en
Feedback
Deacon Biruk Bokicha

Deacon Biruk Bokicha

Open in Telegram

"ይህ የዲያቆን ቡሩክ ቦክቻ የቴሌ ግራም ፔጅ ነው" በዚህ ፔጅ:- ➡የቅዱሳን ጻድቃን ሰማዕታት ገድላቸውን(ታሪካቸውን)እንለቃለን። ➡የቤተክርስትያን አስተምህሮዎችን እንደ አሰፈላጊነቱ የምንለቅ ይሆናል። የYoutube ቻናላችንን Subscribe እያደረጋችሁ https://youtube.com/@dnbirukbokicha?si=vXKnXHeqUjEGmzVU

Show more
1 080
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
photo content

🌾የተባረከች አይን የእግዚሐብሔርን ቃል በማንበብ ትጠመዳለች፤ 🌾የተባረከች ጆሮ የንስሀ መዝሙር በመስማት እራሷን ታንጻለች፤ 🌾የተባረከ ጉሮሮ ላይ የተቀደሰ ውሀ ይንቆረቆርበታል፤ 🌾የተባረከች ምላስ የአምላኳን ስጋና ደምን ትቀበላለች፤ 🌾የተባረከ አንደበት ላይ እግዚሐብሔር ይመስገን የሚል ቃል አይጠፋበትም፤ 🌾የተባረከች አንገት የአምልኮ ደም የፈሰሰበትን ቅዱስ መስቀል ትሸከማለች፤ 🌾የተባረከች ልብ ኢየሱስን እስከ እናቱ አንግሳ በፍቅር ትሞላለች፤ 🌾የተባረከች እጅ የቀረበላትን ምግብ በአምልኮ ስም ትባርካለች፤ 🌾የተባረከች እግር ጠዋትና ማታ የአምላኳን መቅደስ ትረግጣለች። (ዘሌ 11:44) “እኔ እግዚሐብኤር አምላካቹ ነኝና ሰውነታችሁን ቀድሱ ቅዱስም ሁኑ እኔ ቅዱስ ነኝና”

