ፖሊ ግቢ ጉባኤ
Open in Telegram
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን፤ በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ የፖሊ ግቢ ጉባኤ መርሃግብራትና፤ ወቅታዊ የግቢ ጉባኤው መረጃዎች የሚቀርቡበት ቻናል ነው። ለሃሳብና አስተያየቶቻችሁ ☝️👉 @mkpolybot ለመድሎተ አሚን ጥያቄዎቻችሁ ☝️👉 @NikiyamkBot መጻሕፍትን ለማንበብ ☝️👉 @polylibrary ላይ ያስቀምጡልን።
Show more3 574
Subscribers
+224 hours
+47 days
-230 days
Posts Archive
3 574
እንኳን አደረሳችሁ 🙏
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ነሐሴ ሃያ አንድ በዚች ቀን አምላክን በሥጋ የወለደች የእመቤታችን
ድንግል ማርያም የበዓሏ መታሰቢያ ነው :: እርሷ ስለእኛ ሁልጊዜ ትማልዳለችና ::
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን የሕይወትና የድኅነት ወደብ ትሆነን ዘንድ እርሷን እናቱን ስለሰጠን በረከቷም በሁላችን የክርስቲያን ወገኖች ላይ ይደር ለዘላለሙ አሜን ::
ሰላም ለኪ ለዘእምኔኪ ወጽአ :: ዘያድኅን እግዚእ እንስሳ ወሰብአ :: በቍስለ ኃጢአት ሥጋየ አመ በኁበኁ ወጽአ::ኢረከብኩ ማርያም እንበሌኪ አሐደ ባቃዐ::አመ ኢገበርኪ ሊተ ሐዲሰ መልክዐ ::ስንክሳር ዘወርኀ ነሐሴ ፳፩ መፅሐፍትን በማንበብ መንፈሳዊ ዕውቀትዎን ያሳድጉ!!! ────────── ✦ ────────── ፖሊ ግቢ ጉባኤ 📩@polygbigubaecommentbox ለሃሳብ አስተያየትዎ 📚@polylibrary መፅሐፍትን ለማንበብ 📖@polytmhirt ለኮርስ 📷@mkpoly_gallery የፎቶ እና ቪዲዮ ማኅደር ────────── ✦ ────────── Telegram | Instagram
3 574
ሞት በጥር በነሀሴ መቃብር እነዴት ይሆናል ቢሉ?🤔ቅዱሳን ሐዋርያት የእመቤታችንን የከበረ ሥጋዋን ገንዘውና ከፍነው ለማሳረፍ ወደ ጌቴሴማኒ መካነ ዕረፍት ይዘው ሲሄዱ አይሁድ በቅንአት መንፈስ ተነሣሥተው
ቀድሞ ልጇን በሦስተኛው ቀን ከሙታን ተነሣ፤ በዐርባኛው ቀን ወደ ሰማይ ዐረገ እንደገናም ተመልሶ ይህን ዓለም ለማሳለፍ ይመጣል እያሉ ሲያውኩን ይኖራሉ፡፡ አሁን ደግሞ እርሷንም እንደ ልጇ ተነሣች፣ ዐረገች እያሉ ሲያውኩን ሊኖሩ አይደለምን?