en
Feedback
Ministry of Health, Ethiopia

Ministry of Health, Ethiopia

Open in Telegram

The official Telegram Channel of the Ministry of Health of the FDRE. Our vision is to see healthy, productive & prosperous Citizens of Ethiopia. HEALTHIER CITIZENS FOR PROSPEROUS NATION! 📞 +251-11-551-8031 🔗 www.moh.gov.et 📧 moh@ethionet.et

Show more
The country is not specifiedThe category is not specified
4 617
Subscribers
+1024 hours
+1027 days
+64130 days
Posts Archive
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1444ኛው የዒድ አል አድሃ በዓል አደረሳችሁ! #eiduladha @MoHEthiopia
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1444ኛው የዒድ አል አድሃ በዓል አደረሳችሁ! #eiduladha @MoHEthiopia

የካቲት 12 ሆስፒታል የተመሰረተበትን 100ኛ አመት ለማክበር የከፍተኛ የቀዶ ህክምና በመስጠት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት መርሀ ግብር ተጀመረ። የየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ የተመሰረተበትን 10
+9
የካቲት 12 ሆስፒታል የተመሰረተበትን 100ኛ አመት ለማክበር የከፍተኛ የቀዶ ህክምና በመስጠት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት መርሀ ግብር ተጀመረ። የየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ የተመሰረተበትን 100ኛ አመት አስመልክቶ እንዲሁም በአዲስ አበባ ከተማ የጤና ዘርፍ የበጎ ፈቃድ ማስጀመሪያን ምክንያት በማድረግ የህክምና በጎ ፈቃድ አገልግሎት እየተሰጠ ይገኛል። በበጎ ፈቃድ አገልግሎት መርሀ ግብሩ የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ፣ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር አየለ ተሾመ እና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ዮሐንስ ጫላን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች ተገኝተው የቀዶ ህክምና አገልግሎትና የየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ የክረምት የቤት እድሳት የበጎ ፈቃድ አገልግሎቶችን አስጀምረዋል ። የየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ዋና ኘሮቮስት ዶክተር ኤልያስ ተዋበ በበጎ ፈቃድ አገልግሎቱ ነፃ ምርመራና ደም ልገሳ እየተካሄደ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ለቀዶ ህክምና በወረፋ እየተጠባበቁ ላሉ ህሙማን አገልግሎቱን ለማግኘት የሚወስደውን የቆይታ ጊዜ ለመቀነስ ከመደበኛዉ አገልግሎት በተጨማሪ በተከታታይ ቅዳሜዎች ህክምናው እንደሚሰጥ የተናገሩት ዋና ኘሮቮስቱ በቀን 17/10/2015 ዓ.ም በየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ለሚወለዱ ህጻናት ሁሉም የ1000 ብር የህዳሴ ግድብ ቦንድ ግዥ እንደሚፈጸምላቸውም ጠቅሰዋል። ከየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ በተጨማሪ በአበበች ጎበና የእናቶችና ሕጻናት ሆስፒታል በቀዶ ህክምና እናቶችን የማዋለድ ስራም በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተሰጥቷል። @MoHEthiopia

#nextgenerationhealth2023 @MoHEthiopia
#nextgenerationhealth2023 @MoHEthiopia

የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስትያን ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ ካርዲናል ብርሃነ እየሱስ ሱራፌል እና የቤተክርስቲያና አባቶች በሳይንስ ሙዚየም ተገኝተው የጤና አውደ-ርዕዩን ጎበኙ። ጤና ሃብት ነው ያሉት ብፁእ
+5
የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስትያን ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ ካርዲናል ብርሃነ እየሱስ ሱራፌል እና የቤተክርስቲያና አባቶች በሳይንስ ሙዚየም ተገኝተው የጤና አውደ-ርዕዩን ጎበኙ። ጤና ሃብት ነው ያሉት ብፁእ ካርዲናል ብርሃነ እየሱስ ጤና ለሰው ልጆች ከምንም በላይ መሆኑን የካቶሊክ ቤተ ክርስትያን ትረዳለች ብለዋል፡፡ ቤተክርስቲያኗ በርከት ያሉ ጤና ጣቢያዎችን እና ሆስፒታሎችን ከጤና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር እያስተዳደረች እንደምትገኝ ያስተወሱት ብፁእ ካርዲናል ብርሃነ እየሱስ ሱራፌል፤ የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስትያን የጤና አገልግሎትን በየገጠሩ በማዳረስ ግንባር ቀደም ተሳታፊ መሆኗን ተናግረዋል፡፡ ፍጡር ሁሉ ክቡር ነው ያሉት ብፁእ ካርዲናል ብርሃነ እየሱስ ሱራፌል ከፈጣሪ ቀጥሎ የሰውልጆችን ያለ ልዩነት የሚታደገው የህክምናው ዘርፍ ነው ብለዋል፡፡ በካቶሊክ ቤተክርስቲያን ስር የሚገኙ የጤና ተቋማት ነጻ የማዋለድ አገልግሎት በመስጠት ላይ እንደሚገኙ ተናግረዋል። በአዲስ አበባ የተዘጋጀው የጤና አውደ-ርዕይ ወደ ክልሎችም ቢስፋፋ ለበርካታ የማህበረሰባችን ክፍሎች ግንዛቤ ለመፍጠር እንደሚረዳ ሃሳባቸውን የገለጹት ብፁእ ካርዲናል ብርሃነ እየሱስ ሱራፌል፤ የጤና አውደ-ርዕዩ መዘጋጀቱ በተለይም ተማሪዎችን የሚያበረታታ እና የሚያንጽ በመሆኑ እጅግ አስፈላጊ ነው ብለዋል፡፡ ሁሉም የማህበረሰባችን ክፍሎች የተዘጋጀውን አውደ-ርዕይ መጥተው እንዲመለከቱ ብጹእነታቸው ጥሪ አቅርበዋል፡፡ @MoHEthiopia

