en
Feedback
Nejashi TV // ነጃሺ ቲቪ

Nejashi TV // ነጃሺ ቲቪ

Open in Telegram

የነጃሺ ቲቪ ቤተሰብ ስለሆኑ እናመሰግናለን ። የተለያዩ መረጃዎችና እውቀቶች ይገበያሉ ። ተቀላቀሉን ! Facebook: https:// Jeilumedia.com Telegram: https://t.me/nejashitvofficial E-mail: nejashitvaddis@gmail.com https://youtube.com/@nejashitva?si=O8pqOoIDjDmMBX74

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Nejashi TV // ነጃሺ ቲቪ

Channel Nejashi TV // ነጃሺ ቲቪ (@nejashitvofficial) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 12 749 subscribers, ranking 15 670 in the News & Media category and 2 663 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 12 749 subscribers.

According to the latest data from 08 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 182 over the last 30 days and by 13 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 15.15%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 8.20% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 1 932 views. Within the first day, a publication typically gains 1 046 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 13.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
የነጃሺ ቲቪ ቤተሰብ ስለሆኑ እናመሰግናለን ። የተለያዩ መረጃዎችና እውቀቶች ይገበያሉ ። ተቀላቀሉን ! Facebook: https:// Jeilumedia.com Telegram: https://t.me/nejashitvofficial E-mail: nejashitvaddis@gmail.com https://youtube.com/@nejashitva?si=O8pqOoIDjDmMBX74

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 09 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the News & Media category.

12 749
Subscribers
+1324 hours
+467 days
+18230 days
Posts Archive
አዲዳስ በጋዛ ጦርነት እግሩን ያጣ የእስራኤል ወታደርን በማስታወቂያው ማካተቱ ዓለም አቀፍ ተቃውሞ ገጠመው ነጃሺ ቲቪ || ጳጉሜን 3 / 2018 የጀርመኑ ታዋቂ የስፖርት ትጥቅ አምራች ኩባንያ አዲዳስ ፣ በጋዛው ጦርነት ላይ ተሳትፎ እግሩን ያጣን የቀድሞ የእስራኤል ወታደር በአዲስ የማስታወቂያ ዘመቻው ላይ ማካተቱን ተከትሎ ከባድ ዓለም አቀፍ ተቃውሞ እና የቦይኮት ጥሪ ገጠመው። ማስታወቂያው አዲዳስ ለአካል ጉዳተኞች ያዘጋጀውን የነጠላ ጫማ አገልግሎት የሚያስተዋውቅ ሲሆን፤ በዘመቻው ላይም እ.ኤ.አ በ2021 በእስራኤል እና ጋዛ ግጭት ወቅት ቆስሎ እግሩን ያጣውን ሻሌቭ ቢቶን የተባለ የቀድሞ ወታደር ተጠቅሟል። ግለሰቡ በአንድ የእስራኤል የአዲዳስ ሱቅ ውስጥ ጫማ ሲሞክር እና ሲሮጥ የሚያሳየው ይህ ማስታወቂያ፣ የፍልስጤም ደጋፊዎችን እና የሰብአዊ መብት ተሟጋቾችን ከፍተኛ ቁጣ ቀስቅሷል። የቦይኮት፣ ዲቨስትመንት እና ሳንክሽን (BDS) ዘመቻ አስተባባሪዎች በሰጡት አስተያየት፣ ማስታወቂያው እስራኤል በፍልስጤማውያን ላይ የምትፈጽመውን ወንጀል መደበኛ ለማድረግ የሚደረግ ሙከራ መሆኑን ገልጸዋል። የዘመቻው አስተባባሪ ስቴፋኒ ዌስትብሩክ ለአልጀዚራ እንደተናገሩት፤ "ይህ የአዲዳስ ድርጊት ግድየለሽነት ብቻ ሳይሆን፣ በእስራኤል ጥቃት ወዳጆቻቸውን እና የአካል ክፍላቸውን ባጡ ፍልስጤማውያን ላይ የተሰነዘረ ፍጹም ስድብ ነው" ብለዋል። ይህ ውዝግብ የተነሳው እስራኤል የሰው ሰራሽ እግሮች (prosthetics) እና ህክምና ወደ ጋዛ እንዳይገቡ በማገዷ ምክንያት የጤና ዘርፉ በከፍተኛ ቀውስ ውስጥ በሚገኝበት ወቅት መሆኑ የዓለም አቀፉን ማህበረሰብ ቁጣ ይበልጥ አባብሶታል። የዓለም ጤና ድርጅት እና የዩኒሴፍ መረጃዎች እንደሚያሳዩት፣ እ.ኤ.አ ከአክቶበር 2023 ጀምሮ ባለው ጊዜ ውስጥ ከ42 ሺህ በላይ ፍልስጤማውያን ከባድ የአካል ጉዳት የደረሰባቸው ሲሆን፣ ከነዚህ ውስጥ 11 ሺህ የሚሆኑት ህጻናት መሆናቸው ተመላክቷል። ከ1 ሺህ በላይ የፍልስጤም ስፖርተኞች በተገደሉበት እና በርካቶች የአካል ክፍሎቻቸውን ባጡበት አስከፊ ሁኔታ ውስጥ የተሰራው ይህ ማስታወቂያ፣ ታዋቂ ግለሰቦችንም አስቆጥቷል። ስፔናዊው ታዋቂ ተዋናይ ሃቪየር ባርዴም፣ አሜሪካ-ፍልስጤማዊቷ ደራሲ ሱዛን አቡልሃዋ እና ፓኪስታናዊቷ ደራሲ ፋጢማ ቡቶንን ጨምሮ በርካታ ታዋቂ ግለሰቦች በኩባንያው ምርቶች ላይ ማዕቀብ እንዲጣል በማህበራዊ ሚዲያ ገጾቻቸው ጥሪ አቅርበዋል። በ ሐቢብ በሽር

