1 453
Subscribers
-124 hours
No data7 days
-230 days
Posts Archive
1 453
ጥያቄ
ለብዙ የህልም ሰዓታት ፥ ሳለቅስና ሳለቃቅስ በዝምታ ሲሰማኝ ቆይቶ
"ፓራራም... ታራራም... ብዙ ወሬ ወሬ ወሬ... ብዙ ሱሱሱሱ... ልትድን ትወዳለህ?" አለኝ።
"እ?" (ሰምቻለሁ)
"ልትድን ትወዳለህ?"
ለመመለስ ጊዜ ፈጀብኝ...
@amadonart
1 453
23|12|18
"አቶ ደስታን ፈልጌ ነበር" አለች።
እኔ ነኝ ደስታ!
እርስዎ ነዎት ደስታ?
እኔ ነኝ!
ካላመንሽ ንኪኝ። ዳስሽኝ። ጨብጪኝ።
አይ! አይ! አይ! አይሆንም።
ለምን አይሆንም?
"ፈልጊ" እንጂ "አግኚ" አላሉኝም እርስዎን።
ግን አገኘሽኝ።
ግን አላገኘሆትም።
@amadonart
1 453
እንዲሁም በአንድ ወቅት... አይኔን ጨፍኜ ፥ ትናንሽ ሳሮች በሚኖሩበት መሬት በጀርባዬ ተኝቼ ነበር። ከላይ ከሾላው ዛፍ የሚነፍሰውን ነፋስ ፥ እየጠጣሁና ጥላውን እያጣጣምኩ ፥ የሚከተለውን 'እውነት' አልኩ:-
ይሄ (የተፈጥሮ ውበት፣ የዚህች አለም ውበት) ከየትኛውም ክፋት (የአለም ክፋት) ይበልጣል።
1 453
09|12|18
እንዲያው ልበል እንጂ
'አደ'ኩ ፤ ዘመን አየሁ
በእያንዳንዷ ስሜት
እኩል ተጐበኘሁ
ኖርኩኝ ፤ ልምድ አካበትኩ
አወ'ኩ ብዙ ነገር
አለምን ከመጥላት
ከልብ እስከ ማፍቀር...'
የማታ የማታ
ዋናውን አሰብኩት...
እራሴን ናፈቅኩት።
@amadonart
1 453
08|12|18
መነሳት በሌሊት
ሰባት፣ ስምንት ሰዓት
ያለፈውን መዓት
ከመዝገብ ቤት ማውጣት...
አንድ፣ ሁለት እያሉ
ሁሉን መመራመር
የይቅርታን ደጆች
እንደገና መውረር...
የሞቱ ጉዳዮች
ሰዎችና ጉዶች
ተጐትተው ይውጡ
ይህን ስል ይነሱ!
አሁን ይታወሱ። አሁን ይወቀሱ።
አንዴ ገፎ ማንሳት
የመርሳትን ሞራ
መ'ጐንተል፣ መ'ተልተል
በብስጭት ካራ
እንደ ጉድ መዋኘት
በንዴት ገሞራ።
እፎይ.............
@amadonart
1 453
07|12|18
ሁለት የጠዋት ቡናዬን ጠጥቼ በመንገድ ስጓዝ ፥ 'እስከመቼ እጓዛለሁ?' የሚል ሀሳብ መጣልኝ። 'እንግዲያው ለምን አልሮጥም?' በማለት ፥ ቦታው ባልሆነ ቦታ ተንደረደርኩ። ሰዎች ዞር ዞር እያሉ ሊገመግሙኝና ሊያሳፍሩኝ ሲሞክሩ ፥ ግድ አልሰጠኝም። እንደዛም አልረካሁም። "ይሄ በቂ አይደለም!" እያልኩ የጮህኩ ይመስለኛል። "እንግዲያው ለምን አትበርም?" የሚል ድምፅ ሰማሁ። "እውነትም!... እውነትም!..." አልኩና ሁለት እጆቼን ወጥሬ ዘረጋሁ። እንደ መጠራጠርና እንደ አለማመን ሲያደርገኝ "አንተ ሰውዬ ብረር!" በማለት ራሴን አዘዝኩ። እና ተነሳሁ... አንድ ፤ እና ተንሳፈፍኩ... ሁለት ፤ እና በረርኩ... ሶ...ስት። አቅጣጫዬን እየቀያየርኩ በረርኩ። ልክ ስቀዘቅዝ ፥ ሶስተኛ ቡናዬን በሰማይ እያስቀዳሁ። ልወርድ ሲመስለኝ ፥ አራተኛ ቡናዬን እያስቀዳሁ። መወንጨፍ ስፈልግ ፥ አምስተኛ ቡናዬን እያስቀዳሁ። ሳወራው ቀልድ ይመስላል።
@amadonart
1 453
እስከመቼ ስሸሸው እኖራለሁ?
