባቢ የሚመጡ ሰዎች ቀልበ ቢስ፣ ገንዘብ አምላኪ ሰበአዊነት የራቃቸውና ተቅበዝባዢ ናቸው! ግን ቢዘገዩም ባነኑ ! ተነስተው መስራት መታተር ሲጀምሩ እንደህዝብ ተቀየሩ ! ቻይናና ህንድን ተመልከቱ! በምድር ላይ እንደነዚህ አገራት ዘግናኝ እልቂት ርሃብና ድህነት መንፈሳዊ ግራ መጋባት ያሳለፈ ህዝብ ይኖር ይሆን? ዮጋ ፣ ሜዲቴሽን የለየላቸው "መንፈሳዊ ልምምዶች" እንጅ "ሳይንሳዊ ራስን ማግኛ መንገድም" ይሁን " የአካል ብቃት እንቅስቃሴ" አይደሉም!! የሰለጠነው አለም ስለተቀበለው ልክ ነው አይባልም! ገና እያነታረካቸው ያለ ነገር ነው! ሰላም ሱሚ ነው! እንደውም ከራሳችሁ ነው የሚያጣሏችሁ! እደግመዋለሁ "ዮጋና ሜዲቴሽን መንፈሳዊ ፕራክቲሶች አይደሉም" የሚል ተጃጅሎ አጃጃይ ከገጠማችሁ ቅዳሴና ሶላት መንፈሳዊ አይደሉም እንዳላችሁ ቁጠሩት! ከሩቅ ምስራቅም ይሁን ከምዕራቡ መንፈሳዊ መመናጀር አርባ ክንድ ራቁ! ልጆቻችሁን አርቁ! ያለን መቀዣበር ይበቃናል! ማንም ሀላፊነት የማይሰማው የሐሳብ ሸቃጭና የገደል ማሚቱ ምሁር እየተነሳ ዋና የማትችሉ እናተን ወደባህር ሲወረውራችሁ አትወርወሩ ፤የወረወራችሁ ራሱ ዋና አይችልም... ማንም ከሚመጣው ጥፋት አያድናችሁም! ጆሮ ያለው ይስማ!

የፍቅረኞቻችሁን ስም ክንዳችሁ ላይ መነቀስኮ በራሱ ችግር አይደለም! ከመነቀሳችሁ በፊት ግን ይችን አዳምጡኝ! ብዙ ሰው ከተነቀሳችሁ በኋላ ብትለያዩ ምናምን ይላል ... እኔ እሱ አያሳስበኝም! ችግሩ ስታረጁ ታቱው አንዳንድ የትርጉም ለውጥ ሊያመጣ ይችላል! ለምሳሌ አባባ ሳህሌ ወጣት በነበሩበት ዘመን ውጥርጥር ያለ ጡንቻቸው ላይ የራሳቸውንና የባለቤታቸውን ስም ተነቀሱ! "ሳህሌ ፣ ያርበድብዱ " እንደውም የተረፈው ቦታ ላይ ጦርና ጋሻ ጨመሩበት! እያረጁ ጡንቻቸው ሲሟሽሽ ግን ከሚስታቸው ስም የተወሰኑ ፊደላት በቆዳቸው ሽብሽባት ውስጥ እየገቡ ተደበቁ ! እና የቀሩት ፊደሎች ሲነበቡ ትንሽ የባለጌ አይነት ሆኑ (ያው ትገምታላችሁ) ...🤔 የባሰው ነገር ደግሞ የተነቀሱት ጋሻ ቆዳቸውን ተከትሎ ወደታች ታጠፈና የተንጠለጠሉ ሁለት ፍሬዎች መሠለ ! በዛ ላይ ከላይ ጦሩ አለ..."ኧረ ወዲያ ሸፈን ያርጉት አንቱ ሰው አማረብኝ ብለው ነው? ሆሆ በስተርጅና " ይላሉ ሚስቲቱ ባዮት ቁጥር እፍረት ባንዣበበት ፊት! "ምን ሆነ "ብለው ቆዳቸውን ሳብ አድርገው ሲያዪት የተደበቁት ፊደላት ይወጡና ይስተካከላል ፤ ሲለቁት ይባልጋል! እንዲቹ ሲጨቃጨቁ ይውላሉ!