photo content

🌾#ማግባት_ለሚሹ🌾 (የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ምክር) 🍂ከምንም በፊት የጋብቻ ዓላማን ማወቅ አለባችሁ፡፡ በሕይወታችን ለምን ጋብቻ እንደሚያስፈልገን መረዳት አለባችሁ፡፡ ከዚህ ውጪ ሌላ ነገርን አትጠይቁ፡፡ እናስ የጋብቻ ዓላማው ምንድነው? ለምንድነው እግዚአብሔር ጋብቻን የሰጠን? ብጹዕ ጳውሎስን እናድምጠው፤ እንዲህ ያለውን፦ "ስለ ዝሙት ጠንቅ ለእያንዳንዱ ለራሱ ሚስት ትኑሮው፤ ለእያንዳንዲቱ ደግሞ ለራሷ ባል ይኑራት" (1ኛ ቆሮ.7፥2)። ➡"ከድህነት ይወጣ (ትወጣ) ዘንድ" ነው የሚለውን? ወይስ "ሀብት ለማግኘት ሲባል" ነው የሚለውን? አይደለም፡፡ ታዲያ ምንድነው የሚለው? ከዝሙት እንጠበቅ ዘንድ፤ ራሳችንን መቆጣጠር እንችል ዘንድ፤ ንጽህናን ገንዘብ እናደርግ ዘንድ፤ በትዳር አጋራችን ደስ ተሰኝተን እግዚአብሔርን እናመሰግን ዘንድ፡፡ አያችሁ ይኼ ነው የጋብቻ ስጦታው ይኼ ነው የጋብቻ ፍሬው፤ ይኼ ነው የጋብቻ ጥቅሙ፡፡ 🍂ስለዚህ #ልጆቼ! እማልዳችኋለሁ ትልቁን ጥቅም ዘንግታችሁት ዓይናችሁን በትንሹ ላይ አታሳርፉ፡፡ የትዳር አጋርን ስትመርጡ የሀብት ጉዳይ የእናንተ ትልቅ አጀንዳ ሊኾን አይገባም፡፡ ➡ስለ ሀብት ብሎ የትዳር አጋርን መምረጥ ድንቁርና ነው፤ ሀብት ነገ ሊጠፋ ይችላልና፡፡ ስለዚህ ለትዳር የምትመርጡት ሰው ከምንም በላይ መንፈሳዊ ሀብቱን ተመልከቱ፡፡ በዚህም ዓለም በወዲያኛውም ዓለም ይበልጥ የሚጠቅማችሁ ይኼ ነውና፡፡ #አባቶች_ሆይ! አብርሃምን ምሰሉት፡፡ አብርሃም ለልጁ ለይስሐቅ ሚስትን ሲፈልግለት፦ ሀብትን አላየም፤ የንጉሣውያን ቤተሰብን አልተመለከተም፤ አፍአዊ ውበትን መመዘኛ አላደረገም፤ ወይም ይህን የመሰለ ሌላ መስፈርትን አልደረደረም፡፡ የነፍስ ንጽህናን እንጂ፡፡ #እናቶች_ሆይ! ሴት ልጆቻችሁን እንደ ርብቃ አሳድግዋቸው፡፡ ➡እናንተ ማግባትን የምትሹ #ወጣቶች_ሆይ! ይስሐቅን ምሰሉት፦ ዘፈንን፣ ዳንኪራን፣ ሳቅና ስላቅን፣ የከበሮንና የዋሽንት ጫጫታን፣ ሌላውንም የዲያብሎስ ትርኢት በሰርጋችሁ ቀን አታስቡ፡፡ 🍂ከዚህ ይልቅ በምታደርጉት ኹሉም ላይ እግዚአብሔር እንዲቀድማችሁ ለምኑት፡፡ ይህን ያደረጋችሁ እንደኾነ ትዳራችሁ ፍቺ፣ ዝሙት፣ ቅናት፣ ጭቅጭቅ፣ ንትርክ የሌለበት ኾኖ ይፀናላችኋል፡፡ ይህን ያደረጋችሁ እንደኾነ፥ ሌላው በረከትም ተትረፍርፎ ይመጣላችኋል፡፡ የአውሎ ነፋስ ዓይነት በዙሪያችሁ ቢነፍስም፥ አትነዋወፁም፡፡ #እናንተ_ልጃገረዶች_ሆይ! ርብቃን ምሰሏት፡፡ የትዳር አጋራችሁን ፍጹም ለማፍቀር የተዘጋጃችሁ ኹኑ፡፡ ➡ይህን ያደረጋችሁ እንደኾነ ቤታችሁ ፍጹም ሰላማዊ ባሎቻችሁ የምትልዋቸውን የሚያደርጉና በፍቅራችሁ የሚንበረከኩ ይኾናሉ፡፡ ትዳር እንዲህ ኾኖ ሲጀመር፥ እግዚአብሔርንና ወላጆቹን ደስ የሚያሰኝ ልጅ ይገኝበታል፡፡ 🍂የቤት ዕቃዎችን መግዛት ስንፈልግ፥ በጣም እንጠነቀቃለን፡፡ የሻጮቹን ማንነት አይተን፣ የዕቃዉንም ጥንካሬ አገላብጠን ተመልክተን ነው የምንሸምተው፡፡ ➡ሚስት ስናገባም ከዚህ የበለጠ ልንጠነቀቅ ይገባናል፡፡ የገዛነው ዕቃ ችግር ቢኖርበት ለሸጠልን ሰው መመለስ እንችላለን፡፡ ሚስት ስናገባ ግን ወደ ቤተሰቦቿ መመለስ አንችልም፤ እስከ ዕድሜአችን ፍጻሜ ድረስ ከእኛ ጋር ነው የምትኾነው፡፡ ➡ክፉ ናት ብለን ብንመልሳት፥ በሕገ እግዚአብሔር መሠረት አመንዝራ እንኾናለን፡፡ ስለዚህ፥ ሚስት ስትመርጡ የሀገራችሁን ሕገ መንግሥትን ብቻ አታንብቡ፤ ከኹሉም በፊት ሕገ ቤተ ክርስቲያንን አንብቡ እንጂ፡፡