ኑ ተሰብሰቡና ሥጋዋን በእሳት እናቃጥላት ብለው ተማክረው መጡ፡፡ ታውፋንያ የሚባል አይሁዳዊ የከበረ ሥጋዋን የተሸከሙበትን የአልጋ ሸንኮር በድፍረት ያዘ፡፡ የእግዚአብሔር መልአክ በእሳት ሰይፍ ሁለት እጆቹን ቆረጣቸው፡፡ እጆቹ ተንጠልጥለው ከቆዩ በኋላ በእውነት የአምላክ እናት ናት በማለት ስለ አመነ እጆቹ ተመልሰው እንደነበሩ ሆነውለታል፡፡ ከዚህ በኋላ መልአከ እግዚአብሔር የእመቤታችንን የከበረ ሥጋ ከሐዋርያው ዮሐንስ ጋር ነጥቆ ወስዶ በገነት ከዕፀ ሕይወት ሥር አስቀመጠው፡፡ ቅዱስ ዮሐንስም ከጥቂት ጊዜ በኋላ ወደ ሐዋርያት ሲመጣ የእመቤታችንን የከበረ ሥጋ በገነት መኖሩን ነገራቸው፡፡ ሐዋርያትም የእመቤታችንን የከበረ ሥጋ አግኝተው ለመቅበር በነበራቸው ምኞትና ጉጉት ዮሐንስ አይቶ እኛ እንዴት ሳናይ እንቀራለን ብንጠየቅስ ምን እንመልሳለን በማለት በነሐሴ አንድ ቀን ሱባኤ ጀምረው ሲጾሙና ሲጸልዩ ከሰነበቱ በኋላ በ14 ቀን ጌታችን የእመቤታችንን ትኩስ የከበረ ሥጋ አምጥቶ ስለሰጣቸው በታላቅ ዝማሬ፣ በውዳሴ ወስደው ቀድሞ በተዘጋጀው መካነ ዕረፍት በጌቴሴማኒ ቀበሯት፡፡ የእመቤታችን የቀብር ሥነ ሥርዐት በተፈጸመ ጊዜ ከ12ቱ ሐዋርያት አንዱ የሆነው ቅዱስ ቶማስ አልነበረም፡፡ ከሀገረ ስብከቱ በደመና ተጭኖ ወደ ኢየሩሳሌም ሲመጣ፣ እመቤታችን በተቀበረች በሦስተኛው ቀን እንደ ልጇ ትንሣኤ ተነሥታ ስታርግ ያገኛታል፡፡ ቀድሞ የልጅሽን አሁን ደግሞ የአንቺን ትንሣኤ ሳላይ ቀረሁ ብሎ ቢያዝን እመቤታችን ከእርሱ በቀር ሌሎች ሐዋርያት ትንሣኤዋን እንዳላዩ ነግራው ቅዱስ ቶማስን አጽናናችው፡፡ ሄዶም ለሐዋርያት የሆነውን ሁሉ እንዲነግራቸው አዝዛው ለምልክት ይሆነው ዘንድ የተገነዘችበትን ሰበኗን ሰጥታው ወደ ሰማይ ዐርጋለች፡፡ ቅዱስ ቶማስም ሐዋርያት ወደ አሉበት ኢየሩሳሌም በደረሰ ጊዜ የእመቤታችን ነገር እነዴት ሆነ? ብሎ ቢጠይቃቸው፤ እመቤታችንን እኮ ቀበርናት ብለው ነገሩት፡፡ እርሱም ዐውቆ ምስጢሩን ደብቆ
አይደረግም ሞት በጥር በነሐሴ መቃብር እንደምን ይሆናል?»አላቸው፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ አንተ መጠራጠር ልማድህ ነው፡፡ ቀድሞ የጌታን ትንሣኤ ተጠራጠርክ አሁንም አታምንም ብሎ የእመቤታችን መካነ መቃብር ሊያሳዩት ይዘውት ሔዱ፡፡ መቃብሩን ቢከፍቱ የእመቤታችንን የከበረ ሥጋ አጡት፤ ደነገጡም፡፡ በዚህ ጊዜ ቅዱስ ቶማስ አታምኑኝም ብዬ ነው እንጂ እመቤታችንስ ተነሥታ ዐርጋለች ብሎ የሆነውን ሁሉ ተረከላቸው፡፡ ከዚያም ምልክት እንዲሆን የሰጠችውን ሰበኗን አሳያቸው፡፡ እነርሱም ማረጓን አምነው ሰበኗን ለበረከት ከተከፋፈሉ በኋላ ወደየአህጉረ ስብከታቸው ሄዱ፡፡ ከተመችዎ ለጓደኞችዎ ሸር ያድርጉ ! ────────── ✦ ────────── ፖሊ ግቢ ጉባዔ 📩@polygbigubaecommentbox ለሃሳብ አስተያየትዎ 📚@polylibrary መፅሐፍትን ለማንበብ 📖@polytmhirt ለኮርስ 📷@mkpoly_gallery የፎቶ እና ቪዲዮ ማኅደር ────────── ✦ ────────── Telegram | Instagram
3 574
💥ደብረ ታቦር💥
