en
Feedback
አዲስ ትውልድ የቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊዎች ጥምረት

አዲስ ትውልድ የቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊዎች ጥምረት

Open in Telegram

ክለባችን በሶሻል ሚድያ አስተማማኝ በሆነ መልኩ በfb,YouTube,tiktok,instagram,twitter በመጠቀም ከፍተኛ ገቢ ሚያገኝበት መንገድ መፍጠር ነው✌ 💥ሙሉ መረጃ ✌ ትኩስ ዜናዎች ✌ የጨዋታ ዘገባዎች ✌ ታሪኮች

Show more
1 970
Subscribers
No data24 hours
-47 days
-1730 days
Posts Archive
የመርሀ ግብር ለውጥ ! ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 2018 የኢትዮጵያ ዋንጫንና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ጨዋታዎችን መነሻ በማድረግ የተስተካከለው መርሀ ግብር ይፋ ተደርጓል።
የመርሀ ግብር ለውጥ ! ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 2018 የኢትዮጵያ ዋንጫንና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ጨዋታዎችን መነሻ በማድረግ የተስተካከለው መርሀ ግብር ይፋ ተደርጓል።

የዜና መግለጫ ግንቦት 4 ቀን 2018 ዓ.ም ቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ አራት የውጪ ሀገር ዜግነት ያላቸው ተጨዋቾችን አስመጣ ቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ እየተወዳደረ ለሚገኝበት የ2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ተሳትፎውን በተሻለ ውጤትና ብቃት ለማጠናቀቅና በሊጉ ተፎካካሪ ሆኖ እንዲጨርስ ይረዳው ዘንድ የአይቮሪኮስት፣ የኮንጎ ብራዛቪል እና ሁለት የጋና ዜግነት ያላቸው ተጨዋቾችን አስመጥቷል፡፡ ለክለባችን ለመጫወት ወደ ሀገራችን የመጡት ተጨዋቾች፡- 1. ኬልቪን ኤዶ ዶሴህ ኬልቪን ኤዶ ዶሴህ 1.90 ቁመት ያለው የ23 ዓመት ጋናዊ ወጣት ተከላካይ ነው፡፡ ኬልቪን ወደ ቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ክለብ ከመምጣቱ በፊት በጋና እንዲሁም በአልባኒያ ዋናው ሊግ ተጫውቷል፡፡ 2. ካርተር አሂሮ ካርተር አሂሮ አይቮሪኮስታዊ የ29 ዓመት የአማካይ ስፍራ ተጫዋች ነው፡፡ ካርተር በአይቮኮስቱ ታላቅ ክለብ አሴክ ሚሞሳስን ጨምሮ በኮንጎ፣ ቤሩትና ኦማን ሊጎች ልምድ ያካበተ ተጨዋች ነው፡፡ 3. ክሪስት ቶሉንጋ ሌላው አዲስ ፈረሰኛ ሆኖ ወደ ሀገራችን የገባው የኮንጎ ብራዛቪል ተወላጅ የሆነው ክሪስት ቶሉንጋ ነው፡፡ ክሪስት የ20 ዓመት ወጣት የአጥቂ ስፍራ ተጨዋች ሲሆን ለሀገሩ ከ23 ዓመት በታች ብሄራዊ ቡድን ተሰልፎ ተጫውቷል፡፡ ክሪስት ወደ ሀገራችን ከመምጣቱ በፊት በሀገሩ ለሚገኘው ዲያብሌስ ኖይሪስና ለአልጄሪያው ፓራዱ ክለቦች ተጫውቷል፡፡ 4. አልፍሬድ ሜንሳህ የ26 ዓመቱ ጋናዊ የአጥቂ ስፍራ ተጫዋች አልፍሬድ ሜንሳህ ሌላው የክለባችን አዲሱ ተጨዋች ነው፡፡ አልፍሬድ በአልባኒያ፣ በኮሶቮ እና በጋና ፕሪምየር ሊግ ለተለያዩ ክለቦች ተጫውቷል፡፡ ተጨዋቾቹ በዛሬው እለት ያደረጉትን የህክምና ምርመራ በስኬት ያጠናቀቁ ሲሆን የምዝገባ ሂደታቸውን በማጠናቀቅ ከቡድናችን ጋር ልምምድ ይጀምራሉ። ክለባችን የ2018ዓ.ም የፕሪምየር ሊግ የውድድር ዘመንን በተሻለ ደረጃ ላይ ሆኖ ለማጠናቀቅ ያሉንን ወጣት ተጨዋቾች በልምድ እንዲያግዙ እነዚህን ተጨዋቾች ያስመጣ ሲሆን ሁሌም ከቡድናችን የማይለዩት ደጋፊዎችም በአንድ ልብ ሆነው እንደለመዱት ከተጨዋቾቻችን ጎን በመሆን ድጋፋቸውን እንዲሰጡ እንጠይቃለን፡፡ ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ማህበር ፤ ህዝብ ግንኙነት ክፍል፤