photo content

🌾ጠላትህን ውደድ›🌾 (ማቴ. 5፥45) 🌾ባልንጀራህን ውደድ ጠላትህንም ጥላ እንደ ተባለ ሰምታችኋል። እኔ ግን እላችኋለሁ፥ በሰማያት ላለ አባታችሁ ልጆች ትሆኑ ዘንድ ጠላቶቻችሁን ውደዱ።(ማቴ. 5፥43-45) ➡የዚህኛው ሕግ ዋና መልእክት ፍቅር ነው፡፡ ይህን ሕግ የሰጠን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጠላቶችን በመውደድ እኛም እንዲሁ እንድናደርግ አስተምሮናል፡፡ ➡ሰውን ሁሉ መውደድ የክርስትና ሕግ ነው፡፡ ይህ ሕግ ፍጹም የሚሆነው ደግሞ የሚያውቁትን ወዳጅን በማፍቀር ብቻ ሳይሆን ጠላትን በመውደድ በተግባር የተገለጠ እንደሆነ ነው፡፡ 🌾ክርስቶስ ሁሉንም በመውደድ በፍጹም ፍቅር እንደተገለጠ ክርስቲኖች ሁሉ ደግሞ ሁሉን በመውደድ ፍጹማን እንድንሆን ይህ ሕግ ግድ ይለናል፡፡ ማቴ. 5፥43-46 "ወስብሐት ለእግዚአብሔር። (ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ሽኖዳ ሳልሳዊ) (ሕግጋተ እግዚአብሔር ገጽ 211-212)

photo content

🍂በዓለ ሢመቱ ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ዑራኤል🍂 🌾ሊቀ መላእክት ቅዱስ ዑራኤል ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት አንዱ በመሆን ከፍጥረተ ዓለም ጀምሮ በመብረቅና በነጎድጓድ ላይ በጥር ፳፪ ቀን የተሾመ መልአክ ነው፡፡ ➡በመጽሐፈ ሄኖክ እንደተገለጸው መባርቅት ለጥጋብና ለበረከት እንዲበርቁ ነጎድጓድም ለሰላም እንዲሆን ያሠማራል፡፡ ለነቢዩ ሄኖክም የሰማይን ምሥጢርና ሰማያዊውን ዕውቀት ሁሉ የገለጸለት፤ የፀሐይን፣ የጨረቃን፣ የከዋክብትንና የሰማይ ሠራዊትን ብርሃንን የሚመራው ይኸው ገናና መልአክ ነው፡፡ (ሄኖ.፳፰፥፲፫) 🌾ዑራኤል ማለት ትርጉሙ ‹‹የብርሃን ጌታ፣ የአምላክ ብርሃን›› ማለት በመሆኑም መድኃኔዓለም ክርስቶስ ለዓለም ቤዛ ሆኖ በተሰቀለ ጊዜ ክቡር ደሙን በብርሃን ጽዋ ተቀብሎ በብርሃነ መነሳንስ በዓለም ላይ የረጨ መልአክ ነው፡፡ 🌾ለነቢዩ ዕዝራ ሱቱኤል ጽዋ ጥበብን ያጠጣ እንዲሁም ሰማያዊውን ምሥጢር እና ዕውቀት ተሠውሮበት ለነበረው ለኢትዮጵያዊው ሊቅ ለአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫም በእመቤታችን ትእዛዝ ጽዋ ጥበብን አጠጥቶ ሰማያዊውን ምሥጢር የገለጠለት ቅዱስ ዑራኤል ነው፡፡ (ዕዝ.፪፥፩) 🌾የብርሃን እናቱ ድንግል ወላዲተ አምላክን ከልጇ ከአምላካችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ስትሰደድ መንገድ ወደ ግብጽ እና ወደ ሀገራችንን ኢትዮጵያ እየመራ አምጥቷቸዋል፡፡ 🌾አምላካችን እግዚአብሔር የቸርነት ዝናም በምድራችን ላይ ያዘንብ ዘንድ እንዲሁም የእርሻችንን አዝመራ በዝናም አብቅሎ በፀሐይ አብስሎ ለምግብነት እንዲበቃ ከፈጣሪ ዘንድ ምሕረትን የሚለምን መልአኩ ቅዱስ ዑራኤል እንደመሆኑ በሀገራችን ኢትዮጵያ አብዛኞቹ ቅዱሳት ገዳማት በቅዱስ ዑራኤል መሪነት ተመሥርተዋል፡፡ ➡ድርሳኑ ላይ የማይጠቅሳቸው የሀገራችን የከበሩ ቅዱሳት ገዳማትና ቅዱሳን ነገሥታት የሉም፡፡ 🌾የሊቀ መላእክት ቅዱስ ዑራኤል አማላጅነትና ተራዳኢነት አይለየን፤ አሜን፡፡