"አሐደ ለከ ወአሐደ ለሙሴ ወአሐደ ለኤልያስ ንግበር ማኅደረ"ማቴ ፲፯፥፬ እንኳን ለታላቁ በዓል ለበዓለ ደብረ ታቦር በሰላም አደረሳችሁ!! እነሆ የፖሊ ግቢ ጉባኤ ይህንን ከዘጠኙ ዐበይት በዓላት መካከል አንዱ የሆነውን የደብረ ታቦር በዓል በታላቅ ድምቀት ያከብራል። ስለሆነም ሁላችሁ በግቢያችን እና ባህር ዳር አካባቢ ያላችሁ ኦርቶዶክሳዊያን ተማሪዎች በዓሉን አብረን በአንድነት እናክብር ስንል በክርስቶስ ፍቅር ጠርተናችኋል። "ታቦር ወአርሞንኤም በስመ ዚአከ ይትፌሥሁ" መዝ ፹፱፥፲፪ እርስዎ ሲመጡ ፣ ጓደኛዎን ኩሽ ይበሉት : በአንድነት በዓሉን እናክብር !!! ⏰ ሰዓት፡ ከምሽቱ 10:30 ጀምሮ 📅 ቀን፡ ዛሬ ነሐሴ 13 / 2018 ዓ.ም ⛪️ ቦታ፡ አቡዬ ግቢ ጉባኤ አዳራሽ ────────── ✦ ────────── ፖሊ ግቢ ጉባኤ 📩@polygbigubaecommentbox ለሃሳብ አስተያየትዎ 📚@polylibrary መፅሐፍትን ለማንበብ 📖@polytmhirt ለኮርስ 📷@mkpoly_gallery የፎቶ እና ቪዲዮ ማኅደር ────────── ✦ ────────── Telegram | Instagram
3 574
💥ደብረ ታቦር💥
"አሐደ ለከ ወአሐደ ለሙሴ ወአሐደ ለኤልያስ ንግበር ማኅደረ"ማቴ ፲፯፥፬ እንኳን ለታላቁ በዓል ለበዓለ ደብረ ታቦር በሰላም አደረሳችሁ!! እነሆ የፖሊ ግቢ ጉባኤ ይህንን ከዘጠኙ ዐበይት በዓላት መካከል አንዱ የሆነውን የደብረ ታቦር በዓል በታላቅ ድምቀት ያከብራል። ስለሆነም ሁላችሁ በግቢያችን እና ባህር ዳር አካባቢ ያላችሁ ኦርቶዶክሳዊያን ተማሪዎች በዓሉን አብረን በአንድነት እናክብር ስንል በክርስቶስ ፍቅር ጠርተናችኋል። "ታቦር ወአርሞንኤም በስመ ዚአከ ይትፌሥሁ" መዝ ፹፱፥፲፪ እርስዎ ሲመጡ ፣ ጓደኛዎን ኩሽ ይበሉት : በአንድነት በዓሉን እናክብር !!! ────────── ✦ ────────── ፖሊ ግቢ ጉባኤ 📩@polygbigubaecommentbox ለሃሳብ አስተያየትዎ 📚@polylibrary መፅሐፍትን ለማንበብ 📖@polytmhirt ለኮርስ 📷@mkpoly_gallery የፎቶ እና ቪዲዮ ማኅደር ────────── ✦ ────────── Telegram | Instagram
3 574
ተኩሳችሁት የማታውቁትን ጅራፍ ለማጮህ ዝግጁ ናችሁ? 💥
በዕለቱ ኢየሱስ ክርስቶስ ብርሃነ መለኮቱን በደብረ ታቦር ተራራ ሲገልጥ፣ ልጆቻቸው ወደ ኋላ የቀሩባቸው የተጨነቁ ወላጆች ሙልሙል ና ችቦ ይዘው በዚያ በሌሊት ሊፈልጓቸው ወጥተው ነበር።
እኛም ዛሬ በፖሊ ግቢ ጉባኤ የአብነት ትምህርት ለመማር ግቢ የቀረነው እህትና ወንድሞቻችሁ፣ በዓሉን ለማክበር ወደ እኛ ለሚመጡ ተማሪዎችና ኦርቶዶክሳውያን የሚሆን፡
◉ የትምህርት
◉ የቅኔ
◉ የመዝሙር እና
◉ የጭውውት ..........ሙልሙላችንን በኮባ እንደተጠቀለለ ትኩሱን ይዘንላችሁ ለመቅረብ ዝግጅታችንን ጨርሰናል!
