AHADU
Open in Telegram
የ 𝚈𝙾𝚄 𝚃𝚄𝙱𝙴 ቻናሌን 𝚂𝚞𝚋𝚜𝚌𝚛𝚒𝚋𝚎 👏 ያድርጉ 👇👇 👇👇 https://www.youtube.com/c/Ahadu ለማንኛውም አስተያየትዎ - @Ahaduu
Show more9 594
Subscribers
No data24 hours
-357 days
-15430 days
Posts Archive
9 594
ZZZZZZZZZZZZXXXXXXXXXXXXXXXXXXXXXXXXXXXXXXXXXXZZZZZZZZZJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJJVCCCCCCCCCCCCCCCCPUHYYYYYYYYYYYYYYYYYYYYYYYYYYYYYYYYYYYYYY0IU VCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCCC-00[
9 594
Repost from AHADU
𝙰𝙷𝙰𝙳𝚄
ውሃ በተሞላ ድስት ውስጥ አንዲት እንቁራሪት ብንጨምርና ከዚያም ውሃውን ማፍላት ብንጀምር፤ ውሃው እየፈላ በሄደ ቁጥር እንቁራሪቷም የሰውነት ሙቀቷን ማስተካከል ትጀምራለች፡፡
☞ የውሃው ሙቀት ከፍተኛ እየሆነ ሲሄድ እሷም የሰውነቷን ሙቀት በዛው ልክ ማስተካከሉን ትቀጥላለች፡፡ የውሃው ሙቀት ጨምሮ የመፍላት ነጥብ (boiling point) ላይ ሲደርስ ግን ማስተካከል የማትችልበት ደረጃ ስለደረሰ እሯሷን ለማዳን ከድስቱ ዘላ ለመውጣት ትፈልጋለች ትሞክራለች፤ ግን ዘላ መውጣት አቅም አይኖራትም አትችልም፡፡
ምክንያቱም ያላትን አቅም ሁሉ ሙቀቷን በማስተካከል የውሃውን ቃጠሎ ለመከላከልና ለመላመድ ባደረገችው ተጋድሎ ጨርሳዋለችና፤ ወዲያው ትሞታለች፡፡
እንቁራሪቷን ምን ገደላት?
አብዛኞቻቸችን የፈላ ውሃ እንል ይሆናል፤ እውነታው ግን ይህ አይደለም ፡፡ እንቁራሪቷን የገደላት የፈላው ውሃ ሳይሆን መች መዝለል እንዳለባት የመወሰን አቅም ማጣቷ ነው፡፡
አብዛኞቻችን ከሰዎችም ይሁን ከነገሮች ጋር ያለንን ነገር ለማስተካከልና ለመላመድ እንሞክር ይሆናል፤ ግን እስከ መቼ ማስተካከል እንዳለብንና መች መወሰን እንዳለብን ማወቅ ይሳነናል፡፡
አንዳንዴ ነገሮችን የለመድናቸውና ለኛ የማይጎዱ መስለው ይታዩናል፤
በመጨረሻው ቅፅበት ግን እንዳልለመድናቸው ቢገባንም
ማምለጥና መውጣት የማይቻለን ሰአት ይሆናል፡፡ በጥፋት/ወንጀል/ መንገድ ውስጥም ስንሆን እንዲሁ ነው፤ ትንሹን ወንጀል እንለምደዋለን የሚጎዳን አይመስለንም፤ ደስታ ውስጥ ያለን ይመስለናል፤ ደስታው ሙቀት ይፈጥርልናል፡፡ ሙቀቱ ወደ እሳት የተቀየረ ጊዜ ግን . . .!!!??
ከሙቀቱ መውጣት ካልቻልን ከእሳት እንደማንወጣ እውን ነው!
ሙሉ አቅም ባለን ጊዜ እንዝለል!!!
@Ahadu_goh
9 594
Repost from AHADU
"አንድ ሰው መኪና ቢኖረውና የሚሄድበት ቦታ ግን ከሌለው ቤቱ ታቅፎት ይቀመጣል፤ የሚሄድበት ቦታ ያለው ሰው ግን መኪና ባይኖረው በታክሲ ወይ በእግሩ ይሄዳል፤ እግር ባይኖረው እንኳን በዳዴም ቢሆን መድረስ ወደሚፈልግበት ለመሄድ ይንፏቀቃል።
አየህ አላማ የሌለለው ሰው እንደ መጀመሪያው ሰው ነው! ገንዘብ ቢኖረው ጤና ቢኖረው ሁሉ ቢሟላለት እንኳን እዛው ታቅፎት በዘፈቀደ ይኖራል። አላማ ያለው ሰው ግን ምንም ባይኖረው እንኳን መድረሻ ግብ ስላለው ያንን ለማሳካት ሁሌም ይሮጣል። አላማ ወሳኝ ነው!"