"አስተርእዮን በወላይታ ኦቶና ማርያም። "Live ከወላይታ ይከታተላሉ። "በዚያውም Subscribe እያደረጋችሁ። https://www.youtube.com/live/GC-EjhJsd48?si=W3gR8oUrCHYN1t93

photo content

🌾አስተርእዮ ማርያም🌾 🍂አስተርእዮ ማለት መታየት፣ መገለጥ ማለት ነው። ቃሉ አስተርአየ ታየ፣ ተገለጠ ከሚለው የግዕዝ ግሥ የተገኘ ነው። ➡ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በገባው ቃል ኪዳን መሠረት በሥጋ የተገለጠበት(የታየበት) ፣ አንድነት ሦስትነቱም የተገለጠበት ወቅት በመሆኑ ከልደት በዓል እስከ ጥር መጨረሻ በሙሉ ዘመነ አስተርእዮ በመባል ይታወቃል። የእመቤታችን በዓለ ዕረፍት በዘመነ አስተርእዮ ውስጥ ስለሚከበር “አስተርእዮ ማርያም” ተብሏል። 🍂ልቡናዋ በይኩነኒ የጸና ንጽሐ ሥጋ ፣ ንጽሐ ነፍስ ፣ ንጽሐ ልቡና አስተባብራ የያዘች ወላዲተ አምላክ ምንም እንኳን የአምላክ እናት ብትሆንም ሞተ ሥጋ ለሁሉም ዕጣ ፈንታ በመሆኑ በቃል መነገሩ በልብ መታሰቡ ከፍ ከፍ ይበልና ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ “ተንሥኢ ወንዒ” የነፍሴ ደስታ የኾንሽ ውድ እናቴ ሆይ ተነሥተሽ ወደ እኔ ነዪ (መኃ ፪፥፲-2v10) ብሏታል። 🌾ሞታ ለማርያም የዐጽብ ለኲሉ🌾 🍂ቅዱስ ዳዊት “ነኪር ነገሩ በእንቲአኪ ሀገረ እግዚአብሔር” (መዝ.፹፮፥፫ )እግዚአብሔር ማህጸንሽን ከተማ አድርጎ ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን የኖረብሽ ሆይ ስለ አንቺ የተነገረው የተደረገው ነገር ዕጹብ ድንቅ ነው እንዳለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የአምላክ እናት ሆና ማረፏ ይደንቃል። ➡ታላቁ የቤተክርስቲያናችን አባት ቅዱስ ያሬድ ሞቷ የሚያስደንቅ መሆኑን «ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ ሞታ ለማርያም የዐጽብ ለኲሉ፤ ሞት ለማናቸውም ሰው ሁሉ የተገባ ነው የማርያም ሞት ግን ሁሉን ያስደንቃል» በማለት ገልጾታል። 🌾ሞት በጥር ነሐሴ መቃብር🌾 🍂የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ሞትና ትንሣኤ በነገረ ማርያም አበው እንደሚያስረዱት ዕረፍቷ በጥር ፳፩ እሑድ ነው ። አባቶቻችን በጾመ ፍልሰታ ውዳሴ ማርያም ቅዳሴ ማርያም ሲተረጉሙ የእረፍቷን ነገር እንዲህ ብለው ይተርካሉ። ➡የእረፍቷስ ነገር እንደምን ነው ቢሉ ስድሳ አራት ዓመት በዚህ ዓለም ኖራ ጥር ፳፩ በእሑድ ቀን ጌታ እልፍ አዕላፋት መላእክቱን አስከትሎ መጥቶ እናቴ ሆይ ከዚህ ዓለም ድካም ላሳርፍሽ መጣሁ አላት። ➡ልጄ ሰማይና ምድር የማይወስኑህ ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን በማህጸኔ ተሸክሜ በድንግልና ወልጄህ እሞታለሁን? አለችው። በሲዖል የሚሰቃዩ ነፍሳትን አሳይቶ እናቴ ሆይ ሞትሽ ለእነዚህ ቤዛ ይሆንላቸዋል አላት። እሊህን ከማርክልኝስ ይሁን አለችው። ቅድስት ሥጋዋን ከቅዱስ ነፍሷ ለይቶ በቃለ አቅርንት በዝማሬ መላእክት አሳረጋት። ➡ደቀመዛሙርቱንም ከያሉበት በደመና ጠቅሶ ካለችበት አድርሶ እመቤታችሁን ስጋዋን በክብር አሳርፉ አላቸው። ሐዋርያት በአጎበር አድርገው ወደ ጌቴሰማኒ ይዘው ሲሄዱ አይሁድ ቀድሞ ልጇን ተነሳ ዐረገ እያሉ ሲያውኩን ይኖራሉ አሁን ደግሞ እሷን ተነሳች ዐረገች እያሉ ሊያውኩን አይደለምን በእሳት እናቃጥላታለን ብለው ተነሱ። ➡ታውፋንያ የሚባል አይሁዳዊ ተራምዶ አጎበሩን ጨበጠው። መልአክ መጥቶ በሰይፍ ሁለት እጁን ቀጣው ከአጎበሩ ተንጠልጥሎ ቀረ። በድያለሁ ማሪኝ ብሎ ቢማጸናት እጁ ተመልሶለታል። ከዚህ በኋላ ዮሐንስን ጨምሮ በደመና ነጥቆ ከገነት አግብቶ ከዕፀ ሕይወት ሥር አኖራት። 🍂ቅዱስ ዮሐንስን እንደምን ሆነች አሉት ከገነት ከዕፀ ሕይወት ሥር አለች አላቸው ቅዱስ ዮሐንስ አይቶ እኛ ሳናይ ብለው በነሐሴ መባቻ ጾም ጀመሩ ሁለት ሱባዔ ሲፈጸምም እሑድ አምጥቶ ሰጥቷቸው ቀብረዋታል በሶስተኛው ቀን ማክሰኞ “ከመ ትንሳኤ ወልዳ” እንደ ልጇ ተነሥታለች። 🍂ቅዱስ ቶማስ አልነበረም ደመና ጠቅሶ ከሀገረ ስብከቱ ሲመጣ ስታርግ አገኛት ቀድሞ የልጅሽን ትንሳኤ ሳላይ ቀረሁ ዛሬም ደግሞ ያንችን ትንሳኤ ሳላይ ቀረሁን ብሎ “ወፈቀደ ይደቅ እምደመናሁ” ከሀዘኑ የተነሳ ሊወድቅ ወደደ እመቤታችንም አይዞህ አትዘን እሊያ ትንሳኤየን ዕርገቴን አላዩም አንተ አይተሃል ተነሣች ዐረገች ብለህ ንገራቸው ብላ የያዘችውን ሰበን ሰጥታ ሰደደችው። ➡ከዚህ በኋላ ሂዶ የእመቤታችን ነገር እንደምን ሆነ አላቸው አግችተን ቀበርናት አሉት ሞት በጥር በነሐሴ መቃብር ተው ይህ ነገር አይመስለኝም አላቸው። 🍂ቅዱስ ጴጥሮስ አንተ እንጅ ልማድህ ነው አንተ ብቻ ተጠራጥረህ አትቀርም ሰውን ሁሉ ስታጠራጥር ትኖራልህ ብሎ ተቆጥቶ ወደ መቃብሩ ሂዶ ቢከፍተው አጣት ደንግጦ ቆመ ሐዋርያው ቶማስም አታምኑኝም ብየ እንጅ እመቤታችንስ ተነሣች ዐረገች አላቸው የያዘውንም ሰበን ሰጣቸው ለበረከትም ተካፍለውታል። ➡በዓመቱ ሐዋርያት ቅዱስ ቶማስ ትንሣኤሽን ዕርገትሽን አይቶ እኛ ሳናይ ብለው ጾም ጀመሩ በ፲፮ኛው ቀን እመቤታችንን መንበር አድርጎ ቅዱስ ጴጥሮስን ካህን ዘይትራድኦ ቅዱስ እስጢፋኖስን ሠራዒ ዲያቆን አድርጎ በዚያው ላይ ቀድሶ አቁርቧቸዋል። ቤተክርስቲያንም ይህንን መታሰቢያ አድርጋ በየዓመቱ ታከብረዋለች። 🌾ሰአሊ ለነ ቅድስት🌾 ➡የኃጥአንን ለቅሶና ሐዘን አይተሽ ስለእነርሱ ድኅነት(መዳን) ዕረፍትሽን በሀሴት የተቀበልሽ እመቤታችን ሆይ ሐዋርያት በሱባዔ ትንሣዔሽን ለማየት በቅተዋልና እኛም በዓለ ዕረፍትሽን አክብረን ልጅሽ በሰጠሽ ቃል ኪዳን በቀኙ እንቆም ዘንድ ለምኝልን። አሜን።🙏 Deacon Biruk Bokicha

