cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

የሄኖክ አሸብር ግጥሞች እና ወጎች

Advertising posts
3 717
Subscribers
+424 hours
+207 days
+3730 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

#ሃሌል_የመዝሙርና_የስነጽሁፍ_አገልግሎት ✍️ በዚህ ጊዜ እግዚአብሔር በውስጤ ባስቀመጠው ጸጋና ሸክም መሰረት ሙሉ ትኩረቴን በአዲስ ኪዳናዊ መረዳት ክርስቶስ ተኮር መዝሙሮችን በመሥራትና ዘማሪዎችን በማስተማር ላይ አድርጌ እየሠራሁ ነው!! 📌 ለተለያዩ የመዘምራን ሕብረቶች ፣ ለስነጽሁፍ ሕብረቶችና ለሶሎ ዘማሪዎች ስልጠና በመስጠት ፣ መዝሙሮችን በመስጠት ፣ ግጥሞችን በማረም እንዲሁም የእግዚአብሔርን ልጅ የኢየሱስ ክርስቶስን ወንጌል በመስበክና በማስተማር ላይ እገኛለሁ!! ✍️ አልበም እና ሲንግል የምትሰሩ ዘማሪዎች የጸጋውን ወንጌል በመረዳት መልዕክቶቻችን ከኢየሱስ ውጭ እንዳይሆኑ በመሬታዊነት ተጠቅተው ቁስ ቁስ እንዳይሸቱ የተጠናቀቀው የክርስቶስ ኢየሱስ ሥራ ላይ ቆመን እንድንጽፍና እንድንዘምር አብራችሁኝ ትሠሩ ዘንድ ግብዣዬን አቀርባለሁ🙏🙏🙏 📌 እስካሁን ከጌታ የተቀበልኳቸው ዜማ ያላቸውን መዝሙሮች እና ዜማ የሌላቸውን ግጥሞች (መጽሐፎቼ ላይ ያሉትን ግጥሞች ጨምሮ) ለእግዚአብሔር ክብር ለቤተክርስቲያን ጥቅም ይሆን ዘንድ ሁሉንም ግጥሞች በዝማሬ ወደ ሕዝብ እንዲደርሱ ጌታ በረዳኝ መጠን እየተጋሁ ነው!!......ከእኔ ጋር የእግዚአብሔርን ሥራ መስራት የምትፈልጉ ኢየሱስን ብቻ ለመዘመር የቆረጣችሁ ዘማሪዎች እና ስለ ኢየሱስ ብቻ እንዲዘመር ይሄን አገልግሎት በየትኛውም መንገድ መደገፍ የምትፈልጉ ሁሉ በ 0906114984 ወይም በ 0934001968 ልታገኙኝ ትችላላችሁ!! 👉 የወንጌልን እውነት በውብ ስነጽሑፍ እንቀኝ!! #ሃሌል_የመዝሙርና_የስነጽሁፍ_አገልግሎት ✍️ ሄኖክ አሸብር
Show all...
5👍 1
“ፍቅር እንደዚህ ነው“ ካሌብ ጎኣ “FIKIR ENDEZIH NEW” KALEB GOA NEW ETHIOPIAN PROTES... https://youtube.com/watch?v=EsypEyK_OMQ&si=_ND_F8NnEH06ET9c
Show all...

5
✍️ እኔ ነኝ ምክንያትህ ***** ልክ እኔ እንደሌለሁ ካንተ ጋ እንዳልነበርኩ ብቻህን ነጥዬ ፣ ተሰቅሏል አልልም ብቻህን ነጥዬ ፣ ሞቷል ብየ አልልም ብቻህን ነጥዬ ፣ ተነሥቷል አልልም ብቻህን ነጥዬ ፣ ከብሯል ብየ አልልም እኔ ባልኖር ኑሮ ፣ ይሄ ሁሉ አይኖርም ስቅለትም መሞትም ትንሳኤም ፣ የኖረው ካንተ ተለይቼ እኔ ሞቼብህ ነው እናማ ስትመጣ...... አብሬህ ተሰቀልኩ ፣ በሞትህ አበርኩኝ ስትነሣ ጊዜ ፣ አብሬህ ነበርኩኝ ለ'ኔ በሰራኸው ፣ ያለ'ኔ ብትሰራም ያደረከው ሁሉ ፣ ያለ'ኔ አይወራም እኔ ነኝ ምክንያትህ ፣ እኔ ነኝ አላማህ በሞት ተበክሎ ፣ ደሜ ነው ያደማህ ቁስሌ ነው ጅራፉ ፣ ገርፎ ያቆሰለህ አንተማ እንኳን ቁስል ፣ መች ገላ ነበረህ? #ሄኖክ_አሸብር
Show all...
