Sankofa_Readers_Association
Open in Telegram
Read, Change, Share እናንብብ፤ እንለወጥ፤ እናካፍል ፡ This is the channel of sankofa readers association working with the motive "reading leads to change then to nearest perfection in doing art."comment is welcomed Contact: @Poco_L0c0 @markrylos
Show moreEthiopia11 173The category is not specified
1 162
Subscribers
No data24 hours
-27 days
-1430 days
Posts Archive
#የሐምሌ በረከቶች(አዳም ረታና በውቀቱ ስዩም)
እንኳን ተወለዳችሁ!!!
"አዳም ረታ እራሱ ዘመን ኾኗል። የሥነ ጽሑፋችን የመጪው ዘመን ተመራማሪዎች አዳም የዘመን መለወጫ ካላንደራቸው እንደሚኾን ለመገመት እውቀት አይፈልግም። ያኔ "ከአዳም በፊት" "ከአዳም በኋላ" ይባላል። ዓመት መጥቀስ ሳያስፈልግ በአዳም ጊዜ ስለ ኢትዮጵያ የአማርኛ ሥነ ጽሑፍ የዘመን ምዕራፍ ይሰፈራል። የተሰጠው ሃያሲ ቴዎድሮስ ገብሬ
"ዛሬ አዳም ልማድ ኾኗል።" ይላል። እንኳን ልማዳችን ተወለደ።"
#ሄኖክ ስዩም(ተጓዡ ጋዜጠኛ)
"ትላንትና በደስታ ያደራችሁ ሰዎች እግዚአብሔር እንደኔ አያድርጋችሁ"
#አጼ ቴዎድሮስ
አጼ ቴዎድሮስ መቅደላ ከወጡ በኋላ እና ገብርዬ እንደሞተ ሁለቴ ራሳቸውን ለመግደል ይሞክራሉ። መጀመሪያ ላይ ሰዎች ያስጥሏቸዋል (ይሄ የታንጉት ምሥጢር ላይ ይሆን The Barefoot Emperor ላይም ተጽፎ ነበር።) ታድያ ሁለት ደብዳቤዎች ይጽፋሉ። የመጀመሪያውን ሙከራ ከመሞክራቸው በፊት እና ከተረፉ በኋላ። እዩ ሲያሳዝኑ።
ግን በደንብ እንድታዩ የፈለግኩት ራሳቸውን ለመግደል ከመሞከራቸው በፊት ራሳቸውን «ካሳ» ብለው ይጠራሉ። እንዳልሞቱ ካዩ በኋላ «ቴዎድሮስ» ይላሉ እራሳቸውን። እግዚአብሔር እንዳልተለያቸው እያሰቡ ይሆናል ስለተረፉ። ቴዎድሮስ የሚባል ንጉሥ ከምሥራቅ ይመጣል የሚል ትንቢት አልነበረ? ከሱ አይደል ስማቸውንስ መረጡ የሚባለው? ትንቢቱ ደግሞ ከፍካሬ ኢየሱስ የተወሰደ ነው።
ለማንኛውም ደብዳቤዎቹን እዩ።
እራሱን ካሳ የሚልበት ላይ እንዲህ ይላል፡ «ያገሬ ሰው ግብር ሥራት ግባ ብየብለው እምቢ ብሎ ተጣላኝ። እናንተ ግን በስራት በተገዛ ሰው አቸነፋችሁኝ። እኔን ወደውኝ የተከተሉኝ ሰዎች አንድ እርሳስ ፈርተው ጥለውኝ ሸሹ። ... ጌታነኝ መስሎኝ ባልሰላ መድፍ ሥታገል ውየ ነው። ያገሬ ሰው የፈረንጅ ሃይማኖት ይዞአል፡ አስልሞአል እያለ አስሩን ምክንያት ይሰጠኝ ነበረ። እኔ ከፋሁበት እግዚአብሔር መልካም ይሥጠው እንደወደደ ይሁን። እግዚአብሔር ቢሠጠኝ ሁሉን ልገዛ አሳብ ነበረብኝ። እግዚአብሔር ቢነሣኝ ልሞት አሣቤ ይህ ነበረ። ... ትላንትና በደስታ ያደራችሁ ሰዎች እግዚአብሔር እንደኔ አያድርጋችሁ። እንኳን የሀበሻ ጠላቴን ኢየሩሳሌም ዘምቸ ቱርኮችን አስለቅቃለሁ መስሎኝ ነበረ።»
