SAPI
Closed channel
ውድ የቻናላችን ተከታታዮች ማንኛውም አይነት አስተያየት መስጠት፣ ማንነትዎን ደብቀው ፓስት እንዲደረግ የምትፈልጉት ታሪክ፣ ማንኛውም ከሀኪም መልስ የሚፈልግ ጥያቄ፣ ከሱስ ጋር የተያያዘ የስነልቦና እርዳታ ወይም ሕክምና ቢያስፈልግዎት በ @SapiProjectHelp ይፃፉልን። ምላሻችን ፈጣን ነው። ትውልድን እንታደግ
Show moreThe country is not specifiedThe category is not specified
245
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
245
#SAPI training has organized a session by Dr Enqu Deresse (Associate Professor of Psychiatry) for 1st year students.
EMSA through SAPI project has delivered a session on introduction about addiction on Thursday 10/01/2019.
💜💜💜💜💜💜
We believe that addiction is not a choice, a style, or a sign of modernisation: It is chronic treatable illness. We also believe that prevention is the way to decrease the prevalence. Dr Enqu's presentation was also about creating awareness before getting exposed to risk areas. It was such a wonderful session.
We would love to pass our deep gratitude for Dr Thomas who was SAPI trainee for organizing the event.
We would also thank Dawit K/marriam, Muhidin Ibrahim, Trinat Mulugeta and all tournament organizers for your kind heart and valuable time.
245
Merry Christmas 🎄🎁 #StPaulFamily....Given the festive season we would like to,once again,offer you the chance to join our SAPI community and be part of the dynamic change we are spearheading.
REMINDER:-This offer is for a limited time only.
Deadline-18/01/2019
https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSdx1OkcWT7G3jlk2VQaGHx-hq6QDVfWjjMzdJEsNObixv8EOQ/viewform?usp=pp_url
245
ሪፖርት📌የዓለም ጤና ድርጅት ባወጣው አዲስ ሪፖርት በዓለማችን በአማካይ ከ20 ሰዎች ውስጥ አንዱ በአልኮል መጠጥ #እንደሚሞት ጠቁሟል።
በፈረንጆቹ 2016 ብቻ ከ3 ሚሊየን በላይ ሰዎች መሞታቸውም በሪፖርቱ ተካቷል።
ከዚህ ውስጥ ከ75 በመቶ የሚበልጡት ወንደች መሆናቸው ተገልጿል።
የአልኮል መጠጡ ለጉዳት በመዳረግ የሚሞቱት ሰዎች 28 በመቶ ሲሆኑ፣ ለምግብ መፈጨት ችግር በመጋለጥ የሚሞቱት 21 በመቶ ያህል ናቸው።
19 በመቶ ያህሉ ደግሞ የአልኮል መጠጡ በሚፈጥረው የልብ ችግር ህይወታቸውን እነደሚያጡ ሪፖርቱ ጠቁሟል።
ቀሪዎቹ ለካንሰር፣ ለቁስ ህመሞች፣ ለአዕምሮ ችግርና ሌሎች በአልኮል ምክንያት ለሚመጡ የጤና መታወክ በማጋለጥ ሰዎችን ለሞት መዳረጋቸውም ተነግሯል።
የአልኮል መጠጥን መጠቀም በዓለም ላይ ከሚገኙ በሽታዎች 5 በመቶ ያህሉ እንዲባባሱ ማድረጉም ነው የተገለጸው።
በዓለም ላይ 237 ሚሊየን ወንዶችና 46 ሴቶች በአልኮል መጠጥ ምክንያት ለአዕምሮ ችግር መዳረጋቸውንም ሪፖርቱ አሳይቷል፤ ለዚህ ጉዳት ከተዳረጉት መካከል አውሮፓውያን ቀዳሚ ሲሆኑ አሜሪካውያን ይከተላሉ።
የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር #ቴድሮስ_አድሃኖም ጤናማ ትውልድ ለመገንባት ለሚደረገው ጥረት ስጋት የደቀነውን የአልኮል መጠጥ አጠቃቀም መዛባት ለመከላከል በትጋት መስራት አለብን ብለዋል።
በዓለም ላይ 2 ነጥብ 3 ቢሊየን ያህል ሰዎች አልኮል ይጠጣሉ። በርካታ ታዳጊዎችም 15 ዓመት ሳይሞላቸው አልኮል መጠጣት እንደሚጀምሩ የዓለም የጤና ድርጅት መረጃ ያሳያል።
ምንጭ፦ሲኤንኤን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
245
Second year VS Third year !!! Tomorrow at 11:30 LT!! At 1st year hall...Come and enjoy the game!!
245
⚽️🏀🏓🏐⛹⛹♀🤾♂🤾♀🏋♀🏋🏐🏓🏀⚽️
hello everyone🤗🤗
the long anticipated tournament will officially be started by an opening ceremony on Wednesday August 8 at 11:30 in first year classroom
🤸♀🤸♂🤸♂🤸♂🤸♂🤸♂🤸♂🤸♂🤸♂🤸♂
we bring to you a night of
🎷 good music
☕️ coffee
🎳 games
😋 cookies and soft drink
🗣 educational speech
mark your calendar❌❌you don't want to miss this!!👆👆👆
245
🙋🙋🏽♂️hello every one..as we promised before here we are coming with🤾🏼♀️⚽️🏀⛹️🤾🏻♂️🏐 SAPI tournament ⚽️🏆🏆that stay for one month.... starting from august 8 upto september 10.we would like to inform all batch students so as you prepare your self in all kinds of sport and give us the participants name and number within these 5 days for each kind of sports.
245
Shalom everyone,
This is the SAPI community
As stated many times before, we have been striving to bring about tangible and definitive change amongst our fellow students. And without further delay, SAPI is proud to announce the official tournament opening ceremony the coming August 8 where there will be a wide variety of intresting events. Come and witness for yourselves as many have been longing for it. Rise up, be a part of this marvelous expeirence!!!
245
ነገረ በርጫ (KHATOLOGY)
በዶ/ር አባተ ጋሻው
ክፍል አንድ
"ጫት ያመረቅናል
ሱስ ቤት ያስፈረሳል
እማማ አቢሲኒያ እማማ
የጨብሲ የለሽም ወይ bro
እማማ ጦቢያየ እማማ
ይቅርታ አርግልን ቴዲ አፍሮ lol😊."
ጫት (khat) በሳይንሳዊ ስያሜው ካታ ኢዱሊስ የሚባል ባለ አበባ (flowering plant) እፅ ነው:: በአብዛኛው በአፍሪካ ቀንድ እና በአረብ ምድር ላይ የሚገኝ ና በነዚህ አካባቢ ከሚኖሩ ሰወች ጋር ባህላዊ(cultural) ትስስር ያለው እፅ ነው::
አንድ አንድ አጥኝወች እንደሚሉት ከሆነ ኢትዮጵያ የሰው ልጅ ብቻ ሳይሆን
ጫትም የበቀለባት የመጀመርያዋ አገር ናት:: የአፋር ምድር ሉሲን የሐረር ምድር ጫትን ለአለም ያስተዋወቁ ታሪካዊ ስፍራወች ናቸው:: እንደ Sir Richard Burton አገላለጥ ከሆነ ጫት ከሐረር ተነስታ ሞቃዲሾን አቋርጣ ወደ የመን ምድር የገባችው በ 15ኛው ክፍለ ዘመን ነው:: ከዚያም በኋላ ወደ አረብ ከዚያም ወደ ቀረው ዓለም::
በአሁኑ ወቅት በአሜሪካ፣ በካናዳ እና በጀርመን አገር ጫት በአደንዛዥ እፅ ተፈርጃ ህገ ወጥ የሚል ስም ተለጥፎባታል::