https://fb.watch/lnqY52rCc4/?mibextid=Nif5oz በሳይንስ ሙዚየም የተዘጋጀውን ብሔራዊ የጤና ኤግዚቢሽን በመጎብኘት እየተማሩ መልካም ጊዜ ያሳልፉ ! #nextgenerationhealth2023 @MoHEthiopia

የአዲስ አበባ አስተዳደር ከንቲባ ክብርት ወ/ሮ አዳነች አቤቤ እና የከተማ አስተዳደሩ የስራ ኃላፊዎች የጤና ኢግዚቢሽኑን ጎበኙ። አዲስ አበባን የጤና ቱሪዝም መዳራሻ ለማድረግ ከጤና ሚኒስቴር ጋር በመ
+9
የአዲስ አበባ አስተዳደር ከንቲባ ክብርት ወ/ሮ አዳነች አቤቤ እና የከተማ አስተዳደሩ የስራ ኃላፊዎች የጤና ኢግዚቢሽኑን ጎበኙ። አዲስ አበባን የጤና ቱሪዝም መዳራሻ ለማድረግ ከጤና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር እየተሰራ መሆኑንንም ከንቲባ ክብርት ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ተናግረዋል። የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በሳይንስ ሙዚየም ተገኝተው የጤና አውደ-ርዕይ ጎብኝተዋል፡፡ የጤናው ዘርፍ እስከሁን የደረሰበትን ደረጃ እና የሴክተሩን አጠቃላይ እድገት በጉብኝታቸው መመልከት መቻላቸውን ክብርት ከንቲባዋ ተናግረዋል፡፡ በአውደ-ርዕዩ የቀረበው አጠቃላይ የጤና ስራዎችና ውጤቶች በርግጥም አዲስ አበባ የጤና ቱሪዝምን ለመተግበር እንደምትችል ማረጋገጥ የቻልንበት ነው ያሉት ከንቲባ አዳነች፤ በሴክተሩ የተጀመረውን የጤና አገልግሎት ዲጂታላይዝ የማድረግ ስራ አድንቀው ተግባሩን ማስፋፋት እንደሚገባ ከንቲባዋ ተናግረዋል፡፡ ህዝባችን ምርታማ ሊሆን የሚችለው ጤናማ ሲሆን ነው ያሉት ከንቲባ አዳነች፤ በጤናው ዘርፍ ያሉብንን ክፈተቶች የሚሞሉ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን ይዘው ለሚመጡ የጤና ኢንቨስትመንቶችን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል፡፡ አዲስ አበባን የጤና ቱሪዝም ማእከል ለማድረግ ጤና ሚኒስቴር ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጋር በትብብር እንደሚሰራ የገለጹት የጤና ሚኒስትር ክብርት ዶ/ር ሊያ ታደሰ ናቸው፡፡ በሳይንስ ሙዚየም የተዘጋጀው የጤና አውደ ርዕይ በተለያዩ ሁነቶችና መርሃግብሮች አንድ ወር የሚቆይ ነው። @MoHEthiopia

