cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

ወንጌል ያሸንፋል

ወንጌል ስለ ልጁ ነው ልጁም እየሱስ ነው። ሮሜ 1:3-4 በዚ ቻናል ስለ ወንጌል ከወንጌል እናወራለን። በዚ አግኙኝ @beki_Christian ለሌሎች አጋሩ @Tsegabecha

Show more
The country is not specifiedThe language is not specifiedThe category is not specified
Advertising posts
290
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

Repost from N/a
Photo unavailableShow in Telegram
የመስከረም ፀሐይ ወዳጄ ሆይ ! አንዳንድ ሰው በሥራው አሳቦ ይርቅሃል፣አንዳድ ሰው እንከን ፈልጎ በሰበብ ይርቅሃል ፣ አንዳንድ ሰው ትዝታውን አውድሞ ይርቅሃል ፣ አንዳንድ ሰው በውስጤ ፍቅር የለኝም ብሎ ይርቅሃል። በሥራው አሳቦ የሚርቅ ይሉኝታ ያለው ፣ እንከን ፈልጎ የሚርቅ በራሱ የማይተማመን ፣ ትዝታውን አውድሞ የሚርቅ ቀናተኛ ፣ ፍቅር የለኝም ብሎ የሚርቅ ልበ ደንዳና ነው። አውቆ የራቀህን እርሳው። እንከን ፈልጎ የራቀህን የሕሊና ቁስለኛ ነውና እዘንለት ። ትዝታውን የሚያወድም የፈለገውን ያጣ ነውና ሳቅበት፣ ፍቅር የለኝም ብሎ የሚርቅ መኖርያ የለውምና አልቅስለት። አንተ ግን መውደድን እንደተቀበልህ መጠላትንም ተቀበል። ወዳጄ ሆይ ! ልብህ በሰዎች ቢወጋ የሚያመረቅዘው ግን ባንተ አልረሳ ባይነት ነው። እሹሩሩ ሲሉት የሚተኛ ልጅ ብቻ ነው ፣ አሳብ እሹሩሩ ሲሉት ይበልጥ እንደሚነቃ እወቅ። የሚሆነው ሲሆን የነበረ ነውና አትደነቅ። ደንቆሮ የሰማ ቀን ያብዳል፣ ዛሬ የጠላህ ድሮም አይወድህም ነበር። ልብህ አንድ ቀን ሊታለል ይችላል፣ መጫወቻ የሚሆነው ግን ባንተው አልጫነት ነው። ደጋግሞ እንቅፋት የሚመታው ድንዝዝ ነው። ከትላንት ያልተማረ ከፍም ወደ እቶን የሚጓዝ ነው። ልብህ በሰዎች ሊከዳ ይችላል፣ ብስጭት ውጥ ስትገባ ግን ራስህንም ከድተሃል። ከዳተኛ ሲሄድ የመሳፈርያ ስጠው ፤ ቢቆይ የሚያስወጣህ ከዚያ በላይ ነው። የ አንባቢ የ አስተዎይ እና የልበ-ሰፊዎች ቤት። የፈለጉትን መፅሀፍ ለማዘዝ👉0949430347👉0921462425 ይደውሉ።🙏😍 ቤሪያ መፅሐፍት ቤት አድራሻ ሆለታ Tele ፊት ለፊት ያለው ህንፃ ሁለተኛ ፎቅ። https://t.me/beriyabooks
Show all...
Elohim ✍️ድንገት ዛሬ አሁን ከደቂቃዎች ብዋላ በመኪና አደጋ ድንገት ብሞትስ ብለህ/ሽ አስበህ ታቃለህ ተኝተህ ምንም ሳትታመም ከተኛውበት ባልነቃስ ብለህ ታቃለህ ወይ ደግሞ እንቅፋት መቶህ ልሞት እችላለሁ ብለህ እሰብህ ታቃለህ አይ ከነዚ ነገሮች ራሴን ጠብቃለው ካልክ ደሞ በጣም ትንሽ ያልካት ቁስል ወደ ካንሰር ተቀይሮ ሂወትህን ሊያሳጣህ ይችላል ይሄ ሁሉ እደማይ ደርስብህ እርግጠኛ ምቶንበት ነገር የለም እጅ ላይ ያለው ብዙ ገንዘብ ዝና ክብር ብዙ ሰዎችን ማወቅህ ወጣት መሆንህ የትኛውም ነገር ሞት ከሚለው ነገር ሊያስጥልህ አይችልም እጅህ ላይ ያለው ነገር ለሂወትህ ቤዛ መሆን አይችልም 👉የሂወት ዋጋ ውድ ነው ለዛ ነው ነብስህን ከሲኦል ሊያስመልጥ በሚችለው ሞትን ባሸነፈው በክርስቶስ እየሱስ መታመን ያለብህ እሱ ብቻ ነው ሞትን ሲያሸንፍ ያየነው እሱ ብቻ ነው ተስፋ የገባልክ ሂወትህን ካዳኝ ወጥመድ የሚያስመልጥ ። ትምክትህ የታለ ብዙ ገንዘብ ሀብት ዝና መልክ የጊዜው ሰው መሆንህ ነው ይሄ ሁሉ ድንገት ሊመጣብህ ካለው አደጋ አያስመልጥህም ወንድሜ ትምክት አንድ ነው ሊሆን የሚገባው ነብስህን ከክፋት የሚናጠቀውን ብት ሞት እንኳን ከሲኦል የሚያወጣክ ሁል ጊዜ በአብ ፊት ጥብቅና ሚቆምልህ ስላንተ ዋጋ የከፈለው እየሱስ ነው ለዛሬ ቀን በሱ ታመን ሚመካ ቢኖር በእግዚአብሔር ይመካ። #ተባርካቹዋል @truegospell @truegospell @truegospell
Show all...