photo content

🍂ዝርወተ አጽሙ ለቅዱስ ጊዮርጊስ🍂 🌾ጥር ፲፰ ቀን በዚህች ዕለት የሊቀ ሰማዕታት ፣ የፋርሱ ፀሐይ ፣የቤሩቱ ኮከብ፣ የልዳው ሰማዕት ፣የኢትዮጵያ ገበዝ የቅዱስ ጊዮርጊስ የዝርወተ አጽሙ መታሰቢያ በዓል ነው። ➡ቅዱስ ኤፍሬም በውዳሴ ማርያም ላይ ሰማዕታት የዚህን ዓለም ጣዕም ናቁ ስለእግዚአብሔር ክብርና ስለ መንግስተ ሰማያትም መራራ ሞትን ታገሱ እንዲል ቅዱስ ጊዮርጊስ ለሰባት ዓመታት እጅግ ዘግናኝ መከራና ግፍን ተቀበለ ሥጋው በእሳት ተቃጠለ ፣አጥንቱ ተፈጨ በይድራስ ተራራ ላይም ተበተነ —-መንክር እግዚአብሔር በላዕለ ቅዱሳኒሁ። 🍂በአማን እንኳን ለሊቀ ሰማዕት ለቅዱስ ጊዮርጊስ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሰን።🍂 🌾የሰማዕታት ሞገሳቸው የሆነ ታላቅና ክቡር ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስ ከ፯ ዓመታት ስቃይ በኋላ ሰማዕት ሆኗል:: ➡ይህስ ጥንተ ነገሩ እንደምን ነው ቢሉ:- "ቅዱሱ የተወለደው #ከአባቱ_ዘረንቶስ (አንስጣስዮስ) እና #ከእናቱ_ቴዎብስታ የድሮው ፋርስ ግዛት ፍልስጥኤም (ልዳ) ውስጥ ነው:: የተባረኩ ወላጆቹ ክርስትናን ጠንቅቀው አስተምረውት አባቱ ይሞታል:: 🌾ቅዱስ ጊዮርጊስ ፳ ዓመት ሲሞላው የአባቱን ስልጣን እጅ ለማድረግ ሲሔድ የቢሩት የሊባኖስ ሰዎች ዘንዶ/ደራጎን ሲያመልኩ አገኛቸው:: እርሱ ግን የከተማውን ሕዝብ አስተምሮ: አሳምኖ: ደራጎኑንም በፈጣሪው ኃይል ገድሎ መንገዱን ቀጥሏል:: 🌾ቅዱስ ጊዮርጊስ ወደ ዱድያኖስና ፸ ነገሥታት ዘንድ ሲደርስ ክርስቶስ ተክዶ ለጣዖት ይሠገድ ነበር:: በዚያች ሰዓት ድንግል እመቤታችን ወደ ሰማዕቱ መጥታ መከራውንና ክብሩን ነገረችው:: እርሱም በክርስቶስ ስም መሞት ምርጫው ነበርና ከእመቤታችን ተባርኮ ወደ ምስክርነት አደባባይ (ዐውደ ስምዕ) ደረሰ። 🌾ከዚያም ለተከታታይ ፯ ዓመታት ብዙ ጸዋትወ መከራዎችን ተቀበለ፣ ፫ ጊዜ ሞቶ ፫ ጊዜ ተነሳ:: ከሰው ልጅ የተፈጥሮ ትዕግስት በላይ የሆነ ስቃይን ስለ ቀናች ሃይማኖት ሲል በመቀበሉ የሰማዕታት አለቃቸው: ፀሐይና የንጋት ኮከብ በሚል ይጠራል:: “ተውላጠ ጻማሁ ወሕማሙ: ዘተለዐለ ሞገሰ ስሙ” እንዲል መጽሐፍ:: 🌾ከ፯ ዓመታት መከራ በኋላም ከብዙ ተዓምራት ጋር ተሰይፎ ደም: ውሃና ወተት ከአንገቱ ፈሷል:: ፯ አክሊላትም ወርደውለታል:: 🍂ዝርወተ ዓጽሙ🍂 "ይህቺ ዕለት ለሰማዕቱ ‘ዝርወተ አጽሙ’ ትባላለች:: በቁሙ ‘#አጥንቱ_የተበተነበት’ እንደ ማለት ነው:: 🌾ቅዱስ ጊዮርጊስን ለዘመናት በብዙ ስቃያት ሲያስጨንቁት ኖረው በጽናቱ አሸነፋቸው:: 70 ነገሥታትን ከነ ሠራዊታቸው ከማሳፈሩ ባሻገርም በርካታ (በመቶ ሺ የሚቆጠሩ) አሕዛብን ማርኮ ለሰማዕትነት አበቃ:: 🌾በዚህ የተበሳጨ ዱድያኖስም ኮከበ ፋርስ ቅዱስ ጊዮርጊስን እንዲቆራርጡት አዘዘ:: ወታደሮቹም ቅዱሱን ቆራርጠው በብረት ምጣድ ላይ ጠበሱት። ያለ ርሕራሔም አካሉን አሳረሩት። ቀጥለውም ፈጭተው አመድ አደረጉት። በአካባቢው ወደ ነበረው ትልቅ ተራራ ጫፍ (ደብረ ይድራስ) ወጥተውም በነፋስ በተኑት:: “ሐረድዎ ወገመድዎ: ወዘረዉ ሥጋሁ ከመ ዓመድ” እንዲል:: (ምቅናይ) 🌾እነርሱ ይህንን ፈጽመው ዘወር ሲሉ ግን የቅዱሱ ዓጽም ባረፈባቸው ዛፎች: ቅጠሎችና ድንጋዮች ሁሉ “ቅዱስ ጊዮርጊስ ሊቀ ሰማዕታት” የሚል ጽሑፍ ተገኘ:: ስለዚህም ይህቺ ዕለት ቅዱሱ አለቅነትን የተሾመባት ናት ማለት ነው:: 🌾ወዲያው ግን ኃያል ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስ ከተበተነበት ተነስቶ ወታደሮችን አገኛቸውና “በክርስቶስ እመኑ” ብሎ: አስደንቆ ወደ ሕይወት መራቸው፣ ፸ ው ነገሥታት ግን አፈሩ። ወስብሐት ለእግዚአብሔር፣ የእመቤታችን የድንግል ማርያም አማላጅነት፤የጻድቃን የሰማዕታት ተራዳኝነት አይለየን አሜን። (dn_biruk_Bokicha)

