3 588
Subscribers
No data24 hours
+267 days
+12030 days
Posts Archive
ቀን 03/13/2018
ለሁሉም ወረዳ የፈተና ክፍል ኃላፊዎች
ለ2019 የትምህርት ዘመን የ7ኛ እና የ9ኛ ክፍል ምዝገባ በተሳካ ሁኔታ ለማካሄድ ያመች ዘንድ በ2018 የትምህርት ዘመን 6ኛ እና 8ኛ ክፍል ተፈትነው የማለፊያ ውጤት ያመጡ ተማሪዎችን ሮስተር ከሲስተም ላይ በማውረድ ለሚመለከታቸው መረጃውን እንድታሳውቁ እናሳስባለን።
ክልል ትምህርት ቢሮ
ፈተና ክፍል
Date: 03/13/2018
To: All District Examination Unit Heads
To ensure the successful registration of Grade 7 and Grade 9 students for the 2019 academic year, we advise you to download the roster of students who took the Grade 6 and Grade 8 national exams in the 2018 academic year and achieved passing scores from the system, and notify the relevant stakeholders accordingly.
Regional Education Bureau
Examination Unit
ቀን 03/13/2018
ለሁሉም ወረዳ የፈተና ክፍል ኃላፊዎች
ለ2019 የትምህርት ዘመን የ7ኛ እና የ9ኛ ክፍል ምዝገባ በተሳካ ሁኔታ ለማካሄድ ያመች ዘንድ በ2018 የትምህርት ዘመን ተፈትነው የማለፊያ ውጤት ያመጡ ተማሪዎችን ሮስተር ከሲስተም ላይ በማውረድ ለሚመለከታቸው መረጃውን እንድታሳውቁ እናሳስባለን።
ክልል ትምህርት ቢሮ
ፈተና ክፍል
To: All District Examination Unit Heads
To ensure the successful registration of 7th and 9th-grade students for the 2019 academic year, we advise you to download the roster of students who passed their exams in the 2018 academic year from the system and notify the relevant stakeholders accordingly.
Regional Education Bureau
Examination Unit
ማስታወቂያ
የ2018 ዓ.ም. የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ በመደበኛው የትምህርት መርሃ ግብር የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መግቢያ ውጤት ላስመዘገባችሁ ተማሪዎች በሙሉ፡-
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እና የትምህርት መስክ ምርጫችሁን ከነሐሴ 28 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ጳጉሜ 5 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ከታች የተቀመጠውን ማስፈንጠሪያ (Link) በመጠቀም ምርጫችሁን ት/ቤት መሄድ ሳይጠበቅባችሁ ባላችሁበት ቦታ እራሳችሁ በመሙላት እንድታሳውቁ እንገልጻለን።
ማስፈንጠሪያ (Link) https://student.ethernet.edu.et/
ማሳሰቢያ፡-
የህክምና፣ የአካል ጉዳተኝነት፣ ተመሳሳይ ጾታ ያላቸው መንትያዎች እና ከ6 ወር በታች ህፃን የሚያጠቡ እናቶች አስፈላጊውን ሕጋዊ ማስረጃ ማያያዝ ይኖርባችኋል።
የትምህርት ሚኒስቴር
https://www.facebook.com/share/v/1GA8ryLyxp/
#አስቸኳይ_ማስታወቂያ✍️
በፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ለመማር ተመዝግባችሁ ፈተና በመጠባበቅ ላይ ላላችሁ ተማሪዎች በሙሉ፤
👉 ትምህርት ሚኒስቴር ለ2019 የትምህርት ዘመን ትምህርት በሚሰጥባቸው ነባርና አዲስ የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በ9ኛ እና 10ኛ ክፍል ተማሪዎችን አወዳድሮ ለመቀበል ባወጣው ማስታወቂያ መሰረት ተመዝግባችሁ በመጠባበቅ ላይ ያላችሁ ተማሪዎች የፈተና ፕሮግራም መውጣቱ ይታወሳል።
👉 ስለሆነም ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም የሙከራ ፈተና እንዲሁም ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም ለዋናው ፈተና ፕሮግራም የወጣ መሆኑን አውቃችሁ በዚህ ፕሮግራም መሰረት ከጠዋቱ 2:30 በተመደባችሁባቸው ጣቢያዎች ራሳችሁን የሚገልጽ መታወቂያ በመያዝ ተገኝታችሁ እንዲትፈተኑ ጥሪ እናስተላልፋለን፡፡
የመፈተኛ ሊንክ
https://exam2.ethernet.edu.et
ለፈተና የተመዘገባችሁ ስም ዝርዝራችሁን ከታች ማየት ትችላላችሁ
Gambella Education Bureau
‼️ የሪሚዲያል (Remedial) ፈተና ውጤት ይፋ ሆኗል!
በ2018 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርታችሁን ስትከታተሉ የቆያችሁ ተማሪዎች በሙሉ፣ በጉጉት ስትጠብቁት የነበረው የሀገር አቀፍ ፈተና ውጤት አሁን በይፋ ተለቋል።
ውጤታችሁን እንዴት ማየት ትችላላችሁ?
1. ወደ https://result.ethernet.edu.et ድረ-ገጽ ይግቡ
2. "Remedial Examination" የሚለውን መርጣችሁ "View Results" የሚለውን ይጫኑ
3. Username በማስገባት ውጤታችሁን በቀላሉ ይመልከቱ
📌 ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 03/2018 ዓ.ም በተሰጠው በዚህ ሀገር አቀፍ ፈተና ላይ 53,620 ተፈታኞች መሳተፋቸውን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።
ውጤታችሁ ምን ይመስላል? መልካም ዕድል ለተፈታኞች በሙሉ! 🎓
#RemedialResult #Ethiopia #ExamResults #EthernetEdu
