ውሉደ ያሬድ ሰንበት ትምህርት ቤት
Open in Telegram
“ጽዮንን የሚወዳት አይደክምም” ቅዱስ ያሬድ ይኽ በደብረ ይባቤ ቅዱስ ያሬድ ቤተክርስቲያን የውሉደ ያሬድ ሰንበት ትምህርት ቤት የቴሌግራም አውታር ነው፡፡ የውሉደ ያሬድ ሰንበት ት/ቤት መንፈሳዊ ጽሑፎችን፣ ወቅታዊ ኹኔታዎችን የሚገልጹ መረጃዎችን እንዲኹም ማስታወቂያዎችን በዚኽ ገጽ ለተከታታዮቹ ያስተላልፋል፡፡ መልእክት ወይም አስተያየትና ጥቆማ ካሎት ⬇️⬇️
Show more6 018
Subscribers
+524 hours
No data7 days
-2630 days
Posts Archive
✍️Facebook👇🔔
https://www.facebook.com/wuludeyared.sundayschool/
✍️YouTube👇🔔 https://www.youtube.com/@wuludeyaredsundayschool1962
✍️Telegram👇🔔
https://t.me/wuludeyared
✍️ Tiktok
https://www.tiktok.com/@wuludeyared?_t=8Zq6i8ZXkoA&_r=
🌴🌴🌴🌷🌷🌷🌴🌴🌴🌷🌷🌷🌴🌴🌴
እንኳን
#ከሰባ_ሁለቱ_አርድእት አንዱ ለሆነው #ሐዋርያው_ቅዱስ_ጳውሎስ መልእክት ለጻፈለት #ለከበረ_ሐዋርያ_ለቅዱስ_ቲቶ_ለዕረፍቱ_መታሰቢያ_በዓል በሰላም አደረሰን። እግዚአብሔር አምላክ ከቅዱሱ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜
የጳጉሜን ወር በጸሎት በንስሓ ተወስነን ወደ አዲሱ ዓመት የምንሸጋገርባት ድልድይ ናት፡፡ ከዚህም የተነሳ እግዚአብሔር የፈቀደላቸው የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ምእመናን ጸሎት በመጸለይ ጸበል በመጠመቅ ያስቧታል፡፡ በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ካሉት ሁለት የፈቃድ አጽዋማት መካከል አንዱ በዚህ በጳጉሜን ወር የምንጾመው ሲሆን መሠረት የሚደረገውም ጾመ ዮዲት ነው፡፡ የዮዲት ጾም የሚባለውም እርሷ ስለ ጾመችው ነው፡፡ ይህን መሠረት አድርገው ሕዝቡ ሳይቀር “ጳጉሜን ዕድሜ ትሰጠናለች፤ በኋላም ታድነናለች” ብለው ጾም ይጾሙባታል፡፡ (ምንጭ-ቅዱስ መልከ ጸዴቅ ድርሳን)፤ በሀገራችንም ንግሥት ዘውዲቱ እና ምኒልክ የጾም ሥርዐት ይፈጽሙባት ነበር፡፡ ሌሎችም ሽማግሌዎችና ባልቴቶች አክብረው ይጾሙባታል፡፡ የጳጉሜንን አቆጣጠር አንዱ ከቀን ጋራ ሲያደርገው፣ ሌለኛው ደግሞ ከወር ጋራ ቢያደርገውም በሁሉም አቆጣጠር ውስጥ ሕያዊት ሆና መገኘቷ የታወቀ ነው፡፡
የዐውደ ዓመት መሸጋገሪያ ናት፡
ይህም ጳጉሜን ከአሮጌው ዓመት ወደ አዲሱ ዓመት፣ ከክረምት ወቅት ወደ ጸደይ መሸጋገሪያ ናት፡፡ ጳጉሜን የዓመቱ መጨረሻ ወር ናት፡፡ ወርኃ ጳጉሜ አዲሱን ዓመት ለመቀበል የዝግጅት ጊዜ ናት፡፡ ስለሆነም አዲሱ ዘመን የሰላም፣ የፍቅር፣ የአንድነት፣ የልማት፣ የመተሳሰብ ዘመን እንዲሆንልን በጾምና በጸሎት ማሰብ እጅግ አስፈላጊ ነው፡፡
ነገረ ምጽአት የሚታሰብባት ናት
የጳጉሜን ወር የነገረ ምጽአት የሚታሰብባት ስትሆን ምጽአት ማለት የጌታን መምጣት የሚያስረዳ በመሆኑም ቤተ ክርስቲያን የጌታን ምጽአት በዓመት ሁለት ጊዜ ታስታውሳለች፤ ይኸውም በጳጉሜን ወርና በጌታ ጾም እኩሌታ (በደብረ ዘይት) ነው። ቅዱስ ዳዊት ”እግዚአብሔር ግልጥ ሆኖ ይመጣል፤ ዝም አይልም፤ እሳት በፊቱ ይነዳል፤” እንዲል፤ (መዝሙረ ዳዊት ፵፱ ፣ ፪-፬)፡፡ ይህ ስለ ነገረ ምጽአት ያስረዳል፡፡