#አስተርእዮን_በኦቶና_ደብረ_ፅዮን_ቅማርያም (ወላይታ ሶዶ) "እርሱም መልሶ፦ ሰው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ #ቃል ሁሉ እንጂ #በእንጀራ_ብቻ አይኖርም ተብሎ ተጽፎአል አለው።” — ማቴዎስ 4፥4 "በ
#አስተርእዮን_በኦቶና_ደብረ_ፅዮን_ቅማርያም (ወላይታ ሶዶ) "እርሱም መልሶ፦ ሰው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ #ቃል ሁሉ እንጂ #በእንጀራ_ብቻ አይኖርም ተብሎ ተጽፎአል አለው።” — ማቴዎስ 4፥4 "በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በወላይታ ሀ/ስብከት በኦ/ደ/ፅዮን ቅ/ማርያም ና ቅ/በዓለወልድ ቤተክርስቲያን... "የስብከት እና ዝማሬ ማዕበል እንደጅረት ሚፈስበት ታላቅ ጉባኤ ሊካሄድ እንሆ አንድ ቀን ቀረው። "የቤተክርስቲያንን አስተምሕሮት በአንክሮት የሚያስተምሩ ሰባኪያን ወንጌል እንዲሁም በዝማሬ የሚያገለግሉን አንጋፋ ዘማሪያን የሚገኙበት የማይቀርበት ታላቅ ጉባኤ። "የደብሩ ፈለገ ህይወት ሰንበት ት/ቤት 37ተኛ የምሥረታ በዓል ይከበራል። "የነገ ሰው ይበለን 🙏 Deacon Biruk Bokicha