ቅዱስ ጊዮርጊስ vs ሲዳማ ቡና 🗓 አርብ ሚያዝያ 23 /2018 ዓ.ም ⏱ 8⃣ ሰአት 🏟 አዲስ አበባ ስቴድየም 💵 ቲኬቱን በዚህ ሊንክ ይቁረጡ http://ticket.ethiosport.pro
ቅዱስ ጊዮርጊስ vs ሲዳማ ቡና 🗓 አርብ ሚያዝያ 23 /2018 ዓ.ም ⏱ 8⃣ ሰአት 🏟 አዲስ አበባ ስቴድየም 💵 ቲኬቱን በዚህ ሊንክ ይቁረጡ http://ticket.ethiosport.pro

በተጨማሪ ያለ ማሊያ መጥታቹ ስከርቭ ብቻ አርጎ መግባት ስለማይቻል ሁላችሁም ካለአስፈላጊ ንትርክ ለመራቅ ያለ ማሊያ መምጣት አይቻልም።

የድል ቀን የማሸነፍ ቀን የአሸናፊዉ ክለባችን ደጋፊዎች ወደ ስታዲየም ስትመጡ ልታረጉት ሚገቡት ነገሮች 1. ያለ ማሊያ ስለማይገባ ሁላችሁም በዉቡ ቢጫ እና ቀይ ማሊያችን ደምቃቹ ኑልን። 2. ቲኬት ስ
የድል ቀን የማሸነፍ ቀን የአሸናፊዉ ክለባችን ደጋፊዎች ወደ ስታዲየም ስትመጡ ልታረጉት ሚገቡት ነገሮች 1. ያለ ማሊያ ስለማይገባ ሁላችሁም በዉቡ ቢጫ እና ቀይ ማሊያችን ደምቃቹ ኑልን። 2. ቲኬት ስላለቀ እና በር ላይ ስለማይሸጥ ሁላችሁም ስክሪንሹት ያረጋችሁበትን QR CODE ይዛቹ ኑ እምቢ ላላቹ በ @esportgetticket_bot ላይ Start ብላቹ share contact ላይ የቆረጣችሁበትን ስልክ ከገባ የሚመጣላቹ ዝርዝር ላይ ticket 1 ስትነኩት ይመጠላችኋል። 3. የስታዲየም በር ከ5 :30 ጀምሮ ክፍት ነዉ 8 ሰአት ላይ ደሞ ይዘጋል። 4. በተቻለ መጠን መጠጥ ሳትጠጡ ኑ ከድላችን በኋላ ሚከለክለን ምንም ነገር ስለሌለ እንደርስበታለን። 5. ለቲኬተሮች ,ለፀጥታ ሀይሎች እና ለስቲዋርድ አባላቶች ትብብሯን ያሳዩ ሁሌም ምንታወቅበት ጨዋነታችን ዛሬም ማስመስከር አለብን። 6. ሙሉ 90 ደቂቃዉን የተቃራኒ ተጨዋቾችን በሚያፈዘዉ እና በሚያምርብን ዉብ ዝማሬዎቻችን ጀግኖቹን ተጨዋቾቻችንን ማጀገን አለብን። 7. ያዉ ዛሬም እንደለመድነዉ ጎሎችን ማግባታችን አይቀርም በዛ ደስታ መሀል ክለባችን ሊያስቀጡ ሚችሉትን ማለትም ወደ ሽቦ መምጣት እና ወንበር ላይ መቆም ክለባችንን ስለሚያስቀጣ ከወዲሁ መጠንቀቅ ያስፈልጋል። 8. የሚዘጋጁ ሞዛይክ ስለሚኖር በቦታችሁ ላይ ተቀመጡልን ድባቡንም ልዩ ለማረግ ስላለብን። 9. አያሆሆ ማታ ነዉ ድሌ ✌️ 10. ከጨዋታዉ መጠናቀቅ በኋላ ልዩነታችን ሜዳ ላይ መሆኑን አሳይተን ወደ ቤታችን ስንመለስ በፍፁም ሰላም መሆን አለበት የናፈቀንን የክለባችን ጨዋታ ከሸገር ሳይወጣ እዚ ደርሰናል ልናጣዉም አይገባንም። ለጨዋ ደጋፊ ይሄን መንገር አይገባንም ያዉ ለማስታወስ ብቻ ነዉ ✌️ ድል ለኢትዮጵያ አርማዉ እና ለ31 ጊዜ ሻምፒዮናዉ አርበኛዉ ክለባችን ቅዱስ ጊዮርጊስ ✌️✌️✌️✌️