ይህም ጳጉሜን ከአሮጌው ዓመት ወደ ዐዲሱ ዓመት፣ ከክረምት ወቅት ወደ ጸደይ ወቅት መሸጋገሪያ እንደሆነች ሁሉ ምጽአትም ከጊዜያዊው ወደ ዘላለማዊ፣ ከምድራዊ ወደ ሰማያዊ፣ ከዚህ ዓለም ወደ ወዲያኛው መሸጋገሪያ ናትና ነው፡፡ ጳጉሜን የክረምቱ ማብቂያ እንደሆነች ሁሉ ምጽአትም በመጨረሻው ዘመን መከራ የሚበዛበት የዚህ ዓለም ማብቂያ ናት፡፡ ወርኃ ጳጉሜን አዲሱን ዓመት ለመቀበል የዝግጅት ጊዜ እንደሆነች ሁሉ ምጽአትም ጻድቃን ዐዲሲቷን ምድር (መንግሥተ ሰማያትን) ለመውረስ ተዘጋጅተው “ኑ የአባቴ ብሩካን ዓለም ሳይፈጠር የተዘጋጀላችሁን የእግዚአብሔር መንግሥት ውረሱ” የሚባሉባት ቀን ናት፡፡ የጌታ አመጣጥ ሳይታሰብ ነውና በተሰጠን ጸጋ ቅዱስ አምላካችንን እያመሰገንን ተዘጋጅተን እንድንጠብቀው የድንግል ማርያም ልጅ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ይርዳን፤ ቀጣዩ ዘመንም ቃሉን ፈጽመን መልካም ፍሬ የምናፈራበት ዓመት ይሁንልን፤ አሜን !!!
©ማኅበረ ቅዱሳን
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
ጳጉሜን የሚለው ስያሜዋ ግን “ሄፓጉሜኔ” ከሚለው የግሪክ ቃል የመጣ መሆኑን አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ ተነግሯል፡፡ “ኤፓጉሜኔ” ማለት ጭማሪ ማለት ነው፡፡ በግእዝ ቋንቋችን ተውሳክ ማለት ነው፡፡ ተውሳክ ማለት ተጨማሪ ማለት ነው፡፡ “ወሰከ - ጨመረ” ከሚለው የግእዝ ግስ የተገኘ ነው፡፡ (ምንጭ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገበ ቃላት ኪዳነ ወልድ ክፍሌ ገጽ ፱፻፭)፡፡ ምዕራባዊያኑ ጳጉሜን ተጨማሪ ቀን አድርገዋታል፡፡ እኛ ግን የወር ተጨማሪ አድርገናታል፡፡ በጽርዕ ኤፓጉሜኔ ትባል እንጂ ሊቃውንት ግን ተረፍ ይሏታል፡፡ ጳጒሜን የአሮጌው ዓመት ማብቂያ የአዲሱ ዓመት መንደርደሪያ ዕለት እንደሆነች የክርስቶስ ልደትም የዓመተ ፍዳ ማቆሚያ የዓመተ ምሕረት መጀመሪያ በመሆኑ ዕለታቸው ራሱ በተመሳሳይ ቀን ተቀምሮ ይውላል፡፡
የጳጉሜን ወር ‹‹የምሕረት ወር›› ስለመባሏ፡-
ኢትዮጵያ በዓለም ብቸኛዋ የ፲፫ ወራት ጸጋ ባለቤት ስትሆን የጳጉሜን ወርም በኢትዮጵያውያን ዘንድ የምሕረት ወር ተብሎ ይታመናል። በተለይም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ መሠረት ጸሎት የሚያርግበት ዕለተ ምጽአት የሚታሰብበት የምሕረት ወር መሆኑን ታስተምራለች፡፡ በተለይም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እምነት መሠረት ምእመናኑ በጳጉሜን ጸበል በመጠመቅ ድኅነት በማግኘታቸው የምሕረት ወር መሆኑን ምእመናን ያብራራሉ፡፡
🌴🌴🌴🌷🌷🌷🌴🌴🌴🌷🌷🌷🌴🌴🌴
እንኳን
#ለወንጌላዊው_ለቅዱስ_ዮሐንስ_ረድዕ
#ለሐዋርያውና_ለሰማዕቱ_ለከበረ_ዑቲኮስ_ለዕረፍት_በዓል፣ #ለአባ_ሖር_ወንድም #ለሰማዕቱ_ለቀሲስ_ቅዱስ_ብሶይ_ለዕረፍት_በዓል እንዲሁም #መጥምቀ_መለኮት_ቅዱስ_ዮሐንስ ሄሮድስን የወንድምህን የፊልጶስን ሚስት ሄሮድያዳን ማግባት የለብህም ብሎ ይገስጸው ስለነበር በሳምንቱ በልደቱ ቀን መስከረም 2 እስኪገለው ድረስ ወደ እስር ቤት ለገባበት ለመታሰቢያ በዓሉ (ለታሰረበት) አደረሰን። በተጨማሪም በዚህች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከከበሩ #ከአባ_ጳኩሚስ እና #ከአባ_ሰራብዮን ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
