en
Feedback
ጥላ ሚድያ - Tila Media

ጥላ ሚድያ - Tila Media

Open in Telegram

ይህ ቻናል ለቤተክርስቲያን ዘብ የሚቆም በመምህር ሄኖክ አስቻለው የሚመራ ለመንፈሳዊ ህይወቶጥዑም የሆኑ ቃለ እግዚአብሔር የምታገኙበት ነው ።በሁሉም ቦታ ጥላን ይምረጡ !!" ጥላ ያሳርፋል"👇https://youtube.com/@tilamedia?si=oo2BNrtCwXRjXmYk

Show more
6 582
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
-6430 days
Posts Archive
ውድ የተዋህዶ ልጆች ሰላመ እግዚአብሔር ይብዛላችሁ ።አንድ የማስቸግራችሁ ነገር አለኝ መምህር ሄኖክ ነኝ አዲስ የዩቱብ ቻናል ከፍቻለሁ ኦርቶዶክሳውያን ሰብስክራይብ አድርጉኝ ለሌችም በማስደረግ እግዛችሁ ያስፈልገኛል🥺🙏 ሰብስክራይብ ስላደረጋችሁ አመሰግናለሁ 🙏🥺       የዩቱቡ ሊንክ👇 https://www.youtube.com/@tilamedia

ውድ የተዋህዶ ልጆች ሰላመ እግዚአብሔር ይብዛላችሁ ።አንድ የማስቸግራችሁ ነገር አለኝ መምህር ሄኖክ ነኝ አዲስ የዩቱብ ቻናል ከፍቻለሁ ኦርቶዶክሳውያን ሰብስክራይብ አድርጉኝ ለሌችም በማስደረግ እግዛችሁ ያስፈልገኛል🥺🙏 ሰብስክራይብ ስላደረጋችሁ አመሰግናለሁ 🙏🥺       የዩቱቡ ሊንክ👇 https://www.youtube.com/@tilamedia

+1
TikTok - Haq Pictures.mp452.39 MB

ሐዋርያው መነኩሴ ሐዋርያው መነኩሴ የመረጡህ ሥላሴ/2/ ዋስ ጠበቃ ሁናት ተክልዬ(ጻድቁ) ለነፍሴ አዝ ዳሞት ትናገረው የአንተን ሐዋርያነት የወንጌል ገበሬ የጣኦታት ጠላት ጸሎተኛው ቅዱስ አባ ተክለሐይማኖት ክንፍን የተሸለምክ እንደ ሰማይ መልአክ/2/ አዝ ብራናው ሲገለጽ ገድለ ተክለሐይማኖት ከሰወ ልጅ ልቦና ያወጣል አጋንት የቅዳሴው ዕጣን ሲወጣ ከዋሻው ምድርን ይባርካል ጸሎቱ ምህላው/2/ አዝ የኢትዮጵያን ምድር አርስከው በወንጌል ጭንጫው ፈራረሰ ተዘራበት ወንጌል ትላንት የዘራኽው ዛሬ ለእኛ ሆኗል አምላከ ተክልዬ ብለን ተምረናል /2/ አዝ ከሱራፌል ተርታ ቆመህ ስታጥን ቅዱስ ቅዱስ ብለህ ስታመሰግን ጸሎት ትሩፋትህ ትህትና ስግደትህ ፆምህ ከፍ አድርጎ ሰማይ አደረሰህ/2/ አዝ ዛፉ ሲመነገል አምላክ የተባለው መቶሎሚ ሲያፍር ትልቅ ሰው ነኝ ያለው የተክልዬ ጸሎት ብዙ ነው ምስጢሩ ስድስት ክንፍ አወጣ ቢቆረጥ አንድ እግሩ/2/

