2 467
Subscribers
No data24 hours
-187 days
-7330 days
- Subscribers
- Post coverage
- ER - engagement ratio
Data loading in progress...
Subscriber growth rate
Data loading in progress...
ዶ/ር ዓለማየሁ ዋሴ በኢትዮጵያ የስነ ፅሁፍ ዘርፍ የበኩላቸውን አሻራ አሳርፈዋል ከምንላቸው ደራሲያን መካከል ተጠቃሽ ናቸው።እስካሁን እመጓ፣ ዠጎራ ፣መርበብት፣ሰበዝ፣ሚተራዮን የተሰኙ ድንቅ መፅሐፎችን ያደረሱ ሲሆን አሁን ደግሞ ችቦ እያበሩ መጥተዋል ስድስተኛው መፅሐፋቸው ችቦ የተሰኘው መፅሐፍ ለአንባብያን አበርክተዋል።ለሰጡን ሁሉ ባሉበት ትልቅ አክብሮት እና ምስጋና ይድረስ🙏ብለናል።
ለዛሬም በ የእኛ ገፃችን የዶ/ር ዓለማየሁ ዋሴ መፅሐፍቶችን ለመዳሰስ ወደድን።
❤
Open Comments
መ - መጽሐፍ
የቃላት ድርድር ፣ የዐረፍተ ነገሮች ጋጋታ ፣ የአንቀጾች ስብስብ አይሆን እናምናለን፡፡ ነፍስ ሽቶ ነፍስ ይዘራ ፣ ያድር ተማጽኖ በውስጥ ይሰፍን አይሆን ቢታመን ቅጥፈት ይሆን እናምናለን፡፡
ተ - ተደራሲ
በታቀፈው የቃላት ድርድር ፣ የዐረፍተ ነገሮች ጋጋታ ፣ የአንቀጾች ስብስብ ተጀቡኖ ሌላ አይመለከት መሆኑን እንነቅፋለን፡፡ በሸኚ ሀሳቦች ታጅቦ ፣ በተንጠልጣይ ሐረጋት ተንጠልጥሎ ካሰበበት አይደርስ ይታመን ቢሆን እውነት ይሆን እንነቅፋለን፡፡
ደ - ደራሲ
የቃላት ድርድር ፣ የዐረፍተ ነገሮች ጋጋታ ፣ የአንቀጾች ስብስብ ሰዳሪ አይሆን እናውቃለን፡፡ ነፍስ ሽቶ ነፍስ ይዘራ ይሆን በሚሆነው መጽሐፍ የጌትነት ቦታ አይኖረው እናውቃለን፡፡ በገጾች ተጀቡኖ ሌላ አይመለከት መሆኑን ይነቅፍ በሆነው ተደራሲ ዘንድ ፋና ወጊ ይሆን አይችል እንደሆን እናውቃለን፡፡
አምነን ፣ ነቅፈን ፣ አውቀን “ዛሬ ቅዳሜ አይደለም”ን እነሆ እንላለን፡፡
መ - መጽሐፍ
የቃላት ድርድር ፣ የዐረፍተ ነገሮች ጋጋታ ፣ የአንቀጾች ስብስብ አይሆን እናምናለን፡፡ ነፍስ ሽቶ ነፍስ ይዘራ ፣ ያድር ተማጽኖ በውስጥ ይሰፍን አይሆን ቢታመን ቅጥፈት ይሆን እናምናለን፡፡
ተ - ተደራሲ
በታቀፈው የቃላት ድርድር ፣ የዐረፍተ ነገሮች ጋጋታ ፣ የአንቀጾች ስብስብ ተጀቡኖ ሌላ አይመለከት መሆኑን እንነቅፋለን፡፡ በሸኚ ሀሳቦች ታጅቦ ፣ በተንጠልጣይ ሐረጋት ተንጠልጥሎ ካሰበበት አይደርስ ይታመን ቢሆን እውነት ይሆን እንነቅፋለን፡፡
ደ - ደራሲ