ዮሐንስ 3 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁸ በእርሱ የሚያምን ሁሉ አይፈረድበትም፤ በእርሱ የማያምን ግን በአንዱ በእግዚአብሔር ልጅ ስም ስላላመነ፣ አሁኑኑ ተፈርዶበታል። ¹⁹ ፍርዱም ይህ ነው፤ ብርሃን ወደ ዓለም መጣ፤ ሰዎች ግን ሥራቸው ክፉ ስለ ነበረ፣ ከብርሃን ይልቅ ጨለማን ወደዱ፤ ²⁰ ክፉ የሚያደርግ ሁሉ ብርሃንን ይጠላል፤ አድራጎቱም እንዳይገለጥበት ወደ ብርሃን አይመጣም። ²¹ በእውነት የሚመላለስ ግን ሥራው በእግዚአብሔር የተሠራ መሆኑ በግልጽ ይታይ ዘንድ ወደ ብርሃን ይመጣል።” ስራችን በእግዚአብሔር ተሰርቶልናል። አሜን!!!! @tsegabecha @tsegabecha
Show all...
በእውነቱ ውሸት በብዙ ሰዎች ተቀባይነት ስላገኘ ብዙ ሰዎች ስላጨበጨቡለት እውነት አይሆን። እውነትም ተቀባይነት ስላጣ ብዙ ሰዎች ስላልተቀበሉትም ውሸት አይሆንም። ነገር ግን ውሾች እና ውሸታሞች ውሸትንh እውነት ነው ብለው እውነተኞችን ውሸተኞች ይላሉ። ከነዚህ አይነት ሰዎች ተጠንቀቁ። 👇👇👇 “ከውሾች ተጠበቁ፥ ከክፉዎችም ሠራተኞች ተጠበቁ፥ ከሐሰተኛም መገረዝ ተጠበቁ።” — ፊልጵስዩስ 3፥2 👇👇 @tsegabecha @tsegabecha
Show all...
“ስለዚህ፥ ወንድሞች ሆይ፥ የጨዋይቱ ልጆች ነን እንጂ የባሪያይቱ አይደለንም።” — ገላትያ 4፥31 📌በኤክሊሽያ ህብረት የተዘጋጀ ልዩ ውይይት በወንድም #ተሜ ና #ቤኪ ሰምታችሁ ተባረኩበት! @tsegabecha
Show all...
Musiceklishiya2.mp328.11 MB
ትላንት ና ዛሬ እግዚአብሔር ረድቶን መጽሐፉን በደማቅ ሁኔታ አስመርቀናል ክብሩን ሁሉ ጌታ ይውሰድ ውድ የዚህ ቻናል ቤተሰቦች ይህን ድንቅ መጽሐፍ ለማግኘትም ሆነ ገዝታችሁ ማከፋፈል ለምትፈልጉ ሁሉ አጃችን ላይ በቂ መጽሀፎች ስላሉ ልታናግሩኝ ትችላላችሁ በተለይ ወጣት ኮሚቴዎች ካላችሁ ይህን መፅሐፍ ወስዳችሁ ለወጣቶቻችሁ እንድታደርሱ አበረታታለው ብዙ ጊዜ ለሌላ ብዙም ለህይወታችን ለማይጠቅሙን ነገሮች ገንዘባችንን ወጪ እናደርጋለን ታድያ ከነሱ ወጪዎቻችን ውስጥ የተወሰነውን ቀንሰን ይህን ህይወት ለዋጭ መጽሐፍ ገዝተን ብንጠቀምበት ብዙ ነገር እናተርፋለን ስትገዙ ጸሀፊውንም እያበረታታችሁ እንደሆነ እያሰባችሁ ዋጋው፦ 150 ብር ነው @danabera @elohim351 @beki_Christian መጽሐፉን ለማግኘት ካሰቡ ከላይ በላኩላችሁ ሰዎች በኩል መረጃ ማግኘት ትችላላችሁ መጽሐፉን አንብቡ እንጂ አለመለወጥ አትችሉም ! አዲሱ ዓመት አዲስ ምዕራፍን ምትጀምሩበት ዘመን ይሁንላችሁ @slehiywet
Show all...