ጊዮርጊሳውያን ፡ የትም ፡ ቢሆኑ ፡ ልባቸው ፡ ከክለባቸው ፡ ጋር ፡ ነው፡፡የክለባችን ፡ ቀንደኛ ፡ ደጋፊ ፡ እና ፡ የቁርጥ ፡ ቀን ፡ ወዳጃችን ፡ የሆነው ፡ ሚድሮክ ፡ ኢንቨስትመንት ፡ ግሩፕ ፡
+3
ጊዮርጊሳውያን ፡ የትም ፡ ቢሆኑ ፡ ልባቸው ፡ ከክለባቸው ፡ ጋር ፡ ነው፡፡የክለባችን ፡ ቀንደኛ ፡ ደጋፊ ፡ እና ፡ የቁርጥ ፡ ቀን ፡ ወዳጃችን ፡ የሆነው ፡ ሚድሮክ ፡ ኢንቨስትመንት ፡ ግሩፕ ፡ ዋና ፡ ስራ ፡ አስፈጻሚ ፡ የሆኑት ፡ አቶ ፡ ጀማል ፡ አህመድም ፡ ከጊዮርጊሳውያን ፡ አንዱ ፡ ናቸው፡፡ አቶ ፡ ጀማል ፡ ከሚድሮክ ፡ ዋና ፡ መስሪያ ፡ ቤት ፡ ይሄን ፡ መልእክት ፡ አስተላልፈውልናል፡፡ከጨዋታ ፡ ጅማሮ ፡ እስከ ፡ ፍጻሜው ፡ በሚድሮክ ፡ ጽህፈት ፡ ቤት ፡ የመስታወት ፡ ግድግዳ ፡ ላይ ፡ የክለባችን ፡ አርማ ፡ እንዲሁም ፡ "ሆ ፡ ብሎ ፡ ተነሳ" ፡ የሚለው ፡ ዝማሬ ፡ መልእክት ፡ እየተላለፈ ፡ ለደጋፊዎቻችን ፡ እና ፡ ለተጫዋቾቻችን ፡ ሞራል ፡ እና ፡ የመነቃቃት ፡ መልእክት ፡ ሲተላለፍ ፡ ውሏል፡፡ አቶ ፡ ጀማል ፡ በቦታው ፡ ባይገኙም ፡ በብልሃት ፡ ከኛ ፡ ጋር ፡ ቡድኑን ፡ ሲያበረታቱ ፡ እና ፡ ሲደግፉ ፡ ውለዋል፡፡ እናመሰግናለን ፡ አቶ ፡ ጀማል እናመሰግናለን ፡ ሚድሮክ ፡ ኢንቨስትመት ፡ ግሩፕ