54👍 8🔥 4🙏 1
#ኦንላይን  #ለዘማሪዎች 📌 የመዝሙር ግጥም አጻጻፍ ትምህርት 👉 አሁኑኑ ይመዝገቡ!! በኦንላይን ይማሩ!! ስልክ ቁጥር 👉 0906114984 👉 0934001968 https://t.me/Henokashebir #ሄኖክ_አሸብር
Show all...
👍 2
#ሀገር_ውስጥም ሆነ #ከሀገር_ውጭም ላላችሁ ባላችሁበት ሀገር ሆናችሁ መማር ትችላላችሁ!! ✍️ የመዝሙር ግጥም አጻጻፍ #የኦንላይን_ክላስ ምዝገባ ለ 3 ወር በሳምንት 3 ቀን በእያንዳንዱ Online ክላስ ተጨማሪ ትምህርቱን 👉 በቪዲዮ 👉 በኦዲዮ 👉 በPdf ያገኛሉ!! የመዝሙር ግጥም አጻጻፍ በ online መማር የምትፈልጉ ዘማሪዎችና ገጣሚዎች መመዝገብ ትችላላችሁ!! ኑ ወዳጃችን ኢየሱስ በውስጣችን ያስቀመጠውን የግጥምና የዝማሬ ጸጋ እንዴት በመጽሐፍ ቅዱሳዊ እውነትና በስነጽሑፋዊ እውቀት ለመግለጥና ለማገልገል ፤ ስለኢየሱስ ያማረ ቅኔ እንድንቀኝና እንድንጽፍ እንማር። 👉 ሀገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጭ ያላችሁበት ቦታ ሆናችሁ የመዝሙር ግጥም አጻጻፍ መማር ትችላላችሁ!! ለበለጠ መረጃ እና ለመመዝገብ +251906114984 +251934001968 በቴሌግራም ያግኙኝ የመዝሙር ግጥም አጻጻፍ online Class #ሄኖክ_አሸብር
Show all...
👍 10
👉 የመዝሙር ግጥም አጻጻፍ ትምህርት ምዝገባ አሁኑኑ ይመዝገቡ!! 0906114984 0934001968
Show all...
#ሀገር_ውስጥም ሆነ #ከሀገር_ውጭም ላላችሁ ባላችሁበት ሀገር ሆናችሁ መማር ትችላላችሁ!! ✍️ የመዝሙር ግጥም አጻጻፍ #የኦንላይን_ክላስ ምዝገባ ለ 3 ወር በሳምንት 3 ቀን በእያንዳንዱ Online ክላስ ተጨማሪ ትምህርቱን 👉 በቪዲዮ 👉 በኦዲዮ 👉 በPdf ያገኛሉ!! የመዝሙር ግጥም አጻጻፍ በ online መማር የምትፈልጉ ዘማሪዎችና ገጣሚዎች መመዝገብ ትችላላችሁ!! ኑ ወዳጃችን ኢየሱስ በውስጣችን ያስቀመጠውን የግጥምና የዝማሬ ጸጋ እንዴት በመጽሐፍ ቅዱሳዊ እውነትና በስነጽሑፋዊ እውቀት ለመግለጥና ለማገልገል ፤  ስለኢየሱስ ያማረ ቅኔ እንድንቀኝና እንድንጽፍ እንማር። 👉 ሀገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጭ ያላችሁበት ቦታ ሆናችሁ የመዝሙር ግጥም አጻጻፍ መማር ትችላላችሁ!! ለበለጠ መረጃ እና ለመመዝገብ +251906114984 +251934001968  በቴሌግራም ያግኙኝ የመዝሙር ግጥም አጻጻፍ online Class #ሄኖክ_አሸብር
Show all...
👍 2
Show all...
TikTok · Henok Ashebir

Check out Henok Ashebir’s video.

