የካቴድራል፣ ቅድስት ማርያም እና ላዛሪስት ት/ቤት ተማሪዎች ግቢ ጉባኤ
ከመ/ገ/ጽ/ቅ ጊዮርጊስ ቤ/ክ ሰንበት ት/ቤት ጋር በመሆን ☞ ዘወትር ረቡዕ ከ10:00 - 11:30 ☞ በመ/ገ/ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክ ሰ/ት/ቤት አዳራሽ መንፈሳዊ ትምህርት የምንማማር ሲሆን ይህንን የተማሪዎች ጊቢ ጉባኤ አገልግሎት ለማጠናከር የተከፈተ የቴሌግራም ማኅበር ነው። @YeGibi_Gubae ✞ ኢንኅድግ ማኅበረነ ✞ አንድነታችንን አንተው
Show more- Subscribers
- Post coverage
- ER - engagement ratio
Data loading in progress...
Data loading in progress...
የትንሣኤ ልዩ ጉባኤ++++++++++++++++++++++ 📅ቀን ረቡዕ ሚያዚያ 30/2016 ⌚ሰዓት 10:00-11:30 በመናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሰንበት ት/ቤት አዳራሽ የካቴድራል፣ቅድስት ማርያም እና ላዛሪስት ት/ቤት ተማሪዎች ግቢ ጉባኤ ◈◎◈◎◈◎◈◎◈◎◈◎◈◎◈◎◈◎◈ ያወቅነውን በማሳወቅ የበኩላችንን እንወጣ share & join @StGeorge_Gibi_Gubae ለማንኛውም ጥያቄ እና አስተያየት @YeGibi_Gubae ላይ ያናግሩን
አቡነ ዘበሰማያት ይትቀደስ ስምከ ሥረይ ለነ ኩሎ አበሳነ ኢታብአነ ውስተ መንሱት እግዚኦ አድህነነ እምዕለት እኪት ወባልሀነ ውስተ መንሡት። ✝በከመ ምሕረትከ አምላክነ ወአኮ በከመ አበሳነ✝ የየእለቱን ስንክሳር፥ ውዳሴ ማርያም፥ ፀሎተ አርጋኖን፥ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮችን፥ የጻድቃንና የሰማእታትን ገድል፥ የተለያዩ መንፈሳዊ ጥያቄዎችን፥ የድሮ እና አዳዲስ መዝሙራትን የሚያገኙበት ቻናል ነው። ይቀላቀሉን።
ከመ/ገ/ጽ/ቅ ጊዮርጊስ ቤ/ክ ሰንበት ት/ቤት ጋር በመሆን ☞ ዘወትር ረቡዕ ከ10:00 - 11:30 ☞ በመ/ገ/ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክ ሰ/ት/ቤት አዳራሽ መንፈሳዊ ትምህርት የምንማማር ሲሆን ይህንን የተማሪዎች ጊቢ ጉባኤ አገልግሎት ለማጠናከር የተከፈተ የቴሌግራም ማኅበር ነው። @YeGibi_Gubae ✞ ኢንኅድግ ማኅበረነ ✞ አንድነታችንን አንተው
የሕማማት ልዩ ጉባኤ++++++++++++++++++++++ 📅ቀን ረቡዕ ሚያዚያ 16/2016 ⌚ሰዓት 10:00-11:30 በመናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሰንበት ት/ቤት አዳራሽ የካቴድራል፣ቅድስት ማርያም እና ላዛሪስት ት/ቤት ተማሪዎች ግቢ ጉባኤ ◈◎◈◎◈◎◈◎◈◎◈◎◈◎◈◎◈◎◈ ያወቅነውን በማሳወቅ የበኩላችንን እንወጣ share & join @StGeorge_Gibi_Gubae ለማንኛውም ጥያቄ እና አስተያየት @YeGibi_Gubae ላይ ያናግሩን
