1 269
Subscribers
+124 hours
+37 days
+2330 days
Posts Archive
"ክርስቲያናዊ ቤተሰብ"
👉 "My father didn't tell me how to live; he lived, and let me watch him do it."
✍ "አባቴ እንዴት መኖር እንዳለብኝ አልነገረኝም ይልቅስ እርሱ ሲኖር አሳይቶኝ እኔ እንድመለከተው ፈቀደልኝ"
👉 ታዋቂው አሜሪካዊ ደራሲና የጋዜጠኝነት ዘገባ መጽሐፍት ጸሐፊ ክላረንስ ቡዲንግተን ኬላንድ (Clarence Budington Kelland) በ1963 ዓ.ም (እ.ኤ.አ. 1963)Reader's Digest በተሰኘው ታዋቂ መጽሔት የሜይ (May) ዕትም ላይ እንደፃፈው።
ዘመናችን አስቸጋሪ ቢሆንም እግዚአብሔርን የምናምን ሁላችን እንበርታ። የሚያሰነካክሉ ነገሮች ቢኖሩም በማለዳ እግዚአብሔር ያዘጋጀውን መና ለመልቀም አናርፍድ። ለጸሎት ለምስጋና በህብረት ለመትጋት ለምድረበዳው ጉዞ የሚያስፈልገንን ስንቅም ሆነ ትጥቅ ለመቀበል እንዲሁም በጉዞው እንበርታ!!! በጌታ ፀጋ ደግሞ እርስ በርስ እንበረታታ!!! የሚረዳን እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ነው!!!!
እግዚአብሔርን ተጠግተን አርፈናል ። እርሱን የተጠጋ አያፍርምና!!! የተጠጋነውን ወይም የምንጠጋውን እንወቅ!!!
ሰዎች ሆይ ኢየሱስ ያድናል እመኑ!
👉"ኃጢአተኞችን ሊያድን ክርስቶስ ኢየሱስ ወደ ዓለም መጣ የሚለው ቃል የታመነና ሁሉ እንዲቀበሉት የተገባ ነው፤ (1ጢሞ1:15)
✍ አንድ የታመመ ሰው መታመሙን ባያውቅ እንኳ በሽታው በእርሱ ውስጥ እንዳለ የታወቀ ነው። በኢየሱስ ያላመነ ሰውም ኃጢአተኛ እንደሆነ ባያውቅም እንኳ ኃጢአት በእርሱ ውስጥ አለ፤ እንዲሁም አንድ ሰው ሕመምተኛ መሆኑን እያወቀ መታመሙን ባይቀበልና ባይታከም የበለጠ እየታመመ ይሄዳል።
✍ ኃጢአተኛ መሆኑን እያወቀ ራሱን በማዋረድ ኃጢአተኝነቱን አምኖ ንስሐ መግባት የማይፈልግ ሰውም እንዲሁ ኃጢአቱ ከፍተኛ ነው። አንድ ሕመምተኛ በሽታውን አውቆ ወደ ሐኪም ከሄደ በኋላ የታዘዘለትን መድኃኒት ለመውሰድ ፈቃደኛ ሳይሆን ቢቀር ደግሞ ከበሽታው መዳን አይችልም።
✍ ኃጢአተኝነቱን ከተቀበለ በኋላ ከኃጢአት የሚያድነው ብቸኛው መድኃኒት ኢየሱስ መሆኑን የሚያውቅ ሰውም ኢየሱስን በእምነት ሳይቀበለውና ሳይከተለው ከዘላለም ሞት መዳን አይችልም።
✍ ኃጢአተኛ መሆንና ኃጢአትን ማድረግ የወደቀው ሰው ሁሉ ባሕርይ ነው። ሆኖም በኢየሱስ ማመን ከኃጢአት ሁሉ ያድናል፤ በኢየሱስ አለማመን ግን ሰዎች በኃጢአት እንዲኖሩና እንዲሞቱ ያደርጋል።
👉 እኔ እንደሆንኩ ባታምኑ በኃጢአታችሁ ትሞታላችሁ» /ዮሐ. 8:24/።
👉 «ስለኃጢአት በእኔ ስለማያምኑ ነው» /ዮሐ. 16:10/።
*በኢየሱስ አለማመን ኃጢአት ነው!*
👉 ከእውነት ጋዜጣ ቁጥር 25 የተወሰደ
ሰው የሆነው #ኢየሱስ ዘላለማዊ ቃል(The Eternal Word)ነው፤ እርሱ እግዚአብሔር ነው ፥ በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ(ዮሐ1፥1፣14)። ድንቅ መገለጥ!
✍ በሺሁ ዘመን
በሺሁ ዘመን………
በነጋሪት ፈንታ ከበሮ ይመታል
ልጅ በእፉኝት ጉድጓድ ይጫወታል
አልማዝና ዕንቁም ዋጋቸው ይረክሳል
ይልቅስ የሰው ልጅ እጅግ ይወደዳል
በሺሁ ዘመን…………
ሰላም ይሠፍናል በከዋክብት ደምቆ
ከምድር ማዕዘናት የጦር ጥላ ርቆ
ጽድቅ ይነግሣል በዓመፅ ፈንታ
አይኖርም ወቀሳ አይኖርም ቅሬታ
በሺሁ ዘመን ……
ካባዎች ወልቀው ተሽሮ ዘውዱ
የጌታዎች ጌታ ይነግሣል በምድሩ
የወርቁም ምስል እብቅ ሆኖ ጠፍቶ
የክርስቶስ መንግስት ይጸናል በርትቶ
✍በኮሬብ አለማየሁ (፪ሺ፲፰ ዓ.ም)
