en
Feedback
Mission Talk with Aman!

Mission Talk with Aman!

Open in Telegram

Mission Exist because worship doesn't . Mission is the means while worship is ultimate Goal of God. Pastor John piper.

Show more
509
Subscribers
No data24 hours
+17 days
-230 days
Posts Archive
ለሶማሌ ባንቱ የሕዝብ ክፍል እንጸልይ! በዚያን ጊዜ ደቀ መዛሙርቱን፡— መከሩስ ብዙ ነው፥ ሠራተኞች ግን ጥቂቶች ናቸው፤ እንግዲህ የመከሩን ጌታ ወደ መከሩ ሠራተኞች እንዲልክ ለምኑት፡ አላቸው። ማቴዎ
ለሶማሌ ባንቱ የሕዝብ ክፍል እንጸልይ! በዚያን ጊዜ ደቀ መዛሙርቱን፡— መከሩስ ብዙ ነው፥ ሠራተኞች ግን ጥቂቶች ናቸው፤ እንግዲህ የመከሩን ጌታ ወደ መከሩ ሠራተኞች እንዲልክ ለምኑት፡ አላቸው። ማቴዎስ 9፡ 37 - 38 ሰላም  የሚሽን ሞቢላይዜሽን ኢትዮጵያ ቤተሰቦች! ዛሬ አርብ ምሽት ከ3:30 ጀምሮ በቴልግራም ላይቭ ለሶማሌ ባንቱ የሕዝብ ክፍል በህብረት የምንፀልይበት ጊዜ ይኖረናል ከታች ባለዉ የቴሌግራም ቻናል ሊንክ በመግባት አብራችሁን እንድትጸልዩ እንጋብዛችኋለን። https://t.me/MobilizationEthiopia

ቀን 4 🙏 እንጸልይ 🙏 ለባንተቱ የሕዝብ ክፍል በሶማሌ የሰው ልጆች በአስማት እና በመናፍስት ላይ እንዲመኩ የልዑል አምላክ ሐሳብ አልነበረም! ክርስቶስ የሞተው ሰዎችን ከኃጢአትና ከመንፈሳዊ ጭቆና
ቀን 4 🙏 እንጸልይ 🙏 ለባንተቱ የሕዝብ ክፍል በሶማሌ የሰው ልጆች በአስማት እና በመናፍስት ላይ እንዲመኩ የልዑል አምላክ ሐሳብ አልነበረም! ክርስቶስ የሞተው ሰዎችን ከኃጢአትና ከመንፈሳዊ ጭቆና ነፃ ለማውጣት ነው። የሶማሌ ባንቱ ማህበረሰብን ይፈልጋቸዋል። 🙏የጸሎት ርዕሶች🙏 👉 በሶማሌ ባንቱ ህዝብ መካከል የኢየሱስ ስም ጸንቶ እንዲተከል እንጸልይ ። 👉አንድ አምላክ የሆነውን እግዚአብሔርን ብቻ እንዲያመልኩ እንጸልይ። 👉 ብዙ ሰዎች ወደ ጌታ እንዲመጡ እንጸልይ። 👉ከስደትና ከመፈናቀል እንዲላቀቁ እንጸልይ። 👉ለባቱ ሶማሌ ህዝብ ወንጌልን የሚሰብኩ ሃያላን እንዲነሱ እንጸልይ።

ቀን 3 🙏🏽እንጸልይ 🙏🏽 ለባንቱ የሕዝብ ክፍል በሶማሊ አብዛኛው የሶማሌ ባንቱስ ሕዝብ የስም ሙስሊሞች ናቸው። በሎሎች የአፍሪካ ሃገራት የሚኖሩት አንዳንድ የባንቱ ጎሳዎች ባሕላዊ ሥነ-ሥርዓታቸ
ቀን 3 🙏🏽እንጸልይ 🙏🏽 ለባንቱ የሕዝብ ክፍል በሶማሊ አብዛኛው የሶማሌ ባንቱስ ሕዝብ የስም ሙስሊሞች ናቸው። በሎሎች የአፍሪካ ሃገራት የሚኖሩት አንዳንድ የባንቱ ጎሳዎች ባሕላዊ ሥነ-ሥርዓታቸውን መለማመዳቸውን ቀጥለዋል። ብዙዎች የመንፈስ ውዝዋዜን ፣ አኒሚዝምን፣ አስማትን እና እርግማንን ጨምሮ የአባቶቻቸውን የጎሳ እምነት ወጎች ይዘው ኖረዋል። 🙏 የጸሎት ርዕስሶች 🙏 👉 ባህላዊ እምነት ውስጥ ካሉበት ከተለያዩ አጋንንታዊ አምልኮ ነፃ እንዲወጡ እንጸልይ። 👉በክርስቶስ ማረፍ እንዲሆንላቸው ወንጌል ወደ ባንቱ ሶማሌ ህዝብ እንዲገባ ወንጌል በሀይልና በስልጣን እንዲሰበክ እንጸልይ።