የኢትዮጵያ የምግብ ስርዓት እና ስነ ምግብ የሚንስትሮች ስቲሪንግ ኮሚቴ የምስረታ ስብሰባ ተካሄደ። የኢትዮጵያ የምግብ ስርዓት እና ስነ ምግብ የሚንስትሮች ስቲሪንግ ኮሚቴ የምስረታ ስብሰባውን ዛሬ አካ
+3
የኢትዮጵያ የምግብ ስርዓት እና ስነ ምግብ የሚንስትሮች ስቲሪንግ ኮሚቴ የምስረታ ስብሰባ ተካሄደ። የኢትዮጵያ የምግብ ስርዓት እና ስነ ምግብ የሚንስትሮች ስቲሪንግ ኮሚቴ የምስረታ ስብሰባውን ዛሬ አካሂዷል። በጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድ የተቋቋመው የምግብ ስርዓትና ስነ ምግብ የሚንስትሮች ስቲሪንግ ኮሚቴ 14 ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶችን ያካተተ ነው ተብሏል። የምግብ ስርዓትና ስነ ምግብ የሚንስትሮች ስቲሪንግ ኮሚቴውን የግብርና እና የጤና ሚንስትሮች በበላይነት የሚመሩት ሲሆን፤ በምስረታ ስብሰባው ሌሎች ሚንስትሮችም ተገኝተዋል። ስቲሪንግ ኮሚቴው የተቋቋመው የሀገሪቱን የምግብ ስርዓት ሂደት፣ የምግብ እና የተመጣጠነ የምግብ ስትራቴጂ እንዲሁም የሰቆጣ ቃል ኪዳንን ለመምራት እንደሆነም ተገልጿል። በተጨማሪም ፖሊሲዎችንና የህግ ማዕቀፎችን በመምራት እና የክልል መንግስታትን በመደገፍ አተገባበሩን ይከታተላል ነው የተባለው። በስብሰባው ላይ በኢትዮጵያ የምግብ ዋጋ ንረትን ለማረጋጋትና ጤናማ የምግብ ስርዓትን ለማረጋገጥ በቅንጅት መስራት እንደሚገባም ተገልጿል። የምግብና ስነ ምግብ ትራንስፎርሜሽን አጀንዳው የገጠር ኑሮን የማሻሻል እና የምግብ ዋጋ ንረትን የማረጋጋት እንዲሁም ሌሎችም ዓላማዎች ያሉት መሆኑ ተጠቁሟል። @MoHEthiopia

ውይይቱ የተደረገው በሳይንስ ሙዚየም እየተካሄደ በሚገኘው የጤና አውደ-ርዕይ ጎንዮሽ ሲሆን በጤና ላይ የሚመደብ መዋለ ንዋይ ወጭ ሳይሆን ለማህበረሰብ ጤና መጠበቅና ለሀገር ልማት ኢንቨስት እንደተደረገ የሚቆጠር መሆኑን በፓናል ውይይቱ የተሳተፉት የገንዘብ ሚንስትር ዲኤታው ዶ/ር ኢዮብ ተካልኝ ናቸው፡፡ የመንግስት ኢንቨስትመንት ብዙ ቅድሚያ የሚሰጣቸው ጉዳዮች ቢኖሩም ለጤና ግን በቀዳሚነት ትኩረት ከመሰጠቱም በላይ ጤና እና የሃገር እድገት ተነጣጥለው የሚታዮ አለመሆናቸውን ዶ/ር ኢዮብ አስረድተዋል፡፡ በቤተሰብ ደረጃ ጤና ላይ ኢንቨስት እንዲደረግ የመንግስት ድጋፍ ጉልህ እንደሆነ ዶ/ር እዮብ ገልጸው፤ መንግስት በማህበረሰብ ጤና ላይ ያተኮሩ ፕሮጀክቶች ላይ ያፈሰሰው ኢንቨስትመንት ውጤት ማስገኘቱን ተናግረዋል፡፡ ሰለሆነም የመንግሥት እና የግል አጋርነትን ይበልጥ በማጠናከር ጥራት ያለውን የጤና አገልግሎት ተደራሽነት ለማድረግ የሚሰራ መህኑን ጭምር ገልፀዋል። ጤና ሚኒስቴር የተለያዩ ሴክተር መስርያቤቶችን በማስተባበርና በማሳተፍ በተለያዩ ዘርፎች ሞዴል ወረዳ ለመፍጠር እያደረገም ያለውንና እንቅስቃሴ እንደሚበርታታ እና ሌሎች ተቋማትም በአርያነት ሊከተሉት ይገባል ብለዋል ዶ/ር ኢዮብ ። በሳይንስ ሙዚየም እየተካሄደ የሚገኘው የጤና አውደ-ርዕይም ተዘዋውረው ጎብኝተው አበረታተዋል። የጤና ፋይናንስ እየተሻሻለ የመጣ መሆኑን የገለጹት የኢትዮጵያ ጤና መድህን አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ፍሬህይወት አበበ ሲሆኑ፤ የማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን ስርአት ከ56 ሚሊዮን በላይ የማህበረሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ እያደረገ ይገኛል ብለዋል፡፡ እንደ መድሃኒት እና የህክምና መገልገያ ቁሳቁስ ያሉ ከውጭ የሚገቡ ግብአቶችን በሃገር ውስጥ በማምረት በዘርፉ የሚታየውን የውጭ ምንዛሬ እጥረት ለመቅረፍ መስራት እንደሚገባ የተናገሩት ደግሞ የጤና ሚኒስቴር አማካሪ ዶ/ር ግርማይ ዲንሳ ናቸው፡፡ በአለም ላይ በአጠቃላይ የጤና አቅርቦት ከአቅም በላይ እየሆነ የመጣ ቢሆንም በሃገራችን የሚቀርበው የህክምና አገልግሎት ጥራትን መጨመር ብቻ ሳይሆን በአነስተኛ ዋጋ እንዲቀርብ ለማድረግ መስራት እንደሚያስፈልግ የሊያና ፒኤልሲ መስራች እና ዳይሬክተር ዶ/ር ግርማ አባቢ ናቸው፡፡ በአገርአቀፍ የጤና ኢግዚቢሽን ላይ በተለያ የጤና ርዕሰ ጉዳዮች ላይ የሚካሄደው የፓናል ውይይት የሚቀጥል ይሆናል፡፡ @MoHEthiopia