በዱር በገደል፣ በአጥቢያና በሌሊት...
በዋሻና በሜዳ፣ ሰው ባለበትና በሌለበት...
በሚታሰብም በማይታሰብም ሰዓት...
ሲከተለኝና ስሸሸው ኖርሁ...
ይበቃል!
እጋፈጠዋለሁ! ደስታን እጋፈጠዋለሁ!
@amadonart
1 453
01|12|18
እየመሰለ - ለውጥ ያለው ነገር
ዕድል ፈንታዬ - የሚሽከረከር
ዛሬና ነገ - የሚለያዩ
ካሳና ፍርዴ - የሚተያዩ
የምንበሸበሽ - በደስታ ዘመን
ስለተፈተንሁ - በእንባዬ መጠን
የቀንና ሌት - ያለው ፈረቃ
ፍትሕ ለማብሰር - እቺ ደቂቃ
የምትቆጥር...
'በቃ' ልትለኝ
ኤልፒስ ምትጥር
እየመሰለኝ፣ እየጠበቅሁና እየተሞኘሁ።
@amadonart
1 453
"ፍቅር ዝርክርክና ቦርቃቃ አይደለም። የአንድ ሰው ሁለንተናነት ነው። ተኮላን የወደደ ተኮሊስት ነው። እኔን የወደደ ጅማወርቂስት ነው።" ገፅ 67
የስንበት ቀለማት | አዳም ረታ |
1 453
15|11|18
የፈሰሰ - ውሃ ሳፍስ
መቃብር ቤት ለመቃብር
የተዘጋ - ዶሴ ስከፍት
ባዶ ካዝና ስበረብር
በማይጠቅመው ባከተመ
እንዳንዣብብ እንድለፋ
የዘራሁት ተስፋ ሁሉ
እንደ ምንም እንዲጠፋ
ተመርቅያለሁና...
አእምሮዬን እንዳላዘው
መምከር እንኳ እንድፈራ
ያለ ሰበብ እንዲላተም
ከፈለገው ግንብ ጋራ
ዝም እንድልም
እንዳልልም
የእረፍቴን ቀን
ብቻ እንዳልም
ህልሜም ቅዠት እየሆነ
ሳላፈራ እንድከስም
ተመርቅያለሁና...
@amadonart
1 453
በክረምት... የሞቱና የምንወዳቸውን እናስባለን። የት ናቸው?
በሌሊት... የሞቱና የምንወዳቸውን እንናፍቃለን። የት ናቸው?
በዝናብ... የሞቱና የምንወዳቸውን እንተዝታለን። የት ናቸው?
1 453
19|09|18
ባቀዱት አይሄድም
ቀኑ፣ ወሩ፣ አመቱ
አለመገመት ነው
የጊዜ ስኬቱ...
ትንሽ ማጉላላት ነው
የአለም sense of humor
ማለፍ፣ መፈታተን
የትዕግስትዎን መስመር
ሲስቁ መቆንጠጥ
ሲቆጡ መኮልኮል
ማብራትና ማጥፋት
ማንሳትና መዶል...
መኖር ፥ ይህን ማወቅ
በስቃይ መስታወት
እራስን ማጫወት...
@amadonart
1 453
Death in Teheran
A rich and mighty Persian once walked in his garden with one of his servants. The servant cried that he had just encountered Death, who had threatened him. He begged his master to give him his fastest horse so that he could make haste and flee to Teheran, which he could reach that same evening. The master consented and the servant galloped off on the horse.
On returning to his house the master himself met Death, and questioned him, “Why did you terrify and threaten my servant?” “I did not threaten him; I only showed surprise in still finding him here when I planned to meet him tonight in Teheran,” said Death.
( A parable shared in Man's Search for Meaning )
1 453
Psiphon ክፈቱና Server region'ኡን በ France, Belgium, Switzerland ወይ Germany... ምናምን አርጋችሁ ፥ ይህንን ምርጥ አጭር ፊልም እዩ።