እንጸልይ 2017 - 2 እግዚአብሔር ድንቅ ግዜ ሰጠን። በወንጌል ላልተደረሱ የሕዝብ ክፍሎች በየ2 ወሩ የምናደርገው የጸሎት ፕሮግራም ሕዳር 7 - 2017 ተካሂዷል። እግዚአብሔርን እጅግ አስደናቂ ግዜ
+9
እንጸልይ 2017 - 2 እግዚአብሔር ድንቅ ግዜ ሰጠን። በወንጌል ላልተደረሱ የሕዝብ ክፍሎች በየ2 ወሩ የምናደርገው የጸሎት ፕሮግራም ሕዳር 7 - 2017 ተካሂዷል። እግዚአብሔርን እጅግ አስደናቂ ግዜ ሰጥቶናል። ቀጣዩ ላይ አብራችሁን እንድትሆኑ ስለህዝቦች ፊቱን እንድንፈልግ ከወዲው እንጋብዛለን። በወንጌሉ ስራ አብረን እንጠመድ!

ቀን 2 🙏🏽እንጸልይ 🙏🏽 ለባንቱ የሕዝብ ክፍል በሶማሌ የተለያዩ የሶማሌ ባንቱ ጎሳዎች አንድ ሆነዋል በዋነኝነት ለዚህም ምክኒያቱ በሶማሊያ ውስጥ በሚደርስባቸው የዘር መድልዎ ምክንያት ነው። አ
ቀን 2 🙏🏽እንጸልይ 🙏🏽 ለባንቱ የሕዝብ ክፍል በሶማሌ የተለያዩ የሶማሌ ባንቱ ጎሳዎች አንድ ሆነዋል በዋነኝነት ለዚህም ምክኒያቱ በሶማሊያ ውስጥ በሚደርስባቸው የዘር መድልዎ ምክንያት ነው። አብዛኛዎቹ ሶማሌዎች ከሶማሌ ባንቱስ ጋር አይጋቡም  አንዳንዶቹም አብረዋቸው ለመብላትም አይፈልጉም  ወይም ወደ ቤታቸውም አይገቡም። በሶማሊያ የእርስ በርስ ጦርነት ወቅት፣ ሶማሌ ባንቱስ በጣም ተጋላጭ ከሆኑ ቡድኖች አንዱ የነበሩ ሲሆን በጎሳ ሚሊሻዎች እና በወንጀለኞች ቡድኖች አሰቃቂ መከራ ደርሶባቸዋል። ብዙዎችም ሶማሊያን ለቀው ወጥተዋል። 🙏 የጸሎት ርዕሶች 🙏 👉 በከፊል በቋንቋቸው የተተረጎመው መፅሐፍ ቅዱስ እንዲጨረስ፣ ማንበብ ለማይችሉ ደግሞ የድምፅ ቅጂዎች እንዲዘጋጁላቸው እንጸልይ። 👉በሚኖሩበት ሀገር ተቀባይነት ያጡ ስለሆኑ የጌታ ፍቅር እንዲያገኛቸው በመካከላቸው የሚገኙ ቅዱሳን ፍቅርን እንዲያሳዩዋቸው እንጸልይ። 👉በተለያየ ሙያ ወደ ባንቱ ሶማሌዎች የሚላኩ ሚሲዮናዊያን በፍቅር የተሞሉ እንዲሆኑ እንጸልይ።

