cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

ሌላ ሠው

ሁሉም ሠው ሌላ ሠው ሌላውም ሠው አንደኛው ሠው ነው፡፡

Show more
Advertising posts
521
Subscribers
No data24 hours
-77 days
-1530 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

Show all...
DroJob | Get paid doing simple tasks

Make money online by watching ads, filling out surveys, sharing your opinion, solving captcha, answering questions and more.

👆😆እሪ ብዬ ጮኩ😆👆 ኢትዮጵያ ሀገራችን ካፈራችው መንገድ አንድ መንገድ አለ ሁሌ መገድምበት ከቤቴ ስወጣ ስመለስም ሆነ ይችን መንገድ ማለፍ ምርጫዬ ግድ ሆነ በዛ ስመላለስ ያየኝ ሰው በሙሉ ጓደኛው መስዬው ሰላም ነህ ይላሉ እኔም በተራዬ አፀፋውን መልሼ መንገዴን ስቀጥል የሱስ አለህ ጋሼ የሚል ድምፅ ይመጣል ከወደ ኃላዬ በዚህ እድሜ ብትሰራ ለኔም በሰጠኸኝ የሚበላ እንጀራ ብዬ የበኩሌን ምክር መሳይ ቁጣን ከሰጠሁ በኃላ መንገዴን ጀመርኩኝ ደግሞ እንዳይጠንቀኝ ልጁም በበኩሉ ግብራበር ሰብስቦ መንገዴን ዘጋብኝ ግራ ተጋባውኝ እነዚህ ጠብደሎች ሁለት እጄን ይዘው አንዱ በጥፊ ሲል አንዱ ኪስ ሲገባ በመሀል ከተማ ግራ እስክጋባ አየር ለመተንፈስ አፌ ሲለኝ እንቢ ከነሱ ስታገል ለነብስ ውጪ ግቢ እጅኩን ደከምኩኝ ተስፋዬን ቆረጥኩኝ የግዴን አምጬ እየተፍጨረጨርኩኝ ባለኝ በሌለኝ ሀይል እሪሪሪ ብዬ ጮኩ!! Note;አርዕስቱ ገጣሚው በማላስታውሰው ከሌላ ግጥም ላይ የተወሰደ ነው። @Bekiwdu
Show all...
👍
Show all...
bereketalemahyhu on TikTok