✍️ ይስሐቅን መሰዋት የሚችል አባቱ ብቻ ነው!! **** መጽሐፍት ሁሉ ስለ ኢየሱስ እንደሚናገሩ ካልተረዳን መልዕክቶቻቸውን ባልተገባ መልኩ ለመጠቀም እንዳረጋለን!! ✍️ ክፍሉ አብርሃም የእግዚአብሔር ጥላ በመሆኑ እግዚአብሔር ራሱ አብርሃምን  የምትወደውን አንድ ልጅህን ሰዋልኝ እያለ ስለሚወደው ስለራሱ አንድያ ልጅ ያወራበት ክፍል ነው!! 📌 ታሪኩ ሊመጣ ያለውን በአባቱ የሚሰዋ ተወዳጅ አንድያ ልጅ በጥላነት የሚያመለክት ነው!! ✍️ እግዚአብሔር ከአብርሃም ውጭ በየትኛውም ዘመን ማንንም ቢሆን ይስሐቅህን ሰዋልኝ አላለም!!.....ይስሐቅ የሰው አይደለም ይስሐቅ ሰው ጋርም የለም!! 📌 ይስሐቅ እግዚአብሔር ለእኛ ለሰዋው ለክርስቶስ ጥላ የሆነ እንጂ እኛ ቤት ያደገ(ያለ) ውድ ነገር አይደለም!! ✍️ ይስሐቅን ከአባቱ ውጭ መስዋዕት አድርጎ ማቅረብ የሚችል ማንም የለም!!.....ኢየሱስን አባቱ መስዋዕት አድርጎ ያቀረበው ለዛ ነው!! 📌 እግዚአብሔር በየትኛው ሌሊት መጥቶ ይስሐቃችሁን ሰውልኝ አላችሁ? ይስሐቅኮ አንድ ነው እርሱም በአካል የተገለጠው ክርስቶስ!! ✍️ ይስሐቅ መሰዋት የነበረበት ወደ አህዛብ ሁሉ የሚደርስ በረከት ስለነበር ነው.....እኛ የትኛውን ይስሐቅ ሰውተን ምን አይነት በረከት ልናስገኝ ነው? 📌 ባጭር ቃል ይስሐቅ ማለት እግዚአብሔር ራሱ ለአለም ሁሉ ያቀረበው ክርስቶስ የተባለ መስዋዕት ነው!! ✍️ ልብ በሉ የመስዋዕቱን በግ እግዚአብሔር ያዘጋጃል የተባለው የተሰዋው በግ ተራ በግ ስላልነበረ ነው!!....እግዚአብሔር ያዘጋጀው ያ በግ አንድያ ልጁ ነበር!! 📌 እኛ ለእግዚአብሔር የምንሰዋው ይስሐቅ የለንም!! ✍️ እግዚአብሔርን ምንም አድርገን እንደማናስደስተው አምነን ራሱ ባቀረበልን መስዋዕት መደሰት እንጀምር.....እግዚአብሔርን ማስደሰት የምንችለው እኛን ባስደሰተበት መስዋዕት ደስ ስንሰኝ ብቻ ነው!! 📌 "ይስሐቄ ያልኩት ያለኝን ውድ ነገር ነው" የምትሉ ከሆነ በእናንተ ዘንድ እግዚአብሔርን ማስደሰት የሚችል ውድ ነገር የላችሁም በማለት በድፍረት ልነግራችሁ እወዳለሁ!! ✍️ ኢየሱስ እንዲህ አለ፦ " እናንተ በመጻሕፍት የዘላለም ሕይወት እንዳላችሁ ይመስላችኋልና እነርሱን ትመረምራላችሁ፤ እነርሱም #ስለ_እኔ #የሚመሰክሩ_ናቸው፤" (የዮሐንስ ወንጌል 5: 39) ✍️ ሉቃስ 24 (ኢየሱስም).... 