ቀን 1 🙏🏽እንጸልይ 🙏🏽 ለባንቱ የሕዝብ ክፍል በሶማሌ የሕዝብ ብዛት:- 905,000 ዋነኛ ቋንቋ:- ሜይ ብዙ ተከታይ ያለው እምነት:- እስልምና 99.95% ክርስትና:- 0.05% ወንጌላዊያን
ቀን 1 🙏🏽እንጸልይ 🙏🏽 ለባንቱ የሕዝብ ክፍል በሶማሌ የሕዝብ ብዛት:-  905,000 ዋነኛ ቋንቋ:-  ሜይ ብዙ ተከታይ ያለው እምነት:- እስልምና 99.95% ክርስትና:-  0.05% ወንጌላዊያን አማኞች:-  0.05% የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉም: - በከፊል ተተርጉሟል ወንጌል ተኮር ቅጂዎች: - አሉ   መግቢያ / ታሪክ የሶማሌ ባንቱስ ከአፍሪካ አናሳ ጎሣዎች መካከል የሚመደቡ ናቸው። በመጀመሪያ ወደ ሶማሊያ በ19ኛው ክፍለ ዘመን በአረቦች በባርነት ይመጡ ነበር። በዘር የተዋሃዱ ነገር ግን በጠላትነት ከጎሳዎች የተከፋፈሉ ከሶማሌዎች በባህል፣ በአካል እና በጎሳ የተለዩ ናቸው። ሶማሊ ባንቱስ ማይ-ማይ እና ዚጓ በመባል የሚታወቁትን ሁለት ቋንቋዎች ይናገራሉ ። በሶማሊያ የእርስ በርስ ጦርነት ሲቀሰቀስ ብዙ የሶማሊያ ባንቱስ በታጠቁ የሶማሊያ ሚሊሻዎች ከቤታቸውና ከእርሻቸው ተባረዋል። ሕይወታቸውን ለማዳን ሸሽተው ኬንያ ለመግባት በአደገኛ ቦታዎችና ሁኔታዎች ውስጥ አልፈዋል። በመንገድ ላይ ብዙዎች ሞተዋል። በስደተኛ ካምፖች ውስጥ ተቀምጠዋል። ዛሬ አብዛኛው የሚኖሩት በደቡብ ሶማሊያ በወንዞች ዳርቻ ወይም በደቡብ በኩል ወደ ኬንያ በመግባት ነው። ጥቂት ቁጥር ያላቸው በካናዳ ወይም በዩናይትድ ስቴትስ ይኖራሉ። 🙏 የጸሎት ርዕስ 🙏 👉 በሶማሌ ህዝብ የተጠሉ እንዲሆኑ የሚያደርግ፣ ወንጌልን እንዳይሰሙ ልባቸውን የዘጋ፣ አምሮዋቸውን የያዘ ክፉን አትብቀን እንጸልያለን። 👉 0.05% ብቻ የሆነው የአማኝ ቁጥር እንዲቀየር እንዲሁም እነዚህ ጥቂት አማኞች ሌሎችን ደቀ መዝሙር የሚያደርጉ እንዲሆኑ እንጸልይ። 👉 እግዚአብሔር ሀገራቸውን ሰላም እንዲያደርግላቸው ፣ በበረከት እንዲጎበኛቸውና የሰላምና የበረከት አምላክ እግዚአብሔር እንደሆነ እንዲያዩ እንጸልይ።

ጸሎታችን ተጀምሯል ከታች ባለው ሊንክ የቀላቀሉን። https://t.me/MobilizationEthiopia?videochat=76bf0a35f1cba5c517
ጸሎታችን ተጀምሯል ከታች ባለው ሊንክ የቀላቀሉን። https://t.me/MobilizationEthiopia?videochat=76bf0a35f1cba5c517

ለኤርትራ ሕዝብ እና ምድር እንጸልይ! በዚያን ጊዜ ደቀ መዛሙርቱን፡— መከሩስ ብዙ ነው፥ ሠራተኞች ግን ጥቂቶች ናቸው፤ እንግዲህ የመከሩን ጌታ ወደ መከሩ ሠራተኞች እንዲልክ ለምኑት፡ አላቸው። ማቴዎስ
ለኤርትራ ሕዝብ እና ምድር እንጸልይ! በዚያን ጊዜ ደቀ መዛሙርቱን፡— መከሩስ ብዙ ነው፥ ሠራተኞች ግን ጥቂቶች ናቸው፤ እንግዲህ የመከሩን ጌታ ወደ መከሩ ሠራተኞች እንዲልክ ለምኑት፡ አላቸው። ማቴዎስ 9፡ 37 - 38 ሰላም  የሚሽን ሞቢላይዜሽን ኢትዮጵያ ቤተሰቦች! ዛሬ አርብ ምሽት ከ3:30 ጀምሮ በቴልግራም ላይቭ ለኤርትራ ሕዝብ እና ምድር በህብረት የምንፀልይበት ጊዜ ይኖረናል ከታች ባለዉ የቴሌግራም ቻናል ሊንክ በመግባት አብራችሁን እንድትጸልዩ እንጋብዛችኋለን። https://t.me/MobilizationEthiopia