ሴቶች የሕይዎት ድራማ ናቸው! (አሌክስ አብርሃም) "ማህበረሰቡን ብሎም አገርን የለየለት ቀጣፊ ተዋናይ የሚያደርጉት እነማን እንደሆኑ ታውቃለህ? "አለኝ ጓደኛየ ኮስተር ብሎ! "ፖለቲከኞች?" አልኩ! "አይደሉም! ሴቶች ናቸው! ሴቶች! ስማኝ " ...አለኝ! ለመስማት ተዘጋጀሁ! ሰሞኑን ሆድ ብሶታል! የዚች አገር የድራማ ምንጮች ሴቶች ናቸው! እንደውም እነሱ ራሳቸው ድራማ ናቸው! ስክርቢቱን ሰይጣን ይፃፈው ራሳቸው እንጃለታቸው! መጀመሪያ በሜካፕ ፣በፀጉር ፣ በአነጋገር ራሳቸውን ይቀይሩና አንድ ሚስኪን ተመልካች ፊታቸው አስቀምጠው እየተስለመለሙ ኮለል ባለ ድምፅ የፍቅር ድራማ ይተውናሉ! ካስገቡት በኋላኮ ጎርፍ ነገር ናቸውኮ! የአንድ ሰው ቲያትር በለው! ምግብ አልበላኝ አለ ፣ እንደሌሎች ሴቶች እንዳልመስልህ ...ትራሴን አቅፌ አሰብኩህ ...እንዴት ብትወጅው ነው አሉኝ ...ወንዶች አስቸገሩኝ! ሚሊየነሩ ሰውየ መግቢያ መውጫ አሳጣኝ ...ዲያስፖራው ካልወሰድኩሽ ፓስፖርቴን እነጫለሁ አለ (ፀጉር የለውም መሰል) ወዘተ! ይሄው ሚስኪን ተመልካች በዚህ ቲያትር በፍቅር ጠብ ይላል! ራሳቸው መቆሚያ መቀመጫ አሳጥተው በትወና ጠረባ በጓደኞችና መንገደኞች ፊት በጉልበቱ ወድቆ ፕሮፖዝ ሊያደርግ ሲንበረከክ የደነገጡ ያልሰሙ ምናምን ለመመስል "ኦ ማ ይ ጋድ ....ምናምን" እያሉ ይተውናሉ(የተመልካቹ ቁጥር እንዴት እንደሚያድግ ተመልከት) አለና ቡናውን ፉት ብሎ ቀጠለ! ፊቱ ላይ ብስጭት አለ! በእርግጥ የብዙዎቹ ትወና አሪፍ አይደለም! ለጨዋታው ድምቀት ችግር የለውም! ከዛ ሽምግልና ሲላክ ተውኔቱን የቤተሰብ ያደርጉታል! ቤታቸውን ቀለም ቀብተው የሶፋ ልብስ ቀይረው (ወጣ ሲሉ ልጃቸው ይሄን ፍቅረኛዋን እየያዘችው እየሄደች እዛው ኑሮበታልኮ) ሳሎናቸውን ራስ ቲያትር አድርገው ይጠብቃሉ! ወላጆች ደግሞ ይተውናሉ! ሽማግሌዎች ይተውናሉ! ልጁ ማነው ? (ከነአያቱ ያውቁታልኮ) ተምሯል? (ከዘጠኝ አቋርጦ ምንጩ ባልታወቀ ሐብት መበልፀጉን ሽማግሌዎች ቢያውቁም አይናገሩም! እንደውም አሞት ነው ሶስተኛ ድግሪውን ያቋረጠው ሁሉ ይላሉ) ይጠጣል? (ይከለብሰው እያሉ በውስጣቸው) ኧረ ውሃ ራሱ ሲጠጣ ከአንድ አያልፍም ! ለምን ልጃቸው ምጥ ላይ አትሆንም "እኛ ልጃችን ወንድ አታውቅም ፤አንገቷን ደፍታ ነው ያደገችው ዋ ! እንዳያሳዝናት! እናተን አምነን ይሁን ብለናል!" ይላሉ! ባይሉም እንደማይቀር ያውቁታል! ይሄ ሁሉ ተዋናይ ድፍን አገሩን ጠርቶ የለየለት አዳራሽና መድረክ ተሰርቶ ዋናው ድራማ ይተውናል ሰርግ! ሰርግኮ ሙዚቃዊ ተውኔት በለው! ወግ ነው ሲዳሩ ማልቀስ ይሉና ሙሽሪት ትነፋረቃለች! በቀጣዩ ቀን ጧት እነዛ ሚዜ የሚባሉ ጥቃቅን ገፀ ባህሪያት " ብር አምባር ሰበረልዎ" እያሉ ቀለም የተቀባ መሀረብ ይዘው ይመጣሉ! ያውቃሉ በሰገሌ ጊዜ ....! ብቻ መናፈሻ ምናምን አለ! መንገድ ላይ ጠቅላይ ሚንስትሩም ሊያገኟቸው ይችላሉ ፤ እሳቸውም ህዝባቸውን የሚወዱ መሪ ሁነው ለመተወን አብረዋቸው ፎቶ ይነሳሉ!" ተውኔቱ አገራዊ ሆነ! ህዝቡ እየተጋባ ነው፤ የምን የኑሮ ውድነት የምን ስደት ይላል ተመልካች! አለና ጓደኛየ ተከዘ! ከሁለት ሳምንት በኋላ ነው ሰርጉ ..."የተውኔቱ መሃል ላይ ነህ በርታ ትዳር ፀጋ ነው " አልኩትና የዋናው ገፀ ባህሪ ጓደኛ ሆኘ ተወንኩ!

ቆጠራው (አሌክስ አብርሃም) እድሜየ እየገፋ እንደሆነ የገባኝ ፍቅረኞች ሲጣሉ አፈላልገው ሽምግልና ሲልኩኝ ነው! እኔም ስለሚያሳዝኑኝና በፍቅር ስለማልጨክን ለማስታረቅ እሞክራለሁ! በእርግጥ በእኔ ሽምግልና የታረቁ እስከአሁን አላጋጠሙኝም! ለምሳሌ ፍርቱናና ሳሙኤልን እንውሰድ! አንድ ቀን ሳሙኤል ደወለልኝና "ፍርቱና ትታኝ ሄደች፤ ሁለተኛ አይንህን አላይም አለችኝ እባክህ ድረስልኝ " ብሎ እንባ እየተናነቀው ነገረኝ! በእርግጥ ፍርቱና ውበት ከፀባይ አሟልቶ የሰጣት ጨዋ ልጅ ነች ደግሞ ታፈቅረዋለች "ምን አጣላችሁ?" አልኩ "ኧረ ተራ ነገር ነው አብርሽ ! ትራሴ ስር ማንነቷ ያልታወቀ አካል ዘለላ ፀጉር አገኘሁ በሚል ተልካሻ ምክንያት ነው" "ኦ ፀጉርማ ቀላል ነገር አይደለም ሳሚ" ብየ አካበድኩ! የፍርቱና ውብ ፀጉር ትዝ እያለኝ! "እውነቴን ነው! አንዷን አምጥተህ አስተኝተህበት ቢሆንስ ....ስንት ተላላፊ በሽታ አለ? ቋቁቻ አለ ፣ ቅጫም አለ ፣ እከክ አለ ፣ ጭርት አለ ችፌ አለ ....ሂውማን ሄር አለ ....ውብ ፀጉሯ ላይ ቢተላለፍባትስ?" "እንዴ ምነው አካበድከው? ለአንድ ዘለላ ፀጉር ይሄ ሁሉ ... ወይስ ፍርቱና ጋር ነገር አለህ? ብሎ ተቆጣ! "በምን እድሌ" ልል ከአፌ መለስኩት። የሆነ ሆኖ ፍርቱናን አግኝቸ ሳዋራት ወንዶች ውሸታችን ከኢኮኖሚያችን በላይ ማደጉ ነው የገባኝ! ተመልከቱ.... "ምን ነካሽ ፍርቱና ጥሩ ልጅ አልነበርሽ? አንድ ዘለላ ፀጉር አገኘሁ ብለሽ እንደዚህ ... " ከማለቴ ቱግ ብላ ፦ "አንድ ዘለላ ፀጉር አለህ? ይሄ ነው አንድ ዘለላ? ብላ ስልኳ ላይ ለኤግዚቢት የተያዘውን ፀጉር ፎቶ ስታሳየኝ ከብስጭት ይልቅ ሳቄ ቀደመኝ! እንደኮፍያ የሚጠለቅ ሂውማን ሄር ነው ትራሱ ስር ጉብ ብሎ የተገኘው! እኔማ የልጅቱን አንገት ከነፀጉሯ የቆረጠችው ነበር የመሰለኝ! በዚህ ኑሮ ውድነት ምንዓይነት ሴት ናት ይሄን የሚያክል ሂውማን ሄር ረስታ የሄደችው በፈጣሪ?" እያልኩ ሳስብ "ንገረኛ ይሄ ስንት ዘለላ ፀጉር ነው? አለችኝ ውብ ከንፈሯ በብስጭት ይንቀጠቀጣል! ውብ ናት በተለይ እንዲህ ስትበሳጭ .... "ብዙ ነው! ለምን እኔ ቤት ሄደን አንቆጥረውም?"

