en
Feedback
Mission Talk with Aman!

Mission Talk with Aman!

Open in Telegram

Mission Exist because worship doesn't . Mission is the means while worship is ultimate Goal of God. Pastor John piper.

Show more
509
Subscribers
No data24 hours
+17 days
-230 days
Posts Archive
ተልእኳችን ማለዳ ሕዳር 3 - 2017 የርህራሄው አይን የመጸሐፍ ቅዱስ ምንባብ፡ ማቴዎስ ወንጌል 9፡35 – 38 ብዙ ሕዝብም ባየ ጊዜ፥ እረኛ እንደ ሌላቸው በጎች ተጨንቀው ተጥለውም ነበርና አዘነላቸው። ማቴዎስ 9፡36 ቴሌቪዥን፣ ሬዲዮ ወይም ሚዲያ ከመኖራቸው በፊት ሰዎች መረጃ ሚያስተላልፉት አንዱ ለአንዱ በሚያስተላልፈው መልእክት ወይም መረጃ ነው፡፡ ኢየሱስ በነበረበት ዘመንም እንደዛው ነበር፡፡ ኢየሱስ በምድር በተመላለሰበት ዘመን ይኖርበት የነበረውን ማህበረሰብ ስብራት እና ቁስል ይመለከት ነበር ፤ እነርሱን ከመራቅ ይልቅ ግን በርህራሄ ይቀርባቸው ዘንድ መርጧል፡፡ ውስጣቸው ያለውን ፍርሃት እና አይናቸው ውስጥ የሚታየውን ህመም በርህራሄ ተመለከታቸው በዚያም ልቡ ተሰበረ፡፡ ሁሉም ውጤታማ ወንጌል ስርጭት የሚጀመረው ከዚህ ነው፡፡ የሰዎችን ስብራት፣ ጉዳት እና ልባቸውን ከማየት ይጀመራል፡፡ ኢየሱስ እረኛ የሌላቸውን በጎች ተመለከተም አዘነላቸውም፡፡ ብዙ ህዝቦች ተሰብስበው አየ እረኛ እንደሌላቸውም በጎች ተቅበዝብዘው ተመለከታቸው አዘነላቸው፡፡ ማህበረሰባቸሁን፣ ጎረቤቶቻችሁን ስታዩ ምን ትመለከታችሁ? በመንፈሳዊ እይታ ከሐጢያት እስራት አሻግረው ማየት ያልቻሉ ሰዎች ታያላችሁ? በህይወት የዛሉ እና የደክሙ ሰዎች ታያላችሁ? የምታዩ ከሆነ አስታውሱ እነዚህ ሰዎች እርዳታችሁን የሚፈልጉ፣ ርህራሄያችሁን የሚናፍቁ ናቸው፡፡ ጸልዩላቸው፣ ወዳጅ ሁኗቸው፣ በፍቅር ቅረቧቸው በኢየሱስ ፍቅር የህይወታቸውን ሸክም ተካፈሏቸው፡፡ አምላካችን ሆይ የጠፉትን የምንፈልግበት፣ በህይወት ለደከሙ ተስፋን ምንሰጥበት እና ፍቅርን የምንገልጥበት አቅምን አብዛልን፡፡ በዙሪያችን በብዙ ትግል እና መከራ ውስጥ የሚያልፉትን ማየት እንድንችል እርዳን፣ ኢየሱስ በህይወታቸው ላይ ይነግስ እና ጌታ ይሆን ዘንድ መፍትሄ የሆነውን ወንጌል እንድናበስራቸው አግዘን፡፡ አሜን! በዳን ጆግስማ የተጻፈ ከ https://todaydevotional.com/ ድህገ ገጽ ተወስዶ የተተረጎመ

ለኤርትራ ምድር እንጸልይ! የሕዝብ ብዛት - 3,815,000 የሕዝብ ክፍሎች ብዛት : 17 ዋነኛ ቋንቋ - ትግሪኛ እና አረብኛ ብዙ ተከታይ ያለው እምነት - ክርስትና (50.5%) ክርስትና - 50.5
ለኤርትራ ምድር እንጸልይ! የሕዝብ ብዛት -  3,815,000 የሕዝብ ክፍሎች ብዛት : 17 ዋነኛ ቋንቋ - ትግሪኛ እና አረብኛ ብዙ ተከታይ ያለው እምነት - ክርስትና (50.5%) ክርስትና - 50.5% ወንጌላዊያን አማኞች- 2.59% የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉም -  በዋነኛ ቋንቋዎች ተተርጉሟል ወንጌል ተኮር ቅጂዎች - ይገኛሉ  የአሁኗ ኤርትራን እና ሰሜናዊ ኢትዮጵያን የሚሸፍነው የአክሱም መንግሥት የተመሰረተው በመጀመሪያው ወይም በሁለተኛው ክፍለ ዘመን ዓ.ም ነው። በአራተኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ አካባቢ ክርስትናን ተቀበሉ። ባህላቸው ምን ይመስላል? የኤርትራ ባህል የኤርትራ ተወላጆች የሆኑ የተለያዩ ህዝቦች የጋራ ባህላዊ ቅርስ እና በረጅም ታሪካዊ መወራረሶች የበለፀጉ ባህላዊ ቅርሶች ናቸው። ሀገሪቱ በዋናዎቹ ዘጠኝ ብሄረሰቦች ውስጥ የሚካተት የዳበረ የአፍ እና የስነ-ፅሁፍ ባህል አላት፤ በውስጡ በርካታ ግጥሞች እና ምሳሌዎች፣ ዘፈኖች እና ዝማሬዎች፣ ተረቶች፣ ታሪኮች እና አፈ ታሪኮች ያካትታል። በተጨማሪም በቲያትር እና በሥዕል የበለጸገ ታሪክ አለው፣ ብዙ ጊዜ በቀለማት ያሸበረቀ እና የኤርትራ ሕዝብ ታሪክ ነጸብራቅ ነው። የጸሎት ርዕሶች 🙏🏾 👉🏾የኤርትራ ሕዝቦችና ልጆቻቸው በሙሉ ለእውነተኛው አምላክ እግዚአብሔር በ ክርስቶስ ኢየሱስ በኩል እንዲዋጁ  እንጸልይ ። 👉🏾የኤርትራ ሕዝቦች ወንጌልን ለመስማት ክፍት እንዲሆን ጸልዩ።እግዚአብሔር ልባቸውን እንዲያዘጋጅ እና የተልዕኮ ሰራተኞች ወደ መኸሩ እንዲልክ እንጸልይ። 👉🏾መጽሐፍ ቅዱስ እና ቅዱሳት መጽሐፍት በቋንቋቸው የሚገኝ ህዝቦች አሉ ቢሆንም ግን የእግዚአብሔር ቃል በእነሱ ሊነበብ የሚገባ እንደሆነ አቆጥሩም ከዚህ አስተሳሰብ እስራት እንዲላቀቁ እንጸልይ!

እንጸልይ 2017 - 2 “ለምነኝ፥ አሕዛብን ለርስትህ የምድርንም ዳርቻ ለግዛትህ እሰጥሃለሁ።” — መዝሙር 2፥8 እንጸልይ 2017 - 2 ህዳር 7 - 2017 ዓ.ም ከጠዋት 2፡30 - 10፡00 ሰዓት
እንጸልይ 2017 - 2 “ለምነኝ፥ አሕዛብን ለርስትህ የምድርንም ዳርቻ ለግዛትህ እሰጥሃለሁ።”   — መዝሙር 2፥8 እንጸልይ 2017 - 2 ህዳር 7 - 2017 ዓ.ም  ከጠዋት 2፡30 - 10፡00 ሰዓት በሚሽን ሞቢላይዜሽን ኢትዯጵያ አገልግሎት በወንጌል ላልተደረሱ የሕዝብ ክፍሎች  በአዲስ አበባ  ተዘጋጅቷል በዚህ ፕሮግራም ላይ በመገኘት አብራችሁን እንድትጸልዩ ጥሪ እናቀርባለን። በዚህ ፕሮግራም ላይ ለመሳተፍ ከታች ባሉት የቴሌግራም አድራሻዎች በመጻፍ ወይም በስልክ ቁጥሮች በመደወል  ያናግሩን፤ ኑ አብረን የእግዚአብሔርን ፊት ስለሕዝቦች በጋራ እንፈልግ! @FEVIREVIVALIST +251 93 518 3566 +251 93 789 4139 +251 97 820 8912

አዳማ በጋፕስ አለም አቀፍ አገልግሎት ከወንድማማች ቤተክርስቲያን በመተባበር በተዘጋጀ የወንጌል አገልጋዮች ስልጠና ላይ የእግዚአብሔር ተልእኮ ትምህርት እና ስልጠና ተስጥቷል። በወንጌሉ ስራ አብረን እ
+8
አዳማ በጋፕስ አለም አቀፍ አገልግሎት ከወንድማማች ቤተክርስቲያን በመተባበር በተዘጋጀ የወንጌል አገልጋዮች ስልጠና ላይ  የእግዚአብሔር ተልእኮ ትምህርት እና ስልጠና ተስጥቷል። በወንጌሉ ስራ አብረን እንጠመድ!

የጸሎት ፕሮግራማችን ተጀምሯል ከታች ባለው ሊንክ ይቀላቀሉን። https://t.me/MobilizationEthiopia?videochat=8b1f17c61c7bd0620d
የጸሎት ፕሮግራማችን ተጀምሯል ከታች ባለው ሊንክ ይቀላቀሉን። https://t.me/MobilizationEthiopia?videochat=8b1f17c61c7bd0620d

ለኤርትራ የመን አረብ የሕዝብ ክፍል እንጸልይ! በዚያን ጊዜ ደቀ መዛሙርቱን፡— መከሩስ ብዙ ነው፥ ሠራተኞች ግን ጥቂቶች ናቸው፤ እንግዲህ የመከሩን ጌታ ወደ መከሩ ሠራተኞች እንዲልክ ለምኑት፡ አላቸው
ለኤርትራ የመን አረብ የሕዝብ ክፍል እንጸልይ! በዚያን ጊዜ ደቀ መዛሙርቱን፡— መከሩስ ብዙ ነው፥ ሠራተኞች ግን ጥቂቶች ናቸው፤ እንግዲህ የመከሩን ጌታ ወደ መከሩ ሠራተኞች እንዲልክ ለምኑት፡ አላቸው። ማቴዎስ 9፡ 37 - 38 ሰላም  የሚሽን ሞቢላይዜሽን ኢትዮጵያ ቤተሰቦች! ዛሬ አርብ ምሽት ከ3:30 ጀምሮ በቴልግራም ላይቭ ለኤርትራ የመን አረብ ሕዝብ ክፍል በህብረት የምንፀልይበት ጊዜ ይኖረናል ከታች ባለዉ የቴሌግራም ቻናል ሊንክ በመግባት አብራችሁን እንድትጸልዩ እንጋብዛችኋለን። https://t.me/MobilizationEthiopia

ተልእኳችን ማለዳ ጥቅምት 29 - 2016 ለእግዚአብሔር ክብር በፈተናዎች መጽናት
አሁን በብዙ ዐይነት ፈተና ውስጥ ሆናችሁ ለጥቂት ጊዜ መከራን ብትቀበሉም እንኳ በዚህ እጅግ ደስ ይላችኋል። እነዚህ ነገሮች በእናንተ ላይ የደረሱት፣ በእሳት ተፈትኖ ቢጠራም፣ ጠፊ ከሆነው ወርቅ ይልቅ እጅግ የከበረው እምነታችሁ፣ እውነተኛ መሆኑ እንዲረጋገጥና ኢየሱስ ክርስቶስ በሚገለጥበት ጊዜ ምስጋናን፣ ክብርንና ውዳሴን እንዲያስገኝላችሁ ነው። 1ኛ ጴጥሮስ 1:6-7
የተፈተነ ክርስቲያን ካልተፈተነ ይልቅ ለእግዚአብሔር የበለጠ ክብርን ያመጣል። በእስር ቤት ውስጥ ያለ ምእመን በምቾት ካለው አማኝ የበለጠ ክብርን ለጌታው እንደሚያንጸባርቅ በግሌ አስባለሁ፣ በሚነድደው እቶን ውስጥ ያለው የእግዚአብሔር ልጅ፣ ጸጉሩ ገና ያልተቃጠለ፣ የእሳቱ ጠረን ያረፈበት። በራሱ ላይ አክሊል ደፍቶ በአብ ዙፋን ፊት ለዘላለም የመለኮትን ክብር ያሳያል። ለሠራተኛ የሥራው ጽናት ያህል ክብርን የሚያንፀባርቅ ነገር የለም። እግዚአብሔርም እንዲሁ ነው። ቅዱሳኑ ንጹሕ አቋማቸውን ሲጠብቁ እርሱን ያከብራል። ጴጥሮስ ክርስቶስን በምድር ላይ ከቆመበት ይልቅ በውሃ ላይ ሲራመድ አክብሯል። በጠንካራው የባሕር ዳርቻ በመሄዱ ለእግዚአብሔር የተሰጠው ክብር አልነበረም ነገር ግን በውኃ ላይ ሲራመድ የሚንጸባረቅበት ክብር ነበረ። በዚህ በመቆየት በክርስቶስ አክሊል ላይ ተጨማሪ ጌጣጌጦችን መጨመር ከቻልን ከዓለም መውጣት ለምን እንፈልጋለን? “እርሱን የምናከብረው የትም ቦታ መሆን የተባረከ ነው” ማለት አለብን።
የሰማይ አባት፣ ያጋጠመኝን እያንዳንዱን ፈተና እና የተቋቋምኳቸውን ጉዳቶች ታውቃለህ። ልቤን ታውቃለህ ጩኸቴንም ትሰማለህ። ስቃዮቼን ሁሉ ውሰድና እና ለስምህ ክብር ለማምጣት ተጠቀምበት። ኣሜን!
ከቻርልስ ስፐርጅን የማለዳ ቃለ-እግዚአብሔር መልእክት የተወሰደ

ቀን 4 እንጸልይ 🙏🏽ለየመን አረብ ሕዝቦች በኤርትራ🙏🏽 የየመን አረብ ሕዝቦች ከእስልምናን ከ600ዎቹ ጀምሮ መከተል የጀመሩና የጠበቀ ግንኙነት ያላቸው ናቸው። ዛሬ የየመን አረቦች በየትኛውም የ
ቀን 4 እንጸልይ 🙏🏽ለየመን አረብ ሕዝቦች በኤርትራ🙏🏽 የየመን አረብ ሕዝቦች ከእስልምናን  ከ600ዎቹ ጀምሮ መከተል የጀመሩና  የጠበቀ ግንኙነት ያላቸው ናቸው። ዛሬ የየመን አረቦች በየትኛውም የዓለም ክፋ ቢሮሩም አብዛዎቹ ሙስሊሞች ናቸው። ከየመን ሕዝቦች ውስጥ ሁለት ሶስተኛው የሱኒ እስልምናን የሚከተሉ ሲሆኑ አንድ ሶስተኛው የሚሆኑት የሺዓ ሙስሊሞች ናቸው። በጎሳ ታማኝነት ቢለያዩም የየመን አረቦች ሁሉም የሚስማሙበት አንድ ነገር ለእስልምና ሃይማኖታዊ ሥርዓት መሰጠት ነው። የትም ቢኖሩ አንዳቸውም ቢሆኑ በኢየሱስ ክርስቶስ ላይ እምነታቸውን ያደረጉ የሉም። የጸሎት ርዕሶች🤲🏽 👉🏾የመጀመሪያውን የየመን አማኞች ቤተ-ክርስትያን ህብረትን በኤርትሪያ ምድር እግዚአብሔር እንዲያሳየን እንጸልይ! 👉🏾ለየመኒዎች ወደ እምነት መምጣት ዋና ነገር ከሆኑት ውስጥ የእግዚአብሔር ቃል በቋንቋችው የመተርጎም ሾል እንዲጀመር፣ የክርስቲያን ቲቪ እና የሬዲዮ ስርጭቶችን እንዲከታተሉ ጸልዩ። 👉🏾በዲያስፖራ የሚኖሩ የየመን አረቦች በአገራቸው ሰላም ያስፈልጋቸዋል። ሁሉም በጦርነቱ ምክንያት ሕይወታቸው አደጋ ላይ የወደቀ የቤተሰብ አባላት አሏቸው። ለታላቁ ጌታ መገዛት እንዳለባቸው ዕውቅና እስካልሰጡ ድረስ ውጊያው ማብቂያ የለውም። ኢየሱስ ክርስቶስ ጣልቃ እዲገባ እንማልድ! 👉🏾የየመን ሕዝቦች ለኢየሱስ የተመረጡ ደቀመዝሙር የሚያፈሩ ደቀመዛሙርት እንዲሆኑ እንጸልይ !

ተልእኳችን ማለዳ ጥቅምት 28 - 2016 ሰዎችን ለክርስቶስ የመማረክ ጥሪ የጻድቅ ፍሬ የሕይወት ዛፍ ናት፥ ነፍሳትን የሚማርክም ጠቢብ ነው። ምሳሌ 11:30 NKJV ለምንድነው ቅዱሳን ወደ እግዚአብሔ
ተልእኳችን ማለዳ ጥቅምት 28 - 2016 ሰዎችን ለክርስቶስ የመማረክ ጥሪ
የጻድቅ ፍሬ የሕይወት ዛፍ ናት፥ ነፍሳትን የሚማርክም ጠቢብ ነው። ምሳሌ 11:30 NKJV
ለምንድነው ቅዱሳን ወደ እግዚአብሔር በተመለሱ ጊዜ የማይሞቱት? ምክንያቱ እግዚአብሔር ለወንድሞቻቸው የመዳን መንገድ እንዲሆኑ ስለሚፈልግ ነው። በአንተ የምትድን ነፍስ ብትኖር በእርግጥ ከአለም መውጣት አትፈልግም ነበር። ለእኔ የተሰጡኝን ነፍሳት ሁሉ ከመመለሴ በፊት ወደ ክብር መሄድ ከቻልኩ ደስተኛ መሆን አልነበረብኝም። ሥራችን እስካልተፈጸመ ድረስ መንግሥተ ሰማያት መግባትን አንፈልግም፤ ምክንያቱም በእኛ አቅም ለመዳን አንዲት ነፍስ ብትቀር ያሳዝነናል። ኃጢአተኛ ከኃጢአቱ የሚድን፥ ከመንገዱም ስህተት የሚመለስ አመጸኛ አለ፥ ምናልባትም ያ ኃጢአተኛ ከዘመዶችህ አንዱ ነው። ምናልባት በዚህ ዓለም የቆየንበት ምክንያቱ ገና ያልዳነ ሰው፥ ጠማማ ትውልድ ስላለ እና እግዚአብሔር እርሱን ወደ ክብር የምናመጣለት የተወደደ መሳሪያ ሊያደርግህ ስላዘጋጀን ነው። በዙሪያችሁ ላሉ ለምትወዳቸው የክርስቶስ ቤተሰብ ጋና ስላልሆኑ ስትሉ ቆዩ። ምን ያህል እንደምትወዷቸው አውቃለሁ፤ ለእርሱም ስትሉ በትጋት ጥሪውን ተቀበሉ።
አምላክ ሆይ፣ ሌሎችን ወደ አንተ በምመራበት መንገድ ሕይወቴን ለመኖር እመኛለሁ። ለአንተ ያለኝ ፍቅር እና መሰጠት አንተን እንዲያውቁህ እና የዘላለም ህይወትህን የከበረ ስጦታ እንዲቀበሉ እርዳቸው። ኣሜን!
ከቻርልስ ስፐርጅን የማለዳ ቃለ-እግዚአብሔር መልእክት የተወሰደ

ቀን 3 እንጸልይ 🙏🏽ለየመን አረብ ሕዝቦች በኤርትራ🙏🏽 በኤርትራ ኑሮአቸውን ያደረጉ የመኖች ከኤርትራውያን ሴቶች ጋር ለብዙ አስርት አመታት በጋብቻ ተሳስረው ኑሮአቸውን መስርተዋል። በእነዚህ ግ
ቀን 3 እንጸልይ 🙏🏽ለየመን አረብ ሕዝቦች በኤርትራ🙏🏽 በኤርትራ ኑሮአቸውን ያደረጉ የመኖች ከኤርትራውያን ሴቶች ጋር ለብዙ አስርት አመታት በጋብቻ ተሳስረው ኑሮአቸውን መስርተዋል። በእነዚህ ግዜያት ሁሉ፣ አዲስ ሕይወት ቢጀምሩም ያለፉበት የጦርነት ትውስታዎች እና ገጠመኞቻቸውን ያሳደሯቸው ጠባሳዎን ግን መቋቋም አለባቸው። የእስልምና አስተምህሮዎች ቢከተሉም፣ እውነታው ግን በየመኖች መካከል አራት እኩል ያልሆኑ መደቦች አሉ። የየመን አረብ ከፍተኛ ደረጃ ያለው ቡድን ክብራቸውን ያገኙት ከቤተሰባቸው ስም፣ ታሪክ የጎሳ አለቆች የመጡ ናቸው። በትምህርታቸው ክብራቸውን ያገኘ ሌላ ቡድን አለ። የጸሎት ርዕሶች🤲🏽 👉🏾 በኤርትራ የሚገኙ የመኖች  ከተሸከሙት የሃጥያት ሸክም  በኢየሱስ ስም ነጻ እንዲወጡ እንጸልይ! 👉🏾በኤርትራ የሚገኙ  የመኒዎችን የሚወድና በመንፈስ የተሞላ የሰራተኛ ሃይል እንዲያላክላቸው እንጸልይ። 👉🏾እግዚአብሔር ልጁ ኢየሱስ ክርስቶስ እንደሆነ ያምኑ ዘንድ ልባቸውን እንዲያዘጋጅ፣ በህልም፣ በሚያደንቅ ተአምራት ሃይሉን እንዲገልጥላቸው እንጸልይ!

እንጸልይ 2017 - 2 “ለምነኝ፥ አሕዛብን ለርስትህ የምድርንም ዳርቻ ለግዛትህ እሰጥሃለሁ።” — መዝሙር 2፥8 እንጸልይ 2017 - 2 ህዳር 11- 2017 ዓ.ም ከጠዋት 2፡30 - 10፡00 ሰዓት
እንጸልይ 2017 - 2 “ለምነኝ፥ አሕዛብን ለርስትህ የምድርንም ዳርቻ ለግዛትህ እሰጥሃለሁ።”   — መዝሙር 2፥8 እንጸልይ 2017 - 2 ህዳር 11- 2017 ዓ.ም ከጠዋት 2፡30 - 10፡00 ሰዓት በሚሽን ሞቢላይዜሽን ኢትዯጵያ አገልግሎት በወንጌል ላልተደረሱ የሕዝብ ክፍሎች  በአዲስ አበባ  ተዘጋጅቷል በዚህ ፕሮግራም ላይ በመገኘት አብራችሁን እንድትጸልዩ ጥሪ እናቀርባለን። በዚህ ፕሮግራም ላይ ለመሳተፍ ከታች ባሉት የቴሌግራም አድራሻዎች በመጻፍ ወይም በስልክ ቁጥሮች በመደወል  ያናግሩን፤ ኑ አብረን የእግዚአብሔርን ፊት ስለሕዝቦች በጋራ እንፈልግ! @FEVIREVIVALIST +251 93 518 3566 +251 93 789 4139 +251 97 820 8912

ተልእኳችን ማለዳ ጥቅምት 27 - 2016 መቼም አልተውም
ስምህን የሚያውቁ በአንተ ይታመኑብሃል፤ አቤቱ፥ የሚሹህን አትተዋቸውምና። መዝሙረ ዳዊት 9:10
ከክርስቶስ ጋር ያለን ኅብረት በጣም የተከበረ ነገር ነው፤ ስለዚህም እንድንደሰት መከራ መቀበል አስፈላጊ ነው። አንዳንድ ጊዜ በሕይወት በሚኖሩት እና በሚቀሩት ሰዎች ቁጥር ውስጥ እሆን ዘንድ ምኞትን ስገልጽ ሰምታችኋል እናም ከሞትም አምልጫለሁ; ነገር ግን አንድ የምወደው ወዳጄ ከክርስቶስ ጋር በመከራው ኅብረት ከሚኖረው መሞትን ይሻለኛል ይላል፣ እናም ሀሳቡ በደረቴ ውስጥ አስተጋባ። ከኢየሱስ ጋር መሞት ሞትን ፍጹም ሀብት ያደርገዋል። ከእርሱ ጋር በመቃብር ውስጥ ተከታይ መሆን ሞትን አስደሳች ያደርገዋል። ያለፍንበት መከራና ስለ ስሙ የተቀበልነውን ቁስል የሚያረጋግጥ ጠባሳ ባይኖረን፥ በክብሩ ከእርሱ ጋር ኅብረት ቢኖረንም፥ እኔና እናንተ እንደ ፈሪዎች ልንወሰድ እንችላለን። እንዲሁ ደግሞ በዚህ መሆን ለእኛ መልካም እንደሆነ ታያላችሁ; እዚህ ለጥቂት ጊዜ ባንቆይ ከአዳኝ ጋር ያለውን ህብረት ማወቅ ባልነበረብንም ነበር። በመከራ ማዕበል ውስጥ ባልሆን ኖሮ የአዳኙን ፍቅር ግማሽ ያህል ማወቅ አልነበረብንም። ማንም ሳይወደን የአዳኝን ፍቅር መማር እንዴት ደስ ይላል! ጓደኛሞች ሲሸሹ አዳኝ እንደማይተወን ነገር ግን አሁንም እንደሚጠብቀን እና እንደሚይዘን እና ከእኛ ጋር እንደሚጣበቅ እና እንድንሄድ እንደማይፈቅድልን ማየት እንዴት ያለ የተባረከ ነገር ነው! ኦህ፣ የተወደዳችሁ ወንድም እና እህት፣ እዚህ ምድር ላይ መቅረትህ ለዘላለማዊ ጥቅም እንደሆነ እመኑ።
አቤቱ አመሰግንሃለሁ፣ ስለ ማይገደብ፣ ስለ ዘላለማዊ ፍቅርህ። ሁሌም ከእኔ ጋር ነህ። በአንተ እታመናለሁ እናም እመካለሁ። በህይወቴ ውስጥ ምንም አይነት ነገር ቢገጥመኝ፣ ብቻዬን መጋፈጥ እንደሌለብኝ እንድረዳ ስለረዳኸኝ አመሰግናለሁ። ኣሜን!
ከቻርልስ ስፐርጅን የማለዳ ቃለ-እግዚአብሔር መልእክት የተወሰደ

ቀን 2 እንጸልይ 🙏🏽 ለየመን አረብ ሕዝብ በኤርትራ🙏🏽 ሰሜን እና ደቡብ ምስራቅ እካባቢዎች በ70 ዎቹ እና 80 ዎቹ አመታት የተለያዩ ብሔሮች ነበሩ; አንዱ በኮሚኒስቶች እና ሌላው በምዕራቡ ዓ
ቀን 2 እንጸልይ 🙏🏽 ለየመን አረብ ሕዝብ በኤርትራ🙏🏽 ሰሜን እና ደቡብ ምስራቅ እካባቢዎች በ70 ዎቹ እና 80 ዎቹ አመታት የተለያዩ ብሔሮች ነበሩ; አንዱ በኮሚኒስቶች እና ሌላው በምዕራቡ ዓለም የሚደገፉ ነበሩ። ለሁለት ዓመታት ያክል መዋሃድ ችለዋል፣ አሁን ግን እንደገና በግጭት ላይ ናቸው። ኢራን የሺዓ እስልምናን ባንዲራ አድርጋ አንዱን ወገን ስትደግፍ ሌላኛው ደግሞ የሱኒ ሙስሊም መሪ የሆኑ የሀገር መዎችን ተከትለው ይደግፋሉ። የመን አረቦች  ጦርነቱ ቢቆም ደስ ይላቸዋል ነገር ግን ሁኔታው ​​ከቁጥጥር ውጪ ሆኗል። ጦርነቱ ህዝቡን ከየመን ያፈናቀለ ሲሆን በተለይም በአቅራቢያው ባሉ እንደ ኦማን፣ ሳዑዲ አረቢያ፣ ጅቡቲ፣ ኤርትራ፣ ኢትዮጵያ እና ግብፅ ሃገራት በርካታ የየመን ስደተኞች ይገኛሉ። እንደ ዩናይትድ ኪንግደም እና አሜሪካ ባሉ ምዕራባውያን ሀገራት ብዙ የተሰደዱ የየመን ዜጎች ይገኛሉ። የጸሎት ርዕሶች🤲🏽 👉🏾 የየመን ህዝብ እንደ ህዝብ በሃገራቸው እንዳይቆዩ፣ እንዳያድጉ፣ ህይወታቸው እንዳይቀጥል ሰይጣን ሌት እና ቀን ይሰራል፣ እግዚአብሔር ከደረሰባቸው መአት  እንዲገላግላቸው እንጸልይ! 👉🏾እግዚአብሔር የትኛውንም ሁኔታ ለመልካም፣ ለልሹ ክብር መቀየር ይችላል እና የየመን በብዙ ሃገራት መበተን የመዳናቸው ምክንያት እንዲያደርገው እየለመንን እንጸልይ!  እግዚአብሔር በኤርትራ፣ ኢትዮጵያ እና ሌሎች የተሰደዱባቸው ሃገራት ላይ ያሉ የክርስቶስ ተከታዬች እንዲቀብሉዋቸው፣ ወንጌልን ወደቤቶቻቸው በመጋበዝ፣ ለነሱ መልካም በመሆን እና ስለእነሱ በመማለድ እንዲሰብኩላቸው እንጸልይ! 👉🏾እግዚአብሔር ቤተ-ክርስትያን ሾለ የመን ህዝብ እንድትጸልይ በመንፈሱ እንዲያነቃት እንጸልይ!

እንጸልይ 2017 - 2 “ለምነኝ፥ አሕዛብን ለርስትህ የምድርንም ዳርቻ ለግዛትህ እሰጥሃለሁ።” — መዝሙር 2፥8 እንጸልይ 2017 - 2 ህዳር 11- 2017 ዓ.ም ከጠዋት 2፡30 - 10፡00 ሰዓት
እንጸልይ 2017 - 2 “ለምነኝ፥ አሕዛብን ለርስትህ የምድርንም ዳርቻ ለግዛትህ እሰጥሃለሁ።”   — መዝሙር 2፥8 እንጸልይ 2017 - 2 ህዳር 11- 2017 ዓ.ም ከጠዋት 2፡30 - 10፡00 ሰዓት በሚሽን ሞቢላይዜሽን ኢትዯጵያ አገልግሎት በወንጌል ላልተደረሱ የሕዝብ ክፍሎች  በአዲስ አበባ  ተዘጋጅቷል በዚህ ፕሮግራም ላይ በመገኘት አብራችሁን እንድትጸልዩ ጥሪ እናቀርባለን። በዚህ ፕሮግራም ላይ ለመሳተፍ ከታች ባሉት የቴሌግራም አድራሻዎች በመጻፍ ወይም በስልክ ቁጥሮች በመደወል  ያናግሩን፤ ኑ አብረን የእግዚአብሔርን ፊት ስለሕዝቦች በጋራ እንፈልግ! @FEVIREVIVALIST +251 93 518 3566 +251 93 789 4139 +251 97 820 8912

ተልእኳችን ማለዳ ጥቅምት 26 - 2016 ክርስቶስ ለልጆቹ የጸለየው ጸሎት የምለምንህ ከክፉ እንድትጠብቃቸው እንጂ ፤ ከዓለም እንድታወጣቸው አይደለም። ዮሐንስ 17፡15 ይህ የክርስቶስ ጸሎት ለእያንዳ
ተልእኳችን ማለዳ ጥቅምት 26 - 2016 ክርስቶስ ለልጆቹ የጸለየው ጸሎት
የምለምንህ ከክፉ እንድትጠብቃቸው እንጂ ፤ ከዓለም እንድታወጣቸው አይደለም። ዮሐንስ 17፡15
ይህ የክርስቶስ ጸሎት ለእያንዳንዳቸው የማይሻር ፍላጎት ስላላቸው ለሁሉም እውነተኛ አማኞች እጅግ ውድ የሆነ ክፍል ነው። እያንዳንዳችን፣ ወዳጆች፣ የክርስቶስን ቃል ስንሰማ እርሱ ስለ እኛ እየጸለየ መሆኑን እናስታውስ። እርሱ በዚህ ምዕራፍ ውስጥ እና በፊተኛው ላለው አካል የሚማልደው ለታላቁ አካል ቢሆንም፣ እርሱ ግን በተለይ ለእያንዳንዱ አማኝ ይማልዳል። ደካሞች ብንሆን፣ ድሆች ብንሆንም፣ እምነታችን ትንሽ ቢሆንም፣ ጸጋችን ምንም ያህል ትንሽ ቢሆን፣ ስማችን አሁንም በልቡ ላይ ተጽፏል። በኢየሱስ ፍቅር ውስጥ ያለንን ድርሻ አናጣም። ምስኪን ኃጢአተኛ እንደሆንክ ቢሰማምህም እንኳ ስለ ጌታዬ ኃይል አትጠራጠር። የልብሱን ጫፍ ብቻ ንካ ትድናለህም። በሕዝቡ መካከል ተሸማቃ እንደመጣችው እንደዛች ምስኪን ሴት፣ ተነሳና ንካው/ ንኪው፣ እሱ በእርግጠኝነት፣ “ድነሻል/ ድነሃል” ይላችኋል። በዚህ ጩኸት ወደ እርሱ ሂዱ።
ጌታ ሆይ፣ በአንተን በፍቅር ተሸንፌአለሁ… ስለ እኔ ግድ እንደሚልክ ስሜም ለዘላለም በልብህ ላይ እንደተጻፈ ሳአስብ! ነፍሴ ሃሴት ታደርጋለች፤ አንተ እንደወደድከኝ ሌሎችን እንድወድ እርዳኝ። ኣሜን!
ከቻርልስ ስፐርጅን የማለዳ ቃለ-እግዚአብሔር መልእክት የተወሰደ

ቀን 1 እንጸልይ 🙏🏽 ለየመን አረቦች በኤርትራ🙏🏽 የሕዝብ ብዛት፡- 38,000 ዋነኛ ቋንቋ፡- አረብኛ፣ ታይዚ-አዴኒ ብዙ ተከታይ ያለው እምነት፡ - እስልምና 95.00% ክርስትና፡- 0.05%
ቀን 1 እንጸልይ 🙏🏽 ለየመን አረቦች በኤርትራ🙏🏽 የሕዝብ ብዛት፡- 38,000 ዋነኛ ቋንቋ፡- አረብኛ፣ ታይዚ-አዴኒ ብዙ ተከታይ ያለው እምነት፡ - እስልምና 95.00% ክርስትና፡- 0.05% ወንጌላዊያን አማኞች፡ 0.00% የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉም፡- አልተጀመረም የኢየሱስ ፊልም፡- የለም የወንጌል ተኮር ቅጂዎች፡- የሉም ከአረብ ባሕረ ገብ መሬት ከመጡ አረቦች መካከል የመጀመሪያዎቹ ናቸው። የመኖች ወደ ሰሜን መሰደድ የጀመሩት እስልምና እምነት ከመጀመሩ በፊት ከነበረው ዘመን ጀምሮ እንደሆነ የታሪክ መዛግብት ያሳያሉ። በሶሪያ፣ ሊባኖስ፣ ፍልስጤም እና ዮርዳኖስ ውስጥ ረጅም የቤተሰብ የዘር ሃረግ ያሏቸው፣ ብዙ የጋራ ስሞች ያላቸው (ለምሳሌ ሃዳድ፣ ሃዳዲን፣ ትርጉሙ ስሚዝ ወይም ብረት ሰራተኛ) ያላቸው የአረብ ቤተሰቦች ዘራቸውን የያዙት ከየመን ቀደምት ማህበረሰብ ስደት በሓላ እንሆነ ይታመናል። ለምሳሌ ሀዳዲን የሚለው የቤተሰብ ስም የመጣው ከሰነዓ ነው። የጸሎት ርዕሶች🤲🏽 👉🏾 በኤርትራ የሚገኙ የየመን አረብ ሕዝቦች አለማመናቸውን፣ ሃጥያታቸውንበደላቸውን በእግዚአብሔር ፊት ይዘን በመቅረብ ታላቅ የሆነውን ምህረቱ በልጁ በኢየሱስም እንዲያደርግላቸው እንጸልይ። 👉🏾 በኤርትራ የሚጘኙ የየመን ዲያስፖራዎች ወደ አገራቸው እንዲመለሱ የሚያስችል ዘላቂ እና ፍትሃዊ ሰላም እንዲሰፍን እንጸልይ። 👉🏾በኤርትራ የሚገኙ የየመን ሕዝቦች በእስልምና ሃይማኖት ብዙ ዘመናትን አሳልፈዋል፣ የክርስቶስን እውነት መቀበል ማለት ቤተሰባቸውን፣ ባህላቸውን፣ ማንነታቸውን ሁሉ እንደመካድ ሊቆጠር ይችላል ስለዚህ የወንጌልን መልእክት ሰምተው ወደ እውነት የደረሱትን እግዚአብሔር እንዲጠብቃቸው በመንፈሱ ሐይል እንዲታገዙ እንጸልይ።