ተልእኳችን ማለዳ ሕዳር 6 - 2017 በትጋት ጸልዩ የመጸሐፍ ቅዱስ ምንባብ፡- ኤፌሶን 6፡18 በጸሎትና በልመናም ሁሉ ዘወትር በመንፈስ ጸልዩ፤ በዚህም አሳብ ስለ ቅዱሳን ሁሉ እየለመናችሁ በመጽናት ሁሉ ትጉ፤ ኤፌሶን 6፡18 ለውጤታማ ጸሎት አንደኛውና መሰረታዊ እውነት በጽድቅ እና በቅድስና ለመኖር ቆራጥ መሆን ነው ይህንም በያዕቆብ 5፡16 ላይ ተገጾ እናገኘዋለን፡፡ የጻድቅ ሰው ጸሎት በማለት ቃሉ ይነግረናል፡፡ ይህ መጸሐፍ ቅዱሳዊ እውነት አብዛኛውን ግዜ ብዙ አማኖች የሚዘነጉት እና የማያስተውሉት ይሆናል፡፡ ጻድቅ ሰው ማለት እግዚአብሔራዊ የሆነውን የሕይወት መንገድ ለመሄድ የሚሮጥ እና የእውነትንም መንገድ የሚለማመድ ነው፡፡ ምንም እንኳ በእድገታችን ገና ያልጎለበትን እና መውደቅ መነሳት ትግላችን ቢሆንም፤ ልባችንን ለታዛዥነት ማዘጋጀት ግን በጣም ጠቃሚ ነው፡፡ ሳናቋርጥ እንድንጸልይ መጸሐፍ ቅዱስ ያዝዘናል፡፡ ሳናቋወጥ መጸለይን መጸሐፍ ቅዱስ ሁለት መልኮች አሉት ይለናል፡፡ አንደኛው የማያቋርጥ ጸሎት ከእግዚአብሔር ጋር ከተቆራኘች ልብ የሚመጣ ሲሆን፤ ሁለተኛው ደግሞ ሁለተኛው ደግሞ በጽናት ከሚፈልግ ልብ የሚመነጭ ነው፡፡ (ማቴ 7፡7-8፣ ሉቃ 11፡5-10) ሐዋርያው ጳውሎስ በኤፌሶን 6፡18 እና በቆላሲያን 4፡12 ላይ አማኞች ጸንተን እና ያለመታከት እንድንጸልይ ጥሪ ያቀርብልናል፡፡አማኞች በጽናት እና በትጋት መጸለያችን እግዚአብሔር በህይወታችን እና በምድራችን እንደፈቃዱ የሆነውን ልማናችንን እንዲፈጽም ምክኒያት ነው፡፡ በጽናት እና በትጋት የምንጸልይበት የጸሎት ልምምዳችን ምን ይመስላል ወዳጆች፤ እግዚአብሔር ይህን ምን ያህል ሚፈልገው ይመስላቹኃል፡፡ ስለ ግላችን፣ ቤተሰብ፣ ቤተክርስቲያን፣ ስለውንጌል ተልዕኮ፣ በወንጌል ስላልተደረሱ ህዝቦች እና ስለምድራችን በጽናት በፊቱ እንገኝ ዘንድ አባታችን ይፈልጋል፡፡ እግዚአብሔር ሆይ በትጋት ወደፊትህ እንቀርብ ዘንድ ጸጋይ ያግዘን አሜን!

ቀን 4 እንጸልይ 🙏🏽ለኤርትራ ምድር 🙏🏽 በኤርትራ እና በኢትዮጵያ መካከል የነበሩ አለመግባባቶች የተባበሩት መንግስታት ኤርትራ በ1952 ኤርትራ ነፃ የሆነች የኢትዮጵያ ፌደሬሽን አድርጎ በማቋቋሙ የተነሳ እየተባባሰ መጣ።  ይህ የኤርትራ የ 30 ዓመታት የመገንጠል እና እራስ ገዝ ሀገር የመሆን ትግል መጀመሪያ ነበር በ1993 የኢትዮጵያ የፖለቲካ ማሻሻያ ለኤርትራ እንደ ሀገር ነፃነቷን እንድታገኝ በር ከፈተ። እ.ኤ.አ. በ 1998 የድንበር ግጭት እንደገና ተቀሰቀሰ እና ለሁለት ዓመታት በተደረገው ጦርነት በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ወታደሮችንና ዜጎችን ህይወት ቀጥፏል። የሰላም ስምምነቶች የተመሰረቱት እ.ኤ.አ. በ2000 ቢሆንም ኢትዮጵያ በ2018 የሰላም ስምምነት ስምምነቶቹን እስክትቀበል ድረስ ለዓመታት የዘለቀው ፍጥጫ ተከሰተ። ለዓመታት ባደረገው ከፍተኛ ወታደራዊ ኢንቨስትመንት ምክንያት የሀገሪቱ አጠቃላይ ደህንነት፣ መሰረታዊ ስርዓቶች እና መሰረተ ልማቶች አልተጠበቁም። ተገቢ ያልሆነ የግብርና አስተዳደር ሁለት ሦስተኛ የሚሆነው ህዝቧ በምግብ ርዳታ ላይ ጥገኛ እንዲሆን አድርጎ ጥቂት የሰለጠኑ ሠራተኞች እንዲኖሩት አድርጓል። የጸሎት ርዕሶች🤲🏽 👉🏾በኤርትራ ላሉ የተለያዮ የህዝብና የማህበረሰብ ክፍሎች የእግዚአብሔር ቃል በቋንቋችው የመተርጎም ስራ እንዲጀመር፣ የክርስቶስን ወንጌል የሚያበስሩ ቲቪ እና የሬዲዮ ስርጭቶችን እንዲከታተሉ ጸልዩ። 👉🏾ኤርትራ ለተለያዮ የትላልቅ ኢንቨስት ለሚያደርጉ እና የስራና የልማትን እድል ለሚፈጥሩ ድርጅቶች በሯን እድትከፍት ይህንም እግዚአብሔር ለወንጌል በር እንዲያረገው እንማልድ! 👉🏾ለምነኝ፥ አሕዛብን ለርስትህ የምድርንም ዳርቻ ለግዛትህ እሰጥሃለሁ።”   መዝሙር 2፥8  የኤርትራ ህዝብ  ለኢየሱስ የተመረጡ ደቀመዝሙር የሚያፈሩ ደቀመዝሙር እንዲሆኑ፣ ታላቅ የቤተክርስትያን ንቅናቄ እንዲነሳባት እንጸልይ !

እንጸልይ 2017 - 2 “ለምነኝ፥ አሕዛብን ለርስትህ የምድርንም ዳርቻ ለግዛትህ እሰጥሃለሁ።” — መዝሙር 2፥8 እንጸልይ 2017 - 2 ህዳር 7 - 2017 ዓ.ም ከጠዋት 2፡30 - 10፡00 ሰዓት
እንጸልይ 2017 - 2 “ለምነኝ፥ አሕዛብን ለርስትህ የምድርንም ዳርቻ ለግዛትህ እሰጥሃለሁ።”   — መዝሙር 2፥8 እንጸልይ 2017 - 2 ህዳር 7 - 2017 ዓ.ም  ከጠዋት 2፡30 - 10፡00 ሰዓት በሚሽን ሞቢላይዜሽን ኢትዯጵያ አገልግሎት በወንጌል ላልተደረሱ የሕዝብ ክፍሎች  በአዲስ አበባ  ተዘጋጅቷል በዚህ ፕሮግራም ላይ በመገኘት አብራችሁን እንድትጸልዩ ጥሪ እናቀርባለን። በዚህ ፕሮግራም ላይ ለመሳተፍ ከታች ባሉት የቴሌግራም አድራሻዎች በመጻፍ ወይም በስልክ ቁጥሮች በመደወል  ያናግሩን፤ ኑ አብረን የእግዚአብሔርን ፊት ስለሕዝቦች በጋራ እንፈልግ! @FEVIREVIVALIST +251 93 518 3566 +251 93 789 4139 +251 97 820 8912

ተልእኳችን ማለዳ ሕዳር 5 - 2017 እግዚአብሔር ጸሎትን ይመልሳል? የመጸሐፍ ቅዱስ ምንባብ፡- የያዕቆብ መልእክት 5፡ 13-20 እርስ በርሳችሁ በኃጢአታችሁ ተናዘዙ። ትፈወሱም ዘንድ እያንዳንዱ ስለ ሌላው ይጸልይ፤ የጻድቅ ሰው ጸሎት በሥራዋ እጅግ ኃይል ታደርጋለች። ያዕቆብ 5፡16 ያይዕቆብ የጻድቅ ሰው ጸሎት ሃያል እና ውጤት ያለው እንደሆነ ይነግረናል፡፡ ኢየሱስም ሲናገር በስሙ የምንለምነውን ሁሉ እንደሚያደርገው ነግሮናል፡፡ ኢሳያስ 65፡ 24 ላይ ሳይጠሩኝ እመልስላቸዋለሁ ብሎ ይናገራል፡፡ እንደዚያ ቢልም ግን በህይወታችን ብዙ ያልተመለሱ ጸሎቶች እንዳሉን እናስባለን፡፡ ለፈውስ እንጸልያለን ነገር ግን አልተፈወስንም፣ በሮች እንዲከፈቱ ጸልየናል ነገር ግን አልተከፈቱም እንዲያውም ከነጭራሹ ተዘግተዋል፣ ለብዙ ነገሮቻችን መልስ እግዚአብሔርን እንለምናለን ነገር ግን ልመናዎቻችን ሁሉ አልተመለሱም፡፡ እና እንዲህ እንጠይቃለን እውን እግዚአብሔር ጸሎታችንን ይመልሳል? መልሱ አዎ ይመልሳል ነው! ጸሎት ግን እኛ ምንፈልገውን ሁሉ ምንቀበልበት አይደለም፤ በእኛ እና በእግዚአብሔር መካከል ያለው ግንኙነት ሰጥቶ መቀበል ላይ የተመሰረተ አይደለምና፡፡ እግዚአብሔር የጠየቅነውን የሚመልስልን ወይም የሚያደርግልን እንደ ቃሉ እና እንደፈቃዱ የሆነውን ጥያቄያችንን ነው (1ኛ ዩሐ 5፡14-15)፡፡ የምንጸልየው የእኛ ህይወት ከእርሱ ጋር የተቆራኘ፣ ያለእርሱ መኖር ስለማንችል ግንኙነታችን ይቀጥል ዘንድ ነው፡፡ ጸሎት ከእግዚአብሔር ጋር የግንኙነት መስመራችን ነው፡፡ ጸሎታችንን ሁሉ ይሰማናል ደግሞም እንደፈቃዱ እና እንደዘላለማዊ ሃሳቡ ደግሞ ይመልስልናል፡፡ ጸሎት ፊቱን እንጂ እጁን ፈልገን ምንሄድት አይደለም፡፡ እርሱ እርሱ ስለሆነ ከፊቱ እንገኛለን በመገኘቱ ደግሞ እንረካለን፣ ነፍሳችንን ትለመልማለች፤ አባታችን ነውና ፈቃዱን እናደርግ ዘንድ ፈቃዳችንን እናስገዛለን፡፡ በመገኘቱ ውስጥ ብቻ በመቆየታችን ነፍሳችንን ከምንም በላይ ዋናውን ነገር እንመግባታለን፡፡ ጸሎት ምርጫ አይደለምና ህይወት ሚጀምርበት የሚቀጥልበት እንደሆነ ገብቶን በፊቱ እንገኛለን፡፡ አባት ሆይ ለመጸለይ ጉልበቶቻችንን እንዲበረቱ እንለምንሃለን አሜን!

ቀን 3 እንጸልይ 🙏🏽ለኤርትራ ሕዝብ 🙏🏽 የምግብ ዋስትና በኤርትራ ምድር ብዙዎችን የሚያሰጋ ጉዳይ ነው፤ 65% በኤርትራ ገጠራማ ስፍራዎች እና ክልል የሚኖረው ሕዝብ ከድህነት ጋር የሚታገል ነው
ቀን 3 እንጸልይ 🙏🏽ለኤርትራ ሕዝብ 🙏🏽 የምግብ ዋስትና በኤርትራ ምድር ብዙዎችን የሚያሰጋ ጉዳይ  ነው፤  65% በኤርትራ ገጠራማ ስፍራዎች እና ክልል የሚኖረው ሕዝብ ከድህነት ጋር የሚታገል ነው፥ 37% ደግሞ ከፍተኛ የምግብ ዋስትና እጦት ያጋጠመው የማህበረሰብ ክፍል ይገኛል። ሌላው የሃይማኖት ጉዳይ ሲሆን መንግስት እውቅና ካላቸው አራት ሃይማኖቶች - የሱኒ እስልምና ፣ የኤርትራ ኦርቶዶክስ ፣ የሮማ ካቶሊክ እና የሉተራን ናቸው ።  በኤርትራ፣ ክርስቲያኖች በእምነታቸው ምክንያት ከፍተኛ የሆነ ስደት ይደርስባቸዋል። በሺዎች የሚቆጠሩት ክርስቶስን ለመካድ ፈቃደኛ ባለመሆናቸው ለእስር ተዳርገዋል፤ ከእነዚህም መካከል አብዛኞቹ የአካል ጉዳት\ ማሰቃየት አልፎ ተርፎም ሞት ይደርስባቸዋል።  የእምነት ነፃነት በጣም ያስፈልጋል። እንዲያም ሆኖ በኤርትራ ያሉ አብያተ ክርስቲያናት ማዕቀብ ቢደረግባቸውም እየበዙ ነው፣ ብዙ አማኞች የቤት አብያተ ክርስቲያናትን በማቋቋም ከመሬት በታች ተንቀሳቅሰዋል። ጌታ በኤርትራ ያሉ ወገኖቹን እንዲጠብቅ እና ከፖለቲካዊ እና ሃይማኖታዊ ጭቆናዎችና ቁጥጥር እንዲወጣቸው መጸለይ ያስፈልጋል። የጸሎት ርዕሶች🤲🏽 👉🏾የቤት ለቤት ቤተ-ክርስትያን ታላቅ በሆነ ሁኔታ እንዲሰፋ  እንጸል! 👉🏾ከስደት፣ ከግዳጅ ወታደራዊ አገልግሎት እና ከድህነት ስጋት አልፈው ከኢየሱስ ጋር ለመገናኘት እንዲሆንላቸው እንጸልይ። 👉🏾መንግስት የቤተክርስቲያን መሪዎች  እንዲፈታ እና የሃይማኖት ነፃነት እንዲሆንላቸው እንጸልይ!

ተልእኳችን ማለዳ ሕዳር 4 - 2017 ታሪኩን አካፍሉ የመጸሐፍ ቅዱስ ምንባብሐዋርያት ስራ 16፡ 29 – 34 እነርሱም፡— በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ እመን፡ አንተና ቤተ ሰዎችህ ትድናላችሁ፡ አሉት። ሐዋ. ሥራ 16፡31 በፊሊጲሲዩስ የወህኒው ጠባቂ ጩኸት የብዙዎች የጠፉ ሰዎች ጩኸትም ነው፤ ለመዳን ምን ማድረግ አለብን? ከጌታዬ ጋር ሰላምን ለማድረግ ምን ማድረግ አለብኝ? ለህይወት ትርጉም እና አላማዬን ለማግኘት ምን ላድርግ? በደህና ለመኖር ምን ላድርግ? መንፈሳዊ የህይወት ጥያቄ ያላቸው ሰዎች እነዚህ እና ብዙ ጥያቄዎ አሏቸው፡፡ መልሱ ግን ሁሌም አንድ ነው በጌታ በኢየሱስ እመንና የምትፈልገውን ሁሉ ታገኘዋለክ ነው፡፡ እንደ ክርስቲያን የክርስቶስ ኢየሱስን ትንሳኤ እና ንግስና ምንመሰክር ህዝቦች ነን፡፡ የምንናገረው ታሪክ የትናንት ቢመስልም ሁሌም ግን አዲስ የሆነ ዘላለማዊም የሚሆንም ነው፡፡ እግዚአብሔር ይህን መልእክት ካወራን የብዙዎችን ህይወት የሚለውጥበት እንደሚያደርገው ተናግሮናል፡፡ የድህነት ታሪክ ዘመን የማይዘው ቢሆንም በምናጋራበት ወቅት ሁኔታዎች፣ የምንነግራቸውን ሰዎች ማንነት በሚመጥን መልኩ ይቃኛል፡፡ እየጸለያችሁለት የነበረ ሰው አንድ ቀን ድንገት እሺ ይሄ ክርስትና የምትሉት ነገር ምንድን ነው ወይም እንዴት ነው ክርስቲያን መሆን የምችለው ብሎ  ቢጠይቃችሁ ምን ብላችሁ ትመልስለታችሁ? ይህ ወቅት ሲመጣ ታሪኩን ለመናገር የተዘጋጀን እንሆን ዘንድ ያስፈልገናል፡፡ የእግዚአብሔር ማንነት፣ ሰው በእግዚአብሔር ዘንድ ያለው ቦታ፣ የእግዚአብሔር አላማ፣ በልጁ በኩል የሰውን ሐጢያት ዋጋ እንደከፈለበት፣ በዘላለም ያለው እቅዱ የምናጋራው ታሪኩ ናቸው፡፡ ይበልጥ ስለእግዚአብሔር መንግስት  ለማውራት የተዘጋጀን ምስክሮች እንሆን ዘንድ ያስፈልገናል፡፡ እግዚአብሔር ሆይ የድህነት መልእክትህን ለብዙዎች የምንናገር እንሆን ዘንድ እርዳን፤ ስለመንግስትህ ይበልጥ ለማወቅ እንድንተጋ ጸጋ ያግዘን፡፡ በዳን ጆግስማ የተጻፈ ከ https://todaydevotional.com/ ድህገ ገጽ ተወስዶ የተተረጎመ

ቀን 2 እንጸልይ 🙏🏽 ለኤርትራ ምድር 🙏🏽 ለኤርትራ አገራዊ አስተዳደር እንጸልይ! ኤርትራ ሀገሪቱ ከምትከተለው መንግስታዊ ስርአት እኳያ አብዛኛው የንግድ ድርጅቶች ወይም አገልግሎቶች የመንግስት በመሆናቸው በግል የሚተዳደሩ የንግድ ድርጅቶች ወይም አገልግሎቶች ውስን መሆናቸው ይታወቃል። ከቴሌኮሙኒኬሽን አገልግሎት፣ ከፕሬስ እና እስከ አየር መንገድ ድረስ የኤርትራ መንግስት የሁሉም ባለቤት ነው። እነዚያ ኤርትራ ውስጥ የምታያቸው የኢንተርኔት ካፌዎች የግል ንግድ ሊመስሉ ይችላሉ፣ ግን እንደዛ አይደለም። ከኢንተርኔት ካፌዎች ጋር የመንግስትን ኢንተርኔት በመጠቀም እና የትኞቹ መተግበሪያዎች ማውረድ እንደሚችሉ እና የትኛውን ድረ-ገጽ ማግኘት እንደሚችሉ ጥብቅ ቁጥጥር ውስጥ ናቸው። በኤርትራ ለሚገኙ አማኞች ደግሞ ይህ አስተዳደር እጅግ ከባድ ስደትን አስከትሎባቸዋል። በሌሎች ዜጎቻቸውም ላይ በሀገራቸው እየሰሩ የማደግንና የመለወጥን ፣ አዳዲስ ስራዎችና ፈጠራዎችን እንዳይሞክሩም ምክንያት ስለሚሆን አብዛኛው ህዝብ ሃገራቸውን ለቀው ወደ ሌሎች ሀገራ ለመሰደድ ተገደዋል ። የጸሎት ርዕሶች🤲🏽 👉🏾 የኤርትራ መንግስት ሕዝቡን በኮሚኒዝም አገዛዝ ከሰላሳ አመታት በላይ ገዝቶአል  ይህ መሰረታዊ የሆኑ መብታቸውን የሚነፍግ ሲሆን እግዚአብሔር የነፃነትን ዘመን እንዲያመጣላቸው እንጸልይ! 👉🏾በብዙ ስደትና፣ መከራን የተቀበሉና በመቀበል ያሉ የኤርትራ አማኝ ህዝቦችን እግዚአብሔር በተለያዮ አጋጣሚ  ለመልካም፣ ለራሱ ክብር በመቀየር  ለብዙዎች መዳን ምክንያት እንዲያደርጋቸው። ታሪኮቻቸው ህዝቡን ባልተጠበቁ መንገዶች እንዲደርስና ሰዎች በክርስቶስ ላይ እምነታቸውን እንዲጥሉ እንጸልይ! 👉🏾በኤርትራ ምድር ያሉ ቅዱሳን የእግዚአብሔር መንፈስ ምስክርነታቸውን በድንቅና በተአምራት እንዲያፀናላቸው እንለምን። 👉🏾ብዙ ወጣትና ቤተሰብ የመሰረቱ የኤርትራ ተወላጆች በአለም ዙሪይያ መበተን የመዳናቸው ምክንያት እንዲያደርገው እየለመንን እንጸልይ!  እግዚአብሔር በኤርትራ፣ ኢትዮጵያ እና ሌሎች የተሰደዱባቸው ሃገራት ላይ ያሉ የክርስቶስ ተከታዬች እንዲቀብሉዋቸው፣ ወንጌልን ወደ ቤቶቻቸው በመጋበዝ፣ ለነሱ መልካም በመሆን እና ስለእነሱ በመማለድ እንዲሰብኩላቸው እንጸልይ! 👉🏾እግዚአብሄር ህዝቡ የፈለገዉን ስራ መርጦ ፍሬአማ የሚሆንበትን አዲስ ወቅት እንዲያመጣላቸው እንጸልይ!