"ዕለት የሠጠህ እርሱ ለዕለት የሚበቃህንም ይሰጥሃል። (ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ) "ዛሬ በዓለ ዕረፍታቸው ይታሰባል በረከታቸው ይደርብን።አሜን 🙏
"ዕለት የሠጠህ እርሱ ለዕለት የሚበቃህንም ይሰጥሃል። (ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ) "ዛሬ በዓለ ዕረፍታቸው ይታሰባል በረከታቸው ይደርብን።አሜን 🙏

"በዚችም ዕለት የከበረ ሕፃን ቂርቆስ እናቱ ብፅዕት ኢየሉጣ ዳግመኛ ለከበረ ሕፃን ቂርቆስ ማኀበር የሆኑ ዐሥራ አንድ ሺህ አራት ሰዎች በሰማዕትነት ሞቱ። "በረከታቸው ከኛ ጋር ትሁን።አሜን🙏
"በዚችም ዕለት የከበረ ሕፃን ቂርቆስ እናቱ ብፅዕት ኢየሉጣ ዳግመኛ ለከበረ ሕፃን ቂርቆስ ማኀበር የሆኑ ዐሥራ አንድ ሺህ አራት ሰዎች በሰማዕትነት ሞቱ። "በረከታቸው ከኛ ጋር ትሁን።አሜን🙏

ያሳዝናል ❗ “የእግዚአብሔርም ታቦት በአቢዳራ ቤተሰብ ዘንድ በቤቱ ውስጥ ሦስት ወር ተቀመጠ፤ እግዚአብሔርም የአቢዳራን ቤትና ያለውን ሁሉ ባረከ።” (1 ዜና 13፥14) "እንግዲህ እግዚአብሔር በታቦቱ (በማደርያው) ሆኖ የአቢዳራን ቤት ባርኩዋል። "ስለዝህ ቡናከብረው መልሶ ያከብረናል ባናከብረው መልሶ እንደ ሜልኮል ያዋርደናል። "የአባታችንን የርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረኪዳን አጠር ያለ የማያዳግም መልሳቸውን አድምጡ። "ሰላመ እግዚአብሔር አይለየን። ሼር አድርጉላቸው❗

photo content

#ከእርሱ_ጋር_ኀብረት_ፍጠሩ! 🌾እግዚአብሔርን ለማወቅ ለመውደድ ከእርሱ ጋር መተባበር አለባችሁ። ንባብ ብቻውን በቂ አይደለም። ➡ንባብ የሚከፍትላችሁ መዝጊያውን ብቻ ነው። ❗ 🌾ከዚህ በኋላ እናንተ ትገቡና ከእግዚአብሔር ጋር ትኖራላችሁ ከዚያም ከእርሱ ጋር መኖር ጣፋጭ መሆኑን እናንተ ራሳችሁ ታውቃላችሁ። 🌾ስለሆነም ከእግዚአብሔር ጋር የሚሆን ሕይወትን ትሞክሩታላችሁ እርሱ በሁሉም ነገር ውስጥ ተካፋይ እንዲሆንም ትፈቅዳላችሁ። 🌾እንደ ባልጀራችሁ አድርጋችሁ ልትወዱት ሞክሩ አሳቦቻችሁንና ሚስጥሮቻችሁን ለእርሱ ንገሩት። 🌾ከዚህ በኋላ የሚሆነውን ጠብቁና እርሱ ምን ያህል ከእናንተና ለእናንተ እንደሚሰራ ታያላችሁ። 🌾ከዚህ በተጨማሪ በአሳቦቻችሁና በተሰጥኦዎቻችሁ ከመተማመን የበለጠ በእርሱ ላይ መተማመንን ታውቃላችሁ። (አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ)

photo content