27፤ ከሙሴና ከነቢያት ሁሉ ጀምሮ ስለ #እርሱ_በመጻሕፍት_ሁሉ_የተጻፈውን #ተረጐመላቸው። ✍️ ብሉይ ኪዳን የአዲስ ኪዳን ጥላ ነው!! ✍️መጽሐፍት ሁሉ ስለ ኢየሱስ ይናገራሉ!! #የይስሐሃቅ_ህይወት_ስለ_ኢየሱስ_ #ምን_ይነግረናል? ♦️ይስሐቅ የአብርሃም ተወዳጅ አንድያ ልጅ ተብሏል ዘፍ 22፡2 ♦️ኢየሱስ እግዚአብሔር የሚወደው አንድያ ልጅ ተብሏል ማቴ 16:16, ማቴ 17:5, ማር 1:1 📌 ይስሐቅ በወንድሙ የተጠላ ነበር፡፡ ዘፍ 21፡9 📌 ኢየሱስ በወንድሞቹ የተጠላ ነበር፡፡ ማር 3፡21፤ ዮሐ.15፡25 ✍️ ይስሐቅ አባቱ ሊሰዋው ሲወስደው ፈቃደኛ ነበር ። ዘፍ 22:3 ✍️ ኢየሱስ የራሱን ፈቃድ ሳይሆን የአባቱን ፈቃድ በመታዘዝ ፈጽሟል።ሉቃ 22:42 ♦️ይስሐቅ አባቱ ያሸከመውን እንጨት ተሸክሞ በመታዘዝ ወደ ሚሰዋበት ተራራ ወጥቷል። ዘፍ 22:9 ♦️ኢየሱስ የሚሰዋበትን የእንጨት መስቀል ተሸክሟል። ዮሐ 19:17 📌 ይስሐቅ የሚሰዋበትን እንጨት ታግዟል፡፡   ዘፍ 22፡6 📌 ኢየሱስ የሚሰዋበትን እንጨት ታግዟል፡፡ ማቴ 27፡32 ✍️ ይስሐቅ በእንጨት ላይ ታስሮ በመሰዊያው ላይ ተጋድሟል። ዘፍ 22:9 ✍️ ኢየሱስ ስለኃጢአታችን በእንጨት መስቀል ላይ መስዋዕት ሆኗል ። ዮሐ 19:18 ሐሥ5:30  ሐሥ10:39 1ጴጥ 2:24 ♦️ይስሐቅ ( የመስዋዕቱ በግ) ቀንዳም(ኃይል ቢኖረውም) ከምድር በበቀሉ እሾሃማ ሀረጎች ቀንዱ ተይዞ ነበር። ዘፍ 22:13 ♦️ኢየሱስ ( የእግዚአብሔር በግ) ቀንድ (ኃይል ቢኖረውም) በፍቅር ምክንያት ኃይሉን ሳይጠቀም ጠላቶቹ እና በኃጢአታችን ሙታን የነበርነውን ለመታደግ በሸላቾች ፊት ለእርድ እንደሚነዳ ጠቦት ራሱን አሳልፎ ሰጠ። ኢሳ 53 , ሮሜ 5:6-10 ✍️የይስሐቅ መስዋዕትነትና የተሰዋበትን ቦታ እግዚአብሔር ያዘጋጀው ተብሏል። ዘፍ 22:14 ✍️በኢየሱስ በኩልም እግዚአብሔር ያለእኛ ተሳትፎ ሙሉ ደህንነት አዘጋጅቶልናል። ኤፌ 2:8-9, ቲቶ 3:5 ♦️ይስሐቅ ስለተሰዋ የምድር አህዛብ ሁሉ በዘርህ ይባረካሉ ተብሎ ነበር ። ዘፍ 22:18 ♦️በኢየሱስ መስዋዕትነት በእምነት የምድር አህዛብ ሁሉ ተባረኩ። ገላ 3:8-9 ✍️ ይስሐቅ ከተሰዋ በኃላ እንደሚነሳ እና ከአባቱ ጋር እንደሚመለስ አብርሀም ያውቅ ነበር። ዘፍ 22:5 ✍️ኢየሱስም መስዋዕት አድርጎ ራሱን አሳልፎ ቢሰጥም እግዚአብሔር ከሙታን መካከል አስነስቶታል። ማቴ 28 ሐሥ 3:15 , ሐሥ 13:30, ሮሜ 1:3-4, ሮሜ 4:24-25 የተወደዳችሁ፦ ይስሐቅ የክርስቶስ ጥላ ነውና መጽሐፉን መጽሐፉ ሊል በፈለገው መንገድ ብቻ አስብሉት እንጂ ከአውድ ውጭ አትጠቀሙበት!! #ሄኖክ_አሸብር
Show all...
20👍 8👎 4🔥 1