cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

መምህር ግርማ አይበራ ዘተዋሕዶ

በዚህ ቻናል ኦርቶዶክሳዊ መጻሕፍቶችን:ትምህርቶችን እንዲሁም ከፕሮቴስታንት ወገኖቻችን ለሚመጡ ጥያቄዎች የተሰጡ መልሶች የሚተላለፉበት ስለሆነ ሌሎች ወንድሞቻችሁን በመጋበዝ እንድትከታተሉ አሳስባለሁ! @girma7 ያናግሩኝ 👆👆👆

Show more
Advertising posts
221
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
+530 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

Photo unavailable
ልብ የሚሰብር ''''''''''''' ካለሁበት 32 ኪ/ሜ ራቅ ብዬ ከአገልግሎቴ ስመለስ አስደንጋጭ ክስተት ገጥሞኛል! ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ካስተዋወቀችኝ ቅን ወንድሞች እና በደቡብ ክፍል ለምናደርገዉ ሐዋርያዊ አገልግሎት አንጋፋዉን ድርሻ በመዉሰድ ለመምህራነ ቅዱሳት መጻሕፍትን በመግዛት:ለአዳዲስ ተጠማቂያን አስፈላጊዉን ሁሉ ስንጠይቀዉ ፊቱ በደስታ ተሞልቶ የሚረዳን ዉድ ወንድማችን #ታጋይ መንገሻ ዉድ ባለ ቤቱ የጭንቅላት ዕጢ ህመም አጋጥሟት 800ሺ ብር ለህክምና እንደሚያስፈልግ ተግሮታል! ከፈጣሪ በታች እስካሁን በአገልግሎቴ ከጎኔ የነበራችሁ ኦርቶዶክሳዊያን በእመአምላክ እማጸናችኋለሁ ለወንድሜ ድረሱለት:ዉድ ባለቤቱን እንታደጋት! ዲያቆን ግርማ አይበራ ዘተዋሕዶ
Show all...
👍 4
Photo unavailable
እነሆ የምስራች ዜና '''''''''''''''' ያመኑት 68 ነፍሳት በዛሬዉ ዕለት''በቅድስት ሥላሴ ዓመታዊ ክብረ በዓል(ሐምሌ-7) በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ በሸካ ቤንች ሸኮ ምዕራብ ኦሞ ሀገረ ስብከት በቤንች ወረዳ ቤተ ክህነት በጊዲ ቤንች ወረዳ ከጻት ቀበሌ:ከተኩስ ቀበሌ:ከጋጫ ቀበሌ ከኢ-አማኒነት እና ከባዕድ አምልኮ የመጡ ለአንድ ወር መሠረታዊ ትምህርት ሲከታተሉ ቆይተዉ በዛሬዉ ዕለት በዲዙ ቅድስት ኪዳነ ምህረት ቤተ ክርስቲያን ተጠምቀዉ ሀብተ ወልድ እና ስመ ክርስትናን አግኝተዋሉ! ''ስብሐት ለእግዚአብሔር'' እላችኋለሁ፥ እንዲሁ ንስሐ በሚገባ በአንድ ኃጢአተኛ በእግዚአብሔር መላእክት ፊት ደስታ ይሆናል። ሉቃ 15:10! ዲያቆን ግርማ አይበራ ዘተዋሕዶ የቤንች ወረዳ ቤተ ክህነት ዋና ፀሐፊ እና ሰባኬ ወንጌል!
Show all...
3
ሰማዕትነት ''''''''''''''''''''''' ሰማዕት ‹‹ሰምዐ›› ከሚል የግእዝ ቃል የተወሰደ ሲሆን፤ ትርጉሙም ያየነውን፣ የሰማነውን መመስክር መቻል እንደሆነ የኪዳነ ወልድ ክፍሌ መጽሐፈ ስዋስወ ወግስ መዝገበ ቃላት ገጽ 671 ይነግረናል፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ‹‹እኔ ለእውነት ለመመስከር መጥቻለሁ›› በማለት እውነትን እንድንመሰክር አብነት ሆኖናል /ዮሐ.18፥37/፡፡ ሰማዕትነት በሃይማኖታዊ ትርጉሙ ስንመለከተው ስለ እግዚአብሔር፣ ስለቅድስት ቤተክርስቲያን፣ ስለ ሃይማኖታቸው በእውነት በመመስከራቸው ጀርባቸውን ለግርፋት፣ ሰውነታቸውን ለእሳት፣ እግራቸውን ለሰንሰለት፣ አንገታቸውን ለስለት አሳልፈው ለሰጡ፤ በድንጊያ ተወግረው በመንኮራኩር ተፈጭተው በጦር ተወግተው አልያም በግዞትና በስደት በዱር