እናንተም በቤታችሁ ሆናችሁ በረከቱ እንዳያልፋቹ ለዚህ ታላቅ የዝክር ዝግጅት ማካሄጃ የሚሆን የተወሰነ ገንዘብ ስለሚያስፈልገን
የእገዛ ጅራፋችሁን እንድታጮሁ እንፈልጋለን።ተኩሳቹት የማታውቁትን ጅራፍ ለማጮህ ዝግጁ ናችሁ ? እንግዲያውስ ከታች👇 ያለውን አካውንት እየተጫናችሁ 💳 CBE :
1000358173199
👤 ተስፋሁን ገድፍ እሸቴ
📲 Telegram :- ደብረ ታቦር (ስምዎን እና የላኩበትን Screen Shot እዚህ ይላኩልን)
የላካችሁትን የብር መጠን የሚያሳይ screenshot ስትልኩልን አካውንታችን "ጣጣጣጣ!" ብሎ እንዲጮህ አድርጉት! ድምፅ የሌለው ጅራፍ እኮ ጅራፍ አይደለም!😉 📍 ቦታ፡ አቡዬ ግቢ ጉባኤ አዳራሽ 📅 ቀን፡ ነሐሴ 13 / 2018 ዓ.ም ⏰ ሰዓት፡ ከምሽቱ 10:30 ጀምሮ ────────── ✦ ────────── ፖሊ ግቢ ጉባዔ 📩@polygbigubaecommentbox ለሃሳብ አስተያየትዎ 📚@polylibrary መፅሐፍትን ለማንበብ 📖@polytmhirt ለኮርስ 📷@mkpoly_gallery የፎቶ እና ቪዲዮ ማኅደር ────────── ✦ ────────── Telegram | Instagram
3 574
በመጨረሻም ደረሰ !!በየ አመቱ በድምቀት በግቢ ጉባኤያችን ለምናከብረው ከ፱ቱ የጌታችን ዓበይት በዓላት አንዱ ለሆነው መድህን ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ብርሃነ መለኮቱን ለወዳጆቹ ለሀዋርያት ጴጥሮስ ፣ ዮሀንስ እና ያዕቆብ እንዲሁም በብሔረ ህያዋን ካሉት ኤለያስን እና ከአለፉት ሙሴን ጠቅሶ ነገረ - መለኮትን ለገለፀበት ትልቁ የመገለጥ በዓል፤ ደብረ- ታቦር እንኳን በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን!!! አቤት ምን ተሠምቷቸው ይሆን ፤ ጌታን በግርማ መለኮቱ ማየት እንዴት ያለ መታደል ነው?...🤔 እኛም የእናንተው ወድሞች እና እህቶች የ2018 ዓ.ም የፖሊ ግቢ ጉባኤ አብነት ትምህርት ከራሚ ተማሪዎች ይህን ከጥንት ከአባቶችችን ሊቃውንት ጀምሮ ሲዋረስ የመጣውን ትውፊታችን ለማስቀጠል እነዚህን :- ➥ ትምህርት ➥ ቅኔ ➥ መዝሙር ➥ ጭውውት እና ሌሎችም አስተማሪ ፕሮግራሞች እያዘጋጀን ሽር ጉድ እያልን እንገኛለን ። እርስዎም የበረከቱ ተካፋይ እንዲሆኑ :- ለሚኖረው ድምቅ ያለ ቤተሰባዊ መርሃ ግብር ማስኬጃ የሚሆን ፤ ፈቃደኛ የሆናችሁ የቻላችሁትን በዚህ አካውንት በመላክ ስንል እናሳስባለን ። Account CBE:-
1000358173199
ተስፋሁን ገድፍ እሸቴ
Username : ደብረ ታቦር
በዚህ ሙሉ ስማችሁን እና screen shoot ይላኩልን ይደርሰናል
ለታሪክ ይቀመጣል!!