photo content
+2

የብቁ ትውልድ ማፍርያ ቤት ሱመያ ሱመያ ሱመያ ሱመያ ! የመልካምነት ደግ እሴት ሱመያ ሱመያ ሱመያ ሱመያ የነገ ተስፋ ብሩህ ተምሳሌት ሱመያ ሱመያ ሱመያ ሱመያ በእውቀት ብርሃን ገፎ ጨለማ አዕምሮን ሊ
+2
የብቁ ትውልድ ማፍርያ ቤት ሱመያ ሱመያ ሱመያ ሱመያ ! የመልካምነት ደግ እሴት ሱመያ ሱመያ ሱመያ ሱመያ የነገ ተስፋ ብሩህ ተምሳሌት ሱመያ ሱመያ ሱመያ ሱመያ በእውቀት ብርሃን ገፎ ጨለማ አዕምሮን ሊያንጽ አገር ሊያለማ ራዕይ አንግቦ የታየ ፈክቶ ስሙ የነገሰ ከዳር ዳር ናኝቶ ። ለመጪው ተስፋ ለአገር ለወገን የፊቱን አይተው ተማምነው ነገን ስላልሰሰቱ ከእውቀት ከሃብታቸው ምስጋና ይብዛ ለውለታቸው ። እልፍ እያፈራ በእውቀት መስኩ አብቦ ደምቆ ዝናው ታሪኩ ዘመናት ሊዘልቅ ጥሏል መሰረት የእውቀት ቅርስ ነው የህዝብ ንብረት ። አኽላቅ ሚዘራ ብርሃን የሚያትም ገናና ስሙ ይጠራል የትም ! ለወግ ያበቃ ሺዎች አትርፎ ህይወት ሚያስተምር ከቀለም አልፎ ። የብቁ ትውልድ ማፍርያ ቤት ሱመያ ሱመያ ሱመያ ሱመያ ! የመልካምነት ደግ እሴት ሱመያ ሱመያ ሱመያ ሱመያ የነገ ተስፋ ብሩህ ተምሳሌት ሱመያ ሱመያ ሱመያ ሱመያ ! ከትምህርት አልፎ ሰው የሚሰራ ስሙ ለዓመታት ደምቆ ያበራ ትውልድ ያነጸ ከእውቀት ባሻገር ብቻውን ብዙ ግዙፍ እንደአገር ! ስሙን ያተመ በወርቅ ቀለም የምግባር አምባ የእውቀት ዓለም ተግቶ የጸና ትውልድ በማፍራት የጽናት አርማ የወላጅ ብስራት ። ስኬት ላይ ስኬት እየደረበ የድል ታሪኩን እየከተበ በትጋት ቆሞ አድማሱ ሰፍቷል በምግባር በእሴት ትውልድ አፍርቷል ። ህያው ምስክር ድሉን ተራኪ ሺዎች አፍርቷል ዑማ ተተኪ በለውጥ መንገድ ጎዳና አልፏል 25 ዓመት ድሉ ተጽፏል ።

ኢራን በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ አስተማማኝ የጉዞ መስመር ለመክፈት ከኦማን ጋር መስማማቷን አስታወቀች ነጃሺ ቲቪ || ጳጉሜ 3 / 2018 የኢራን መንግስት በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ ጊዜያዊ እና
ኢራን በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ አስተማማኝ የጉዞ መስመር ለመክፈት ከኦማን ጋር መስማማቷን አስታወቀች ነጃሺ ቲቪ || ጳጉሜ 3 / 2018 የኢራን መንግስት በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ ጊዜያዊ እና ደህንነቱ የተጠበቀ የባህር ላይ የጉዞ መስመር ለመክፈት ከኦማን ጋር ስምምነት ላይ መድረሱን አስታወቀ። የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ እንዳብራሩት፤ ይህ ከሙስካት ጋር የተደረገው አዲስ ስምምነት በቀጣዮቹ ጥቂት ቀናት ውስጥ በዓለም አቀፉ የባህር ኃይል ድርጅት  ዘንድ በይፋ ይመዘገባል ተብሎ ይጠበቃል። ይህ ስምምነት የተደረሰው፤ አሜሪካ እና እስራኤል በኢራን ላይ የከፈቱትን ጦርነት ተከትሎ በባህር ወሽመጡ ላይ የተፈጠረውን ከፍተኛ ውጥረት ለማርገብ መሆኑ ተገልጿል። ዋሽንግተን በኢራን ወደቦች ላይ የባህር ኃይል እገዳ በመጣል ጫና ለማሳደር ብትሞክርም፤ ቴህራን በበኩሏ የነዳጅ ማመላለሻ መርከቦቿን በውሃው ላይ በማሰማራት እና ዓለም አቀፉን የነዳጅ ንግድ በመቆጣጠር በአሜሪካ ላይ የኢኮኖሚ ጉዳት ለማድረስ ስትሰራ መቆየቷ ይታወሳል። በሌላ በኩል ዩናይትድ ስቴትስ፣ ብሪታንያ፣ ፈረንሳይ እና ጀርመን፤ ኢራን የኑክሌር ስምምነት ግዴታዋን አልተወጣችም በሚል ጉዳዩን ወደ ተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት ለመምራት የሚያስችል የውሳኔ ሃሳብ እያዘጋጁ መሆኑ ተሰምቷል። ሆኖም የኢራን መንግስት ይህንን የምዕራባውያን ዲፕሎማሲያዊ እንቅስቃሴ "ከእኩይ ዓላማ የመነጨ" እና ቀውሱን ይበልጥ ለማባባስ ያለመ ነው ሲል አጣጥሎታል። በቃለላህ ሳዲቅ