#እሪ ብዬ ጮኩ🙄 😁😁😁

👍
✝ዛሬም ፋሲካ ነው✝ @lelasw በሕግ ተወጥሬ - በኀጢአት ታስሬ ከፅድቅ ተገፍቼ - ለኩነኔ ሞቼ ለድካም ዘብ ቆሜ - ቀንበር ተሸክሜ ምርኩዜ ሸንበቆ - የሚሰበር ወድቆ ፍሬ የሌለበት - በደረቅ ሰውነት በጨለማ ህይወት - በድንግዝ መሰረት ሁሌ እንደሚናፍቅ - እንደሚሻ ልቡ ከከነሀን ወተት - የግብፅን ባርነት የሶስቱን ቀን መንገድ - አርባ እደሆነበት እንደዛ ነበረ - የሁላችን ህይወት @lelasw ይህን ተመልክቶ - አልችል ቢለው ልቡ እንደተስፋ ቃሉ - ሊታደገን ወዶ ከሰማይ ሰማያት - ከዙፋኑ ወርዶ እኛኑ ሊያነፃ - ሊታደገን ወዶ በሸላቾቹ ፊት - ቃልም አላወጣ እሱ ፃድቅ ሳለ - ቀንበር የበዛብን እኔና እናንተን - ነፃ ሊያወጣ የእግዚአብሔር ልጅ እሱ - እኛን መስሎ መጣ @lelasw ይሄ ሆኖ ሳለ - በመስቀል መሞቱ ሞቱን የአንድ ቀን - እያደረጋቹ እንዳትሳሳቱ እለት እለት እንጂ - መዳን የሚሆነው ለአንድ ቀንማ - ለአንድ ለሊትማ አይደል መጠረቁ - ኀጥያት መውሰዱ ለዘመናት መርገም - ነውንጂ መሞቱ እርቃኑን በስቃይ - በመስቀል መዋሉ አይደለም የአንድ ቀን - እውነት አታብሉ @lelasw እርግማን ስለኛ - የሆነው መድህኔ ህይወትን ሊቸረን - ፅድቅን ሊያስታጥቀን መሀዛ ጠረኑን - ለኛ ያለበሰን በህይወት ሊቀይረው - እንዳዲስ ሊያስውበው መች ሆነ የአንድ ቀን - የመስቀል ላይ ስራው ለአዲስ ኪዳን ትዉልድ - መስቀሉን ለያዝነው በእየሱስ ስራ - ዘመን ለተቸረው በክርስቶስ አምነን - በስሙ ለዳንነዉ ልጁ የሞተበት - ደም የፈሰሰበት አትርሱ አስታውሱ - ዛሬም ፋሲካ ነዉ!! @lelasw ✝ ✝ 😍😍😍😍 ተባረኩ 😍😍😍😍 ✍በረከት አለማየሁ @Bekiwdu ...... ☺️☺️☺️
Show all...
👍
😘😘ባልኩልሽ😘😘 @lelasw              @lelasw ፍቅር ላንቺ ቃላት ጠፋ መውደድ ላንቺ ቅኔ ታጣ የቅርፅሽን ውበት ገልፆ የሚያወጣ የሰራ አካላትሽን ጥበብ የሚያወራ አንዳች ቅኔ ጠፋ አንቺን የሚያብራራ ያ ወለላ ከንፈር በምን ይገለፃል ያ ተክለ ሰውነት እንዴት ይተረካል ያ ተረከዝ ባትሽ በምን ይናገራል እንኳን ጎረምሳውን ቄሱን ያስከጅላል                  @lelasw እነዛ ወይዛዝርት አንቺን ሲሳደቡ ወይባ እየታጠኑ ሂና እየተቀቡ ያንቺ ውበት ደብዝዞ እነሱ ሲያብቡ ቃላት ጠፍቶኝ እንጂ አይደለም ፈርቼ ያልተደባለቀ የተፈጥሮ ውበት አንቺ ላይ አይቼ በሀገሬም እንዳለው የተፈጥሮ ውበት ያልተቀላቀለ የእግዜር ሸማ ጥለት እንደ ፀደይ ዘመን እንደብራው ወራት እንደ እቡጥ አበባ የፈካ አካላት እንደ አባይ ጅረት እንደ እጣን ጢሱ ባልኩልሽ ውበትሽን ለሚያንኳስሱ!! @lelasw              @lelasw ✍በረከት አለማየሁ(ቤኪ ውዱ) @Bekiwdu.......😍😍😍
Show all...
👍
😇ዘመኔን አስታውቀኝ😵‍💫 @lelasw በድንገት እንዳይሆን የመምጣቴ ጥሪ ዘመኔን አስታውቀኝ የቀኖቼን ቀሪ ጀምበር ሳትቆለቁል ድካም ደጅ ሳይደርስ በጉብዝናዬ ወራት ጭንቁ ቀን ሳይነግስ እንደባለ አእምሮ ፈቃድህን መርምሬ መክሊቱን ነግጄ ላንተ ክብር ኖሬ ባላፊዋ ዓለም ግብዣ ሳልደለል ሰልፉን ተዋግቼ ገድሉን እንድጋደል እባክህ ጌታዬ ዘመኔን አስታውቀኝ ምን ያህሉን ኖሬ ምን ያህሉ ቀረኝ?? @lelasw ✍ ወርቁ ለገሰ
Show all...
👍
@Lelasw ስኮትላንዳዊውና እንግሊዛዊው ዱር ውስጥ እየተንሸራሸሩ ሳሉ አንበሳ ከፊት ለፊታቸው ሲመጣ አዩ። ይኼኔ ስኮትላንዳዊው ያደረገውን ትልቅ የቦት ጫማ በፍጥነት አውልቆ ቀለል ያለ ሸራ ጫማ ማጥለቅ ጀመረ። <<ይኼ ምን ይጠቅምሃል ወዳጄ??>> አለ እንግሊዛዊው በመገረም <<መቼም አንበሳን ሮጠህ ማምለጥ አትችልም??>> <<ልክ ነህ እሱንማ አልቀድመውም አንተን ግን እቀድምሃለው>>። አለው አሉ አረፈዓይኔ ሐጎስ (የስኮትላንዳዊያን ቀልዶች 2005) 👇👇 https://t.me/Lelasw
Show all...
ሌላ ሠው

ሁሉም ሠው ሌላ ሠው ሌላውም ሠው አንደኛው ሠው ነው፡፡

👍
😞የሞት ሸለቆ😄 @Lelasw ማለፊያው ሸለቆ - ጨለማ ታጭቆ ላይዘለቅ ርቆ - ቢያጠላም ደቅድቆ ጸንቶ ለዘለቀ - ቃሉን ለጠበቀ እየጨለመ ቀን - ቢከብድም ጽልመቱ አይቀርም በጌታ - ታልፎ መረሳቱ። @Lelasw ✍ ወርቁ ለገሰ
Show all...
👍
😋ቀኑልኝ ቀኖቼ🧐 @Lelasw እኔ ስጠብቀው እሱም ሲጠብቀኝ ተራርቀን ከረምን ከቀን ሳንገናኝ ለካስ ጌታም አለው ጊዜና ዘመኑ ከሱ ጋር ስታረቅ ቀኖቹም አቀኑ። @Lelasw ✍ ወርቁ ለገሰ
Show all...
👍