መልዕክቱን ለሁሉም ወንድሞች እና እህቶች አድርሱልን !!🏛ቦታ ፡ አቡዬ ግቢ ጉባኤ አዳራሽ 📅ቀን: 13/12/2018 ዓ.ም 🕰 ሰዓት ፡ 10፡30 - 12፡30 AM ────────── ✦ ────────── ፖሊግቢ ጉባኤ
3 574
እኔስ ቤቴ ናፈቀችኝ!!!😢
ቀኑ እየቀረበ ሲሄድ ትዝታዎቸ ተቀሰቀሱብኝ ናፍቆቴ ጨመረ በዕለቱ የሚካሄዱትን ሳስብ ሙልሙል ዳቦው ፣ ጠላው ፣ ቆሎው ፣ መዝሙሩ ፣ ጭውውቱ ኧረ ስንቱ ብቻ ለመግለጽ ቃል ያጥረኛል ።
ይህን ናፍቆት ልታስታግስ ውድ ግቢ ጉባዔያችን :-
➥ ትምህርት
➥ ቅኔ
➥ መዝሙር
➥ እና ሌሎች ፕሮግራሞችን አዘጋጅታ እኛን በመጠባበቅ ላይ ትገኛለች ።
ይህን ሁሉ ካረገችልን ከእኛ ምን ይጠበቃል ?😊
በባህር ዳር አካባቢ ለምትገኙ በዕለቱ በመገኘት ፣ መገኘት ላልቻላችሁ ደግሞ ለዝክርት ማዘጋጃ የሚሆን ከታች ባለው አካውንት የቻሉትን ድጋፍ በማድረግ የበረከቱ ተካፋይ ይሁኑ!!
እመሰ ረሳይኩኪ ቤተ ጉባዔ ለትርስዓኒ የማንየ ወይጥጋዕ ልሳንየ በጉርዔየ መዝ 136÷8💳ንግድ ባንክ:-
1000358173199
ተስፋዬ ገድፍ አባተ
Username :- ደብረ ታቦር በዚህ ስምዎትን እና
screen shoot ይላኩልን ።
መልዕክቱን ለጓደኞቻችሁ በማጋራት ይተባበሩን!!
⏱ቀን:- 13/12/2018 ዓ.ም
🏛ቦታ :- አቡዬ ግቢ ጉባዔ አዳራሽ
────────── ✦ ──────────
ፖሊግቢ ጉባኤ
📩@polygbigubaecommentbox ለሃሳብ አስተያየትዎ
📚@polylibrary መፅሐፍትን ለማንበብ
📖@polytmhirt ለኮርስ
📷@mkpoly_gallery የፎቶ እና ቪዲዮ ማኅደር
────────── ✦ ──────────
Telegram | Instagram3 574
ለምን የአብነት ተማሪዎች የደብረታቦር ዕለት ይዘክራሉ ? 🤔
በማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ ፲፯ ከቁጥር ፩-፱ ያለው የእግዚአብሔር ቃል :-
ከስድስት ቀንም በኋላ ÷ ጌታችን ኢየሱስም ጴጥሮስን፣ ያዕቆብን እና ወንድሙንም ዮሐንስን ይዞ ወደ ረዥም ተራራ ብቻቸውን አወጣቸው። መልኩም በፊታቸው ተለወጠ፤ ፊቱም እንደ ፀሓይ በራ ልብሱም እንደ ብርሃን ነጭ ሆነ። እንሆም ሙሴና ኤልያስ ከርሱ ጋራ ሲነጋገሩ ታዩዋቸው።
ጴጥሮስም መልሶ ጌታችን ኢየሱስን ጌታ ሆይ በዚህ መኾን ለእኛ መልካም ነው ብትወድስ በዚህ ሦስት ዳስ አንዱን ለአንተ አንዱንም ለሙሴ አንዱንም ለኤልያስ እንሥራ አለ።
እርሱም ገና ይህን ሲናገር እንሆ ብሩህ ደመና ጋረዳቸው እንሆም ከደመናው ውስጥም ''በርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው ርሱን ስሙት'' የሚል ድምፅ መጣ።