በመካከለኛው ምስራቅ ውጥረት መባባስ ምክንያት የዓለም አቀፍ የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ ማሳየቱ ተገለጸ ነጃሺ ቲቪ || ጳጉሜ 3 / 2018 በመካከለኛው ምስራቅ ያለው ግጭት ረዘም ላለ ጊዜ ሊቀጥል እና የአቅ
በመካከለኛው ምስራቅ ውጥረት መባባስ ምክንያት የዓለም አቀፍ የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ ማሳየቱ ተገለጸ ነጃሺ ቲቪ || ጳጉሜ 3 / 2018 በመካከለኛው ምስራቅ ያለው ግጭት ረዘም ላለ ጊዜ ሊቀጥል እና የአቅርቦት መስተጓጎል ሊፈጥር ይችላል በሚል ስጋት የዓለም አቀፍ የጥሬ ነዳጅ ዋጋ እያሻቀበ መምጣቱ ተገለጸ። የብሬንት የጥሬ ነዳጅ ዋጋ በ34 ሳንቲም ወይም በ0.35 በመቶ ጭማሪ በማሳየት አንድ በርሜል 97.34 ዶላር የገባ ሲሆን፣ የአሜሪካው ደብሊውቲአይ (WTI) የነዳጅ ዋጋ ደግሞ በ1.15 ዶላር ወይም በ1.26 በመቶ በመጨመር በበርሜል 92.63 ዶላር ደርሷል። ዋጋው ከባለፈው ሐምሌ ወር ወዲህ ከፍተኛው ደረጃ ላይ ሊደርስ የቻለው፣ ኢራን በአሜሪካ ለሚሰነዘርባት ማንኛውም ጥቃት አፀፋዊ ምላሽ እንደምትሰጥ ማስጠንቀቋን ተከትሎ፣ ለዓለም አቀፍ የነዳጅ አቅርቦት ወሳኝት በሆነው የሆርሙዝ መስመር ላይ ስጋት በመፈጠሩ መሆኑን ሮይተርስ ዘግቧል። በ ሐቢብ በሽር

አሜሪካ በኢራን ላይ የከፈተችው ጦርነት ከ100 ቢሊዮን ዶላር በላይ አክስሯታል ሲሉ አንድ የአሜሪካ ሴናተር ዶናልድ ትራምፕን ተቹ ነጃሺ ቲቪ || ጳጉሜ 3 / 2018 የዲሞክራቲክ ፓርቲ ሴናተር ማርክ
አሜሪካ በኢራን ላይ የከፈተችው ጦርነት ከ100 ቢሊዮን ዶላር በላይ አክስሯታል ሲሉ አንድ የአሜሪካ ሴናተር ዶናልድ ትራምፕን ተቹ ነጃሺ ቲቪ || ጳጉሜ 3 / 2018 የዲሞክራቲክ ፓርቲ ሴናተር ማርክ ዋርነር፣ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኢራን ላይ የከፈቱት "አላስፈላጊ ጦርነት" የአሜሪካን ህዝብ ከ100 ቢሊዮን ዶላር በላይ እያስወጣ መሆኑን በመግለጽ የጦርነቱን አካሄድ አጥብቀው ነቅፈዋል። ሴናተሩ በኤክስ (X) ገጻቸው ባሰራጩት የቪዲዮ መልዕክት፤ በጦርነቱ ምክንያት በየሁለት ደቂቃው አንድ ሚሊዮን ዶላር እንደሚባክን ጠቁመው፣ ፕሬዝዳንቱ ያስቀመጡትን ግብ ለማሳካት ምንም የተገኘ ውጤት እንደሌለ ተችተዋል። ዋርነር አክለውም "ምንም አይነት ግልጽ እቅድ፣ ስትራቴጂ፣ አጋር እና የመውጫ መንገድ ሳይኖር ጦርነት ሲከፈት ውጤቱ ይህ ነው" በማለት ዜጎች ተቃውሟቸውን እንዲያሰሙ ጥሪ አቅርበዋል። በ ሐቢብ በሽር

የአረብ ሊግ ኮሚቴ የአልአቅሷ መስጅድ የምንደራደርበት ጉዳይ አይደለም አለ ነጃሺ ቲቪ || ጳጉሜ 3 / 2018 የአረብ ሊግ ኮሚቴ የአልአቅሷ መስጅድ  የምንደራደርበት ጉዳይ አይደለም ሲል ጠንከራ መግለጫ አውጥቷል። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት እና የዩኔስኮ ውሳኔዎችን በመጥቀስ፣ ሙሉው 144 ዱናም ስፋት ያለው የአልአቅሷ መስጅድ ሐራም አልሸሪፍ ግቢ ሙሉ በሙሉ የእስልምና እምነት ተከታዮች የመስገጃ ስፍራ መሆኑን የአረብ ሊግ ኮሚቴ አረጋግጧል። ኮሚቴው በኢየሩሳሌም ቅዱሳት ስፍራዎች ላይ የዮርዳኖስን ታሪካዊ ጠባቂነት ያረጋገጠ ሲሆን፣ በዮርዳኖስ የሚመራው የኢየሩሳሌም አውቃፍ መምሪያ ቦታውን የማስተዳደር ብቸኛ ባለስልጣን መሆኑን ገልጿል፤ አክሎም የእስራኤልን ጥሰቶች ለመከታተልና ይፋ ለማድረግ በካታር የቀረበውን የመገናኛ ብዙሃን መድረክ የማቋቋም ሃሳብ ተቀብሎታል። በኢየሩሳሌም እና በሌሎች የተያዙ የፍልስጤም ግዛቶች የሚፈጸሙ ህገወጥ እርምጃዎችን ለማስቆም፣ ከአረብ ሊግ እና ከእስልምና ትብብር ድርጅት (OIC) ጋር በመቀናጀት የተቀናጀ የዲፕሎማሲና የሜዲያ ዘመቻ ለማካሄድ ማቀዱንም ይፋ አድርጓል። በተጨማሪም እስራኤል ታሪካዊና ህጋዊ ይዞታዎችን እንድታከብርና የእምነት ነጻነትን እንድታስጠብቅ በተባበሩት መንግሥታት የጸጥታው ምክር ቤት በኩል ዓለም አቀፍ ጫናዎች እንዲበረቱ ኮሚቴው ጥሪ ማቅረቡን  ጆርዳን ኒውስ ዘግቧል። በመሐመድ ሚፍታህ

በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፈው የመርከቦች ዝውውር በከፍተኛ ሁኔታ ማሽቆልቆሉ ተገለጸ ነጃሺ ቲቪ || ጳጉሜ 3 / 2018 በመካከለኛው ምስራቅ እየተባባሰ የመጣውን ውጥረት ተከትሎ በስትራቴጂካዊው የሆርሙ
በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፈው የመርከቦች ዝውውር በከፍተኛ ሁኔታ ማሽቆልቆሉ ተገለጸ ነጃሺ ቲቪ || ጳጉሜ 3 / 2018 በመካከለኛው ምስራቅ እየተባባሰ የመጣውን ውጥረት ተከትሎ በስትራቴጂካዊው የሆርሙዝ መስመር በኩል የሚያልፉ የመርከቦች ዝውውር እየቀነሰ መምጣቱን የባህር ላይ ትራንስፖርት መከታተያ መረጃዎች አመላከቱ። ክፕለር የተሰኘው ተቋም ያጠናቀረውን መረጃ ጠቅሶ ሮይተርስ እንደዘገበው፤ ሰኞ ዕለት የንግድ ሸቀጥ የጫኑ ሰባት መርከቦች ብቻ በወሳኙ የውሃ መንገድ አቋርጠው ያለፉ ሲሆን፣ ይህም እሁድለት ካለፉት ስምንት መርከቦች ዝቅ ያለ ነው። በመሆኑም በቀጠናው ባለው አለመረጋጋት ምክንያት በዓለም አቀፉ የባህር ንግድ እንቅስቃሴ ላይ የታየውን መቀዘቅዝ በግልፅ የሚያሳይ መሆኑ ተመላክቷል። በ ሐቢብ በሽር

በኢትዮጵያ ከ46 በመቶ በላይ የሚሆኑ ወጣቶች በሱስ ተጠቂ መሆናቸውን አንድ ሀገራዊ ጥናት ይፋ አደረገ ነጃሺ ቲቪ || ጳጉሜ 3 / 2018 በኢትዮጵያ የወጣቶች የሱስ ተጋላጭነት ከፍተኛ ደረጃ ላይ መ
በኢትዮጵያ ከ46 በመቶ በላይ የሚሆኑ ወጣቶች በሱስ ተጠቂ መሆናቸውን አንድ ሀገራዊ ጥናት ይፋ አደረገ ነጃሺ ቲቪ || ጳጉሜ 3 / 2018 በኢትዮጵያ የወጣቶች የሱስ ተጋላጭነት ከፍተኛ ደረጃ ላይ መድረሱን አንድ ሀገራዊ ጥናት አመለከተ። ጥናቱ ከ15 እስከ 24 ባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ ከ46 በመቶ በላይ የሚሆኑ ወጣቶች የሱስ ተጠቂ መሆናቸውን አመላክቷል። በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል የአእምሮ ሕክምና ስፔሻሊስት የሆኑት ዶክተር አስካለማሪያም ቢክስ ለብስራት ሬዲዮ እንደገለጹት  በወጣቶች ዘንድ የአልኮል ፣ ጫት፣ ሲጋራ እና ለማስታገሻነት የሚያገለግሉ መድኃኒቶች ለሱስ የመጋለጥ ሁኔታው እንዲባባስ ማድረጋቸውን አስረድተዋል። የሱስ ተጠቂነት የሚያስከትለው አእምሯዊና አካላዊ ጫና ከፍተኛ በመሆኑ፣  ወጣቶች ጊዜያቸውን በስፖርት፣ በበጎ ፈቃድ አገልግሎቶችና ትርጉም ባላቸው ተግባራት ላይ በማሳለፍ ራሳቸውን ሊጠብቁ እንደሚገባ ተመላክቷል።

በጋዛ በእስራኤል ጥቃት የተገደሉ ፍልስጤማውያን ቁጥር ከ73 ሺህ 600 በላይ አለፈ ነጃሺ ቲቪ || ጳጉሜ 2 / 2018 እስራኤል በጋዛ ሰርጥ እያካሄደች ባለው ጦርነት የተገደሉ ፍልስጤማውያን ቁጥር
በጋዛ በእስራኤል ጥቃት የተገደሉ ፍልስጤማውያን ቁጥር ከ73 ሺህ 600 በላይ አለፈ ነጃሺ ቲቪ || ጳጉሜ 2 / 2018 እስራኤል በጋዛ ሰርጥ እያካሄደች ባለው ጦርነት የተገደሉ ፍልስጤማውያን ቁጥር 73 ሺህ 658 መድረሱን የፍልስጤም የህክምና ምንጮች አስታወቁ። የዋፋ ዜና ወኪል የህክምና ምንጮችን ጠቅሶ እንደዘገበው፤ ጦርነቱ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ እስካሁን ከ174 ሺህ በላይ ዜጎች ከባድ ጉዳት ደርሶባቸዋል። ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ የሰባት ሰዎች ህይወት ሲቀጠፍ፣ ከ30 በላይ  ቁስለኞች ደግሞ ወደ ሆስፒታል መግባታቸው ታውቋል። ጥቅምት 11 ከተደረገው የተኩስ አቁም ወዲህ ባለው ጊዜ ውስጥ ብቻ 1,352 ንጹሃን የተገደሉ ሲሆን፤ አሁንም በርካታ አስከሬኖች በፍርስራሾች ስር እና በመንገዶች ላይ እንደሚገኙ ተመላክቷል። በተያያዘ ዜና፤ ከዚህ ቀደም በደረሰባቸው የእስራኤል ጥቃት ክፉኛ ቆስለው ማገገም ያቃታቸው ፍልስጤማውያን ህይወት እያለፈ ይገኛል። ከሳምንታት በፊት በሰሜን ጋዛ በጥይት ተመትቶ የነበረው የ6 ዓመቱ ታዳጊ ዳውድ ሙቃታ፣ ከደረሰበት ከባድ ጉዳት ማገገም ሳይችል ቀርቶ ህይወቱ አልፏል። በተመሳሳይ ትናንት ምሽት በጋዛ ከተማዋ ሪማል ሰፈር በንጹሃን ላይ በተሰነዘረ የአየር ጥቃት የቆሰለው ሱብሒ አል-ባትሪኪም ህይወቱ ማለፉ ተረጋግጧል። በ ሐቢብ በሽር