አስቻለው እንዴት በቁሙ ጠፋ? (አሌክስ አብርሃም) ሰባተኛ ክፍል ሆነን አስቻለው የሚባል ጉልበተኛ ልጅ ነፊሳ ከምትባል ተማሪ የፈተና መልስ እየተቅለሰለሰ ኮረጀ! ብዙሀኑ የሚያደርገው ነው! ችግሩ አስቻለው የኮረጀው ከነስሟ ስለነበር ክፍላችን ውስጥ ሁለት ነፊሳ ኖረና አስቻለው ግን እያለ ሳይኖር ቀረ። ያን ሁሉ ጡንቻ ፣ያን ሁሉ ተፈሪነትና የድብድብ ብቃት ይዞ በአኮራረጅ ችግር በቃ ሳይኖር ቀረ! በዚህ የተናደደው አስቻለው ወደማንነቱ ከመመለስ ይልቅ ነፊሳን ጠራና ኮስተር ብሎ "ነፊሳ አይደለሁም በይ" አላት! "እና ማነኝ? " አለች በፍርሃት ፤ "አስቻለው ነሽ!" አላት! "እንዴ! አንተስ ማነህ?" "ነፊሳ ነኝ! " አለና ወደእኛ በቁጣ ዙሮ "አይደል እንዴ? " ሲለን "ልክ ነህ ነፊሳ" አልነው! ነፊሳ ዘወርወር አለባት! ሁለቱም ሰባተኛውን መልስ " False " ብለው በትክክል ከመሳሳታቸው በተጨማሪ አስቻለው በትክክል ባለመኮረጁ ተጨማሪ ሰባት መልስ ተሳስቶ ነበር! ይሄ ዘመን የአስቻለው ዘመን ይመስለኛል! የኮረጁት ልክ እንዲሆኑ ልክ የሆኑትን የማሳደድ ዘመን!

ቀጥ ብለህ ቁም! (አሌክስ አብርሃም) ጎተራ ኮንዶሚኒየም ስኖር ወጣት ባልና ሚስት ጎረቤቶች ነበሩኝ! በጣም የሚፋቀሩ ! እና ሌሊት ሌሊት አንዳንድ ተቀባይነት የሌላቸው ድምፆች ያለዕቅድ ግድግዳውን አልፈው ይረብሹኝ ነበር! ሌላ ሌላው ነገር ሳይሆን በተለይ ሚስቱ የባሏን ስም በቁልምጫ ስትጠራው "ምናለ ይሄን ለቁልምጫ የማይመች ስም ቢያስቀይረው" እያልኩ በሌሊቱ አስባለሁ! ወይም የብዕር ስም እንደሚባለው የእንትን ...ስም ቢጠቀሙ! ከነገሩ ይልቅ የስሙ ቁልምጫ ነበር በሀፍረት ጆሮየን የሚያግለው! (ለአንባቢወቸ የስነ ልቦናና የስነ ተዋልዶ ስሜት ስል ስሙን እዘለዋለሁ) አንድ ቀን ድንገት ቤቱን ለቀው ሄዱ! ለአንድ ሳምንት ከደበረኝ በኋላ😀 ሌሎች ባልና ሚስቶች ተከራዮች ገቡ! በተለይ ሚስትየዋ የፆሎት ሰው ነች! ባሏ ስራ ሲሄድ ቤቷን ዘግታ ይሄን አጋንንት ስትለበልበው ነው የምትውለው...ከጎተራ ልቀቅ ...ከሳሪስ ልቀቅ ...ከቦሌ ልቀቅ...ከቡልቡላ ....ስገስፅ ነው የምትውለው! ለወሬ ነጋሪ አንድ አጋንንት አዲሳባ አታስቀርም! ድምጿ ራሱ ጎርናና እና አስፈሪ ከመሆኑ ብዛት እኔ ራሱ ልለቅ ይቃጣኝ ነበር! ፀባችን ከስጋና ደም አይደለም ስትል ሻንጣየን አስቀምጨ ተረጋጋሁ! እና አንድ ሌሊት ያ ድምፅ አነቃኝ ! መጀመሪያ ሹክሹክታ ነበር በኋላ ግን ድምጿ ጨመረ " በአንተ ላይ በተሰጠኝ ስልጣን አዝሃለሁ... ቀጥ ብለህ ቁም ! የተፈጠርክበትን አላማ ትፈፅም ዘንድ ቀጥ ብለህ ቁም ! ስራህን እስክታከናውን ፀንተህ ቁም! የሚያልፈሰፍስህ መንፈስ አሁን ተመታ! ..." "አሜን" ይላል ባሏ በሚያሳዝን ድምፅ! ምንድነው ይሄ ቁም የሚባል ነገር ? ብየ እኔም በቀስታ ፀለይኩ "ጌታ ሆይ ምንም ድምፅ የማያሳልፍ ግድግዳ ባለው ቤት ባርከኝ! ልጅህን ክፉ የሚያሳስበውን መንፈስ ከጎተራ ...ወሎ ሰፈር ...ከቦሌ... ከቡልቡላ ...ንቀለው! ከሶስት ወር በኋላ ፆሎቴ ሰመረ እኔን ከጎተራ ነቀለኝ!