+2

#ጾመ_ነቢያት_የገና_ጾም ✞  👉🏽 ገና ሚባል በተለምዶ ነዉ ጌና ነዉ ትክክለኛዉ ጌና  ብሂል ልደተ ክርስቶስ አምላክ እንዲል፡፡ ❖ ጾመ ነቢያት በየዓመቱ ከኅዳር ፲፭ ቀን ጀምሮ እስከ በዓለ ልደት ዋዜማ ድረስ የሚጾም፤ ከሰባቱ አጽዋማት መካከል አንደኛው ጾም ነው፡፡ እግዚአብሔር አምላክ ዓለምን ለማዳን ሲል የሰውን ሥጋ ስለ መልበሱ፤ ወደ ግብጽ ስለ መሰደዱ፤ በባሕረ ዮርዳኖስ ስለ መጠመቁ፤ በትምህርቱ ብርሃንነት ጨለማውን ዓለም ስለ ማብራቱ፤ ለሰው ልጆች ድኅነት ልዩ ልዩ መከራን ስለ መቀበሉ፤ ስለ መሰቀሉ፣ ስለ ሞቱ፣ ትንሣኤው፣ ዕርገቱና ዳግም ምጽአቱ በየዘመናቱ የተነሡ ቅዱሳን ነቢያት በመንፈስ ቅዱስ ተቃኝተው ትንቢት ተናግረዋል፤ ትንቢቱ ደርሶ፣ ተፈጽሞ ለመመልከትም ‹‹አንሥእ ኃይለከ ፈኑ እዴከ፤ ኃይልህን አንሣ፤ እጅህን ላክ›› እያሉ በጾም በጸሎት ተወስነው አምላክ ሰው የሚኾንበትን ጊዜ በቀናት፣ በሳምንታት፣ በወራትና በዓመታት እያሰሉ ሲጠባበቁ ቆይተዋል፡ ✤ ይህ ጾም የእግዚአብሔርን ሰው መኾን ሲጠባበቁ የኖሩት የነቢያት ትንቢትና ጸሎት በጌታችን መወለድ ፍጻሜ ያገኘበት ወቅት በመኾኑ ‹‹ጾመ ነቢያት (የነቢያት ጾም)›› እየተባለ ይጠራል፡፡ ለአዳም የተነገረው የድኅት ተስፋ ስለ ተፈጸመበትም ‹‹ጾመ አዳም (የአዳም ጾም)›› ይባላል፡፡ ❖ ስለ እግዚአብሔር ሰው መኾን በስፋት ትምህርተ ወንጌል የሚሰጥበት ወቅት በመኾኑም ‹‹ጾመ ስብከት (የስብከት ጾም)››፤ የጾሙ መጨረሻ (መፍቻ) በዓለ ልደት በመኾኑ ደግሞ ‹‹ጾመ ልደት (የልደት ጾም)›› በመባል ይታወቃል፡፡ እንደዚሁም ‹‹ጾመ ሐዋርያት›› ይባላል፡፡ ቅዱሳን ሐዋርያት ‹‹በዓለ ትንሣኤን ዐቢይ ጾምን ጾመን እናከብረዋለን፤ በዓለ ልደትንስ ምን አድርገን እናከብረዋለን?›› በማለት ነቢያት የጾሙትን ከልደተ ክርሰቶስ በፊት ያለውን ጾም ጾመዋልና፡፡      ✤ በተመሳሳይ መልኩ ይህ ጾም ‹‹ጾመ ፊልጶስ (የፊልጶስ ጾም)›› ተብሎ ይጠራል፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ፊልጶስ በአፍራቅያና አውራጃዋ ዅሉ እየተዘዋወረ በጌታችን አምላካችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ወንጌልን በማስተማር፣ ድንቅ ድንቅ ተአምራትን በማድረግ ብዙዎችን ወደ አሚነ እግዚአብሔር ሲመልስ ቆይቶ ትምህርቱን በማይቀበሉ የአፍራቅያ ሰዎች አማካይነት በሰማዕትነት ዐርፏል፡፡ ደቀ መዛሙርቱ ሥጋውን ሊቀብሩ ሲሉም ስለ ተሰወረባቸው የሐዋርያውን ሥጋ ይመልስላቸው ዘንድ ሱባዔ ይዘው፣ በጾም በጸሎት ተወስነው በለመኑት ጊዜ እግዚአብሔር ልመናቸውን ተቀብሎ በ፫ኛው ቀን መልሶላቸው ሥጋውን (አስከሬኑን) በክብር አሳርፈውታል፡፡ ደቀ መዛሙርቱ የሐዋርያውን ሥጋ ካገኙ በኋላ እስከ ጌታችን ልደት ድረስ ጾመዋል፡፡ ስለዚህም ጾመ ነቢያት ‹‹ጾመ ፊልጶስ›› እየተባለ ይጠራል፡፡        ❖ ከዚሁ ዅሉ ጋርም ወልደ አምላክ ክርስቶስን በግብረ መንፈስ ቅዱስ እንደምትፀንሰው እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ካበሠራት በኋላ እመቤታችን ‹‹ሰማይና ምድር የማይወስኑትን አምላክ ፀንሼ ምን ሠርቼ እወልደዋለሁ?›› በማለት ጌታችንን ከመውለዷ አስቀድማ ጾማዋለችና ይህ ጾም ‹‹ጾመ ማርያም›› በመባልም ይታወቃል፡፡ @Terha_Tsion #የጾመ_ነቢያት_መግቢያ የጾመ ጌና መግቢያ ሁልጊዜ (በአራቱም ወንጌላውያን) ኅዳር 15 ቀን ይገባል፡፡ ይህን አስመልክቶ የሕጉ መጽሐፍ #ፍትሐ_ነገሥት "ወጥንተ_ዚኣሁ_መንፈቀ_ኅዳር_ወፋሲካሁ_በዓለ_ልደት" መጀመሪያው የኅዳር እኩሌታ ፋሲካውም የልደት በዓል ነው ይላል (አን 15) እኩሌታ የሚለውን ይዘው የኅዳር እኩሌታ 16 ነው የሚሉ አሉ፡፡ ለዚህ ምላሽ የሚሆነን! *15+15=30 ይሆናል እንጅ 15+16=30 አይሆንም፡፡ * መንፈቁ ለኅዳር ዝ ውእቱ ሚናስ ይላል #የቅዱስ  ሚናስ  በዓሉ ነገ መሆኑ ልብ እንበል። (በ15) *ስንክሳሩ ወበዛቲ ዕለት አመ ፲ወ፭ ጥንተ ባዓለ ጌና በኅዳር 15 ቀን የገና ጾም መጀመሪያ ነው ይላል፡፡ (ስንክሳር ዘኅዳር 15) @Terha_Tsion *ፍትሐ ነገሥቱ የኅዳር እኩሌታ ብሎ በማለቱ *ቅዱስ ሲኖዶስ በ1983 ጾሙ በአራቱም ወንጌላውያን በኅዳር 15 ብቻ እንዲገባ ወስኗል፡፡ ሌላኛው በኅዳር 19 ይገባል የሚለው የተቀብዐ ወገኖች ሐሳብ ነው ስንክሳራችን ግን በዚህችም ዕለት የሮም፣ የአፍርንጊ፣ የሶርያ፣ የአርማንያ ክርስቲያኖች ከግብጽ፣ከኢትዮጵያና ከኖባ በቀር   የጌናን ጾም የሚጀምሩበት ነው ይላል  (ስንክሳር ዘኅዳር 19) ስለዚህ የ19 መግቢያ የኛ ባሕል አይደለም፡፡