የአወሊያ የጤና ማዕከል በነጻ የአይን ሞራ ገፋፋ ህክምና ሊሰጥ ነው ነጃሺ ቲቪ || ጳጉሜ 2 / 2018 የአወሊያ የጤና ማዕከል መቀመጫውን በዩናይትድ ኪንግደም ካደረገው አል-በስር ኢንተርናሽናል ፋው
የአወሊያ የጤና ማዕከል በነጻ የአይን ሞራ ገፋፋ ህክምና ሊሰጥ ነው ነጃሺ ቲቪ || ጳጉሜ 2 / 2018 የአወሊያ የጤና ማዕከል መቀመጫውን በዩናይትድ ኪንግደም ካደረገው አል-በስር ኢንተርናሽናል ፋውንዴሽን ጋር በመተባበር ከአቅም በላይ ለሆኑ እና በአይን ህመም ለሚሰቃዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ነፃ የአይን ሞራ ገፋፋ ህክምና ሊሰጥ መሆኑን አስታወቀ።  በዊንጌት በሚገኘው የማዕከሉ ግቢ ከ መስከረም 4 እስከ 7 ቀን 2019 ዓ.ል የሚሰጠው ነፃ የህክምና አገልግሎት፤ የአወሊያ ዕርዳታና ልማት ድርጅት ህዝብን ተጠቃሚ ለማድረግ ከሚያከናውናቸው ህብረተሰብ ተኮር ስራዎች አካል መሆኑን ድርጀቱ ለነጃሺ ቲቪ በላከው መግለጫ አስታውቋል። ህክምናውን ማግኘት የሚፈልጉ የህብረተሰብ ክፍሎች ከጳጉሜ 1 ቀን ጀምሮ በጤና ማዕከሉ በአካል በመገኘት መመዝገብ እንደሚችሉ ተገልጿል። በሌላ በኩል የአወሊያ የጤና ማዕከል አገልግሎቱን የበለጠ ለማስፋፋት እና ለማሻሻል በሚደረገው ጥረት ከፍተኛ የሆኑ መዋቅራዊና የቁሳቁስ ለውጦችን ማድረጉ ተጠቁሟል። ማዕከሉ ዘመናዊ የአልትራ ሳውንድ፣ የኤክስሬይ፣ የኬሚስትሪ ማሽኖችን እና የጥርስ ህክምና ወንበሮችን  ጨምሮ በርካታ አዳዲስ የህክምና መሳሪያዎችን በማሟላት እንዲሁም ህንጻውን አድሶ እንደ አዲስ በተደራጀ መልኩ ስራ ለመጀመር ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አስታውቋል። በመሐመድ ሚፍታህ

አሜሪካ በኢራን ላይ የከፈተችው የኢኮኖሚ ጦርነት ዓለም አቀፉን የነፃ ንግድ ሥርዓት የሚጎዳ መሆኑን ቴህራን አስታወቀች ነጃሺ ቲቪ || ጳጉሜ 2 / 2018 አሜሪካ በኢራን ላይ የከፈተችው የኢኮኖሚ ጦ
አሜሪካ በኢራን ላይ የከፈተችው የኢኮኖሚ ጦርነት ዓለም አቀፉን የነፃ ንግድ ሥርዓት የሚጎዳ መሆኑን ቴህራን አስታወቀች ነጃሺ ቲቪ || ጳጉሜ 2 / 2018  አሜሪካ በኢራን ላይ የከፈተችው የኢኮኖሚ ጦርነት በቴህራን ላይ ብቻ ያነጣጠረ ሳይሆን፣ አጠቃላይ ዓለም አቀፉን የነፃ ንግድ እንቅስቃሴ የሚጎዳ መሆኑን የኢራን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለጸ። የመህር ዜና ወኪል እንደዘገበው፤ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ኢስማዔል ባጋኢ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ አሜሪካ በኢራን እና በህዝቦቿ ላይ ለፈጸመችው ወታደራዊ ጥቃት እና ህገ-ወጥ ድርጊቶች ተጠያቂ ልትሆን ይገባል ብለዋል። ሀገራቸው እ.ኤ.አ ከማርች 29 ጀምሮ አሜሪካ ከጽዮናዊው አገዛዝ ጋር በመተባበር ተከታታይ ወታደራዊ ጥቃቶች እና ህገ-ወጥ እርምጃዎች ሲሰነዘሩባት መቆየቷን ያስታወሱት ባጋኢ፤ የአሜሪካ የኢኮኖሚ ጦርነት አዲስ የጫና እና የህገ-ወጥነት ማዕበል መሆኑን አብራርተዋል። ይህ የጫና እርምጃ በኢራን ላይ ብቻ የተወሰነ ሳይሆን በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ፣ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ቻርተር መርሆዎች፣ በሀገራት ሉዓላዊነት እና በነፃ ንግድ ስርዓቱ ላይ የተቃጣ መሆኑንም ቃል አቀባዩ አክለው ገልጸዋል። በ ሐቢብ በሽር