የትምህርት ዕድል ያመለጠህ መስሎህ ነው? ገና ሺህ የትምህርት ዕድሎች አሉህ:: ዕድሜህ ያመለጠህ መስሎህ ነው? ነገ የሚጠብቁህ ብሩሕ ዘመናት እኮ ቁጭ ብለው አሉ? የሚረዳኝ ሰው የሚያስብልኝ ሰው አጥቼያለሁ? ብለህ ከሆነም ካልሰሙህ ጥቂቶች በላይ ልንሰማህ የምንሻ "ሁላችን ከዚህ አለንና በራስህ ክፉ ነገር አታድርግ" መከራ ጸናብኝ ኑሮ ጨለመብኝ የሀገሪቱ ሁኔታ ተስፋ አሳጣኝ ብለህ ይሆን? እኛስ አብረንህ አይደልንም? አብረን ከገባንበት ችግር አብረን ብንወጣ አይሻልም? ከአንተ በባሰ ሁኔታ የታሰርንና የተገረፍን ጳውሎሶችና ሲላሶች "ሁላችን በዚህ አለንና በራስህ ክፉ አታድርግ" ስንልህ ስማን:: ይልቅ አንተም እንደ ወኅኒው ጠባቂ "እድን ዘንድ ምን ላድርግ ብለህ?"ነፍስህን የምታድንበትን መንገድ ወደ መቅደሱ ቀርበህ ጠይቅ:: ወዳጄ ይህንን ጽሑፍ ያነበብኸውም በሕይወት ስላለህ ነው:: የአንተን ዓይን የሚጠብቁ ብዙ ጽሑፎች ፣ የአንተን ጆሮ የሚፈልጉ ብዙ ድምፆች ፣ የአንተን መሐረብ የሚፈልጉ ብዙ ዕንባዎች ፣ የአንተን ሳቅ የሚፈልጉ ብዙ ቀልዶች ... ገና ብዙ ብዙ አሉ:: ስለዚህ ሰይጣንን አሳፍረው:: እንዲህ በለው :- "ጠላቴ ሆይ፥ ብወድቅ እነሣለሁና፥ በጨለማም ብቀመጥ እግዚአብሔር ብርሃን ይሆንልኛልና በእኔ ላይ ደስ አይበልሽ" ሚክ. 7:8 ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ ጥቅምት 2016 ዓ.ም. ሜልበርን አውስትራሊያ ለተጨነቀች ነፍስ ዕረፍት የሆነው የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ :: እኔም ለእናንተ ከሰበክሁ በኁዋላ የተጣልሁ እንዳልሆን አጥብቃችሁ ስለ እኔ ጸልዩልኝ! በኮሜንት መስጫው ሥር "ለሚሰሙት ጸጋን ይሰጥ ዘንድ፥ እንደሚያስፈልግ ለማነጽ የሚጠቅም ማናቸውም በጎ ቃል እንጂ [ዋጋን በምድር የሚያስቀር ውዳሴም ሆነ ሌላ] ክፉ ቃል ከአፋችሁ ከቶ አይውጣ" (ኤፌ 4:29)