@Ahadu_goh
9 594
Repost from AHADU
✅ 🔻ብሪታኒያ ውስጥ ነው፤ አንዲት ሴት አውራ-ጎዳና ላይ እርቃኗን ስትንጎራደድ ትቆዪና መንገድ ዳር ቆመው ተሳፋሪ ከሚጠብቁ ታክሲዎች ወደ አንዱ ዘው ብላ ትገባለች። የገባችበት ታክሲ ቻይናዊ ሹፌርም ግራ በመጋባትና በመገረም ከራስ ፀጉሯ እስከ እግር ጥፍሯ በጥያቄ ስሜት መላልሶ ማየት ይጀምራል።
አጅሪት ግን ምንም ያልተፈጠረ በማሥመሰል መሄድ የምትፈልግበትን ተናግራ እንዲንቀሳቀስ በዓይኗ ምልክት ትሰጠዋለች። ቻይናዊው ታክሲ ሹፌር ግን ያልተመለሠለት ጥያቄ ነበርና አሁንም ከእግር እስከራሷ መላልሶ ማየቱን ይቀጥላል።
ይኼኔ ቆንጂት በሷ ብሶ በስጨት እንደማለት እያደራረጋት "👩🦰 ልብስ ያልለበሰች ሴት አይተህ አታውቅም???" ብላ ታፈጥበታለች። ይኼኔ ቻይናዊው ታክሲ ሹፌር እንዲህ በማለት በትህትና መለሠ "🤔... የኔ እህት... እኔ ግራ ተጋብቼ የማይሽ እርቃንሽን መሆንሽ ገርሞኝ ሳይሆን... ለአገልግሎቴ ልትከፍዪኝ የሚገባኝ ገንዘብ የቱጋ እንዳለሽ ጥያቄ ስለሆነብኝ ነው።"
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
*እየውልህ ወንድሜ በዚህች ዓለም ስትኖር ልክ እንደቻይናዊው ሹፌር ማተኮር ያለብህ ሰለሚመለከትህ ጉዳይ ብቻ ነው። ስለማያገባህ ጉዳይ ስትፈተፍት በመዋልና በማደር ለራስህ የምትጨምረው ነገር የለም። አቅምህ እስከቻለው ለሌሎች መልካም አድርግ የሌሎችን ግላዊ ህይወት ግን ለባለቤቶቹ ተውላቸው።
✅ @Ahadu_goh
9 594
Repost from AHADU
መሬትን ስትረግጣት ታሰምጠኝ ይሆን አንድ ነገር ታደርገኝ ይሆን ብለህ አትረግጣትም፤ አምነህ ነው ምትራመድባት፤ ታዲያ መሬትን የፈጠረውን ፈጣሪ ምን ያህል ታምነዋለህ?
አንድ ነገር አስተውል 🤔 እውቀት ከሞላው እምነት የሞላው ይበልጣል።
ዳዊት ጎልያድን እንዲጥለው ያደረገው ጉልበቱ አይደለም!
የሆነ ነገር ጀምረህ የምታቆመው እኮ እምነት ስለሌለህ ነው፤ ነገሮች ባልፈለከው መንገድ ሲሄዱ አይ ይሄ ነገር ለኔ አይሆንም ብለህ ታቆማለህ። ለምን? ስለማታምን ነዋ!