ባለፉት ሶስት ዓመታት ውስጥ ከ1,300 በላይ ሐኪሞች እስራኤልን ለቀው መውጣታቸው ተገለጸ ነጃሺ ቲቪ || ጳጉሜ 2 / 2018 እ.ኤ.አ ከ2023 እስከ 2025 ባሉት ሶስት ዓመታት ውስጥ ቢያንስ 1,
+1
ባለፉት ሶስት ዓመታት ውስጥ ከ1,300 በላይ ሐኪሞች እስራኤልን ለቀው መውጣታቸው ተገለጸ ነጃሺ ቲቪ || ጳጉሜ 2 / 2018 እ.ኤ.አ ከ2023 እስከ 2025 ባሉት ሶስት ዓመታት ውስጥ ቢያንስ 1,370 እስራኤላውያን ሐኪሞች ሀገራቸውን ለቀው መሰደዳቸውን በቴል አቪቭ ዩኒቨርሲቲ የተካሄደ አዲስ ጥናት ይፋ አደረገ። ታይምስ ኦፍ እስራኤል፣ ዋሽግተን ፖስት እና ሌሎች የዜና ወኪሎች የጥናቱን ውጤት ጠቅሰው እንደዘገቡት፤ ይህ አሃዝ እ.ኤ.አ ከ2013 እስከ 2015 ባሉት ዓመታት ሀገር ጥለው ከወጡት 705 ሐኪሞች ጋር ሲነጻጸር እጥፍ ብልጫ እንዳለው ያሳያል። ጥናቱ አንድን የህክምና ባለሙያ 'ከሀገር ወጥቷል' ብሎ የሚመድበው በመጀመሪያው ዓመት ውስጥ ከ270 ቀናት በላይ ከሀገር ውጪ ካሳለፈ እና ከተከታታይ ሶስት ወራት በላይ ወደ እስራኤል ካልተመለሰ እንደሆነ አብራርቷል። የጥናቱ ተባባሪ ጸሃፊ ኢታይ አተር ለሀአሬትዝ  ጋዜጣ እንደተናገሩት፣ የኢኮኖሚ ባለሙያዎች በመንግስት ፖሊሲዎች ምክንያት ከፍተኛ ባለሙያዎች ሀገር ሊለቁ እንደሚችሉ ቀደም ብለው ሲያስጠነቅቁ ቆይተዋል። ፍልሰቱ በፍትህ ማሻሻያ ውዝግቡ ወቅት የጀመረ ሲሆን፤ ከጥቅምት 7ቱ የሐማስ ጥቃት፣ ከጦርነቱ መከፈት እና ከወታደራዊ አገልግሎት ጋር ተያይዞ በተፈጠሩ ልዩነቶች ምክንያት ይበልጥ እየከፋ መምጣቱን ገልጸዋል። በተለይም ሀገር ጥለው ከወጡት ሐኪሞች መካከል 20 በመቶ (ከአምስት አንዱ) ዕድሜያቸው ከ45 ዓመት በላይ የሆኑና ለታዳጊ ሐኪሞች ስልጠና በመስጠት ማዕከላዊ ሚና ያላቸው አንጋፋ ባለሙያዎች መሆናቸው የችግሩን አሳሳቢነት አጉልቶታል። በ ሐቢብ በሽር

ኢራን በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) የሚሰራ አዲስ ሀገር በቀል የጸረ-ቫይረስ ሶፍትዌር ይፋ አደረገች ነጃሺ ቲቪ || ጳጉሜ 2 / 2018 የኢራን መንግስት ያልታወቁ የሳይበር ጥቃቶችን እና ማልዌሮች
ኢራን በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) የሚሰራ አዲስ ሀገር በቀል የጸረ-ቫይረስ ሶፍትዌር ይፋ አደረገች ነጃሺ ቲቪ || ጳጉሜ 2 / 2018 የኢራን መንግስት ያልታወቁ የሳይበር ጥቃቶችን እና ማልዌሮችን መለየት የሚያስችል በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) የሚሰራ አዲስ ሀገር በቀል የጸረ-ቫይረስ ሶፍትዌር ይፋ አደረገ። ‘አይዛ’ የሚል ስያሜ የተሰጠው ይህ ቴክኖሎጂ ይፋ የተደረገው፤ በቴህራን በተካሄደው ግዙፉ የኤሌክትሮኒክስ፣ የኮምፒውተር ቴክኖሎጂዎች እና የኢ-ኮሜርስ አውደ ርዕይ ላይ መሆኑ ተገልጿል። ይህ አዲሱ ሀገር በቀል ቴክኖሎጂ የሀገሪቱን ዲጂታል መሠረተ ልማቶች፣ የባንክ ስርዓቶች እና ተቋማት ከተወሳሰቡ የሳይበር ጥቃቶች ለመጠበቅ ታስቦ የተሰራ መሆኑ ተገልጿል። ሶፍትዌሩ የኢራንን እያደገ የመጣ የሳይበር ደህንነት አቅም የሚያሳይ ከመሆኑም በላይ፤ በውጭ ቴክኖሎጂዎች ላይ ያላትን ጥገኝነት በመቀነስ የሳይበር መከላከያዋን ራሷን ችላ መገንባት መጀመሯን የሚያመላክት ትልቅ ስኬት ሆኖ ተቆጥሯል። ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ ባለሙያዎች እና ኢንጂነሮች የተገነባው ይህ የጸረ-ቫይረስ ሶፍትዌር፤ የኢራን የሳይበር ደህንነት ኢንዱስትሪ ከሸማችነት ወደ ስትራቴጂካዊ የቴክኖሎጂ አምራችነት መሸጋገሩን ያረጋገጠበት ነው ተብሏል። አዲሱ ቴክኖሎጂ ይፋ የተደረገበት ይኸው አውደ ርዕይ፤ በሳይበር ደህንነት እና በሶፍትዌር ዘርፍ የተሰማሩ ከ350 በላይ ተቋማትን ያሳተፈ መሆኑም በዘገባው ተካቷል። በቃለላህ ሳዲቅ