በገደል ተንከራተው ለዐረፉ ቅዱሳን አባቶችና ቅዱሳት እናቶች የሚሰጥና ተጋድሎአቸውን ጠቅለል አድርጎ የሚገልጽ ቃል ነው፡፡ ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊው እመቤታችንን ባመሰገነበት ድርሳኑ “ሰማዕታት የዚህችን ዓለም ጣዕም በእውነት ናቁ፤ ደማቸውንም ስለ እግዚአብሔር አፈሰሱ፤ስለ መንግሥተ ሰማያትም መራራ ሞትን ታገሱ” በማለት የሰማዕታት ተጋድሎአቸው መራራ እንደሆነ ገልጿል፡፡ (ውዳሴ ማርያም ዘሐሙስ) ጌታችን ‹‹በሰው ፊት ለሚመሰክርልኝ ሁሉ እኔ ደግሞ በሰማያት ባለው አባቴ ፊት እመሰክርለታለሁ፡፡ በሰው ፊት የሚክደኝን ሁሉ ደግሞ በሰማያት ባለው አባቴ ፊት እክደዋለሁ›› ሲል ስለ ሃይማኖታችን የምንመሰክረው ከሰማዕትነት ጋር ያለውን ቁርኝት ነግሮናል፡፡ /ማቴ.10፥32-33/፡፡ ከዚህ አንጻር ያለ ክርስትና ሰማዕትነት ያለ ሰማዕትነት ክርስትና የለም ማለት ነው፡፡ ዛሬ ሰማዕተ ኢየሱስ ክርስቶስ ጴጥሮስ ወጳዉሎስ ብለን በታላቅ ድምቀት የምናከብራቸዉ በዚህ ሁሉ መንገድ ያለፉ በፍጻሜ ሕይወታቸዉ ስለ ጣዕመ መንግስተ ሰማያት መራራ ሞትን የታገሱ:ጣዕመ ዓለምን የናቁ የፈጣሪያቸዉን ክብር በአላዊያን ነገሥታት ፊት መስክረዉ ምስክርነታቸዉን#ጴጥሮስ ተዘቅዝቆ ተሰቅሎ በመሞት#ቅዱስ ጳዉሎስ አንገቱን በመቆረጥ ያረፉበት የክብር እረፍታቸዉን በድምቀት እናከብራለን! ''የሰማዕታቱ በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን! ዲያቆን ግርማ አይበራ ዘተዋሕዶ
Show all...
  • Photo unavailable
  • Photo unavailable
  • Photo unavailable
በ3500 ብር እንደነዚህ አይነት ምርጥ ምርጥ የመጻሕፍት ማስቀመጫ ማሰራት የምትፈልጉ በሚዛን-አማን ዙርያ የምትገኙ በዉስጥ መስመር አናግሩኝ! ዲያቆን ግርማ አይበራ ዘተዋሕዶ
Show all...
👍 2
01:54
Video unavailable
ጉባኤ አረጋዊያን በአማን ክፍለ ከተማ በአጉ መንደር ዛሬ ደስ በሚል ሁኔታ አሳልፈናል! በሁሉም ቦታ መለመድ ያለበት ተግባር
Show all...
111.35 MB
🙏 4
Photo unavailable
የምስራች ዜና '''''''''''''' ክቡር ዶ/ር አባ ኃይለ ገብርኤል ግርማ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከ27 በላይ የጥናትና ምርምር ጽሑፎችን ያሳተሙ ሲሆን 11 አካባቢ የሚጠጉ መጽሐፍቶችን በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ አሳትመዋል። #በተጨማሪ:-አባታችን በሥነ ልቡና ሳይንስ ፣ በምክር አገልግሎት ፣ በትምህርት አመራርና አስተዳደር ፣በኢኩሚኒዝም ፣ በኦርቶዶክሳዊ መንፈሳዊነትና ወ.ዘ.ተ... ሠፊ የምርምር ሥራዎችን የሠሩና ያበረከቱ በዘመናችን የተገኙ ብቸኛ አባት ናቸው። (Researcher whose interdisciplinary work spans Counseling, Psychology, Educational Leadership and Management, Ecumenism, Mystical Theology, and Spiritual Direction) 👉በዛሬዉ ዕለት የፕሮፌሰርነት ማዕረግ በማግኘታቸዉ ደስ ብሎኛል! ''ቀሪ ዘመንዎትን አምላከ ሊቃዉንት ይባርክልን! ዲያቆን ግርማ አይበራ ዘተዋሕዶ
Show all...
🙏 3
Photo unavailable