በኢትዮጵያ የጤና ፋይናንስ ላይ ያተኮረ የፓናል ውይይት ተደረገ። @MoHEthiopia
+4
በኢትዮጵያ የጤና ፋይናንስ ላይ ያተኮረ የፓናል ውይይት ተደረገ። @MoHEthiopia

የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ ከተመሰረተ 20 ዓመታት ያስቆጠረው እና በርካታ የጥራት የምስክር ወረቀት ያገኘው የኢትዮጵያ አይን ባንክ ያለበትን ሁኔታ ከጎበኙ በኋላ በአገልግሎት አሰጣጥ፣ በሙያ ስ
+7
የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ ከተመሰረተ 20 ዓመታት ያስቆጠረው እና በርካታ የጥራት የምስክር ወረቀት ያገኘው የኢትዮጵያ አይን ባንክ ያለበትን ሁኔታ ከጎበኙ በኋላ በአገልግሎት አሰጣጥ፣ በሙያ ስነምግባርና ብቃት ዙሪያ ባዩት አፈፃፀም የተሰማቸውን አድናቆት ገልፀው ወደፊት አገልግሎቱን ለማስፋት እና ለማሳደግ በሚቻልበት ሁኔታ ከተቋሙ አመራሮች እና ባለሙያዎች ጋር ውይይት አድርገዋል። የአይን ባንኩ ለምስራቅ አፍሪካ የምርምር የስልጠና እና የልህቀት ማዕከል የመሆን እድል እንዳለው የገለፁት የአይን ብሌን ንቅለ ተከላ ሐኪምና የኢትዮጵያ ዓይን ባንክ ሜዲካል ዳይሬክተር ዶ/ር መነን አያሌው በሀገራችን እርሳቸውን ጨምሮ 11 የአይን ብሌን ንቅለ ተከላ ሀኪሞች መኖራቸውንና አይን ባንኩ በጥቂት የሰው ሀይል የ2957 ሰዎችን የአይን ብርሃን መመለስ መቻሉን ጠቁመው የአይን ብሌን ከለጋሽ በጎ ፈቃደኞች ከተሰበሰበ በኋላ ለተጠቃሚ እስኪሰጥ በሚደረግ የምርመራ ሂደት የሚያሰፈልጉ የወቅቱን ቴክኖሎጂ ያማከሉ መሳሪያዎች ቢኖሩ እየተሰጠ ካለው አገልግሎት በላይ መስራት እንደሚቻል አስረድተዋል። የኢትዮጵያ ዓይን ባንክ ቴክኒካል ማኔጀር ሲ/ር ሊያ ትካቦ በበኩላቸው የአይን ባንኩ በአዲስ አደረጃጀት ከደምና ህብረ ህዋስ ጋር በመዋሀዱ ያለውን መልካም አጋጣሚ እና ስጋት በተመለከተ እንዲሁም ተቋሙ ያለበትን አንዳንድ የግብአት እጥረት አንስተው የመፍትሔ እርምጃ ላይ ተወያይተዋል። በውይይቱ ማጠቃለያ ዶ/ር ሊያ የሰው ሃይል ከማስፋት ጀምሮ ዘመናዊ የምርመራ መሳሪያዎች እንዲኖሩ ለማድረግ በትኩረት እንደሚሰራ ጠቁመው አዲሱ አደረጃጀትም አገልግሎቱን በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች ለማስፋት እና ለማዘመን እንዲሁም የልህቀት ማዕከል ለማድረግ የሚያግዝ መሆኑን በመግለፅ የተቋሙን አመራሮችና ሰራተኞች አበረታተዋል። @MoHEthiopia