ደቀ መዛሙርቱም ሰምተው በፊታቸው ወደቁ እጅግም ፈርተው ነበር። ጌታችን ኢየሱስም ቀርቦ ዳሰሳቸውና ተነሡ አትፍሩም አላቸው። ዐይናቸውንም አቅንተው ሲያዩ ከጌታችን ከኢየሱስ ብቻ በቀር ማንንም አላዩም። በማለት ይነግረናል።
ይህ ዕለት ከተሰዓቱ ዐበይት በዓላት መካከል አንዱ ሲሆን በዚህ ወቅት ለሐዋርያት የክርስቶስ የባህርይ ልጅነት ከባህርይ አባቱ ተገልጧልና፣ እንዲሁም የባህርይ አምላክነቱን በመግለጥ በልባቸው የነበረውን ጥርጣሬ አስወግዶላቸዋልና፣ በተጨማሪም ነገረ ሥጋዌውን እንዲሁም ምስጢረ ሥላሴን ገልጦላቸዋልና።
የአብነት ተማሪዎችም አቤቱ በዚህ ዘመን ላለን ሐዋርያትን በመምሰል አርድዕተ ሊቃውንት ለሆንን ለእኛም ትምህርታችንን ግለጥልን፣ የራቀውን አቅርብልን የቀረበውንም አራቅልን በማለት በየዓመቱ ነሐሴ ፲፫ የደብረታቦር ዕለት ዝክር ይዘክራሉ።
ይህ ዕለትም በፖሊ ግቢ ጉባዔ አብነት ተማሪዎች በደመቀ እና በአማረ መልኩ ይከበራል ።
ለበዓሉ ማዘጋጃ ድጋፍ ለምታደርጉ :-
ንግድ ባንክ :-
1000358173199
ተስፋሁን ገድፍ እሸቴ
እመሰ ረሳይኩኪ ቤተ ጉባዔ ለትርስዓኒ የማንየ ወይጥጋዕ ልሳንየ በጉርዔየ መዝ 136÷8ትርጉም:- የአብነት ቤተ ጉባዔ ሆይ ብረሳሽ ቀኘ ትርሳኝ፣ ባላስብሽም ጉረሮየ ከተናጋየ ትጣበቅ። እርስዎም ድጋፍ በማድረግ ፣ በዕለቱ በመገኘት የበረከቱ ተካፋይ ይሁኑ ❗️ ⏰ሰዓት:- ምሽት 11:00 📆ቀን:- ነሃሴ 13/12/2018 ዓ.ም 🏛ቦታ:- አቡዬ ግቢ ጉባዔ አዳራሽ አዘጋጅ :- ፖሊ ግቢ ጉባዔ አብነት ተማሪዎች ────────── ✦ ────────── ፖሊግቢ ጉባኤ 📩@polygbigubaecommentbox ለሃሳብ አስተያየትዎ 📚@polylibrary መፅሐፍትን ለማንበብ 📖@polytmhirt ለኮርስ 📷@mkpoly_gallery የፎቶ እና ቪዲዮ ማኅደር ────────── ✦ ────────── Telegram | Instagram
3 574
ለተከታታይ ቀናት የወረብ ጥናት ☺️
🔶ውድ ተመራቂያን እንደሚታወቀው እሁድ በ21/10/2018 ለሁሉም ኦርቶዶክስ የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ተመራቂ ተማሪዎች ሰላም አርጊው ማርያም ምርቃት ይኖራል።
🔶 እዚህ መርሃ ግብር ላይ ደግሞ እንደ እኛ ግቢ ጉባኤ ወረብ በመዘጋጀት ላይ እንገኛለን ስለሆነም በፈተና ምክንያት በደንብ ስላልተዘጋጀን ከዚህ በኋላ ባሉት ቀናት ተከታታይ ጥናት ስለሚኖር ተቀሳቅሰን በሰዓት በመገኘት እንድናጠና ይሁን።
ነገ ማክሰኞ ከቀኑ 9፡00 -11፡30 ጥናት ይኖራል
ቦታ፡ ግቢ ጉባኤ አዳራሽ
ሰላመ እግዚአብሔር አይለየን 🙏
3 574
በጉጉት የምንጠብቀው ቀን ደረሰ🎉
ሰላም ለእናንተ ይሁን ውድ ተመራቂዎች