ኢራን ከታጂኪስታን ጋር ያላትን ትብብር ማጠናከር ዋነኛ የውጭ ፖሊሲዋ መሆኑን አስታወቀች ነጃሺ ቲቪ || ጳጉሜን 02 / 2018 የኢራን እስላማዊ ሪፐብሊክ ከታጂኪስታን ጋር ያላትን ሁሉን አቀፍ የሁለ
ኢራን ከታጂኪስታን ጋር ያላትን ትብብር ማጠናከር ዋነኛ የውጭ ፖሊሲዋ መሆኑን አስታወቀች ነጃሺ ቲቪ || ጳጉሜን 02 / 2018 የኢራን እስላማዊ ሪፐብሊክ ከታጂኪስታን ጋር ያላትን ሁሉን አቀፍ የሁለትዮሽ ትብብር ማስፋፋት ዋነኛ የውጭ ፖሊሲዋ መሆኑን የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ማሱድ ፔዜሽኪያን አስታወቁ። ፕሬዝዳንቱ ይህንን የገለጹት፤ ታጂኪስታን ለምታከብረው 35ኛ ዓመት የነጻነት በዓል ለአቻቸው ፕሬዝዳንት ኢሞማሊ ራህሞን የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት ባስተላለፉበት ወቅት መሆኑ ተነግሯል። ፕሬዝዳንት ፔዜሽኪያን በመልእክታቸው፤ ይህ የነጻነት በዓል የታጂክ ህዝብ ለነጻነቱ፣ ለክብሩ እና ለኩራቱ ያለውን ጽኑ አቋም የሚያንጸባርቅ ታሪካዊ ቀን መሆኑን ገልጸዋል። አክለውም፣ በሁለቱ ሀገራት መካከል ለዘመናት የቆየው ታሪካዊ፣ ባህላዊ እና የቋንቋ ትስስር፤ የኢራን እና የታጂኪስታንን የወንድማማችነት ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር እና ለማስፋፋትም  ትልቅ አቅም መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል። በመጨረሻም ፕሬዝዳንቱ፤ ቴህራን ከዱሻንቤ ጋር ያላትን ወዳጅነት ይበልጥ ለማስፋፋት ቁርጠኛ መሆኗን አረጋግጠዋል። ይህ ሁሉን አቀፍ ትብብር የሁለቱን ሀገራት የጋራ ተጠቃሚነት ከማረጋገጥ ባሻገር፤ ቀጣናዊ መረጋጋትን እና ደህንነትን ለማስፈን ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረውም በመግለጫቸው አመላክተዋል። በቃለላህ ሳዲቅ

በሳውድ አረብያ ድንበር ጥሰው ለመግባት ሲሞክሩ ከተያዙት መካከል 58 በመቶ የሚሆኑት ኢትዮጵያውያን መሆናቸው ተገለጸ ነጃሺ ቲቪ || ጳጉሜ 2 / 2018 የሳውድ አረብያ የሀገር ውስጥ ሚኒስቴር ከነሐ
በሳውድ አረብያ ድንበር ጥሰው ለመግባት ሲሞክሩ ከተያዙት መካከል 58 በመቶ የሚሆኑት ኢትዮጵያውያን መሆናቸው ተገለጸ ነጃሺ ቲቪ || ጳጉሜ 2 / 2018 የሳውድ አረብያ የሀገር ውስጥ ሚኒስቴር ከነሐሴ 21 እስከ ጳጉሜ 2 ባሉት ሰባት ቀናት ውስጥ ባካሄደው ሀገር አቀፍ የአደን ዘመቻ፣ የሀገሪቱን የመኖሪያ፣ የድንበር ደህንነት እና የሰራተኛ ህግጋት የጣሱ 14,165 ህገ-ወጥ ነዋሪዎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታውቋል። በዚሁ ኦፕሬሽን ወቅት ድንበር ጥሰው ወደ ሳውድ ለመግባት ሲሞክሩ ከተያዙ 1,315 ሰዎች መካከል ከፍተኛውን ድርሻ - ማለትም 58 በመቶውን - የያዙት ኢትዮጵያውያን መሆናቸው የተረጋገጠ ሲሆን፣ የተቀሩት 41 በመቶ የየመን ዜጎች እና 1 በመቶ የሌሎች ሀገራት ዜጎች ናቸው። ከተያዙት አጠቃላይ ሰዎች መካከል 7,121ዱ በመኖሪያ ህግ ጥሰት ፣ 3,636ቱ የድንበር ደህንነት ህግ በመተላለፍ እንዲሁም 3,408ቱ በሰራተኛ ህግ መጣስ የተከሰሱ ናቸው። በተጨማሪም የሳውድ ባለስልጣናት በዚሁ ሳምንት ውስጥ 12,363 ህገ-ወጥ ነዋሪዎችን ወደ ሀገራቸው የመለሱ ሲሆን፣ 18,937 ሰዎችን ደግሞ የጉዞ ሰነድ እንዲያዘጋጁላቸው ወደየሀገራቸው ዲፕሎማቲክ ሚሲዮኖች መምራታቸውን ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅት 27,845 ወንዶች እና 1,928 ሴቶችን ጨምሮ በጠቅላላው 29,773 የውጭ ሀገር ዜጎች በህጋዊ የህግ ማስከበር ሂደት ላይ ይገኛሉ። በመሐመድ ሚፍታህ