የፓናል ውይይቱ የተካሄደው በትላንትናው ዕለት የተከፈተው አገርአቀፍ የጤና አውደ-ርዕይ እየተካሄደ በሚገኝበት በሳይንስ ሙዚየም ሲሆን፤ የፓነል ውይይቱ አካል የነበሩት የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ የግል ጤና ዘርፍ የጤና ስርዓቱን ለማጠናከርና አገልግሎቶችን ለማሻሻል ወሳኝ እንደሆነ ጠቁመው እስካሁን ባለው እንቅስቃሴ በሀገራችን የግሉ ዘርፍ ተሳትፎ እያደገ ቢመጣም ከሌሎች ሀገራት አንጻርና ሊኖረው ከሚችለው አስተዋጽኦ አኳያ ተሳትፏቸው ከዚህ ይበልጥ መጠናከር እና ወደ ላቀ ደረጃ ሊሸጋገር ይገባል ብለዋል፡፡ አሁን ላይ ሁሉአቀፍ የጤና ሽፋን አገልግሎትን ለማዳረስ ያሉብንን ውስንነቶች ለመሙላት የግል የጤናው ዘርፍ ቀጥተኛ ተሳትፎ ወሳኝ ነው ያሉት ዶ/ር ሊያ፤ መንግስት የግሉ ዘርፍ እንዲጠናከር በመድሃኒት እና የህክምና ቁሳቁስ ምርት ላይ የሚያደርገው የግብር እፎይታ ጊዜ መስጠት እና በመንግስትና የግሉ ዘርፍ አጋርነት ምርመራና ስፔሻላይዝድ ህክምና ለማስፋት እየተደረገ ያለው ጥረት የሚጠቀሱ ናቸው ያሉት ሚኒስትር ሊያ፤ አሁንም የግል የጤና ዘርፍ እድገት ላይ ያሉ ውስንነቶች እና ተግዳሮቶቹን ለመፍታት ጤና ሚኒስቴር ከሚመለከታቸው ሴክተር መ/ቤቶችና ከግሉ ዘርፍ ጋር እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የግሉ የጤና ዘርፍ በሃገራችን ጤና የሚታዩ ክፍተቶችን እንደ መልካም አጋጣሚ መመልከት እንዳለባቸው የተናገሩት በፓናል ውይይቱ የተሳተፉት የፕላንና ስትራቴጂ ሚኒስቴር ተወካይ አቶ ሰንዱቃን ደበበ ሲሆኑ፣ በረጅም ግዜ እቅድ የተቀመጡ ግቦችን ለማሳካት እንዲቻል የግሉ ዘርፍ አስተዋጾ ምን መሆን እንዳለበት በእቅዱ በግልጽ ተቀምጧል ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ ጤና እንክብካቤ ፌደሬሽን የግል ጤና ተቋማት እና በመንግስት መሃል ያለውን ግንኙነት ለማሳለጥ መቋቋሙን የተናገሩት የማህበሩ ፕሬዘዳንት ዶ/ር ማርቆስ ፈለቀ፤ ማህበሩ የግል የጤና ተቋማት የጋራ ድምጽ እንዲኖራቸው ማስቻሉን ገልጸዋል፡፡ በፓናል ውይይቱ የተሳተፉት የዩኤስኤአይዲ የጤና ቢሮ ዳይሬክተር ጆናታን ሮስ በበኩላቸው እንደተናገሩት ዩኤስኤአይዲ ከግል የጤና ተቋማት ጋር በትብብር ለመስራት ያላቸውን ቁርጠኝነት አስታውቀው፤ ከጤና ሚኒስቴር እና ከፕላንና ስትራተጂ ሚኒስቴር ጋርም በትብብር እንደሚሰሩ እና ለግል እና ለመንግስት የጤና ተቋማት የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ቃል ገብተዋል፡፡ በሌላ በኩል በግል የጤና ተቋማት ስለሚሰጠው አገልግሎት ጥራት ዙሪያ ሁለተኛ የፓናል ውይይት የተደረገ ሲሆን በውይይቱ በግል ጤና ተቋማት ስለሚታዩ የአገልግሎት ጥራት ጉድለቶቸ እንዲሁም በዘርፉ ሰለሚታየው ስርዓት ማነቆዎች ተነስተው በስፋት ውይይት ተደርጎባቸዋል። መንግስት በጤና ተቋማት የሚሰጡትን አገልግሎቶች ጥራትን የሚከታተል ቡድን በማቋቋም ለ24 ሰአታት የሚከታተል መሆኑን ገልጸው፤ ይህን ተሞክሮ ወደ የግል ተቋማት ለማውረድ እየተሰራ መሆኑን የተናገሩት በጤና ሚኒስቴር መሪ ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ኢሊባቦር ናቸው። የፓናል ውይይቱ በተካሄደበት መድረክ ላይ በዋሽግተን ሄልዝ ኬር እና ከህንድ ሃገር በመጣው አፖሎ ሆስፒታልስ መሃል የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ የተፈረመ ሲሆን፤ በስምምነቱ መሰረት አፖሎ ሆስፒታልስ ዋሽግተን የህክምና ማእከል የሚያስገነባውን ተርሸሪ ሆስፒታል ግንባታ እና አስተዳደር ተርክቦ ለማካሂድ ተስማምቷል፡፡ በአገርአቀፍ የጤና ኢግዚቢሽን ላይ በተለያ የጤና ርዕሰ ጉዳዮች ላይ የሚካሄደው የፓናል ውይይት የሚቀጥል ይሆናል፡፡ #NextGenerationHealth @MoHEthiopia