ተጨማሪ የድል ዜና የተስፋ ቡድናችን የሁለተኛ ዙር ውድድሩን ዛሬ ቡራዩ ስቴድየም ላይ ከቀኑ 8 ሰአት ጀምሯል፡፡አዲስ አበባ ከነማንም 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡ የሴቶች ቡድናችን ሰበታ ስቴድየም ላይ ከወላ
ተጨማሪ የድል ዜና የተስፋ ቡድናችን የሁለተኛ ዙር ውድድሩን ዛሬ ቡራዩ ስቴድየም ላይ ከቀኑ 8 ሰአት ጀምሯል፡፡አዲስ አበባ ከነማንም 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡ የሴቶች ቡድናችን ሰበታ ስቴድየም ላይ ከወላይታ ድቻ ጋር ጨዋታ አድርጎ ከአስገራሚ ፍልሚያ በኋላ 1 ለ 1 ተለያይቷል፡፡

የማሸነፊያዋን ጎል ያስቆጠረው ፍጹም የጨዋታው ኮከብ ተብሎ ተመርጧል፡፡ፍጹም በበኩሉ የጨዋታው ኮከብ እኔ ሳልሆን ሀብታሙ ጉልላት ነው በማለት ሽልማቱን አበረከተ፡፡እኛ ጊዮርጊሳውያን በበኩላችን ሁለታች
የማሸነፊያዋን ጎል ያስቆጠረው ፍጹም የጨዋታው ኮከብ ተብሎ ተመርጧል፡፡ፍጹም በበኩሉ የጨዋታው ኮከብ እኔ ሳልሆን ሀብታሙ ጉልላት ነው በማለት ሽልማቱን አበረከተ፡፡እኛ ጊዮርጊሳውያን በበኩላችን ሁለታችሁም ኮከቦቻችን ናችሁ ብለናል 💛❤️

የ2018 ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ከ29ኛ እስከ 38ኛ ሳምንት ውድድር መርሃ ግብር ይፋ ሆነ፥ የ2018 ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ከኢትዮጵያ ዋንጫ መልስ ሚያዝያ 21/2018 ዓ.ም ይጀም
+1
የ2018 ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ከ29ኛ እስከ 38ኛ ሳምንት ውድድር መርሃ ግብር ይፋ ሆነ፥ የ2018 ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ከኢትዮጵያ ዋንጫ መልስ ሚያዝያ 21/2018 ዓ.ም ይጀምራል። በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩንቨርሲቲ ስታዲየም እና በአዲስ አበባ ስታዲየም የሚደረጉትን ከ29ኛ እስከ 38ኛ ሳምንት ያሉትን የአስር ሳምንት(ቀሪ የሊጉ ሙሉ ፕሮግራም) መርሃ ግብር ይፋ ሆኗል። 33ኛ እና 34ኛ ሳምንት የሊጉ መርሃ ግብር የኢትዮጵያ ዋንጫን ታሳቢ በማድረግ ሊሻሻል ይችላል። እንዲሁም የ37ኛ እና 38ኛ ሳምንት መርሃ ግብርም የክለቦችን ውጤት መሰረት በማድረግ ሊሻሻል ይችላል።

ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ኢትዮጵያ ቡና የሚያደርጉት የ20ኛ ሳምንት ተስተካካይ ጨዋታ ሚያዝያ 18 ፤ 9፡00 በአዲስ አበባ ስታዲየም እንደሚካሄድ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ አክስዮን ማሕበር አሳውቋል።
ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ኢትዮጵያ ቡና የሚያደርጉት የ20ኛ ሳምንት ተስተካካይ ጨዋታ ሚያዝያ 18 ፤ 9፡00 በአዲስ አበባ ስታዲየም እንደሚካሄድ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ አክስዮን ማሕበር አሳውቋል።

መልዕክት ለመላው ቅዱስ ጊዮርጊሳውያን ===========//========= ክለባችን ቅዱስ ጊዮርጊስ ያለበትን ወቅታዊ ችግር በመረዳት በተለይም በውጭ ሀገራት የሚገኙ ጊዮርጊሳውያን ክለባችንን በምን እ
መልዕክት ለመላው ቅዱስ ጊዮርጊሳውያን ===========//========= ክለባችን ቅዱስ ጊዮርጊስ ያለበትን ወቅታዊ ችግር በመረዳት በተለይም በውጭ ሀገራት የሚገኙ ጊዮርጊሳውያን ክለባችንን በምን እናግዝ የሚል ጥያቄ እያቀረቡልን ይገኛሉ፡፡ በመሆኑም ክለባችንም ይህንን በምን እናግዝ ጥያቄ ተቀብሎ ለማስተናገድ በዝግጅት ላይ የሚገኝ ሲሆን በማህበራዊ ሚዲያው ላይ ተፅዕኖ ፈጣሪ የሆናችሁ ደጋፊዎቻችን እና የስፖርት ቤተሰቦች ለዚህ የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም እራሳችሁን ለማዘጋጀት ትብብራችሁን ስንጠይቅ በውጭ የምትገኙ ጊዮርጊሳውያንንም ለእገዛ እንዲትዘጋጁ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡ በዚህ አጋጣሚ ይህን ስራ ልትተባበሩን የምትሹ ተፅዕኖ ፈጣሪ የሆናችሁ የማህበራዊ ሚዲያ ስዎች የክለባችንን የህዝብ ግንኙነት ክፍል በነገው ዕለት እንድታናግሩ በታላቅ አክብሮት እንጠይቃለን።

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በስሩ ያሉ የጠቅላላ ጉባዔ አባላት በመካከላቸው የሚፈጠሩ ውስጣዊ እና ሀገራዊ ያለመግባባቶችን የመዳኘት በመተዳደርያ ደንብ ስልጣን የተሰጠው ተቋም እንደመሆኑ በቅዱስ ጊ
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በስሩ ያሉ የጠቅላላ ጉባዔ አባላት በመካከላቸው የሚፈጠሩ ውስጣዊ እና ሀገራዊ ያለመግባባቶችን የመዳኘት በመተዳደርያ ደንብ ስልጣን የተሰጠው ተቋም እንደመሆኑ በቅዱስ ጊዮርጊስ ክለብ ውስጥ ባለው አለመግባባት ምክንያት ወደ መደበኛ ፍርድ ቤት የሄደውን ጉዳይ በአስቸኳይ እንዲቆም እና ከሁለቱም ወገኖች ማለትም ከከሳሽም ከተከሳሽም ወገን የተውጣጣ አካላትን ያካተተ የሽግግር ኮሚቴ መጋቢት 4/2018ዓ.ም መዋቀሩ ይታወሳል፡፡ ይህ ኮሚቴ በቀጣይ ጊዜያት የሚያከናውናቸው ተግባር እና ኃላፊነቶች የተሰጠው ሲሆን ከዚህ በተቃራኒ ስፖርታዊ አለመግባባትን ወደ መደበኛ ፍርድ ቤት በመውሰድ ሥራውን ለማስተጓጎል የሚሞክር አካል ካለ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የቅዱስ ጊዮርጊስ ስፖርት ማኅበርን የሚያግድ መሆኑን በጥብቅ ያሳስባል። ጉዳዩንም ለዓለም አቀፍ እግር ኳስ ማህበር (FIFA) ማሳወቁን ይገልፃል፡፡

የ2018 ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ከ25ኛ እስከ 28ኛ ሳምንት ውድድር መርሃ ግብር ይፋ ሆነ፥ የ2018 ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 25ኛ ሳምንት ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ጨዋታ መልስ መጋ
የ2018 ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ  ከ25ኛ እስከ 28ኛ ሳምንት ውድድር መርሃ ግብር ይፋ ሆነ፥ የ2018 ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 25ኛ ሳምንት ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ጨዋታ መልስ መጋቢት 25/2018 ዓ.ም ይጀምራል። በሀዋሳ ዩንቨርሲቲ ስታዲየም እና በአዲስ አበባ ስታዲየም የሚደረገው ከ25ኛ እስከ 28ኛ ሳምንት ያለው የአራት ሳምንት መርሃ ግብር ይፋ ሆኗል።

የ2018 ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሁለተኛው ዙር ከ20ኛ እስከ 24ኛ ሳምንት ውድድር መርሃ ግብር ! የ2018 ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሁለተኛው ዙር የካቲት 14/2018 ዓ.ም ይጀምራል
የ2018 ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ  ሁለተኛው ዙር ከ20ኛ እስከ 24ኛ ሳምንት ውድድር መርሃ ግብር ! የ2018 ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሁለተኛው ዙር የካቲት 14/2018 ዓ.ም ይጀምራል። በሀዋሳ ዩንቨርሲቲ ስታዲየም እና በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩንቨርሲቲ ስታዲየም የሚደረገውን ከ20ኛ እስከ 24ኛ ሳምንት ያለውን የመጀመሪያ አምስት ሳምንት መርሃ ግብር ይፋ ሆኗል።

ዛሬ የጨዋታ ቀን ነው✌️ ትኬቱን አሁን ይቁረጡ ✅ http://ticket.ethiosport.pro
ዛሬ የጨዋታ ቀን ነው✌️ ትኬቱን አሁን ይቁረጡ ✅ http://ticket.ethiosport.pro

🏟️የስታዲየም የመግቢያ ትኬቶን ከታች ባለው ሊንክ ይቁረጡ http://ticket.ethiosport.pro
🏟️የስታዲየም የመግቢያ ትኬቶን ከታች ባለው ሊንክ ይቁረጡ http://ticket.ethiosport.pro

እርስ በርስ መወቃቀስ ፤ ታፔላ መለጣጠፍ #ጊዮርጊስን የጠቀመው አንድም ነገር የለም። የሆነ ችግር በተፈጠረ ቁጥር ከመጨቃጨቅ ይልቅ መፍትሔ መፈለግ ለምን ከበደን? የደጋፊውን መብት እና ፍላጎት ምናስ
እርስ በርስ መወቃቀስ ፤ ታፔላ መለጣጠፍ #ጊዮርጊስን የጠቀመው አንድም ነገር የለም። የሆነ ችግር በተፈጠረ ቁጥር ከመጨቃጨቅ ይልቅ መፍትሔ መፈለግ ለምን ከበደን? የደጋፊውን መብት እና ፍላጎት ምናስከብርበትን መንገድ ለምን አንፈልግም? መጀመሪያ እስኪ እንደ ደጋፊ #አንድ እንሁን። እንቀራረብ #እንወያይ አቅጣጫ እናስቀምጥ የክለባችንን #ከፍታ እናስቀድም እኛ ዝቅ ማለት ካለብንም ዝቅ ብለን #ጊዮርጊስ ከፍ ይበል🙏🙏🙏። የጀማ፣የእድሮች እና የተለያዩ ጊዮርጊሳዊ ማህበራት ስብሰባ አድርጉ መፍትሄ ምትሉትን አስቀምጡ። ከዛ አቅራቢያ ካሉ ማህበራት እድሮች ጋር የጋራ ምክክር እናድርግ የጊዮርጊስ ባለቤት #ደጋፊው ነው ካለበት ችግር የሚያወጣውም #ደጋፊው ነው። በተቻለን መጠን እኛ ዝቅ ብለን ጊዮርጊስ ወደ #ከፍታው እንመልሰው። መሀላችን ያለውን ኩርፊያ ቂም እና ክፍተት እናስወግድ። #አንድ_ክለብ_አንድ_ቤተሰብ እንሁን ያኔ ሁሉም ነገር ይቀለናል እናሸንፋለን ክለባችንን ከፍ እናረጋለን✌️ ብቻ አንድ እንሁን

ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 2018 ከ10ኛ እስከ 19ኛ ሳምንት ውድድር መርሃ ግብር ማሻሻያ! የ2018 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ከ10ኛ እስከ 19ኛ ሳምንት ውድድር በአዲስ አበባ፣ አዳማ እና ሀ
+1
ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 2018 ከ10ኛ እስከ 19ኛ ሳምንት ውድድር መርሃ ግብር ማሻሻያ! የ2018 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ከ10ኛ እስከ 19ኛ ሳምንት ውድድር በአዲስ አበባ፣ አዳማ እና ሀዋሳ ከተማ የሚካሄድ መሆኑ ቀደም ብሎ ተገልጿል። የተወሰነ የሰዓት እና የቀን ለውጥ የተደረገበት መርሃ ግብርን አያይዘናል። የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አክሲዮን ማህበር