በኦሮሚያ ክልል ሞጆ ከተማ ኢቅራ የቁርአን ት/ቤት ተማሪዎቹን በደማቅ ሁኔታ አስመረቀ በኦሮሚያ ክልል ሞጆ ከተማ የሚገኘው ኢቅራ የቁርአን ት/ቤት በቁርአን እና በእስላማዊ እውቀት ዘርፎች ሲማሩ የቆዩ ተማሪዎቹን በደማቅ ሥነ-ሥርዓት አስመርቋል። የምረቃ መርሃ ግብሩ ጷጉሜ 1 ቀን 2018 ዓ.ል. በሞጆ ከተማ ዳኤማ ሆቴል የተካሄደ ሲሆን፣ በዝግጅቱ ላይ የት/ቤቱ አመራሮች፣ ታዋቂ ዱአቶች፣ መምህራን፣ የተማሪዎች ወላጆች እና የአካባቢው የሙስሊም ማህበረሰብ ተገኝተዋል። ነጃሺ ቲቪም በሥፍራው ተገኝቶ የምረቃ መርሃ ግብሩን ተከታትሎ ዘግቧል። በዝግጅቱ የተመረቁ ተማሪዎች በቁርአን ንባብ፣ በተጅዊድ እና በተለያዩ የእስላማዊ እውቀት ዘርፎች ያሳዩት እድገት ተወድሷል። ለተማሪዎቹም የእውቅና ሰርተፍኬት ተበርክቶላቸዋል። የኢቅራ የቁርአን ት/ቤት አስተዳደር እና መስራች ኡስታዝ ሰኢድ ካሳ ባስተላለፉት መልዕክት፣ ተመራቂ ተማሪዎች የተማሩትን የቁርአን እውቀትና እሴቶች በተግባር በማዋል ለማህበረሰባቸው ጠቃሚ ዜጎች እንዲሆኑ ገልጸዋል። በምረቃ መርሃ ግብሩ ላይ ተማሪዎቹ የቁርአን ንባብ፣ የእስላማዊ ትምህርት ትርኢቶች እና ልዩ ልዩ ፕሮግራሞችን በማቅረብ የተሳታፊዎችን ቀልብ ስበዋል። በተጨማሪም ለተመራቂዎቹ የስኬትና የተባረከ የወደፊት ሕይወት የሚመኙ ዱአዎች ተደርገዋል። የቁርአን ትምህርት የሃይማኖታዊ እውቀትን ከማስጨበጥ ባለፈ ሥነ-ምግባርን፣ ሀላፊነትን እና የተሻለ ማህበረሰብ ግንባታን ለማጠናከር ከፍተኛ ሚና እንዳለው በመርሃ ግብሩ ተገልጿል።

photo content
+6

አዱረቱ አል መክኑና የተርቢያ እና የቁርዓን ማዕከል 95 ተማሪዎችን በቁርዓን ሒፍዝ እና በሸሪዓ ትምህርት አስመረቀ ነጃሺ ቲቪ || ጳጉሜ 1 / 2018 የአዱረቱ አል መክኑና የተርቢያ እና የቁርዓን
+5
አዱረቱ አል መክኑና የተርቢያ እና የቁርዓን ማዕከል 95 ተማሪዎችን በቁርዓን ሒፍዝ እና በሸሪዓ ትምህርት አስመረቀ ነጃሺ ቲቪ || ጳጉሜ 1 / 2018 የአዱረቱ አል መክኑና የተርቢያ እና የቁርዓን ማዕከል «ኑኽባ» በሚል መሪ ቃል የቁርዓን ሐፊዞችን ለሶስተኛ ዙር  አስመርቋል።  በዚህ የምረቃ ስነ ስርዓት ላይ በተመላላሽ፣ በክረምት አዳሪ  እና በአመት አዳሪ ፓኬጆች እስከ ሁለት ዓመት ሲከታተሉ የቆዩ አጠቃላይ 95 ተማሪዎች ተመርቀዋል። በዕለቱም  ልዩ ልዩ አዝናኝና አስተማሪ ፕሮግራሞች የቀረቡ ሲሆን፣ ከፍተኛ ውጤት ላመጡና የተሻለ አፈጻጸም ላሳዩ ተማሪዎች የሽልማትና የእውቅና ስነ ስርዓት ተካሂዷል። በምረቃው ስነ ስርዓት ላይ ንግግር ያደረጉት የማዕከሉ መስራች እና ስራ አስኪያጅ ኡስታዛ ጀሚላ መሐመድ ለተመረቁ ተማሪዎችና ለቤተሰቦቻቸው የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። አክለውም የ2018 የትምህርት መርሃ ግብር መስከረም 8 ተጀምሮ ተማሪዎች በተለያዩ መመዘኛዎች አልፈው ወደ ሒፍዝ መግባታቸውን አብራርተዋል። በቆይታቸውም ከቁርዓን ሒፍዝ ባሻገር ተፍሲር፣ ሐዲስ፣ ፊቅህ እና ሲራን ያካተቱ የሸሪዓ ትምህርቶችን፣ ለአካላዊ ጥንካሬ የሚረዱ የስፖርት እንቅስቃሴዎችን እና ሀገራቸውን የሚያውቁበትን የመስክ ጉብኝቶች ከወትሮ ትምህርታቸው ጎን ለጎን እንዲወስዱ መደረጉን ገልጸዋል። የአዱረቱ አል መክኑና የተርቢያ እና የቁርዓን ማዕከል ላለፉት 15 ዓመታት በቁርዓን ሒፍዝ፣ በተርቢያ፣ በሐዲስ እና በሲራ ትምህርት ዘርፍ በጽናት ሲያገለግል የቆየ መሆኑ ተመላክቷል። በመጨረሻም የማዕከሉ ስራ አስኪያጅ ኡስታዛ ጀሚላ የአላህን ቃል ለትውልድ ለማሻገር ለረዳቸው ፈጣሪ ምስጋና አቅርበው፣ ለዚህ ታላቅ ስኬት ከጎናቸው ለነበሩ አካላት ሁሉ ላቅ ያለ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። በመሐመድ ሚፍታህ