የቃላት ድርድር ፣ የዐረፍተ ነገሮች ጋጋታ ፣ የአንቀጾች ስብስብ ሰዳሪ አይሆን እናውቃለን፡፡ ነፍስ ሽቶ ነፍስ ይዘራ ይሆን በሚሆነው መጽሐፍ የጌትነት ቦታ አይኖረው እናውቃለን፡፡ በገጾች ተጀቡኖ ሌላ አይመለከት መሆኑን ይነቅፍ በሆነው ተደራሲ ዘንድ ፋና ወጊ ይሆን አይችል እንደሆን እናውቃለን፡፡
አምነን ፣ ነቅፈን ፣ አውቀን “ዛሬ ቅዳሜ አይደለም”ን እነሆ እንላለን፡፡
#ነገም ሌላ ቀን ነው
ይህ መፅሐፍ በማርጋሬት ሚሼል "GONE WITH THE WIND " በሚል ተፅፎ በገጣሚና ተርጓሚ ነቢይ መኮንን "ነገም ሌላ ቀን ነው " ተብሎ ተተርጉሟል፡፡
#ደራሲዋ ማርጋሬት ሚሼል መፅሀፉ ሲታተም ሰላሳ ስድስት ዓመቷ ነበር ። "ጎን ዊዝ ዘ ዊንድ"ን ፅፎ ለመጨረስ አስር ዓመት ፈጅቶባታል። በሃያ ስድስት ዓመቷ ባጋጠማት የቁርጭምጭሚት ጉዳት ከአልጋ በዋለችበት ወቅት ነው ይህንን መፅሀፍ የጀመረችው ፤ ስለ አሜሪካ የእርስ በርስ ጦርነት ሲተረት ፣ሲወሳ ፣ ሲነገራት ከአትላንታና ጦርነቱ ጋር ጥርሷን ነቅላ ያደገች ናት ። መፅሀፉም በመጀመሪያ እትም ከአንድ ሚሊዮን ኮፒ በላይ የተሸጠ ፣ እስከ 1965 በአርባ ሀገሮች በሰላሳ የተለያዩ ቋንቋዎች ተተርጉሟል። እያንዳንዱ አሜሪካ ጠንቅቆ ያውቀዋል ።
#ተርጓሚው ገጣሚና ተርጓሚ ነቢይ መኮንን ማዕከላዊ እስር ቤት ታስሮ ሳለ "ነገም ሌላ ቀን ነው” ሲል ይህን መፅሀፍ የተረጎመው በሲጋራ ወረቀት ላይ በመፃፍ ነው፡፡ በዚያ አስቸጋሪ ጊዜ ይህንን ትልቅ መፅሀፍ በአስቸጋሪና ለመመኮር እንኳን ከባድ በሆነ መልኩ ተርጉሞ ለንባብ ያበቃው መጋቢት 1982 ዓ/ም በ670 ገፆች ተሰናድቶ ነው፡፡
እናም ደራሲዋም ፣ ተርጓሚውም ፣ የመፅሀፉም ታሪክ በአስቸጋሪና ከባድ በሆነ ሁኔታ ውስጥ ብንሆንም በጥንካሬ ማለፍን ይነግሩናል ፤ ያስተምሩናል ። ስለዚህ አሁን በዓለማችን የተፈጠረው ሁሉ ያልፋል ፣ ይነጋል። ምክንያቱም #ነገም ሌላ ቀን ነው!!
#ነገ ሲሰራ
ወንድሜ! ጨንቆUል? ቀፎሀል? ፈርተሀል? ሰግተሀል? በል አንሳ 'ጽዋህን - ሀዘንህ እስኪጨንቀው ፤ የቀረህን ፍሬ በወኔ ጭመቀው ።
ታዲያ ዋ! የጭማቂህ ሙሌት እንዳይበዛው አረፋ ፤ ትዝታ የወለደው ነስንስበት ተስፋ ።
#መፅሐፋን በpdf ለምትፈልጉ እነሆ በረከት ብለናል!
#ይስማዕከ
#አዲስ መፅሀፍ እነሆ
#ግፋዓን
ጦርነት ሲጀምር ፓለቲከኞች ጥይት ያቀብላሉ።ባለፀጎች ምግብ ያቀርባሉ ድሆች ልጆቻቸውን ይለግሳሉ ጦርነቱ ሲይበቃ ፓለቲከኞች ቀሪ ጥይቱን ይሰበስባሉ።ባለፀጎች ከጦርነት በተረፈው ሀብታቸው ማደግ ይጀምራል።ድሆች ግን ልጆቻቸውን በመቃብር ስፍራ ይፈልጋሉ።