እንኳን
ከዐሥራ ስድስቱ ነቢያት አንዱ #ለታላቁ_ነቢይ _ሚልክያስ_ለዕረፍቱ_በዓል፣
#ለሀገረ ፈርማ ኤጲስቆጶስ #አባ_ሙሴ_የዕረፍቱ_መታሰቢያ በሰላም አደረሰን።
በተጨማሪም በዚህች ቀን ጌታችን በባሕር ውስጥ ለሐዋርያው እንድርያስ በሊቀ ሐመር አምሳል ተገልጦ ድንቅ ተአምር አደረገለት። እግዚአብሔር አምላክ ከቅዱሳኑ ረድኤትና በረከትን ይክፈለን።
🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜
🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨
"ከእግዚአብሔር ቤት መረቅናችሁ " መዝ ፻፲፰፥ ፳፮በሰንበት ትምህርት ቤታችን በመደበኛ የህፃናት መርሐ ግብር ዓመቱን ሙሉ እና በክረምት ያስተማርናቸዉ ተማሪዎች የምርቃት መርሐ ግብር
ቅዳሜ ነሐሴ 30 ቀን 2018 ከቀኑ 7:00ደብረ ይባቤ ቅዱስ ያሬድ ቤተክርስቲያን አዘጋጅ ዉሉደ ያሬድ ሰ/ት/ቤት ህፃናት ክፍል 🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
እንኳን
#ለቅዱስ_አባ_ዮሐንስ_ሐጺር_(ፍልሠቱ)
#ለቅዱስ_አትናቴዎስ_ሰማዕት፣ #ለቅዱሳን_ገርሲሞስና_ቴዎዶጦስ_(ሰማዕታት)፣ ዓመታዊ የመታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሰን።
በተጨማሪም በዚህች ቀን ከሚታሰቡት፡- #ከአባ_ባስልዮስ_ጻድቅ_(ዘትግራይ) ከመታሰቢያ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ይክፈለን።
🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜
🌴🌴🌴🌷🌷🌷🌴🌴🌴🌷🌷🌷🌴🌴🌴
እንኳን
#ለቅዱስ_አብርሃም_(የአባቶች አለቃ)፣ #ለቅዱስ_ይስሐቅ_(የአባቶች አለቃ)፣ እንዲሁም #ለቅዱስ_ያዕቆብ_(የአባቶች አለቃ) ዓመታዊ የመታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሰን። እግዚአብሔር አምላክ ከቅዱሳኑ ረድኤትና በረከት ያሳትፈን።
🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜
🌴🌴🌴🌷🌷🌷🌴🌴🌴🌷🌷🌷🌴🌴🌴
እንኳን
#ከሰባቱ_ሊቃነ_መላእክት_አራተኛ ለሆነው ለመላእክት አለቃ #ለቅዱስ_ሱርያል ለበዓሉ መታሰቢያ፣ #ለኢትዮጵያዊው_ጻድቅ ሲዖል ውስጥ ገብተው ይጸልዩ ለነበሩት ለታላቁ አባት #ለአቡነ_ዘርዐ_ብሩክ_ለልደታቸው_በዓል፣ ለአባቶቻችን #ለዐሥራ_ሁለቱ_ለቅዱስ_ያዕቆብ_ልጆች ለመታሰቢያቸው በዓል፣ በሊቀ ካህናት ኤሊ ዘመን #ለነቢዩ_ቅዱስ_ሳሙኤል_ለመጠራቱ ለመታሰቢያው በዓልና ሰብሲር ከሚባል አገር ለሆነ #ለቅዱስ_ብንያሚንና_ለእኅቱ_ለቅዱስ_አውዶክስያ ሰማዕትነ ለተቀበሉበት ለዕረፍታቸው በዓል በሰላም አደረሰን።
በጨማሪም በዚህች ቀን ከሚታሰቡ፦ #ከእሰክድርያው_ቅዱስ_ፊቅጦርና #ከእናቱ_ሣራ ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜
✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
የወንድሞች እና የእህቶች ጉባኤ
🗓 ዛሬ
🕕ከ12:00 ሰዓት ጀምሮ በሰንበት ት/ቤታችን አዳራሽ
ሁላችኹም ከዚህ መልካም መዓድ ከምሽቱ 12:00 ጀምሮ እንድትቋደሱ ተጋብዛችኋል!
