cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

ሕያው ቃል

''ነዋ ወንጌል መንግሠተ ሰማያት "፦ ወደ መንግሥተ ሰማያት የምታገባ ወንጌል እንሆ። "

Show more
Advertising posts
5 905
Subscribers
No data24 hours
-147 days
-8830 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

ኤሌክትሮኒክስ ጥገና መማር ለምትፈልጉ ይህን ቻናል ተቀላቀሉ https://t.me/electronics_xegena
Show all...
ኤሌክትሮኒክስ ጥገና

የምንሰጣቸው አገልግሎቶች . የቲቪ LED . Crt .ቲቪ ጥገና . ጂፓስ ሪሲቨር እና የመሳሰሉት

👍 4 1
ኤሌክትሮኒክስ ጥገና መማር ለምትፈልጉ ይህን ቻናል ተቀላቀሉ https://t.me/electronics_xegena
Show all...
ኤሌክትሮኒክስ ጥገና

የምንሰጣቸው አገልግሎቶች . የቲቪ LED . Crt .ቲቪ ጥገና . ጂፓስ ሪሲቨር እና የመሳሰሉት

👍 8 1
Photo unavailableShow in Telegram
48
ይሄን ሊንክ በመንካት ቀጥታ ወደ ፌስቡክ አካውንታችን በመግባት ፎሎው ያድርጉን ። በአዲስ መልኩ የተከፈተ ነው አዳዲስ ነገር ያገኙበታል ። 👇👇 https://www.facebook.com/profile.php?id=100090438198637
Show all...
Log in or sign up to view

See posts, photos and more on Facebook.

ከመታወቅ በላይ! እግዚአብሔር በእግዚአብሔር ታዉቆ ይኖራል እንጂ በፍጡር አዕምሮ የማይደረስበት ትልቅ አምላክ ነዉ። እግዚአብሔርን ያወቅነው እርሱ የሆነውን ያህል ሳይሆን እኛ ለማወቅ የቻልነውን መጠን ነው።  እርሱ ከቃላችን ከስብከታችን በላይ ነው።  ቃላት እርሱን ለመግለጥ ያነክሳሉ፣ አሳብም እርሱን ለማጠናቀቅ ይብረከረካል፣ እንዳይጠፋ ይሰጋል።  እግዚዓብሔር ከመታወቅ በላይ ቢሆንም እውነት ነውና እንድናውቀው ይፈልጋል። እርሱ ጨለማ የሌለበት ብርሃን ነው።  እንኳን እግዚዓብሔር የሰማይ ስፋት፣ የባህር ጥልቀት እንኳን አልተደረሰበትም። የፈጠረዉ ካልተደረሰበት ፈጣሪው ባይደረስበት ምን ይደንቃል! እግዚአብሔር ህልውናው ምክንያት የለውም፣ ለመኖሩም በማንም አይደገፍም፣ በራሱ ሕይወተ ባህርይ ይኖራል። ምሳሌ አልባ፣ ድካም የሌለበት አምላክ ነው። አባቶች እንደተናገሩለት ኃይሉ በመብረቅ፣ ፍጥነቱ በነፋስ፣ ልዕልናው በሰማይ፣ ስፋቱ በምድር፣ አስፈሪነቱ በእሳት፣ ጥልቀቱ በባህር አይመሰልም። ከፍጡራን አስረጅነት በላይ የሆነ በራሱ ታውቆ የሚኖር የእውቀት እውቀት ነው።  ጎዶሎው ሰው ፍፁሙን አምላክ በሙሉነት ማወቅ አይችልም። እግዚአብሔር ስለራሱ የገለጸልንን አለማወቅም ተገቢ አይደለም። እርሱ ግን በራሱ ታውቆ፣ ባሕርይው ባሕርዩን አክብሮት ይኖራል። በመታወቅም ባለመታወቅም ያስደስታል። ፅንፍ የለሽ ክብሩ ይወደስ!!!!!!!!!!!!
Show all...
ኀጢአተኞች ኹሉ ምሕረት ያገኘንበት አዲሱ ኪዳናችን፣ ክርስቶስ ኢየሱስ ነው፤ የምሕረት ኪዳኑም ላይሻር በቅዱስ ደሙ ታትሞአል! አሜን።
Show all...
Photo unavailableShow in Telegram
አቤቱ ጾም አስለምደኝ ጌታዬ ኢየሱስ ሆይ፦ ጾም ምግብን ከሥጋ ከመከልከል እንደሚጀመር አውቃለሁ። የሰባውን መተው እንደሆነም ተምሬአለሁ። ምግቤን በመቀየር መጾም አስቸግሮኝ አያውቅም። ነገር ግን እንዳንተ ወደ ምድረ በዳ መውረድን አልለመድኩም። ስሜቶቼን ከመብላቸው ልከለክላቸው አልቻልኩም። አርባ ቀን እስክትራብ ጾመሃል። ከዓለም ጫጫታ ተሰውረህ ብቻህን ከርመሃል። ሰይጣን መራብህን አይቶ የዘረጋውን የፈተና ወጥመድ ሰብረሃል። ልጅህ ግን ከምግብ ለውጥ ያለፈ የጾም ማዕረግ የለኝም። በተራብኩ ጊዜ ለብዙ ፈተና እጋለጣለሁ። ንዴት፣ ፍርድ፣ ስንፍና፣ ፌዝ የተባለ የሰባማዕድ ዛሬም ከፊቴ አልተነሳም። የምወደውን ለመጨበጥ ያለኝ ጉጉት ሰከን አላለም። ያየሁት ሲያምረኝ ሰውነቴ ሆይ ጾም ላይ ነህ! አልለውም። ከንፈሬ እስኪደርቅ ከውሃ እከለከላለሁ። ስንፍናን ለመናገር ግን መልሼ ከንፈሬን በምላሴ አረጥባለሁ። መልሼ ጾመኛ መሆኔን እናገራለሁ። አየህ ጌታዬ ያልተማርኩት ብዙ ጥበብ አለ። ያልደስረኩበት ብዙ መንፈሳዊ ማዕረግ አለ። ከነርሱ አንዱ መንፈሳዊ ጾም ነው። መጾምን እንድታስተምረኝ አለምናለሁ። ሁል ጊዜ በፊትህ የእውነት መኖርን እንድትሰጠኝ እለምናለሁ። የማያድግና በልማድ ዓለም የተዋጠ ህይወት እንዲኖረኝ አልሻም። እንደትንሽ ዘለላ በወደቀበት አድጎ የሚነሳ ታደርገኝ ዘንድ ከልቤ እጸልያለሁ። ተባረኩበት።
Show all...
አሳርፎናል! ✔ለዘላለም ሕይወት ሰው ለእግዚአብሔር የሚሠራለት ምንም ነገር የለም፡፡ የኃጢአታችን ደመወዝ ሞት እንደ ሆነ ሁሉ፤ የዘላለም ሕይወት ደግሞ በክርስቶስ ኢየሱስ የእግዚአብሔር የጸጋ ስጦታ ነው (ሮሜ 6፥23)፡፡ ሰዎች ሁሉ የሚድኑበት የእግዚአብሔር ጸጋ፤ ኃጢአተኝነትንና ዓለማዊን ምኞት የሚያስክድ ጸጋ ከእግዚአብሔር ለእኛ ተገልጦአል፡፡    ✔  ክርስቲያን ስላመነ እንዳመነ ሰው በእምነት ይኖራል (ሮሜ 1፥17) እንጂ ለዘላለም ደኅንነት እግዚአብሔር ከተግባሩና ከእጅ ሥራው (ከሰው) የሚፈልገው ምንም ነገር የለም፡፡ ጌታችን "እኔ ላደርገው የሰጠኸኝን ሥራ ፈጽሜ በምድር አከበርሁህ . . " /ዮሐ. 17፥4/ እንዳለ፤ "ኢየሱስም ሆምጣጤውን ከተቀበለ በኋላ፡- ተፈፀመ አለ፤ ራሱንም አዘንብሎ ነፍሱን አሳልፎ ሰጠ" (ዮሐ. 19፥30)፡፡ 🙏 የፈፀመው ጌታ አሳርፎናል!
Show all...
መስጠት ) አይችልም፡፡( ማቴ .16÷26) ፡፡ ቤዛነት ምትክ ሆኖ ከእስራት ነጻ ለማውጣት የሚከፈል ዋጋ ከሆነ፤ኢየሱስ ብዙዎች ስለሆንነው ስለሁላችን ነፍሱን ቤዛ አድርጎ ከኃጢአትና ከዘላለም ሞት ነጻ ሊያወጣን ህይወቱን አሳልፎ ሰጠ፡፡አምላክ ለፍጡር እንጂ ፍጡር ለፍጡር ቤዛ መሆን ከቶ አይቻለውም፡፡ኃጢአት ላረከሰው የሰውልጅ ኃጢአትና ዕድፍ ፈጽሞ የሌለበት የእግዚአብሔር በግ ኢየሱስ ያስፈለገው ለዚህ ነው፡፡ ስለዚህ የኃጢአት ክስ ያለበት የትኛውም አዳማዊ ፍጡር መዳን የሚችለው በአንዱ ቤዛ በተሰቀለው መድኃኒት ማመን ሲቻለው ብቻ ነው፡፡እስከዛሬ ለበደለ ባርያ የሞተ ጌታ ወይም አንድ የስስት ልጁን የሰጠ ጌታ አልሰማንም፡፡ጌታ አብ ግን ልጁን እስኪሰጠን በእንዲሁ ፍቅር ወደደን ( ዮሐ .3÷16) ፤ ወልድም ገና ደካሞች ሳለን ቤዛ ሆኖ በሞቱ ሊታረቀንና ሊያስታርቀን ወደእኛ መጣ፡፡( ሮሜ፣5÷6) እኛ ወደእርሱ የሚያቀርብ ምንም ነገር ስለሌለንና የህይወት በራችንን በራሳችን ላይ ስለዘጋን እርሱ ወደ እኛ የተዘጋውን በር ከፍቶ መጥቶ ተቤዠን፡፡ፍቅሩ ከህሊና መረዳት ከማስተዋል ይረቃል!!! ተመርቆ የተከፈተውን ህያውና አዲስ መንገድ የሚያስተዋውቀውና የሞቱን ነገር በልባችን የሚስለውም መንፈስ ቅዱስ ድንቅና ፍቅር ነው፡፡ አዎ ! ኢየሱስ መስዋዕት ሆኖ ባፈሰሰልን ደሙ ቤዛችን ሆነልን፡፡ከእርሱ በቀርም ማንም፤ምንም ቤዛ የለንም፡፡.በቤዛችን እንዲህ ተወደናልና ደስ ይበለን፡፡
Show all...
Choose a Different Plan

Your current plan allows analytics for only 5 channels. To get more, please choose a different plan.