+ በራስህ ክፉ ነገር አታድርግ + ይድረስ ለተከፋኸው ወንድሜ መኖር ለደከመህ ፣ ሕይወት ለታከተህ ፣ የሚሰማህ ላጣኸው ፣ የሚረዳህ ሰው ላላገኘኸው መከረኛው ወዳጄ! ከሞት ውጪ ሌላ መፍትሔ አልታይ ካለህ የአንተ ቢጤ መከረኞቹ ጳውሎስና ሲላስ እስር ቤት ውስጥ ሆነው እንዲህ ይሉሃል:: "በራስህ ክፉ ነገር አታድርግ" ሐዋ. 16:28 አውቃለሁ ዙሪያው ገደል ሆኖብሃል:: ምነው ባልተፈጠርሁ እስክትል ድረስ ተጨንቀሃል:: ግን ይህ ስሜት በአንተ አልተጀመረም:: ሰው ሆኖ ተፈጥሮ ኑሮ ያልመረረው ማን አለ? መሞት ያልተመኘስ ማን አለ? ሞት ያማረህ አንተን ብቻ መሰለህ? " ስለ ምን ከማኅፀን አወጣኸኝ? ዓይን ሳያየኝ ምነው በሞትሁ" ያለውን ጻድቅ ኢዮብ አልሰማህም? (ኢዮ. 10:18) "ከአባቶቼ አልበልጥምና ነፍሴን ውሰድ" ብሎ እንዲሞት የለመነውን ኤልያስን አላየኸውም? 1ነገሥ. 19:4 ዮናስንስ "አሁንም፥ አቤቱ፥ ከሕይወት ሞት ይሻለኛልና እባክህ፥ ነፍሴን ከእኔ ውሰድ፡ አለው" ሲል አልሰማኸውም? (ዮናስ 4:3) ወንድሜ እመነኝ ምክንያቱ ምንም ይሁን ምን መኖር ያላስጠላው ሰው በታሪክ ፈልገህ አታገኝም:: ሞት ሞት የሸተተው ልቡ የተሰበረ ብዙ ነው:: አንተ ላይ ብቻ የደረሰ ልዩ ፈተና የለም:: "ለሰው ሁሉ ከሚሆነው በቀር ምንም ፈተና አልደረሰባችሁም፤ ነገር ግን ከሚቻላችሁ መጠን ይልቅ ትፈተኑ ዘንድ የማይፈቅድ እግዚአብሔር የታመነ ነው፥ ትታገሡም ዘንድ እንድትችሉ ከፈተናው ጋር መውጫውን ደግሞ ያደርግላችኋል" ይላል መጽሐፍ:: 1ኛ ቆሮ. 10:13 ምናልባት የልብህን መሰበር የኀዘንህን ጥልቀት አይቶ ምቹ ጊዜ አገኘሁ ብሎ ራስህን እንድትጎዳ ሰይጣን ሊገፋፋህ ይችላል:: እንዴት እንዲህ ዓይነት ሃሳብ በልቤ ሊመጣ ቻለ ብለህ አትረበሽ:: ሰይጣን ይህንን ክፉ ሃሳብ ላንተ ብቻ ሳይሆን ለክርስቶስም አቅርቦለታል:: "የእግዚአብሔር ልጅስ ከሆንህ፥ ወደ ታች ራስህን ወርውር" ብሎ ክርስቶስን እንኳን [ማንነቱን ሳያውቅ] ራሱን እንዲወረውር ሊገፋፋው የሞከረ ደፋር ነው:: የእግዚአብሔር ልጅ የሆነ ሰው ግን ራሱን አይጎዳም:: "ጌታ አምላክህን አትፈታተነው" "ሒድ አንተ ሰይጣን" ብለህ ሰይጣንን ገሠፀው:: ሰይጣን ክርስቶስን "ከሕንፃ ጫፍ በመወርወር የእግዚአብሔር ልጅ መሆንህን አሳይ" ሲለው ክርስቶስ ሰይጣንን ሒድልኝ ብሎ በመገሠጹ በክብር ወደ ሰማይ ዐርጎ በእግዚአብሔር ቀኝ ተቀመጠ:: ወንድሜ ሆይ አንተም ሰይጣንን አትስማው ሃሳቡ ራስህን ጎድተህ ከፈጣሪህ እንድትጣላ ሊያደርግህ ነው:: ሰይጣንን ከገሠጽከው በእግዚአብሔር ቀኝ ከበጎቹ ጋር ትቆማለህ:: አሁን ያለህበት ችግር ያልፋል:: የሚሰማህ ክፉ ስሜት መቼም የማይለወጥ አይምሰልህ:: ኀዘኑም ፣ ብቸኝነቱም ፣ ተስፋ ቢስነቱም ያልፋል:: ጨለማው ይነጋል:: የተዘጋው በር ይከፈታል:: ችግሩ ሲፈታ አንተ ከሌለህ ግን ትርጉም የለውም:: ስለዚህ ለሚፈታ ችግር የማይቀለበስ ውሳኔ አትወስን:: ራስን ማጥፋት ከጊዜያዊ ችግር ለመሸሽ ሲሉ ዘላቂ ችግር ውስጥ መግባት ነው:: ጊዜያዊ ሕመምን ለማስታገስ የዘላለም ሕመምን ለምን ትመርጣለህ? "የሞተ ተገላገለ" ሲሉ ሰምተህ እንዳትታለል ሞት ዕረፍት የሚሆነው ራሱ እግዚአብሔር ሲጠራህ ብቻ ነው:: "እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ወደ እኔ ኑ እኔም አሳርፋችኋለሁ" ያለው ጌታ ሳይጠራህ ራስን ማጥፋት የዘላለም ስቃይ ያመጣል:: ወዳጄ "በራስህ አንዳች ክፉ አታድርግ" የሕይወትህን ዋጋ ታውቅ ይሆን? አንተ እኮ የእግዚአብሔር ልጅ ለአንተ ሲል የሞተልህ ነህ:: ሊፈውስህ የቆሰለ ፣ ሊያከብርህ የተዋረደ ፣ ሊያረካህ የተጠማ ፣ ሊያለብስህ የተራቆተ ለአንተ እኮ ነው:: ክርስቶስ ስለ አንተ ሞቶአል:: አንተን ግን የጠየቀህ እንድትሞትለት ሳይሆን እንድትኖርለት ነው:: ለሞተልህ አምላክ እንዴት መኖር ያቅትሃል? ወዳጄ ሆይ ሰውነትህ በአምላክ ደም የተገዛ ክቡር ሰውነት ነው:: አካልህ "አንተ" እንጂ "ያንተ" አይደለም:: "በዋጋ ተገዝታችኋልና ለራሳችሁ አይደላችሁም፤ ስለዚህ በሥጋችሁ እግዚአብሔርን አክብሩ" ይላል ስለዚህ በከበረ የእግዚአብሔር ልጅ ደም የተገዛ ሰውነትህን ለሰይጣን በርካሽ አትሽጠው:: አትግደል የሚለው ሕግ ራስህንም ይጨምራል:: ቤተ መቅደስ የሆነ ሰውነትህን ለማፍረስ አታስብ:: "ማንም የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ቢያፈርስ እግዚአብሔር እርሱን ያፈርሰዋል፤ የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ቅዱስ ነውና፥ ያውም እናንተ ናችሁ" 1ኛ ቆሮ. 3:17 ሰዎች አስቀይመውህ ይሆን? "አሳያቸዋለሁ ፤ ስሞት የእኔን ነገር ይገባቸዋል" ብለህ በሰዎች ተቀይመህ ራስህን አትጉዳ:: እመነኝ ብትሞት ሰዎች ከሳምንት በላይ አያስታውሱህም:: ለሕይወትህ ዋጋ ያልሠጡ ሰዎች ለሞትህ ዋጋ አይሠጡም:: ፈጥነውም ይረሱሃል:: ለሚረሱህ ሰዎች ብለህ የማይረሳህን አምላክ አታሳዝን:: ሰው ስለ አንተ ግድ የለውም እግዚአብሔር ግን የራስህን ቁጥር ሳይቀር በቁጥር ያውቀዋል :: እንኳንስ ራስህን ልትጎዳ አንዲት ጸጉር እንኳን ከአንተ እንድትወድቅ አይፈልግም:: እግዚአብሔርን በኃጢአት ብታሳዝነው እንኳን ኖረህ ንስሓ እንድትገባ እንጂ እንድትሞት አይፈልግም:: አባትህ ነውና ከእርሱ ጋር ባትሆንም እንድትኖር ይፈልጋል:: በምሳሌ ልንገርህ :- ሁለት ሴቶች አንድን ሕፃን "የኔ ልጄ ነው" ብለው እየተከራከሩ ጠቢቡ ሰሎሞን ፊት ቀረቡ:: ጠቢቡ ሰሎሞን ሰይፍ አመጣና "ልጁን ቆርጬ ለሁለት ላካፍላችሁ" አላቸው:: አንደኛዋ ሴት "እሺ እንካፈል" ስትል እውነተኛዋ እናት ግን "ልጄ ከሚሞት እርስዋ ትውሰደው" አለች:: እናት መሆንዋም በዚህ ታወቀ:: ወዳጄ ያንተም ኑሮህ ከእግዚአብሔር ጋር ላይሆን ይችላል:: ዓለም የራስዋ አድርጋህም ይሆናል:: በሱስ ውስጥ ትዘፍቀህ ፣ እንደ ሶምሶን በደሊላ እቅፍ ፣ እንደ ዴማስ በተሰሎንቄ ውበት ተማርከህ ይሆናል:: እግዚአብሔር ግን አባትህ ነውና ሞትህን አይፈልግም:: "ልጄ ከሚሞት እርስዋ ትውሰደው" እንዳለችው እናት ፈጣሪህ ከነኃጢአትህም ቢሆን እንድትሞት አይፈልግም:: ከእርሱ ጋር ባትኖርም መኖርህን ይፈልጋል:: "የሟቹን ሞት አልፈቅድምና፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር፤ ስለዚህ ተመለሱና በሕይወት ኑሩ" ሕዝ. 18:32 የይሁዳ ኃጢአቱ ጌታውን መሸጡ አልነበረም:: ራሱን መግደሉ ነው:: እግዚአብሔር የሚያዝነው ከበደልህ በላይ በእርሱ ተስፋ ቆርጠህ ራስህን ስትጎዳ ነው:: ወዳጄ የአንተን መኖር የሚፈልጉ ብዙ ናቸው:: ፈጣሪ ወደዚህች ዓለም ያለ ምክንያት አላመጣህም:: በአንተ አለመኖርም የሚጎድል ነገር አለ:: አንተን የሚመስል ሌላ ሰው አልፈጠረምና ለዚህ ዓለም አንተን የሚተካ የለም:: በክብር ወደዚህ ዓለም ያመጣህ አምላክ በክብር ወደራሱ እስኪወስድህ ድረስ "በራስህ ላይ ክፉ ነገር አታድርግ" "የወኅኒውም ጠባቂ ከእንቅልፉ ነቅቶ የወኅኒው ደጆች ተከፍተው ባየ ጊዜ፥ እስረኞቹ ያመለጡ መስሎት ራሱን ይገድል ዘንድ አስቦ ሰይፉን መዘዘ። ጳውሎስ ግን በታላቅ ድምፅ፦ ሁላችን ከዚህ አለንና በራስህ ክፉ ነገር አታድርግ፡ ብሎ ጮኸ" ሐዋ. 16:27-28 ይህ ሰው እስረኛ ያመለጠ መስሎት ራሱን ሊያጠፋ ሲል ጳውሎስ "ሁላችን ከዚህ አለንና በራስህ ክፉ ነገር አታድርግ" አለው:: ወዳጄ አንተስ ተስፋ የቆረጥኸው ምን ያመለጠ መስሎህ ነው?