@Ahadu_goh
9 594
Repost from AHADU
💎አይምሮህ ውስጥ በሀሳብ የዘራኸውን በገሀዱ አለም በተግባር ታጭደዋለህ፤ ይሄ ሁሉ በድብቁ የአይምሮ ክፍል (Subconscious Mind) ምክንያት ነው። ገብስ የዘራ ገበሬ ገብስ ያጭዳል፤ በስንፍናው ሳይዘራ የቀረ ደግሞ አረም የወረረው ማሳ ታቅፎ ይቀራል። አሁን ይሄንን የአይምሮ ምስጢር እያወቅን ካለማድረግ በላይ ደካማነት የለም። አይምሯችን ውስጥ እችላለው የሚል መንፈስ መዝራት አለብን፣ ከባድ ሁኔታ ውስጥ እንኳን ብንሆን አይ ይቺንማ በቀላሉ አልፋታለው ማለት አለብን፤ ድብቁ አይምሮ ስራው ደጋጋግመን የነገርነውን በተግባር ገልጦ ማሳየት ነው።
👇👇👇
ᴊᴏɪɴ ᴜs @Ahadu_Goh
@Ahadu_Goh
9 594
Repost from AHADU
😎 ዛፍ እስከምን ድረስ ያድጋል ቢባል መልሱ ማደግ እስከሚችለው ድረስ ነው ፤ እንጂ እስከ ግማሽ ድረስ የሚባል ነገር የለም ። ስለዚህ አንተስ ኢትዮጵያ ውስጥም ሁን ዉጪ ሀገር ብቻ ያለህበት ቦታ ማደግ እስከምትችለው በአንተ ስራ መድረስ እስከሚቻለው ለማደግ ለምን አትጥርም ፤ ልክ ይሄን ውሳኔ የወሰንክ ሰዓት ድሮ የተዘጉብህ እድሎች ሲከፈቱልህ ታያለህ ።
💎ይህ ሀሳብ ለሚያስፈልጋቸው ወዳጆቻችሁ ሁሉ ሼር አድርጉ ቤተሰቦች💎
ᴊᴏɪɴ ᴜs @Ahadu_Goh
@Ahadu_Goh
9 594
Repost from AHADU
ከባለፀጎች አንደበት !#ቢል_ጌትስ
ጋዜጠኛዋ ቢሊኒየሩን ቃለመጠይቅ እያደረገችለት ነው… የስኬትህ ሚስጥር ምንድነው?
ቢሊየነሩ ባዶ ቼክ ለጋዜጠኛዋ አቀበላትና የፈለግሽውን ያህል ገንዘብ ፃፊበት አላት!
ጋዜጣኛዋ በእንቤታ ቼኩን እየመለሰች «አይ እኔ እንደሱ አይነት ነገር ፈልጌ አይደለም የስኬት ሚስጥሮን መጠየቅ ፈለጊ ነው» አለች።
ቢሊየነሩ ድጋሚ ቼኩን መልሶ ሰጣትና «የፈለግሽውን ያህል ገንዘብ ፃፊ» አላት።
ጋዜጠኛዋ እንቢ አሻፈረኝ አለች።
ቢሊየነሩ ቼኩን እያሳያት «የስኬቴ ሚስጥር አሁን አንቺ ያጋጠመሽን አይነት እድል አሳልፌ አለመስጠቴ ነው…የስኬቴ ሚስጥር ያገኘሁትን እድል ሁሉ መጠቀሜ አሁን አንቺ እንድልሽን ተጠቅመሽ ቢሆን ኖሮ የአለማችን ሃብታሟ ጋዜጣኛ ትሆኚ ነበር… እኔ ሁለቴ እድል እንደሰጠሁሽ አለም ሁለተኛ ዙር እድል አትሰጥሽም አንዴ ያጋጠመሽን እድል መጠቀም የስኬት ሚስጥር ነው»
@Ahadu_Goh
@Ahadu_Goh
9 594
Repost from AHADU
ትናንት የት ነበርኩ? አሁንስ ምን ላይ ነኝ?? ነገስ የት ነዉ መዳረሻዬ??? 🤔
ይሄን ማሰብ ስትጀምር መለወጥ ትጀምራለህ 😎✌️
https://t.me/joinchat/R0YHmwLVVePkDJ_v
9 594
Repost from AHADU
የምንፈልገውን ነገር ማድረግ እንድንጀምር የሚያነቃቃ ሀሳብ፣ የሚያነቃቃን ሰው መኖሩ አሪፍ ነው ጥያቄው ግን የሚጀምሩ ሁሉ ይጨርሳሉ ወይ ነው? አይጨርሱም! የጀመርነውን እንድንጨርስ የሚያደርገን የማያቋርጥ ጥረታችን ብቻ ነው።
ስለዚህ የምንፈልገውን ለማሳካት ደስ ቢለንም ቢደብረንም ሁሌ መጣር አለብን። አሸናፊዎች በፍፁም አያቆሙም፤ የሚያቆሙ በፍፁም አያሸንፉም!
𝐉𝐨𝐢𝐧 𝐔𝐬 @Ahadu_Goh
𝙰𝚑𝚊𝚍𝚞 𝚢𝚘𝚞𝚛 𝙱𝚎𝚜𝚝 𝙵𝚛𝚒𝚎𝚗𝚍
9 594
😎ቃላት የማይገልጿቸው ስሜቶች አሉ፤ ከቃላት በላይ ግን ድርጊት ይገልፃቸዋል። ህልምህን፣ ፍቅርህን እና ማንነትህ ከቃላት በላይ ተግባር እንዲገልፃቸው ከጣርክ ትክክለኛው መስመር ላይ ነህ።
𝐉𝐨𝐢𝐧 𝐔𝐬 @Ahadu_Goh