ነገ ማለትም እሁድ ከ ቀኑ 8:30 መርሃ ግብሮቻችን ስለሚጀምሩ
የመጀመሪያው ፕሮግራም ፎቶ መነሳት (photo shoot ) ስለሆነ እና መጀመሪያ ካለፈን ድጋሚ ለመነሳት ስለማንችልበተባለው ቦታ (ከራዲዮን)በሰአቱ እንገኝ አደራ በማርፈዳችን ምክኒያት ለዘመናት ማስታወሻ የሚሆኑንን ፎቶዎች እንዳናጣ! ⏰ሰዓት:- 8:30 📆ቀን:- 14/10/2018 ዓ.ም 🏛ቦታ:- ከራድዮን ሆቴል ቀበሌ 04 ከ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዋናው መስሪያቤት ፊት ለፊት ────────── ✦ ────────── ፖሊ ግቢ ጉባኤ 📩@polygbigubaecommentbox ለሃሳብ አስተያየትዎ 📚@polylibrary መፅሐፍትን ለማንበብ 📖@polytmhirt ለኮርስ 📷@mkpoly_gallery የፎቶ እና ቪዲዮ ማኅደር ────────── ✦ ────────── Telegram | Instagram
3 574
እንዴት ናችሁ ውዶቼ 👋
ከይቅርታ ጋር የዛሬው አዳር ምቹ ቦታ ባለመገኘቱ ምክንያት ቀርቶ ምሽት 11፡00 ሆኗል ዘይግተን በማሳወቃችን አሁንም በድጋሚ ይቅርታ እንጠይቃለን ።
ዛሬ ቅዳሜ ምሽት 11፡00
ቦታ ግቢ ጉባኤ አዳራሽ
3 574
ሰላም እንዴት ናችሁ ውድ ተመራቂያን
የመውጫ ፈተና የተፈተናችሁ እንኳን በሰላም ጨረሳችሁ ፤ ገና ለምትፈተኑ ደግሞ መልካም ፈተና ይሁንላችሁ እያልኩኝ
ቅዳሜ ለእሁድ አዳር የወረብ ልምምድ ስለሚኖር ሁላችንም ከአሁኑ አስበንበት ሌላ ፕሮግራም ሳንዳንደርብ እንድንገኝ ይሁን ።
ድምፁ መልካም በሆነ ጸናጽል አመስግኑት፤ እልልታ ባለው ጸናጽል አመስግኑት ፤ እስትንፋስ ያለው ሁሉ እግዚአብሔርን ያመስግን => መዝ 150፥5-6⏰ ምሽት 2፡00 📅 ቅዳሜ በ13 - 2018 ዓ.ም ⛪️ ግቢ ጉባኤው አዳራሽ ────────── ✦ ────────── ፖሊ ግቢ ጉባኤ
3 574
ልዩ የGC እራት መግቢያ ትኬት ሳይገዙ አልፈዎታልን!😚
እንግድያውስ ነገ የመጨረሻው ትኬት መሸጫ ቀን ነው። ከታች ባሉት ስልክ ቁጥሮች በመደወል ፈጥነው ይግዙ ።
👬እርስዎ ሲገዙ ጓደኛዎን አይርሱት ፣ መልዕክቱን ያድርሱት ፣ፕሮግራሙን አብረው ያሳልፉት ።📞
0908011840 (ንዋይ)
📞 0973438584 (እህተ ሙሴ)
📆ቀን:- የመጨረሻ ነገ 09/10/2018 ዓ.ም
────────── ✦ ──────────
ፖሊ ግቢ ጉባኤ
📩@polygbigubaecommentbox ለሃሳብ አስተያየትዎ
📚@polylibrary መፅሐፍትን ለማንበብ
📖@polytmhirt ለኮርስ
📷@mkpoly_gallery የፎቶ እና ቪዲዮ ማኅደር
────────── ✦ ──────────
Telegram | Instagram3 574
ታውቃላችሁ አይደል 🤔?