ዛሬ ከተመረቁ ከቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርሲቲ የነገረ መለኮት ምሩቃን! 1ኛ ኢ/ር መ/ር ታዴዎስ መንግስቴ ከወልዲያ ሀገረ ስብከት ከፍተኛ ነጥብ በማምጣት 1ኛ ደረጃ ''የወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ'' 2ተኛ መ/ር ክብሮም ገብረ ሕይወት ከሸካ ቤንች ሸኮ ምዕራብ ኦሞ ሀገረ ስብከት 2ተኛ ደረጃ በመዉጣት የነዐስ ሜዳሊያ ተሸላሚ! 3ተኛ መ/ር ልዑል ቦጋለ ከጂማ ሀገረ ስብከት ሦስተኛ በመዉጣት ተሸላሚ! ሦስቱም የቀን መደበኛ ደቀ መዛሙርት በእጅጉ ኮርተንባችኋል! ቀሪ የሥራ ዘመናችሁን በነፍስም በሥጋም በረከት የምታገኙበት ዘመን እንዲሆንላችሁ ወንድማዊ ምኞቴ ነዉ! መምህር ታዴዎስ መንግስቴ ተወዳጁና የቅርብ ጓደኛዬ የጀመርከዉ መጻፍሕ በቅርቡ በእጃችን ገብቶ እንደምንጠቀምበት በመተማመን ደግመ ደጋግመኽ የምትጽፍበትን እዉቀት እና ጥበቡን እንዲጨምርልኽ እመኛለሁ! ዲያቆን ግርማ አይበራ ዘተዋሕዶ
Show all...
Photo unavailable
የሚሰጡ ቡሩካን እጆች በእጅጉ ይባረኩልን! ባኮስ መጽሕፍት መደብር ለ5 ቀን የሚቆይ ከዚህ በታች የተቀመጡትን 7 በነገረ መለኮት ዙርያ የተጻፉትን መጻሕፍት ቻሌንጅ ከሰዓታት በፊት ማጋራቱ ይታወቃል! ይህንንም ባጋራሁት መሠረት በስም እንጂ በአካል የማላዉቀዉ አንድ ወዳጄ መጻሕፍቶቹን በእጄ አስገብቶልኛል! '''ክብር ያድልልን! እናንተምባኮስ መጻሕፍት መደብር - Bakos Book Store ተባረኩልን! ዲያቆን ግርማ አይበራ ዘተዋሕዶ
Show all...
  • Photo unavailable
  • Photo unavailable
አመሠግናለሁ ''''''''''''''''' ዘመኑን የዋጀ አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ ማሰብ እና አስቤ ከጀመርኩት አንድ ዓመት ሞልቶኛል! በአንድ ዓመት ዉስጥ ከtiktok ቻናል ጋር ከተዋወኩት 7 ወር የሆነኝ ሲሆን በእነዚህ ወራት ዉስጥ 30k ''ሠላሳ ሺ ተከታይ''አፍርቼያለሁ! ተከታይ ማፍራት ብቻ ሳይሆን ከእነዚህ ዉስጥ 100% ኦርዶክሳዊያን ወንድም እህቶቼ ናቸዉ።እነዚህም በቤንችኛ ቋንቋ የማስተላልፈዉን ኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮችን በማጋራት በገንዘባቸዉ በመደገፍ:የሚያስፈልገኝን ቅዱሳት መጻሕፍትን በመግዛት ከጎኔ የነበሩ አሁንም ያሉ በክርስቶስ ፍቅር አብዝቼ የምወዳቸዉ ዘመዶቼ ናቸዉ። '''እግዚአብሔር ያክብርልኝ! አሁንም የኔ ቤተሰብ መሆን የምትፈልጉ እነዚህ 30 ሺ ቤተሰቦቼ ጋር መተዋወቅ የምትፈልጉ በዚህ link እየገባችሁ ተቀላቀሉን👉tiktok.com/@girmaaybera0 👉tiktok.com/@girmaaybera0 👉tiktok.com/@girmaaybera0
Show all...
01:39
Video unavailable
ዲያቆኑ ''ሊቀ ሊቃዉንት ስምዓኮነ መልአክ! '''የትህትና ጥግ! ለበለጠ መንፈሳዊ ትምህርት ቴሌግራም ቻናሌን ይቀላቀሉ።👇👇👇👇 https://t.me/seratekidase ዲያቆን ግርማ አይበራ ዘተዋሕዶ
Show all...
97.80 MB
🙏 1
Choose a Different Plan

Your current plan allows analytics for only 5 channels. To get more, please choose a different plan.