ትላንት ና ዛሬ እግዚአብሔር ረድቶን መጽሐፉን በደማቅ ሁኔታ አስመርቀናል ክብሩን ሁሉ ጌታ ይውሰድ ውድ የዚህ ቻናል ቤተሰቦች ይህን ድንቅ መጽሐፍ ለማግኘትም ሆነ ገዝታችሁ ማከፋፈል ለምትፈልጉ ሁሉ አጃችን ላይ በቂ መጽሀፎች ስላሉ ልታናግሩኝ ትችላላችሁ በተለይ ወጣት ኮሚቴዎች ካላችሁ ይህን መፅሐፍ ወስዳችሁ ለወጣቶቻችሁ እንድታደርሱ አበረታታለው ብዙ ጊዜ ለሌላ ብዙም ለህይወታችን ለማይጠቅሙን ነገሮች ገንዘባችንን ወጪ እናደርጋለን ታድያ ከነሱ ወጪዎቻችን ውስጥ የተወሰነውን ቀንሰን ይህን ህይወት ለዋጭ መጽሐፍ ገዝተን ብንጠቀምበት ብዙ ነገር እናተርፋለን ስትገዙ ጸሀፊውንም እያበረታታችሁ እንደሆነ እያሰባችሁ ዋጋው፦ 150 ብር ነው @danabera @elohim351 @beki_Christian መጽሐፉን ለማግኘት ካሰቡ ከላይ በላኩላችሁ ሰዎች በኩል መረጃ ማግኘት ትችላላችሁ መጽሐፉን አንብቡ እንጂ አለመለወጥ አትችሉም ! አዲሱ ዓመት አዲስ ምዕራፍን ምትጀምሩበት ዘመን ይሁንላችሁ @slehiywet
Show all...
ሮሜ 12 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ እንግዲህ፥ ወንድሞች ሆይ፥ ሰውነታችሁን እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝና ሕያው ቅዱስም መሥዋዕት አድርጋችሁ ታቀርቡ ዘንድ በእግዚአብሔር ርኅራኄ እለምናችኋለሁ፥ እርሱም ለአእምሮ የሚመች አገልግሎታችሁ ነው። ² የእግዚአብሔር ፈቃድ እርሱም በጎና ደስ የሚያሰኝ ፍጹምም የሆነው ነገር ምን እንደ ሆነ ፈትናችሁ ታውቁ ዘንድ በልባችሁ መታደስ ተለወጡ እንጂ ይህን ዓለም አትምሰሉ። #በልብ መታደስ :- ማለት ልብ አይምሮን ይውክላል መታደስ ደግሞ ያረጀን ነገር ወደ ነበረበት መመለስ መለወጥ ደግሞ በታደሰው የሕይወት ማንነት አዲስ የሆነን የሕይወት ስርዓት መከተል ነው።  ይህም ማለት ሰው በክርስቶስ ማመን ሲጀምር አይምሮው ሙሉ በሙሉ እግዚአብሔርን በእውነተኛ መንገድ የመፈለግ ውሳኔ ማድረግ ይጀምራል ለመለወጥ ግን ሂደት ያስፈልጋል ዛሬም በልብ በመታደስ ለመለወጥ የሚያስችለንን መርሆዎች እናጠናለን። 1. #በልብ_መታደስ_ለመለወጥ_ምን_ያስፈልጋል ።  1.1. #እራስን_የተወደደ_መስዋዕት_አድርጎ_ማቅረብ  ይህ ማለት ስጋችንን ብዙ ነገር ቢፈልግም እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኘውን መንገድ በመከተል በሰዎች ፊት የእግዚአብሔርን መንግሥት ስንገልጽ #ለአእምሮ_(ለታደሰው) የሚመች አገልግሎት መስጠት ሰው በእኛ ውስጥ እግዚአብሔርን እንዲያይ ከፈለግን ከታደሰ አእምሮ የመሚነጭ አገልግሎት ያስፈልጋል  1.2. #በጎ_እና_ደስ_የሚያሰኘውን_የእግዚአብሔርን_ፍቃድ_መፈጸም  በእግዚአብሔር ቃል ውስጥ በጎ እና ደስ የሚያሰኝ የእግዚአብሔር ፍቃድ ሆኖ የተገለጠው የኢየሱስ ሕይወት ነው ሰው በክርስቶስ ሕይወት ቁጥጥር ውስጥ ሆኖ የሚወስነው ሁሉ ወደ እግዚአብሔር ደስታ ያስጠጋዋል ደስ የሚያሰኝ የእግዚአብሔር ፍቃድ ማለት ቅድሚያ ለእግዚአብሔር ደስታ መኖር ማለት ነው የእግዚአብሔር ደስታ ደግሞ ሀይላችን ነው ።  ምንም ደስታ ውጤታማ ሚሆነው የእግዚአብሔርን ደስታ ፍጹም ማድረግ ስንችል ነው።  1.3. #ይህንን_ዓለም_ባለመምሰል_ነው።  #ይህ ዓለም የሚከተለው የራሱ የሕይወት ርዕዮት አለው (ስርዓት) አለው በእግዚአብሔር ቃል ደግሞ አሮጌ ስለተባለ የትኛውም በዓለም ያለ የሕይወት ፍልስፍና በእግዚአብሔር መንግሥት የሕይወት ክልል ለሚኖር ሰው የተመቸ መሆን አይችልም  #እኛ የምንከተለው የሕይወት ስርዓት በእግዚአብሔር መንግሥት ውስጥ በክርስቶስ የተገለጠውን የሕይወት ስርዓት ያንን መቀበል እንዲችል አይምሮዋችን ታድሷል በሁለንተናችን ደግሞ የዛን ዓለም ክብር ለማንፀባረቅ እየተለወጥን መሄድ አለብን። #የካድከው_ዓለም_አይረዳህም #የአንተ_የሕይወት_ስርዓት_የሚቀዳው_በካድከው_ሳይሆን_በገባህበት_ዓለም_ነው።  @truegospell @truegospell 👈 #ይቀላቀሉን @truegospell @Truegospell
Show all...
Helina Dawit " ይቅርታዬ " @MARKENGETA የክብር ልብሷን ለብሳ እንደ ቆመች ንጉሱ ፊት የወርቁንም ዘንግ እንደ ነካች ጥያቄዋን እንደመለሰላት እኔም እየሱስን ለብሼ አብ ፊት ሞገስ አገኘው አባ አባት ማለት ድፍረቴ ተመለሰልኝ ወደ ህይወቴ አባቴ የማለት እምነቴ ተመለሰልኝ ወደ ቤቴ የመማጸኛ ከተማዬ ዘልዬ የማመልጥበት ከአሳዳጅ ከአስጨናቂዎቼ ተሸሽጌ ምገባበት እየሱስ በተባለው ድንቅ ስም ነፍሴ አርፋለች ከምንም እርሱ የከፈለውን ዋጋ አልፎ ማነው እኔን ሚነካ በደም የከፈለውን ዋጋ ደፍሮ ማነው እኔን ሚጠጋ ከሳሾቼ ብዙ ናቸው ተጨባጭ መረጃ አላቸው በህጉ መሰረት ቢሄዱ አሳማኝ ነው ምክኒያታቸው በየትኛው ቅድስናዬ ልጋፈጥ ልቁም ለራሴ አንገት መድፋት መሸማቀቅ ዝምታ ብቻ እንጂ መልሴ የቤቴ ክፍተት ሳይገፋው ገፍቶ ባይገባ ከደጄ የልቤ ርቀት ሳይመልሰው ባያቅፈኝ ባይሆን ወዳጄ ሁሉን በራሱ ፈጽሞ ባያደርገኝ ኖሮ ቀና ጽድቄ ብዬ ማስቆጥረው የማሳየው ምን አለና ፍርድ አልተዛባም ልክ እኮ ነው ተከድኖ ሳይሆን ተከፍሎ ነው በከንቱ አይደለም ደስታዬ ኢየሱስ ሆኖኝ ነው ይቅርታዬ ፍርድ አልተዛባም ልክ እኮ ነው ተከድኖ ሳይሆን ተከፍሎ ነው በከንቱ አይደለም ደስታዬ ስለሆነኝ ነው ይቅርታዬ ____ like & share በማድረግ ለሌሎች ያጋሩ ▷ @markenzema_bot ◁ ▷ @markenzema_bot ◁ 👆&👇△Join Us△ @tsegabecha @tsegabecha
Show all...
ይቅርታዬYIKRTAYENEWAMHARICGOSPELSONGBYYEABSIRADAWITANDHELINADAWIT.mp34.68 MB
Choose a Different Plan

Your current plan allows analytics for only 5 channels. To get more, please choose a different plan.