photo content

ፈጣሪን ለማክበር የእጁን ስራ ማንቋሸሽ ትሁትነት ነው? ሐይማኖተኝነት ነው? ወንጌል ነው? ምንድነው? በየመድረኩ ከመናገር አልፎ መዝሙር እስከማድረግ መድረስ? እኔን ትቢያውን እኔን ምናምንቴውን እኔን ቆሻሻውን እኔን የማረባውን እኛን የማንጠቅመውን እኔን ወለፈንዲውን እኔን አናሳውን እኔን ቁሪሳውን ... እኔን ዋጋ ቢሱን ከዛ አንስተህ ከዚህ አንስተህ ... ሰው የሆንከው ስሪ ፒስ ስለለበስክ ማይክ ስለጨበጥክ አይደለም! አማኝ የምትሆነውም ሰው ለመሆን አይደለም! ሰውነት ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ቀድሞ ሳይሸራረፍ የተሰጠህ ተፈጥሮ ነው! ነፃ ፈቃድህ የዚህ አንዱ መገለጫ ! እምቢ ትቢያ ነኝ ካልክ... የእውነት ስለሚገርመኝ ነው ... እስከሚገባኝ ሰው ትቢያም ምናምንቴም ቆሻሻም አይደለም ...ከትቢያ ኑሮ ከቆሸሸ አኗኗር ይወጣ ዘንድ የከበረ ዋጋ የተከፈለለት የከበረ ፍጡር ነው!"እፁብና ድንቅ ሁኘ ተፈጥሪያለሁ" እንዳለው መዝሙረኛው ዳዊት! አይ ትቢያ ነኝ ካልክ የራስህ ጉዳይ ነው! ምናገባኝ!

"ስንቱን እያጤሰው" (አሌክስ አብርሃም) " አላህ አላህ አላህ ... በቀን አስረዜ እንዳልተመላለስኩባት ፣ ይችው መንገድ ሁና ትንፉሸ ቁርጥ ቁርጥ አለኮ ....'እርጅና ብቻህን ና' አሉ ጋሽ ሲራጅ! ...እንዴት ዋላችሁ ? " አሉ ጎረቤታችን እማማ ሩቅያ ... በር ላይ ቁመው ጫማቸውን እያወለቁ ! ድምፃቸውን ስሰማ ደስ ይለኛል! እናቴ አንዳች ነገር ሊያድን እንደሚሮጥ ከጓዳ ተቻኩላ ወደበሩ ሮጠችና "አንቱ ደሞ ...በሉ ጫማሁን አርጉ ሁልጊዜ እንግዳ ትሆናለሁ እንዴ? " ... አለች እንዳያወልቁ እየታገለች! "አቧራውን ተሸክሜው ነው የመጣሁት አሴ ...ግዴለሽም... " "ግዴለሁም ገና ቤቱንም አልጠረኩት " አለች ! (ገና በጧት ነበር የጠረገችው ግን) ይሄው ነፍስ ካወኩ ጀምሮ እማማ ሩቁ እቤታችን በመጡ ቁጥር ይች የበር ላይ ክርክር የማትቀር ናት! "ሁሌ ከመጨቃጨቅ ቁጭ ብለው ተነጋግረው አንዴ ቢፈራረሙ " እላለሁ ለራሴ! "የታለ ኢብሩ ... እያሉ በአይናቸው ፈለጉኝ፤ ከውጭ ስለገቡ ቤታችን ጨልሞባቸው እንጅ አጠገቤ ነበሩ! ...ካልታመምኩ በስተቀር ከእናቴ የልብስ ሳጥን የማይወጣ አዲስ ባለቀይ ጥለት ጋቢ ለብሸ ፣ እንግዳ ካልመጣ የማይወጣ አዲሰ አልጋ ልብስ የለበሰች ድንክ አልጋችን ላይ ጋደም ብያለሁ! ጠያቂ ጎረቤት ይመጣል ተብሎ ቤታችን ዘንጣ ነው እንግዲህ! "ኢብሩ አላህ ያሽርህ እናቴዋ... አላህ ያሽርህ ...ያንተ ምላስና እግር ከተያዘማ ቢያምህ ነው ውነትም ..." እያሉ መጡና እናቴ ገና ቅድም ወደተኛሁበት ያስጠጋችላቸው ባለጠፈር ዱካ ላይ አረፍ ብለው ለስላሳ እጃቸውን ግንባሬ ላይ አሳረፉ! እጃቸው እቤታቸው የሚጨሰውን የወሎ ጭስ ይሸታል! መዳፋቸውን ግንባሬ ላይ እንዳደረጉት ከንፈራቸውን እያንቀሳቀሱ ቆዩና (ዱዐ ሳይሆን አይቀርም) ሲጨርሱ ወደእናቴ ዙረው "ሀኪሙ ምናለ?" አሏት "ኧረ ተውኝ ! ቆጣ ቆጣ የሚያረገው አዲስ ሀኪም ነው ...ታለዛሬም አይቸው አላቅ ! 'ብርድ ይሆናል መርፌ ውጋው' ብል ... 'ብርድ የሚባል ነገር የለም' አለኝ " "ብርድ የለም ? ስንቱን እያጤሰው?!" አሉ እማማ ሩቁ! እናቴ ጋር በረዢሙ መሳቅ ጀመሩ ! ሲስቁ ደስ ይሉኛል! አፋቸውን ከላይ ጣል በሚያደርጉት ክንብንብ ከለል አድርገው ሰውነታቸው እየተርገፈገፈ ...ሳቅ ባፈነው ድምፅ "ወላሂ ! እኔንኳ ስንተዜ አጢሶኛል" ሳቃቸው ቀጠለ ... ከዛን ጊዜ ጀምሮ እስካሁን "ስንቱን እያጤሰው" አሉ እማማ ሩቁ ይባላል በሰፈሩ ....እንደተረት !

አጭበርባሪ አምላክ (አሌክስ አብርሃም) በዓለማችን ላይ እውቅና ያላቸው አራት ሺ ሐይማኖቶች አሉ! ሁሉም "አንድ አምላክ ብቻ አለ ያም እኛ የምናመልከው ነው " ብለው ያስተምራሉ! ይሄ ማለት ሁሉም ቢያንስ 3999 ባልሰራው የሚመሰገን ፣ባልፈጠረው የሚመለክ ፣ ባልሰጠው ስለት የሚገባለት ፣ ባልተዋጋበት የሚሞገስ የሚወደስ ፣ ላይመጣ በተስፋ የሚጠበቅ ፣ ላያድን የሚማፀኑት አጭበርባሪ አምላክ መዓት አለ ብለው ያምናሉ ማለት ነው! ትክክለኛው አምላክ ትክክለኛ መንገዱን ይምራን እንጅ ሌላ ምን ይባላል🙏

"ጭንቅላትና ቅንጭላት" (አሌክስ አብርሃም) ከዓመታት በፊት በአንድ የአገራችን ትልቅ ዩኒቨርስቲ አቅራቢያ ያለች ካፌ በረንዳ ላይ ተቀምጨ እዛ ይማር የነበረ ልጅ እጠብቃለሁ! ፊት ለፊት ስድስት ተማሪዎች ተቀምጠው እንግሊዝኛ በየመሀሉ እየቀላቀሉ ያወራሉ ይሳሳቃሉ ይንጫጫሉ፤ አራቱ ሴቶች ሲሆኑ ሁለቱ ወንዶች ናቸው ! ሁሉም የከተማ ልጆች መሆናቸው ከአነጋገራቸው ከሁኔታቸው ያስታውቃል! አንድ እድሜው ዘጠኝ ወይም አስር የሚሆነው ጎስቋላ ህፃን የተቀቀለ እንቁላል በፕላስቲክ ሰሀን ካለአቅሙ ተሸክሞ ያለቀች ነጠላ ጫማውን እየጎተተ ወደበረንዳዋ መጣ ... የተቀቀለ እንቁላል እያዞረ የሚሸጥ ልጅ ነው! ተማሪዎቹ ልክ ተዓምር እንዳዩ ሁሉ እየተንጫጩ ጠሩት ...ህፃኑ አጠገባቸው ያለ ጠረጴዛ ላይ ሸክሙን ከማሳረፉ በየጃቸው እንቁላል አነሱ ... እናም የገረመኝ ነገር እዚህ ላይ ነው የተፈጠረው ... ተማሪወቹ እንቁላሉን ሰብሮ ለመላጥ ጠረጴዛው ጠርዝ ላይ ማጋጨት ወይም ልጁ የያዘውን የብረት ማንኪያ መጠቀም ይችሉ ነበር ፤ እነሱ ግን ልጁን "ጠጋ በል " እያሉ የልጁ የፈጠጠ ግንባር ላይ ነበር እያጋጩ የሚሰብሩት ... ልጁም የልጅ ፈገግታ ፈገግ እንዳለ እንደግዑዝ እቃ ራሱን ያስጠጋላቸዋል! ከሽ ያደርጉና በግሩፕ አካባቢውን በሚረብሽ ድምፅ ያሽካካሉ! ያውም የእኔ ተራ ነው እየተባባሉ! አምስት እንቁላል ቆጠርኩ ...በአካባቢው የነበረው ሰው የሆነ ነገር ይላል ብየ ብመለከት እንደተለመደ ነገር ፈገግ ብሎ ያያቸዋል! ከተማሪዎቹ አንዷ ብቻ ኮስተር ብላ ትቆጣቸዋለች ....ደጋግማ አቁሙ ትላለች ...እናም በመጨረሻ ጮክ ብላ በእንግሊዝዝኛ እንዲህ አለቻቸው " ልጁ ንፁህ አይደለም" ያሳቀቃት ንፁህ ባልሆነ ህፃን ግንባር ላይ የሚበላ ነገር መስበራቸው እንጅ ልጁን እንደእንቁላል መስበሪያ መጠቀማቸው አልነበረም! እንቁላል ባየሁ ቁጥር ይሄ ደባሪ ነገር ትዝ ይለኛል!

photo content

photo content

አለማየትን ማየት! (አሌክስ አብርሃም) መቸም ማንም ሰው የለበሰውን ልብስ፣ ያለውን ደህና ነገር፣ ላቡን ጠብ አድርጎ ያፈራውን ሀብት ፣ ስኬቱን ዘመድ ወዳጅ ቢያይለት ደስ ይለዋል! "ለምን ሀብታም ከሆነ ሌሎችን አይረዳም" የሚል በሰው ገንዘብና ፍላጎት የማዘዝ ፍላጎቱም ስልጣኑም የለኝም! ግን የራበው ሰው ፊት "ተርፎኝ የምደፋውን ምግብ ተመልከት" ዓይነት የሌሎችን ስሜት የሚጎዳ እንቁልልጭ የሚያሳፍር ነገር ነው! ሚዲያው በዚህ የታይታ ነገር ተበክሏል! ቤቴን እዩ፣ ልብሴን እዪ ፣ውበቴን እዪ ልጀን እዩ ሚስቴን እዩ ባሌን እዩ ... በቃ ታይቸ ልሙት! አታሳዩ የሚል ምድራዊ ህግ ባይኖርም የሞራል ህግ ግን አለኮ ! ይችን ነገር ያዝ ... Dwayne Johnson ወይም በአድናቂዎቹ አጠራር "The Rock" ዱኒያ የተትረፈረፈለት ቤቱን መኪናውን ምናምኑን ሳይጨምር 800 ሚሊየን ዶላር የሚገመት ሀብት ባለቤት ነው...ወደየትም ሲሄድ የአለማችን ምርጥና ዘመናዊ የጅም (የስፖርት መስሪያ ቁሳቁሶች) ተሸክሞ የሚከተለው አውሮፕላን አይጠፋም! ታዲያ ስለስፖርት ይመክራል ያበረታታል ፤ እንዴት መስራት እንዳለባቸው በራሱ የሶሻል ሚዲያ አካውንቶች ያሳያል፤ በእነዚህ ውድ እና ቅንጡ መሳሪያወች ስፖርት ሲሰራ ግን ብዙም ሶሻል ሚዲያ ላይ ፎቶና ቪዲዮ አይለቅም ! ሚሊየኖች ይከተሉታል! ... "ለምንድነው እኒህን ውድ ቁሳቁሶች የማታሳየው" አለችው ጋዜጠኛዋ .... (((የስፖርት ፍቅር ያላቸው ግን እኒህን መሳሪያዎች ማግኘት የማይችሉ ስሜታቸው እንዲጎዳ፣ የበታችነት እንዲሰማቸው አልያም የተጋነነ ምኞት ውስጥ እንዲገቡ ስለማልፈልግ ነው! ))) አለ! ጓድ ( ጓዲቶች ) አንተ ስትታይ ሀዘን ሰዎች ውስጥ የበታችነትና መገፋት የሚፈጠር ከሆነ፣ አንተ እነሱን እያቸው፤ ያኔ አንተ ውስጥ ደግነት ይፈጠራል! መታየትህን ሳይሆን አለማየትህን ነው ማየት!

" ጤና ካለህ ፣ውለህ የምትገባበት ስራ ካለህ፣ የዕለት ጉርስ የአመት ልብስ ካለጣህ ...ፈጣሪህን ተመሰገን ብለህ በሰላም በደስታ መኖር ነው " የሚል ምክር በአገራችን በጣም የተለመደ ነው ... የእውነት ግን እነዚህ ነገሮች ለሰላምም ሆነ ለደስታ ዋስትና ይሰጡናል ወይ? የሰው ተፈጥሮ እንደዛ ነው ? የሚበዛው ተማራሪ እነዚህ ነገሮች ያሉት አይደለም ወይ?

ጤናማ የሆነ ውድድርኮ ጥሩ ነው! የኛን አገር ለየት የሚያደርገው ጠበቃው ከመሐንዲሱ ጋር ይፎካከራል፣ ፓይለቱ ከሀኪሙ ጋር ፣ አራት የወለደችው ባለትዳር ከአስራ ሰባት አመት የሀይስኩል ቀበጥ ጋር ... ጋዜጠኛው ከእምነት ሰባኪው ፣ ፖለቲከኛው ከሯጩ ..አንዱ አንዱን ለመናቅና ለማንቋሸሽ ያለው ፍላጎት ደግሞ ልክ የለውም! ለምን በራሳችን 'ትራክ' እንደማንሮጥ አይገባኝም!

እና ዘፈን ሀጢያት አይደለም? (አሌክስ አብርሃም?) የእምነቱ እና የጥቅሱን ጉዳይ እናቆየውና እንዲህ እንየው ... ስለገጠር ሴቶች ቁንጅና ስንት ዘፋኝ ዘፈነ? እስቲ አስታውሱ ! " እንስራዋን ይዛ ውሃ ስትቀዳ...ልቤ ሸፈተላት ለገጠሯ ቆንጆ ... " (ለምን እንስራዋን አይሸከምላትም?) በሰው ድካም ሮማንቲክ ለመሆን ይጣጣራል እንዴ? ከገባየ ስትመለስ ትርንጎ ይዛ ልቤ ተከትሏት ሄደ ... አንች የገጠር ወጣት ነይ አብረን እንኑር ...የአደሷ ሽታ ይጠራል ከሩቁ ...(ዞር ብሎኮ የቅቤዋ ሽታ ይቆንናል ባይ ነው) ሹርባሽ አራደኝ እንጨት ስትለቅሚ ... እንኮይ የመሰለች የገጠሯ ጉብል ሎሚ ተረከዟ ... እሽ ከመጨረሻው እንጀምር ..."ከሎሚ ተረገዟ የገጠር ሎጋ " ማለቴ ነው ወገኖቸ እኔ መቸም በሰሜንም በደቡብም በምስራቅም በምዕራብም ያለ ገጠር አይቻለሁ ...በዚህ ሁሉ ዙረቴ አንዲትም ሎሚ ተረከዝ ያላት የገጠር ሴት አልያም የገጠር ሴት ተረከዝ የመሰለ ሎሚ አይቸ አላውቅም! ከልጅነት እስከዕውቀት በባዶ እግሯ ምድጃ ለምድጃ ስትዳክር ፣እርሻ ውስጥ ስትማስን እግሯ በሙጀሊ እዳውን ያየ ፣ ተረከዟ መጅ ያወጣ፣ ጥፍሯ በእንቅፉት የተገማመጠ የደደረ ፣ገበያ ወጣ ካለች እግር በላብ በሚያንገረግብ የቻይና ኮንጎ ጫማ የሰዓታት የእግር መንገድ የምትጓዝ ሴት ተረከዟ በምን ሒሳብ ሎሚ ሆነ? ለናሙና ሶስት ሚሊየን የገጠር ሴት ብትወስዱ አንድም ተረከዘ ሎሚ አታገኙም! ለዛ ነው የገጠር ሴት ወክለው የከተማ አልዝዞች የቪዲዮ ክሊፕ የሚሰሩት!የገጠር ዘፋኝ ራሱ ትንሽ "ሲሰለጥን" የከተማ ሴት ነው የሚያገባው! ሁለተኛውና አንገብጋቢው ጉዳይ ይሄን ሁሉ ሙገሳ የሰማች የገጠር ሴት ጓዟን አዝላ ከተማ ብትመጣ ምን ይጠብቃታል? ፍቅር? ልነጠፍልሽ የሚል የከተማ ወንድ? እርሱት! እጣ ፋንታዋ ወይ የቤት ሰራተኛ አልያም ሴተኛ አዳሪ መሆን ነው! እና ዘፈን ሀጢያት ነው ብንል ይፈረድብናል?😀

photo content