ጫት ይህ ስያሜ የተሰጣት አምፊታሚንን የሚመስል ካቲነን (cathinone) የሚባል አደንዛዥ ንጥረ ነገር በውስጧ ስለያዘች ነው:: ይህ ኬሚካል ደግሞ በደም ዝውውር አማካኝነት የተለያዩ የአንጎል ክፍሎችን በማነቃቃት የሚፈጥረው መጠነኛ የስነልቦናዊ ጥገኝነት ( dependence) ስላለ ነው::
ይህ ጥገኝነት ከጊዜያት በኋላ አካላዊ ጥገኝነትን በማምጣት ቃሚው ካልቃመ በቀር ስራ መስራት እንዳይችል (functional impairment) እና ማህበራዊ ህይወቱን በአግባቡ እንዳይመራ( social impairment) ያደርገዋል:: በተጨማሪም ጫቱ የፈጠረውን የምርቃና ሁናቴ (euphoric state) ለመስበር( ጨብሲ) አልኮል ወደ መጠጣት እና ትንባሆ ወደማጨስ ይወስዳል::
ለረዥም ጊዜ በዚህ ሁኔታ የሚኖር ሰው ከስነልቦናዊ እና አካላዊ ጥገኝነቱ በላይ በእፅ ምክንያት ለሚከሰት የአዕምሮ መቃወስ (substance induced psychosis) ሊዳረግ ይችላል:: አንዴ እዚህ ደረጃ ላይ ከደረሱ በኋላ ደግሞ ለመውጣት ለሀኪሙም ሆነ ለቃሚው እጅግ አስቸጋሪ ይሆናል::
ያኔ ትዳር ይፈርሳል፤ ቤተሰብ ይበተናል፤ ማህበራዊ ጤና ይታወካል:: በዚህ የጫት ሱስ የሚጠቁት(ለጊዜው እንቅልፍን ስለሚከላከል እና ድብርትን ስለሚያስወግድ) በአብዛኛው ከ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት እስከ ከፍተኛ ት/ት ተቋማት ያሉ ተማሪወች ናቸው:: ይህ ደግሞ በአገሪቱ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ጉዳይ ላይ የራሱ የሆነ አሉታዊ ተፅዕኖ ይኖረዋል::
በዚህ ምክንያት የአለም የጤና ድርጅት እ.ኤ.አ በ 1980 ዓ.ም ጫትን ከ ሲጋራ እና አልኮል ቀጥሎ በአደንዛዥ እፅነት ሰይሞታል::
ከዚህም በተጨማሪ የታካሚወችን ዶሴ በማጥናት በተደረገ የኋልዮሽ ጥናት(retrospective study) መሰረት ጫትን ለረዥም ጊዜ የሚቅሙ ሰወች ለተለያዩ የውስጥ ደዌያት የመጋለጥ
እድላቸው ሰፊ ነው::
በጥቂቱ ለመጥቀስ ያህል፦ የደም ግፊት፣ የሆድ ድርቀት፣ ፣የጉበት እና የጨጓራ ህመም፣ ስንፈተ ወሲብ እና የመሳሰሉትን የጤና ችግሮች ሊያስከትል ይችላል::
ብዙውን ጊዜ ሰወች ወደዚህ የሱስ ህይወት የሚገቡት ባላሰቡትና ባልጠበቁት ሁኔታ ነው::
አብዛኞቹ እራሴን መቆጣጠር እችላለሁ ብለው ይጀምራሉ:: አንዳንዶቹ ለረዥም ጊዜ እየሰሩ (እያነበቡ) ለመቆየት፣ በአቻ ወይም በአካባቢ ተፅዕኖ፣ ድብርታቸውን ለመርሳት ሌሎቹ ደግሞ የስልጣኔ ምልክት መስሏቸው( ለሙድ) መቃም የሚጀምሩ አሉ:: ከዚያ በኋላ ሱስ ውስጥ መግባታቸውን ሳያውቁት ሱሰኞች ሆነው ይገኛሉ::
በጫት ተጠቃሚች አብዛኛውን ጊዜ የሚነሱ ጥያቄወች እና መልሶቻቸው፦
በመጀመርያ መረዳት ያለብን ነገር በመቃም አለመቃም ጉዳይ ላይ መከራከር አይጠቅምም ምክንያቱም መቃም የሚጀምሩት እያወቁ ስለሆነ ከዚያ በኋላ የሚያነሱት ሀሳብ እና የሚጠይቁት ጥያቄ አብዛኛውን ጊዜ ቃሚነታቸውን ለመደገፍ የሚደረግ ሩጫ ከመሆን በቀር እውነትን ለመቀበል የተዘጋጀ ልብ ስለማይኖራቸው ክርክሩ ጉንጭን ከማድከም የዘለለ ፋይዳ አይኖረውም::
ከዚያ ባለፈ ሱስ የአዕምሮ መዛባት (adaptation) መሆኑን መረዳት አለብን በመሆኑም ከመተቸት ይልቅ ለመቃም ያነሳሳቸውን ምክንያት በመጠየቅ ከችግሩ ሊወጡ የሚችሉበትን መንገድ መጠቆም እና ተገቢውን የሀኪምና የመንፈሳዊ እርዳታ እንዲያገኙ ማድረግ ተገቢ ነው:
ግንቦት 4 2010 ዓ.ም ሸገር
@sapiproject