🌷እንኳን አደረሳችሁ ለዐቢይ ጾም ሰባተኛው ሰንበት🌷ኒቆዲሞስ🌷 ➡️ የዐቢይ ጾም ሰባተኛው ሳምንት ኒቆዲሞ ይባላል። ስያሜውን ያገኘው እውነተኛ እውቀትንና ሕይወትን ፈልጎ ነገር ግን ምድራዊ ሥልጣኑን በአይሁድ ሸንጎ እንዳይነጠቅ ፈርቶ በሌሊት ወደ ጌታ እየሄደ ይማር ከነበረው ከአይሁድ አለቃ ከኒቆዲሞስ ነው።
➡️ ዳግም ልደትን በተመለከተ ኒቆዲሞስ የጠየቀው ጥያቄና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የመለሰው መልስ በዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 3 ላይ በሰፊው ተብራርቶ ተጽፏል።➡️ ኒቆዲሞስ በፍርሃት ተውጦ እየተደበቀ በሌሊት ብቻ ኢየሱስ ክርስቶስን ሲከተለው የነበረ ሲሆን በኋላ በቃሉ ተመስጦና በፍጹም ፍቅሩ ተስቦ በድፍረት ተከትሎታል። የኢየሩሳሌም ሸንጎ ኢየሱስን ሊከሰው ሲፈልግ ኒቆዲሞስ ግን መከሰስ እንደሌለበት በድፍረት ሲመሰክር እናየዋለን (ዮሐ 7፥45-52)።
➡️ በተጨማሪም ኢየሱስ ክርስቶስ ከተሰቀለ በኋላም ሌሎች ደቀ መዛሙርት በፍርሃት ተውጠው ሲሸሹ እርሱ ለመግነዝ የሚሆን መቶ ንጥር የሚያህል የከርቤና የእሬት ቅልቅል ይዞ በድፍረት በቦታው ሲገኝም እንመለከተዋለን (ዮሐ 19፥39)።➡️ የዘለዓለም ሕይወትን መውረስ የሚፈልግ ሁሉ በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን ከውኃና ከመንፈስ ዳግመኛ መወለድ እንዳለበት የዮሐንስ ወንጌል ምዕ 3 ያስተምረናል።
➡️ ክርስቶስ ” ከሥጋ የተወለደ ሥጋ ነው፥ ከመንፈስም የተወለደ መንፈስ ነው ” ብሏል። የመጀመሪያው ልደት ከእናትና አባት ከሥጋ መወለድ ሲሆን ዳግም ልደት ደግሞ ከመንፈስ ቅዱስ የመወለድ ሚሥጢር ነው። ይህ ደግሞ በሰው ኃይል ሳይሆን በእግዚአብሔር ኃይል ነው የሚሆነው።➡️ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለኒቆዲሞስ ያስተማረው ዘለዓለማዊ ሕይወት የሚገኝበት ዳግም ልደት ለእኛም ጭምር የተነገረ መሆኑን ከልብ ልናስተውል ይገባል። ምክንያቱም የእግዚአብሔር ቃል ሕያውና ዘለዓለማዊ ነው።
➡️ ጠቅለል ባለ መልኩ ” ኃጢአተኞችን ሊያድን ክርስቶስ ኢየሱስ ወደ ዓለም መጣ የሚለው ቃል የታመነና ሁሉ እንዲቀበሉት የተገባ ነው” (1ኛ ጢሞ 1፥15) ብሎ ሐዋርያው እንደተናገረው ክርስቶስ የከፈለልንን የደም ዋጋ ከልብ በማመንና ዘወትር ያለማቋረጥ ፍቅሩንና ቤዛነቱን በማሰብ በፍርሃትና በሌሊት ሳይሆን በፍጹም እምነትና በብርሃን ልንከተለው ይገባል።➡️ የዳግም ልደት ዋናው ጽንሰ ሃሳብም ለምድራዊው ሥልጣንና ሀብት ቅድሚያ በመስጠት በሥጋ ልደት ጸንቶ መኖር ሳይሆን ለዘለዓለማዊ ሕይወት ቅድሚያ በመስጠት ዳግም ከመንፈስ ቅዱስ በመወለድ ሰማያዊ ዜግነትን ማግኘት ነው።
✍ከዋክብት የሚያመሰግኑት በስማቸውም የሚጠራቸው የጸጋው ብዛት የማይታወቅ ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ለሐዋሪያት እንዲሁም ለቀደሙ አባቶቻችን ሚሥጢሩን እንደገለጽክላቸው ለእኛም ግለጽልን። አሜን አሜን አሜን!!