cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

ብርቅርቅታ💕

✍"የትንሽ ሰው ትንሽ ፀባይ ሊያወርድህ ሲል አንተን ከላይ ከቻልክ አውጣው ከፍ አድርገው ግን አትውረድ አንተ አብረኸው!" . . . ▼ ⓌⒺⓁⓁ ⒸⓄⓂⒺ For anther group @frduuu ለአስተያየት @leyluti_bot By #L_E_Y_L_A

Show more
Advertising posts
797
Subscribers
No data24 hours
+37 days
+1530 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

" አንዳንዴ…" : #አንዳንዴ ልትጠላው በማይፈቀድልህ ሰው መፈተን ይከብዳል። ልትርቀው ከማይፈቀድልህ ሰው የሚደርስህ ግልምጫ መቋቋም ይከብድሀል። ትናደዳለህ። ንዴትህ ግን አንተን ከመጉዳት የዘለለ ፋይዳ የለውም። . . #አንዳንዴ ልትቆርጠው በማይፈቀድልህ ግንኙነት ስትገለል ማስረዳት የማትችለው ህመም ያምሀል። ህመምህን በራስህ ቋንቋ እየታመምክ ትሰነብታለህ እንጂ በቃል ለማስረዳት ሁሉም ይተናነቅሀል። የሚገፋህን ገፍተኸው መሔድን ስላልተፈቀደልህ ትንገበገባለህ። . . #አንዳንዴ በሩቅ ተቀብሮ ከሚጎዳህ ቦንብ የበለጠ በቅርብህ ሆኖ የሚወጋህ እሾኽ ይበልጥ ያሰቃይሀል። ገፍተውህ የማትገፋቸውን እየተመለከትክ " ምነው እኔም እንደነሱ መሆን በቻልኩበት " ብለህ ጨካኝ ምኞት ትመኛለህ። ብዙ ነገር ልትመኝ እንደምትችል አልጠራጠርም። እኔ ልልህ የምችለው የሁሉም ነገር ሚዛን ያለው አላህ ጋር ነው። ሀቅን ለባለ ሀቁ ማድረስህን ቀጥል። . . #አንዳንዴ ሀቃችንን ሲያጎድሉ ሀቃቸው የሌለብን ይመስለናል። ካንተ የተሻለ ጠለቅ ብዬ ህመምህን ላውቀው አልችልምና አላፅናናህም። ብቻ ይህን አውቃለሁ። ጊዜ ረቂቅ ነው። በጊዜ ውስጥ መልስ አለ። . . አንዳንዴ… : #ለዊ @berkrekta
Show all...
1👏 1🤗 1
Photo unavailableShow in Telegram
ሰውየው አዲስ የገዛትን መኪና ቀለም ቀብቶ እንደጨረሰ የ4 አመት ልጁ ድንጋይ አንስታ በመኪናው በአንደኛው ጎን ፋቀችበት፡፡ አባት በጣም ተናዶ የልጁን እጅ አንስቶ ደጋግሞ መታት፡፡ አባት በጣም ከመናደዱ የተነሳ የልጁን እጅ ለመምታት የተጠቀመው የብረት መፍቻ መሆኑን እራሱ አላገናዘበም፡፡ ልጅ ሆስፒታል ብትወሰድም የእጆቿ አጥንቶች በሙሉ በመድቀቃቸው 5 ጣቷን አጣች፡፡ አባቷን እንዳየችም "አባ ጣቶቼ መቼ ነው የሚያድጉት?" ስትል ጠየቀችው፡፡ አባት የፀፀት አለንጋ እየገረፈው የሚናገረው አጣ፡፡ ወደ ቤቱ  ተመልሶ የልጁን ጣቶች እንዲያደቅ ምክንያት የሆነውን አዲስ መኪና ደጋግሞ በእግር እጁ እየቀጠቀጠ በፀፀት ማልቀስ ጀመረ፡፡ ከመኪናው ፊት ለፊት እንደተቀመጠ ቀድንገት ልጁ መኪናው ላይ ስትፅፍ የነበረውን ተመለከተ፡፡ "አባ እወድሀለው" ብላ ነበር የፃፈችው፡፡ ይህን ባየ ግዜ ህመሙ ይበልጥ ጨመረ፡፡ #ጭብጥ ፡- ንዴታችንን መቆጣጠር ካልቻልን በህይወታችን ላይ ጥቁር ጠባሳ ጥለን የምናልፍበትን ስተት እንሰራለን፡፡ ደሞ ልብ በሉ ዕቃን ልንጠቀምበት (ልንገለገልበት)፤ የሰው ልጅን ደሞ ልንወድና ልናፈቅር ነው የሚገባው፡፡ ነገር ግን አሁን አለማችን ላይ በተገላቢጦሽ የሰው ልጅ መጠቀሚያ፤ ዕቃ (ቁሳቁስ) የሚወደድና የሚፈቀር ሆኗል፡፡ @berkrekta
Show all...
🥰 4😢 2
አንዳንድ ጊዜ ዝም አይነቅዝም! #በዝምታህ_አሸንፋቸው! አንድ ሰው እየተጣላህ ከሆነ፥ በጸጥታ ተቀምጠህ አስተውለው። በምንም መንገድ ምላሽ አትስጠው። ዝምታ ቁልፍ ነው! የሆነ ትወና እየተመለከትክ እንደሆነ አስብ። እንዲህ ዓይነቱ ገጠመኝ እውነተኛ ማንነታቸውን ለማጋለጥ ጥሩ አጋጣሚ ነው።