በጤናው ሴክተር የግሉ ዘርፍ ተሳትፎን ማጠናከር በሚልና በግል ጤና ተቋማት የሚሰጥን የጤና አገልግሎት ጥራት ማሳደግ በሚሉ የመወያያ አርእስቶች የፓናል ውይይቶች ተደረጉ። #NextGenerationHea
+9
በጤናው ሴክተር የግሉ ዘርፍ ተሳትፎን ማጠናከር በሚልና በግል ጤና ተቋማት የሚሰጥን የጤና አገልግሎት ጥራት ማሳደግ በሚሉ የመወያያ አርእስቶች የፓናል ውይይቶች ተደረጉ። #NextGenerationHealth @MoHEthiopia

"#NextGenerationHealth" በሚል መሪ ሃሳብ በሳይንስ ሙዚየም እየቀረበ የሚገኘው የጤና አውደ-ርዕይ ትናንት ሰኔ 13 ቀን 2015 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ በይፋ የተከፈተ ሲሆን በአውደ ርዕዩ ላይ በጤናው ዘርፍ የተገኙ የተለያዩ ስኬቶችን የሚያሳዩ የምርምርና የፈጠራ ስራዎች፣ ዲጂታላይዜሽንና ዘመናዊ የጤና ቴክኖሎጂዎች ለዕይታ ቀርበዋል። በዛሬው እለት የጤና ሚኒስቴር እና የደምና ህብረ ህዋስ ባንክ አገልግሎት የስራ ኃላፊዎችና ሰራተኞች በሳይንስ ሙዚየም በመገኘት አውደ-ርዕዩን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል። የጉብኝቱ ታዳሚዎች በጉብኘቱ በርካታ የጤናውን ዘርፍ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ውጤቶችን የተመለከቱ ሲሆን በቀጣይ በየተሰማሩበት የስራ ክፍል የጤናውን ዘርፍ ለማጠናከርና የጤና አገልግሎቱን ለማሻሻል መነሳሳት እንደፈጠረባቸውም ተናግረዋል። በጤናው ዘርፍ የተገኙ ስኬቶችና የፈጠራ ስራዎች ለዘርፉ እድገት ትልቅ ተስፋ የሰነቁ በመሆናቸው ጥሩ ጅምር ነው ሲሉ አድናቆታቸውን ጎብኝዎች ገልጸዋል። የጤና ሚኒስቴርን እና የደምና ህብረ ህዋስ ባንክ አገልግሎትን ኃላፊዎችና ሰራተኞች የጤና አውደ ርዕዩን መመልከታቸው የላቀ ፋይዳ እንዳለው የገለጹት ደግሞ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱግማ ናቸው። ለጤናው ዘርፍ ቀጣይነት ላለው እድገት አልፎም ለማህበረሰባችን ጤና መጠበቅ በተለይም የዘርፉ የስራ ኃላፊዎችና ሰራተኞች በውጤታማነት፣ በትጋት እና በላቀ ደረጃ ሊሰሩ ይገባል ብለዋል ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱግማ ። የጤና ሚኒስትር ዲኤታ ዶ/ር አየለ ተሾመ በበኩላቸው አውደ-ርዕዩ በጤናው ዘርፍ ሃገራችን የደረሰችበትን ደረጃ የሚያሰይ በመሆኑ በተለይም በጤና ሙያ የተሰማሩ ባለሞያዎች አውድ-ርዕዩን እንዲጎበኙ ጥሪ ያስተላለፉ ሲሆን፤ ወላጆች ልጆቻቸውን ወደ ተዘጋጀው አውደ-ርዕይ ይዘው በመምጣት የምርምርና የፈጠራ ስራዎች፣ ዲጂታላይዜሽንና ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች እንዲያስጎበኟቸው ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል፡፡ የጤና ሚኒስቴርን እና የደምና ህብረ ህዋስ ባንክ አገልግሎትን ኃላፊዎችና ሰራተኞች ከጉብኝታቸው በኋላ በባለሙያ የተደገፈ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ አድርገዋል። በበጎ ፍቃደኝነትም ደም የመለገስ ተግባር ፈጽመዋል፡፡ በሳይንስ ሙዚየም የተዘጋጀው የጤና አውደ ርዕይ በተለያዩ ሁነቶችና መርሃግብሮች አንድ ወር የሚቆይ ነው። #NextGenerationHealth @MoHEthiopia

የጤና ሚኒስቴር እና የደምና ህብረ ህዋስ ባንክ አገልግሎት የስራ ኃላፊዎችና ሰራተኞች የጤና አውደ ርዕዩን ጎበኙ። #NextGenerationHealth @MoHEthiopia
+5
የጤና ሚኒስቴር እና የደምና ህብረ ህዋስ ባንክ አገልግሎት የስራ ኃላፊዎችና ሰራተኞች የጤና አውደ ርዕዩን ጎበኙ። #NextGenerationHealth @MoHEthiopia

National Health Exhibition @ National Science Museum #neaxtgenerationhealth2023 www.healthexhibition.moh.gov.et @MoHEthiopia
National Health Exhibition @ National Science Museum #neaxtgenerationhealth2023 www.healthexhibition.moh.gov.et @MoHEthiopia

የዓለም ደም ለጋሾች ቀን ተከበረ። የዓለም ደም ለጋሾች ቀን በሀገራችን ለ20ኛ ጊዜ "ደም እንለግስ፤ ህይወት እናጋራ፤ ዘወትር እናጋራ" በሚል መሪ ቃል በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል አሶሳ ከተማ ተከብሯል
+6
የዓለም ደም ለጋሾች ቀን ተከበረ። የዓለም ደም ለጋሾች ቀን በሀገራችን ለ20ኛ ጊዜ "ደም እንለግስ፤ ህይወት እናጋራ፤ ዘወትር እናጋራ" በሚል መሪ ቃል በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል አሶሳ ከተማ ተከብሯል። የደምና ህብረ ህዋስ ባንክ አገልግሎት ም/ዳይሬክተር ወ/ሮ ጤናየ ደምሴ በተለያየ ምክንያት ደም ለሚያስፈልጋቸው ታካሚዎች ደም የሚሰጡትን በጎ ፈቃደኛ ሰዎች ደግመን ደጋግመን እናመሰግናለን ያሉ ሲሆን ደም የሚያስፈልጋቸው ሰዎች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ በመሆኑ በጎ ፈቃደኞች ይህንን ሰብዓዊ አገልግሎት በየሶስት ወሩ በቋሚነት በመለገስ ሕይወት እንዲቀጥሉ ጠይቀዋል። የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ፍቃዱ ረጋሳ በበኩላቸው ደም የሚያስፈልጋቸውን ዜጎች ህይወት ለመታደግ ደም እና የደም ተዋፅዖ አስፈላጊ እንደሆነ ገልፀው በክልሉ በፀጥታ ችግር ምክንያት ተዘዋውሮ ደም የማሰባሰብ ስራ መስራት ባለመቻሉ በክልሉ የደም ዕጥረት መኖሩን ገልፀው አሁን የፀጥታው ሁኔታ በመሻሻሉ በተሻለ ሁኔታ እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑን ገልፀዋል። በመድረኩ በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች ለበርካታ ጊዜያት ደም ለለገሱ በጎ ፈቃደኞች የምስጋና የምስክር ወረቀት ተሰጥቷል፤ የደም ልገሳ መርሐ ግብር እንዲሁም በማርሽ ባንድ የታጀበ የግንዛቤ መፍጠሪያ የእግር ጉዞም ተደርጓል። @MoHEthiopia

https://fb.watch/l9WZRIhF0M/?mibextid=Nif5oz በአይነቱ ልዩ የሆነ የጤና ኤግዚቢሽን በቅርብ ቀን በብሔራዊ ሳይንስ ሙዚየም #neaxtgenerationhealth2023 @MoHEthiopia

እንኳን ለአለም ደም ለጋሾች ቀን በሰላም አደረሳችሁ! ደም ይለግሱ ህይወትን ያጋሩ፣ ዘወትር ያጋሩ! #blooddonation @MoHEthiopia
እንኳን ለአለም ደም ለጋሾች ቀን በሰላም አደረሳችሁ! ደም ይለግሱ ህይወትን ያጋሩ፣ ዘወትር ያጋሩ! #blooddonation @MoHEthiopia

National Health Exhibition #neaxtgenerationhealth2023 Coming soon at Science Museum @MoHEthiopia
National Health Exhibition #neaxtgenerationhealth2023 Coming soon at Science Museum @MoHEthiopia

በዩኤስኤአይዲ ኢትዮጵያ ይፋ የተደረገው ፕሮጀችት የማይበገር የጤና ስርአት ለመገንባት (USAID Health Resilience Activity) በዩኤስአይዲ የገንዘብ ድጋፍ የሚተገበር የአምስት ዓመት ፕሮጀክት ነው። ፕሮጀክቱ በማኔጅመንት ሳይንስ ለጤና (MSH) ከኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር (ERCS) ጋር በመተባበር እንደሚተገበር የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ ፕሮጀክቱ ይፋ በተደረገበት መድረክ ላይ የተናገሩ ሲሆን፤ ዩኤስኤአይዲ ፕሮጀክቱን በገንዘብ በመደገፉ እንዲሁም ኤምኤስኤች እና የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ፕሮጀክቱን ከጤና ሚ/ርና ከኢትዮጲያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዪት ጋር የሚተገብሩ በመሆኑ ላበረከቱት አስተዋጾ ምስጋና አቅርበዋል። ፕሮጀክቱ የኢትዮጵያን የድንገተኛ ጤና ችግሮች ዝግጁነትና ምላሽ አቅም ለመዳበር እንደሚያግዝ ያሳታወቁት ዶ/ር ሊያ፤ ፕሮጀክቱ በወረዳ ደረጃ የሚተገበር በመሆኑ ማህበረሰቡን በቀጥታ በማሳተፍ የድንገተኛ ምላሽ አሰጣጥን እንደሚያሻሽል ተናግረዋል፡፡ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ተቀናጅቶ በመስራት ፕሮጀክቱን እንዲያስፈጽሙ ጥሪ ያቀረቡት የጤና ሚኒስቴሯ፤ ፕሮጀክቱ የዉስጥ አቅምን የሚያጠናክር መሆኑ ዘላቂነት ያለዉ ያደርገዋል ብለዋል። ለህብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋዎችን፣ የመዘጋጀት፣ የመለየት እና ምላሽ የመስጠት አቅምን ማጠናከር የፕሮጀክቱ ዋነኛ አላማ መሆኑን የዩኤስኤአይዲ ኢትዮጵያ ሚሽን ዳይሬክተር ቲም ስቴይን የተናገሩ ሲሆን፤ በፕሮጀክቱ የሚደገፉ አካባቢዎች 90% በወረርሽኞች የሚከሰት የሞት መጠን ቁጥጥር እንዲደረግባቸው በማድረግ ከህዝባዊ ጤና ድንገተኛ አደጋዎች ጋር ተያይዘው የሚመጡ በሽታዎችን እና ሞትን መቀነስ እና 90% የጤና ተቋማት በድንገተኛ አደጋ ጊዜ አስፈላጊ አገልግሎቶችን መስጠት እንዲችሉ ማረጋገጥ ያስችላል ብለዋል። የፕሮጀክቱ ትግበራ ከኢትዮጵያ መንግስት የህብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋ አስተዳደር ስትራቴጂ እና የአደጋ ስጋት አስተዳደር ፍኖተ ካርታ ጋር የተጣጣመ መሆኑን ማኔጅመንት ሳይንሶች ለጤና (ኤምኤስኤች) ካንትሪ ዳይሬክተር ዶ/ር ዳንኤል ገመቹ የተናገሩ ሲሆን፤ የአመራርን፣ የጤናው ዘርፍ የመቋቋም አቅምን እና የማህበረሰብ ተሳትፎን በማሳደግ የተሻለ የድንገተኛ ምላሽ መስጠት እንደሚያስችል ተናግረዋል። ፕሮጀክቱ የሚተገበርባቸውን ቦታዎች በተመለከተ የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ዋና ጸሃፊ አቶ ጌታቸው ጣሃ እንደተናገሩት፤ ፕሮጀክቱ በሶስት ክልሎች (አማራ፣ ኦሮሚያ እና ደቡብ ክልል) እና በአንድ ከተማ አስተዳደር (ድሬዳዋ) በተመረጡ 45 ወረዳዎች ላይ ተግባራዊ ይሆናል። በፕሮግራሙ አፈጻጸም ዙሪያ የፓናል ውይይት የተደረገ ሲሆን በኢትዮጵያ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የሚገኘው ብሄራዊ የህብረተሰብ ጤና ኢመርጀንሲ ማስተባበሪያ ማእከል ጉብኝትም ተደርጓል፡፡ @MoHEthiopia