የተመራቂ ተማሪዎች ወረብ ጥናት መጀመሩን ግን የምትቀሩበት ምክንያት የወረብ እንቅስቃሴ ስለማንችል ነው ብላችሁ እንደሆነ ሰምቻለሁ ፤ ይሁን እንጂ ፍላጎት ኖሮት አልችልም ብሎ ማንም ከምስጋናው እንዳይቀር ታስቦ የወረብ እንቅስቃሴ ልምምድ ስለተዘጋጀ መለማመድ የምትፈልጉ በሙሉ በሰዓት እንድትገኙ ይሁን።
ድምፁ መልካም በሆነ ጸናጽል አመስግኑት፤ እልልታ ባለው ጸናጽል አመስግኑት ፤ እስትንፋስ ያለው ሁሉ እግዚአብሔርን ያመስግን => መዝ 150፥5-6⏰ 11፡00 📅 እሁድ 7 - 2018 ዓ.ም ⛪️ ግቢ ጉባኤው አዳራሽ ────────── ✦ ────────── ፖሊ ግቢ ጉባኤ
3 574
የማይረሳ ትዝታ በ450 ብር ብቻ 🙏
ውድ ተመራቂዎቻችን እንዴት አላችሁ ? በጉጉት የምንጠብቀው የGC የጋራ ማዕድ መርሐ ግብር በታዋቂው ከራዲዮን ሆቴል በድምቀት ተዛጋጅቷል።
በዕለቱም
➊ ትምህርት
➋ መዝሙር
❸ አዝናኝ ጨዋታዎች
❹ የተለያዩ ሽልማቶች
➎ የፎቶ መርሐ ግብር
➏ የልምድ ልውውጥ
እነዚህን የመሰሉ የማይረሱ ትዝታዎች የሚፈጥሩ አዕምሮ የሚያድሱ ልዩ ልዩ መርሐ ግብር ተዘጋጅተዋል።
ይህ እንደዚህ ከተዘጋጀ ከእኛ ፣ከዕርስዎ ምን ይጠበቃል ?
ከተጠቀሱት ቀናት በፊት ብር በመላክ የፕሮግራሙ ተሳተፊ ይሁኑ !
📅 ቀን:- እስከ 09/10/2018 ዓ.ም
🏛 ቦታ:- ከራዲዮን ሆቴል
────────── ✦ ──────────
ፖሊ ግቢ ጉባኤ
📩@polygbigubaecommentbox ለሃሳብ አስተያየትዎ
📚@polylibrary መፅሐፍትን ለማንበብ
📖@polytmhirt ለኮርስ
📷@mkpoly_gallery የፎቶ እና ቪዲዮ ማኅደር
────────── ✦ ──────────
Telegram | Instagram
3 574
ሰላም ለእናንተ ይሁን ውድ የ2018 ተመራቂ ተማሪዎቻችን!
ከእግዚአብሔር ቤት መረቅናችኹ መዝ 117÷26🔶የወረብ ዝማሬ ጥናታችን ሃሙስ ስለሚቀጥል የተለቀቁትን ዜማዎች አዳጠን ሁላችንም ተመራቂ ተማሪዎች ተቀሳቅሰን በሰአት እንድንገኝ ይሁን። ✨ኑ! አብረን አጥንተን በምርቃታችን ዕለት ለአምላካችን በዝማሬ ምስጋናን እናቅርብ🤲 ⏰ሰዓት: 10:30 📅ቀን: ሃሙስ 4 - 2018 ዓ.ም ⛪️ቦታ: ግቢ ጉባኤው አዳራሽ ────────── ✦ ────────── ፖሊ ግቢ ጉባኤ