ሁለተኛው ደብዳቤ ደግሞ እንዲህ ይላል በከፊል
«ያገሬ ሰው ከትዛዝ መውጣቱን አይቸ። ብገለው ብቀጣው አልመለስልኝ ቢል ቢነደኝ ብቀና በገዛ ጠበንጃዬ እሞታለሁ ብየ ሰይጣን አሣብ አሳደረብኝ። አይ ይህን ሁሉ ሠራዊት ዋቢ አልቦ ትቸው አልሂድ እግዚአብሔር ይጣላኛል ብየ አጣድፌ ከርስዎ ሠደድሁት እኔ ስሞት ሲድበለበል ቃሌ ሣይደርስልዎ ይቀራል ብየ። ከሰደድሁልዎ በኋላ ግን ጠበንጃየን ቃታ ከፍቸ ካፌ አጉርሼ ብስበው ብስበው እምቢ አለኝ። ሰዎች ሩጠው መጥተው ካፌ ሲመዙት ተተኮሰ። እግዚአብሔር አትሙት ካለኝ ግን ብተርፍ። ... ፊታውራሪ ገብርየን የኔን ወዳጅ ሣላስነሣው ያደርሁ ከሞትሁኝ ሁሉንም አብረው ይቅበሩን ብየ ነበር ቁሜ ከዋልሁ ግን ልቅበረው ይፍቀዱልኝ።»
በሙሉ አንብቧቸው ጊዜ ሲኖራችሁ።
ምንጫችን፡ Appleyard & Pankhurst, The Two Last Letters of Emperor Tewodros II of Ethiopia, 1987.
@EthiopiaInHistory(ጦቢያን በታሪክ)
ትንሽ ቦታ
በዚህ ዓመት፣
ብንጣላ መታረቂያ
ብንታረቅ ለመጣያ
ትንሸ ቦታ መጠለያ
ትንሽ ቦታ መሠደጃ፡፡
ምናለበት፣ ለምናልባት ብንተውለት
ፍፁም መሆን ስለማንችል
ትንሽ ቦታ እንዋዋል፣በልባችን ደግ እንሁን፡፡
በአንጎላችን መላወሻ፣
ትንሽ ቦታ እንተውለት
<<ምናልባት›› የምንልበት!!
ልክ እንደአምና ለዚህ ዓመት
ብንጣላ መታረቂያ
ብንታረቅ ለመጣያ
ብንታሠር ይቅር ማያ
ትንሽ እንተው ባዶ ቦታ፡፡
ጥግ ድረስ የለም ስራ፣ጥግ ድረስ የለም ፋታ፡፡
በልባችን ደግ በኩል፣ እንፈልግ ባዶ ቦታ፣
የጳጉሜ አይነት ትንሽ ቦታ፡፡
ለዘመን መለወጫ፡፡
ነብይ መኮንን(1948 ዓ.ም-2016ዓ.ም)
2005 ዓ.ም
ስውር ስፌት ቁጥር 2.
#ነብይ መኮንን
#sankofa readers association
#Read,change, share
"አጽንዕዋ ለጥበብ፤ ጥበብን አጥኗት"
መዝሙረኛው ቅዱስ ዳዊት
ሁሉም ነገር በመጫር ይጀምራል!
፩ኛ ዓመት🎉🎉🎉
@sankofabooks
ጭረት ፱
"A lot can happen in a year"
🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆
ጭረት በ1ኛ ቅጿ "ሳንኮፋን" ፣በ፪ኛ "ብርቧክስ" ፣በ፫ኛ" የካሮ ጎሳ"ን፣ በ፬ኛ "ጋሽ ኃ/ሥላሴ መሀሪን፣ በ፭ኛ "Loving Vincent"ን፣ በ፮ኛ "The kite runner"፣ በ፯ኛ " ካራማራ"፣ በ፰ኛ "A Sufi"ን ይዛ አንድ ዓመትን ከእናንተ ጋር ዘልቃለች።
እንኳን አደረሰሽ ጭረት!!!
በጭረት ፱ ደግሞ
ምቁር ዜማ፣ ከጫማው ስር፣ ለውጥ፣ ጎለጎታ፣ ጥበበኛ እጆች፣ modern vs contemporary፣ የህማም ቁልፎች፣የሩሒ ማስታወሻዎች፣ በሀሳብ መንገድ፣ የአሌክስ ብዕሮች፣ ከብዕር ሙሉዓለም፣ የጭረት ቆይታ፣ ግጥሞች፣ የመጽሐፍና ፊልም ዳሰሳዎች፣ ደብዳቤና ትውስታዎች ተካተውበታል።
" ሁሉም ነገር መጫር ይጀምራል"
🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆
ሐሙስ ሰኔ 27 በሳንኮፋ የቴሌግራም ገጽ ላይ ጭረት ፱ን ይጠብቁ።
#ጭረት ፱
#ሳንኮፋ የአንባብያን ማኅበር
#እናንብብ፣እንለወጥ፣እናካፍል
# ርዕስ አልቦ
📄📄📄📄📄📄📄📄📄📄📄📄
እስከዛሬ ስም አውጥተን በጠራናችሁ ድግስ የተሳተፋችሁ እድምተኞቻችን፣ የዛሬን እንኳ ታድማችሁ ስም እንድታወጡለት አሰብ አድረግንና ርዕስ አልቦ ልንጠራችሁ ወደድን!
"ርዕስ የለንም፣ ርዕስ የለውም"!
📄ደብዳቤ
✍ግጥም
🎼Lip sync
🎸ሙዚቃ
📄ወግ
✍መጣጥፍ
📄📄📄📄📄📄📄📄📄📄📄📄📄📄
ሁሉም የየግሉን ስም ሰጥቶ የሚሄድበት የጥበብ ድግሳችን አርብ ዕለት፣ ከምሽቱ አንድ ሰዓት ጀምሮ እናንተን ይጠብቃል።
📄📄📄📄📄📄📄📄📄📄📄
መታችሁ፣ ታድማችሁ፣ ርዕስ አውጡ!!!
📄📄📄📄📄📄📄📄📄📄📄
#አርብን በሳንኮፋ
#እናንብብ፣እንለወጥ፣እናካፍል
#ሳንኮፋ የአንባብያን ማኅበር
#የሥነ ጽሑፍ ውድድር
ሳንኮፋችን ከሰኔ 1 እስከ ሰኔ 15 ድረስ የሥነ ጽሑፍ ውድድር ለማካሄድ አስባለችና ግጥም ወግና አጭር ልብወለድ ያላችሁ ሁሉ በተባሉት ቀናት ስራችሁን ይዛችሁ እንድትቀርቡ አደራ ትላለች።
✍✍✍✍✍✍✍✍✍✍✍✍✍
ለአሸናፊዎቹ የንባብ ቤት እንደመሆኗ መጽሐፍ የምታበረክት ይሆናል።
#ውድድር
#ሳንኮፋ የአንባብያን ማኅበር
#እናንብብ፣እንለወጥ፣እናካፍል
ሙዚቃን በጉሮሮ ከማዜም ባሻገር እንደ አንድ ሳይንስ ግኝት ተጠንቶና ተብላልቶ ለአድማጭ ጆሮ ማድረስ እንደሚገባና ለጥበብ ስራ የሚሰጥን ክብር እውቀትና ልብ ለመረዳት ከደጋ ሰው አልበም ጀርባ የተሰራውን ዶክመንተሪ ማየት በቂ ነው። ምንአልባት የዚህ ዓመት ምርጡ አልበም ቢባል የሚያንሰው ፣ ከግጥምም ሆነ ዜማ አንድም የሚጣል ሙዚቃ ይኖረዋል ለማለት በራሱ የማይቻልልለት ነው "የደጋ ሰው" ።
አልበሙ ከወጣ አምስት ወራትን ያስቆጠረ ሲሆን የማ(የማርያም ቸርነት) በማዜም ኢዩኤል መንግስቱ ደግሞ ፕሮዲውስ በማድረግ ተሳትፈውበታል።
🎼🎼🎼🎼🎼🎼🎼🎼🎼🎼🎼🎼🎼🎼
እናም አድማጮች ሆይ አዲስ ሊያውም አሪፍ ነገር ማድመጥ አያስደብራችሁምና
"የደጋ ሰው" ን እንድታደምጡት ጋበዝን
#የደጋ ሰው
#ሳንኮፋ የአንባብያን ማኅበር
#እናንብብ፣እንለወጥ፣እናካፍል
#ሌላኛዋ ሴት
"They Went Home"
They went home and
told their wives,
that never once in all their lives,
had they known a girl like me,
But... They went home.
They said my house was licking clean,
no word I spoke was ever mean,
I had an air of mystery,
But... They went home.
My praises were on all men's lips,
they liked my smile, my wit, my hips, they'd spend one night, or two or three.
But..."
📄📄📄📄📄📄📄📄📄
ይሄ ግጥም በ1970s አካባቢ በ ማያ አንጄሎ የተጻፈ ሲሆን ሶስት ሰዎችን በውስጡ የያዘ ነው ማለትም ሌላኛዋ ሴትን(The other woman), ሰውዬው( The man) እና ባለቤቱ( The wife):: ከሁሉም ይልቅ ግን የሌላኛዋን ሴት የፈረሰ ተስፋና ሀዘንን የሚጎላው ይሄ ግጥም እንደሚወዷት መንገራቸውና ቢነግሯትም አብረዋት አለመቆየታቸውን ጸሀፊዋ "They went home" እያለች በየመሀሉ በምትደጋግመው ቃል ሀዘኗን ታስረግጥላታለች ::
"They went home" ን ለሌላኛዋ ሴት ጋበዝን...
#They went home
#sankofa readers association
#read,change, share
#Bestfriendoch ነነ
"Family isn’t always blood. It’s the people in your life who want you in theirs. The ones who accept you for who you are. The ones who would do anything to see you smile, and who love you no matter what."
Maya Angelou
Happy best friends day☺️☺️☺️
#Best friends
ይህ "Anguish" የተባለው ስዕል እ.ኤአ 1878 በጀርመናዊው ሰዓሊ Friedrich schenck የተሳለ ሲሆን በሰሙ በገዳዮቹ ቁራዎች መሀል፣ የሞተ ጠቦቷ ሀዘን ለማውጣት ወደላይ ለአቤቱታና ለእርዳታ የምትጮህ እናት በግን የሚያሳይ በወርቁ ደግሞ ያለንን ወስደውና ሰውነታችንን ገድለውን ሲያበቁ፣ ሀዘናችንን እንኳን ለማውጣት ሳያስጠብቁ የተቀረውን ደግሞ ለመቀራመትና ለመብላት በሚናጠቁ ቁራዎች መሀል መኖራችንንና አቅም እንዳጣችው በግ መልሰን በማንዋጋቸው ጠላቶቻችን በደል ወደላይ የምንጮህ እኛን የሚያመላክት ነው።
#Anguish
#ሳንኮፋ የአንባብያን ማኅበር
#እናንብብ፣እንለወጥ፣እናካፍል
*የካፊያ ምች**
አርቲስት ተፈሪ አለሙ
ሳልላክ ተልካ እንሂድ አለቺኝ
ካላጣችዉ ሰዓት ከቤት አስወጣቺኝ
ጥርቅም ዕቅፍ አርጋ በካፊያ ሳመቺኝ
የዕድሜ ልክ ልክፍቴን ያኔ አስለከፈቺኝ።
መብረቅ እየጮኸ ዝናብ እያካፋ
የኔ ልብ በሷ የሷ በኔ ጠፋ
የሰማዩ ባህር ቁልቁል ተንዶብን
ዉሃ ጠማኝ ዉሃ እየዘነበብን።
ጠፍቼ ስመለስ ከእቅፏ ስወጣ
በርዶኝ አተኮሰኝ እቤቴ ስመጣ
እያደር አደረ ከርሞ ከረመብኝ
የዘመን ሕመሜን ያን ዕለት ታመምኩኝ።
አሁን አሁን ታዲያ!
ደመናዉ ሲጠቁር ነጐድጓድ ሲያጓራ
ነፋስ ሲያስገመግም ክረምቱን ሊጣራ
ግንቦት ማለቂያ ላይ ይነሳል ህመሜ
ሲያቀብጠኝ በዝናብ በካፊያ ተስሜ፥
ምች ተሳልሜ።
#ግንቦት
#እናንብብ፣እንለወጥ፣እናካፍል
#ሳንኮፋ የአንባብያን ማኅበር
ጭረት ፰(8)
«Between me and you there is only me. Take away the me, so only you remain»
Mansur al hallaj
ሁሉም ነገር በመጫር ይጀምራል!
@sankofabooks
ጭረት ቅጽ 8
🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆
" I once had a thousand desires , but in my one desire to know you, all else melted away. "
በዚኛው እትሙ ከምድራዊ ፍቅር ተለቃልቆና ተላቆ ከተሰውፎች(Sufi) ጋር ወደ ላይ ተመንጥቆ በሰማያዊ ፍቅርንና ናፍቆት ይነሸጣል።
የጭረት 8(፰)
የአንደኛ ዓመት ዋዜማ የመጨረሻው መጽሔት ረቡዕ ግንቦት 14 በሳንኮፋ ቴሌግራም ይጠብቁ።
📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚
ሁሉም ነገር በመጫር ይጀምራል!!!
📄📄📄📄📄📄📄📄📄📄📄📄
አምደኞች
መግደላዊት፣ዳዊት የአለም ዘውድ፣Niksen፣ረድኤት የኔሽት፣ጌራ፣ሳሮን ኤሊያስ፣ሙሳፊር ና ፍናማርያም፣ዕዝራ ጥላሁን፣እጸህይወትና ቢኒያም፣አንዋር ያህያ፣ረድ ዘሁሩታና phoebe፣ያብስራ ብርሃኑ፣ነጃት ሀሰን።
#ጭረት
#ሳንኮፋ የአንባብያን ማኀበር
#እናንብብ፣እንለወጥ፣እናካፍል
"ዘጠኝ ሞት መጣ፣ አንዱን ግባ በለው!"
🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆
አርብን በሳንኮፋችን ተመልሳለች
ሞት
የሞት ምሽት
ሞት አምሮሀል?
ሞት ናፍቆሻል?
ሞት ፈርተሻል?
የሞትን ዙፋን በልብህ ማን/ምን ሰራው?
ሳትሞት ምን ሞቶ ማየት ትመኛለህ?
ማንን ምንንስ መግደል ናፈቀሽ? ናፈቀህ?
ዐርብ ማታ ምን እንግደል?
🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆
ስለሞት እንመርምር ስለሞት እንጠበብ ስለሞት እንሳቅ ስለሞት እንረፍ....የት?...በG.C ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ካለችው ድንቅ ደሴት ከሳንኮፋ !። ሞት ከሸተተን ቦታ ሁሉ ሞት ካልሸተተን ቦታ ሁሉ በሞቴ ስለሞት መድረክ በሞት እንረፍ።
ነገ ዐርብ በተማሪዎች ህብረት ቢሮ ፊትለፊት
ሟች ሁላ ስለሞት ይገናኛል።
ሁላችሁም ተጋብዛችኋል!!!
ሚያዚያ 4/2016 ዓ.ም
ከምሽቱ 12:30 ጀምሮ
ከተማሪዎች ህብረት ፊትለፊት
"ከሞት ጋር ቀጠሮ"
#ሞት
#አርብን በሳንኮፋ
#እናንብብ፣እንለወጥ፣እናካፍል
https://youtu.be/XD_3KnbpASw?si=UU5QMXecFfO9Cn7z
ለትውስታ
📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚
ዶ/ር አለማየሁ ዋሴ እሸቴ በ2011ዓ.ም በሳንኮፋ መርሐ ግብር ላይ የተናገሩት።
"እሱና እንደሱ የተሰው ሁሉ ሞቱ አይባሉም፣በታሪክ ይኖራሉ።"
📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚
ውድ አንባብያን
እንኳን ለ46ኛው የካራማራ ድል አደረሳችሁ!
የድል ወር የተባለ የካቲት የሚዘክር ጭረት ቅጽ ፯(7) እንካችሁ🤗
ሁሉም ነገር በመጫር ይጀምራል!!!
ጭረት
📚📚📚📚📚📚📚📚📚📚
#ጭረት ፯
#ሳንኮፋ የአንባብያን ማኅበር
#እናንብብ፣እንለወጥ፣እናካፍል