Show all...
2🥰 2👍 1👏 1
🔥ድፍረት ማለት ያለ ፍርሀት መኖርና እየደነፉ ማውራት ማለት ሳይሆን ፣ ከሚገባው በላይ ብንፈራና ብንደነግጥም እንኳን ያሰብነውን ነገር ከማድረግ ወደ ኋላ አለማለት ነው ። በአስቸጋሪ ጊዜና ሁኔታ ውስጥ ተረጋግቶ መውጫ ቀዳዳ በመሻት  መውጣት የድፍረት አንድ አካል ነው ድፍረት ማለት የፍርሀት አለመኖር ሳይሆን ፍርሀት ላይ የምንቀዳጀው ድል እንደሆነ ተማርኩ፤ ጀግና የሚባለው ፍርሀት የማይሰማው ሳይሆን ፍርሀትን መማረክ የቻለው ነው! ----ኔልሰን ማንዴላ
Show all...
2🥰 2👍 1👏 1
"ሁልጊዜ ከሰዎች የማነስ ስሜት የሚሰማህ ከሆነ የቅናት ማዕከላት የሆኑትን የማሀበራዊ ሚዲያዎች መጠቀም አቁም 🚫" ATOMIC HABIT Ⓑ
Show all...
4🥰 2👏 1
አንዳንዴ . . . ያለ ነው! አንዳንድ ጊዜ ማመንታት ያለ ነው - በፍጹም ግን ወደ ኋላ አንመለስም! አንዳንድ ጊዜ መፍራት ያለ ነው - በፍጹም ግን አንንበረከክም! አንዳንድ ጊዜ ተስፋ መቁረጥ ያለ ነው - በፍጹም ግን አናቆምም! አንዳንድ ጊዜ መሸነፍ ያለ ነው - በፍጹም ግን ሕይወት ከሚያቀብለን የየእለት ጦርነት አንሸሽም! አንዳንድ ጊዜ መድከም ያለ ነው - በፍጹም ግን ዝለን አንወድቅም! አንዳንድ ጊዜ ግራ መጋባት ያለ ነው - በፍጹም ግን አንቅበዘበዘም! አንዳንድ ጊዜ በሰው መገፋት ያለ ነው - በፍጹም ግን ከዚያ ሰው ውጪ መኖር አየቅተንም! አንዳንድ ጊዜ ድብርት ያለ ነው - በፍጹም ግን ደንዝዘን አንቀርም! አንዳንድ ጊዜ ለጥያቄ መልስ ያለማግኘት ያለ ነው - በፍጹም ግን ከመጠየቅ አናርፍም! አንዳንድ ጊዜ ክፋት ያሸነፈ መምሰሉ ያለ ነው - በፍጹም ግን መልካምነትን አንጥልም!
Show all...
🥰 3 2👍 1👏 1
#አንድ_ቀን_ታረጃለህ! በወጣትነትህ ሽማግሌውን አክብር ጠንካራ ስትሆን ደካሞችን እርዳ ሰዎች ሲሳሳቱ አታሳቃቸው ምክንያቱም አንድ ቀን በህይወት ታረጃለህ፣ ደካማ ትሆናለህ፣ ትሳሳታለህም!!! #ስሜትን_በብልኃት_መምራት መጽሐፍ #EMOTIONAL_INTELLIGENCE
Show all...
2🥰 2👍 1👏 1🤗 1
#እያለህ_ካልሆነ_ከሌለህ_የለህም! 👌 ማንም ሰው ያልሰራኸውን፣ ያልጣርክበትን ነገር አምጥቶ አይሰጥህም! ማንም ሰው በልፋት ስላመጣኸው ነገር ግድ አይሰጠውም። ብታወድመው ተው የሚልህ ማንም አይኖርም። 👌ማንም ሰው በመገለል ላሳለፍከው የስቃይ ህይወት ጉዳዩ አይደለም። ስትወድ ለተሰበርከው የሚታመምልህ ማንም የለም። ስለዚህ ያን የስቃይ ጊዜ እያሰብክ በእልህ መጣር የበለጠ የተሻለ ምርጥ ውጤት ለራስህ መሸለም ያለብህ አንተው ነህ። ያሳለፍከውን ከባድ ህይወት ብትጽፈው፣ ብትናገረው፣ ብታለቃቅሰው አንድም ሰው እውነቱን አያውቅልህም። ስለዚህ በየተገኘህበት ምሬትህን በማሰማት ፈንታ ያንን ጊዜ በስራ፣ በማግኘት ተበቀለው። ና ራስህን አበርታ ና ለራስህ አመስግን ና ራስህን አድንቅ ና ራስህን በማግኘት በማሳካት በመቀጠል ሸልም ☑️ ህይወት ስለሌሎች አይደለም። ስለራስ የሚቆስሉት የሚታመሙት የሚድኑት ትግል ነው። ════❥━━━❥═════      🌾ነገ መልካም ይሆናል !  🌾 💫 https://t.me/philoso_phy 💫              🎖  @cekuaa 🎖
Show all...
👏 5👍 1
👉 ማንበብ የሰው ልጅ ሰው ከሆነ በዃላ ሰው የሚሆንበት መንገድ ነው። 👉 ማንበብ ለእያንዳንዷ የህይወት ተግዳሮቶች ቅድመ መፍትሄ ማዘጋጀት ነው። ይህም ማለት ነገ ለሚገጥሙን ችግሮች ታብሌቶችን (መድሀኒቶችን) ማዘጋጀት ነው። ( ቡርሀን አዲስ) @berkrekta
Show all...
3🥰 2👏 1