✨"ጽዮንን የሚወዳት አይደክምም"
ቅዱስ ያሬድ✨
✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨
✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨
“ትሕትና ማለት ራስን መጥላት ሳይሆን፣ ራስን ማወቅ ነው። ራስህን ስታውቅ፣ ያለ እግዚአብሔር ጸጋ ምንም እንደማትሆን ትረዳለህ፤ ያኔ በትክክል ትሑት ትሆናለህ።››
ቅዱስ አውግስጢኖስ
የሰው ልጅ የልቡን በር ከውስጥ እንጂ ከውጭ መክፈት አይችልም ፡ እግዚአብሔርም ቢሆን በሩን ያንኳኳል እንጂ ሰብሮ አይገባም ፡ መክፈትና አለመክፈት የአንተ ፈቃድ ነው ፡፡
አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
"ዕለትን የሠጠህ እርሱ ለዕለት የሚበቃህንም ይሠጥሃል!"
ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ
“በጠላቶችህ እጅ እንዳትወድቅ ወደ አቆምካቸው ኃጢአቶች አንዳትመለስ በሌሎች ላይ አትፍረድ ምንም እንኳን ምክኒያት ቢኖርህ ማንንም አትንቀፍ ህጉን ለመፈፀም አቅቶት ወንድምህን ብታየው እንኳን አትማው ስሙንም አታጥፋ።''
ቅዱስ አባ አንጦንስ
✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨
🌴🌴🌴🌷🌷🌷🌴🌴🌴🌷🌷🌷🌴🌴🌴
እንኳን
#ለብጽዕት_ሣራ_(የአብርሃም ሚስት) #ለቅዱሳን_አባ_ሞይስስና_እህቱ_ሣራ_ሰማዕታት ዓመታዊ የመታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪም በዚህች ቀን ከሚታሰቡ፡- #ከቅዱሳን_አጋቦስና_ቴክላ_ሰማዕታት_ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜
🌴🌴🌴🌷🌷🌷🌴🌴🌴🌷🌷🌷🌴🌴🌴
እንኳን #ለአባ_እንጦንስ_ደቀ_መዝሙር_ለሆነ ታላላቅ ተአምራቶችን ላደረገ ለታላቁ አባት #ለአባ_ቢጻርዮን_ለዕረፍት_በዓል፣ #ለቅዱስ_እንድርያኖስና_ሃያ_አራቱ_ባልንጀሮቹ ሰማዕታት ለዕረፍታቸው በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪም በዚህች ቀን ከሚታሰቡ፦ #ከኤልያኖስ_ከእኅቱ_አውዶክስያ ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜
🌴🌴🌴🌷🌷🌷🌴🌴🌴🌷🌷🌷🌴🌴🌴
የእናታችን የቅድስት ክርስቶስ ሠምራ የዕረፍት በዓል እና የጻድቁ አቡነ ተክለሃይማኖት የዕረፍት በዓል በሥጋና ደብራችን በደብረ ይባቤ ቅዱስ ያሬድ ቤተክርስቲያን በዚህ መልኩ ተከብሮ ውሏል።
እናታችን ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ በቃል ኪዳኗ ከእግዚአብሔር ጋር ታስታርቀን ዘንድ ፈቃዷ ይሁንልን።
🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜
