en
Feedback
ETHIO-INFO

ETHIO-INFO

Open in Telegram

ወቅታዊ ዜና!

Show more
1 398
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
#ማስታወቂያ #DebreMarkosUniversity ለነባር አንደኛ ዓመትና ሪሜዲያል ተማሪዎች እንዲሁም ለአዲስ ገቢ የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በሙሉ‼️ በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ በ2015 ዓ.ም የ1ኛ ዓመት 2ኛ ወሰነ ትምህርት መደበኛ የቅድመ-ምረቃ ተማሪዎች እና በ2015 ዓ.ም የአቅም ማሻሻያ (Remedial) ትምህርት ተከታትላችሁ የማለፊያ ውጤት ያላችሁ ተማሪዎች፣ እንዲሁም በ2016 ዓ.ም አዲስ የተመደባችሁ የጀማሪ መርሀ-ግብር (Freshman) ተማሪዎችና የአቅም ማሻሻያ መርሀ-ግብር Program) ተማሪዎች ከዚህ በፊት በወጣው ከየካቲት 14-15/06/2016 ዓ.ም እንድትመዘገቡ ማስተላለፋችን ይታወቃል። ይሁን እንጂ የምዝገባ ጊዜው የተራዘመ መሆኑን እየገለፅን ወደፊት ጥሪ እስከምናደርግ ድረስ #በትዕግስት እንድትጠባበቁ እናሳውቃለን፡፡ @ethio_new_information @ethio_new_information

photo content

#አስቸኳይ_ማስታወቂያ!! በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ #ቡሬ_ካምፓስ የመውጫ ፈተና የማይሰጥ መሆኑን ከታች የተያያዘውን ማስታወቂያ ልከውልናል። @ethio_new_information @ethio_new_information

photo content

ጎንደር ዩንቨርስቲ ለምን officially  አይገልፅልንም ብላችሁ በርካቶች ጥያቄ ስታደርሱን ነበር ዛሬ በደረሰን መረጃ እስካሁን ድረስ የተቀየረ ነገር የለም መግቢያ በ 27 ነው :: በርካታ ተማሪዎች ticket ለመቁረጥ ግቢው ማስታወቂያ እስኪያወጣ እየተጠባበቁ ነው ተማሪዎች በ27 ይገባሉ የሚለው መረጃ ከላይ ካሉ አካላት ቢነገረንም መግለጫ እንደወጣ የምናሳውቅ ይሆናል ። እስካሁን ትኬት ✅የቆረጠ ✅ያልቆረጠ @ethio_new_information @ethio_new_information

#Update በታጣቂዎች መንገድ ላይ “እየተዘረፍን” እና እየተንገላታን ነው ሲሉ ተማሪዎች 👉ለአዲስ ማለዳ ተናገሩ‼️ በአማራ ክልል ከተለያዩ ስፍራዎች ወደ መቅደላ አምባ ዩንቨርስቲ የሚገቡ ተማሪች በመንገድ ላይ በታጣቂዎች የሚደረግ ፍተሻ መኖሩንና ተማሪዎች እንዲሁም መምህራን እንዳያልፉ እየተከለከሉ መሆኑን አዲስ ማለዳ ሰምታለች። ለአዲስ ማለዳ ሃሳባቸውን የሰጡ ተማሪዎች እንደገለጹት ታጣቂዎቹ “ተማሪዎች እና መምህራን እንዲያልፉ አይፈልጉም”። ከጎንደር መነሻውን ያደረገ ሌላ የመቅደላ ዩኒቨርሲቲ ተማሪም ደብረ ታቦር ሲደርሱ ከፊት ለፊታቸው በመኪና መንገድ እንደተዘጋባቸው ይገልጻል። “ከተሳፋሪዎቹ መካከል የሱዳን ስደተኞች ሲቀሩ ሌላውን ተሳፋሪ ስልክ፣ ገንዘብ እና ሌሎች ነገሮችንም” እንደወሰዱ ገልጾ ከዛ በኋላ ግን ከመከላከያ ሠራዊት ጋር በመሆን መጓዛቸውን ለአዲስ ማለዳ ተናግሯል። ተማሪዎች በተለይም ከመካነ ሰላም እና መርጡ ለማርያም አካባቢዎች ወደ ዩኒቨርሲቲው የመጡ ጥቂት ሲሆኑ፤ በርከት ያለ ቁጥር ያላቸው ተማሪዎች ከመንገድ እንዲመለሱ መደረጋቸውን አዲስ ማለዳ ማወቅ ችላለች። አዲስ ማለዳ “ታጣቂዎቹ እነማን ናቸው? ምን ዓይነት ናቸው?” በሚል ለተማሪዎች ላቀረበችው ጥያቄ “ማንነታቸውን በእርግጠኝነት መናገር ይከብዳል፤ ነገር ግን ሬንጀር ዩኒፎርም የለበሱም፤ ሲቪሎች እንዲሁም ልብስ ያልበሱ ጭምር አሉ” መኖራቸውን ተማሪዎቹ ያነሳሉ። በተጨማሪም ታጣቂዎቹ “ተማሪዎች ወደ ተቋማት እንዳይገቡ ብለን ነበር፤ አንድ ዩኒቨርሲቲዎቹ ላይ ችግር ቢፈጠር የምትጎዱት እናንተ ናቹ፤ ለዚህ ነው የምንመልሳቹ” ሲሉ ለተማሪዎች መናግራቸውን አዲስ ማለዳ ሰምታለች። የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎቹ ሲመጡ ለደህንነታቸው ኃላፊነት መውሰድ ያለባቸው እራሳቸው ተማሪዎቹ እንደሆኑ በይፋ መግለጹ የሚታወስ ሲሆን፤ በዚህ ሳምንት ጥር 15 ቀን 2016 ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ዘንዘልማ ካምፓስ ተኩስ ተከፍቶ እንደነበር ምንጮች ለአዲስ ማለዳ ገልጸዋል። በካምፓሱ ያለው ሁኔታ አስጊ በመሆኑም ተማሪዎችን በጊዜያዊ ምደባ ወደ ፖሊ ካምፓስ እንዲዘዋወሩ የተደረገ ሲሆን ተማሪዎች ጊቢውን ለቀው እንዲወጡ የሚያዝ ወረቀት መለጠፉን አዲስ ማለዳ ከተማሪዎች ብትሰማም ወረቀቱን ዩኒቨርሲቲው አልያም ሌላ አካል ይለጥፈው ማወቅ አልተቻለም። ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎቹን ለመቀበል ሶስት ቀናት ሲቀረው የአዲስ እና የሬሜዲያል ተማሪዎችን መግቢያ ቀን ላልተወሰነ ጊዜ ማራዘሙን ሲገልጽ ለምን እንድተራዘመ የሰጠው ማብራሪያ የለም። በተያያዘ ከቀናት በፊት የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ በማንኛውም ጊዜ የፀጥታ ችግር ቢከሰት ሃላፊነቱን አልወስድም ማለቱም አይዘነጋም። አዲስ ማለዳ ያነጋገረቻቸው ተማሪዎች ከመርጡ ለማርያም ተነስተው ወደ መካነ ሰላም ለመጓዝ ዓባይ ወንዝ ላይ ከባድ ፍተሻ በታጣቂዎች እንደሚከናወን ገልጸው ከመርጡ ለማሪያም ወደ መቅደላ ለመሄድ ሾፌሮችም ፈቃደኛ አለመሆናቸውን ተናግረዋል። “የተማሪነት መታወቂያ እና የትምህርት ማስረጃ የያዘ ሰው ማለፍ ቀርቶ፣ የሚወርድበት የዱላ መዓት አይጣል ነው” የሚለው የመቅደላ አምባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪ ለመጀመሪያ ዓመት ምዝገባ የሚያስፈልገውን የትምህርት ማስረጃ ይዞ በመጓዝ ላይ ነበር። መንገድ ላይ መኪናውን ያስቆሙት ታጣቂዎች ግን ቦርሳውን በመፈተሽ ማስረጃዎቹ በሙሉ ከፊቱ ለፊቱ ቀደው እንደጣሉበት ለአዲስ ማለዳ ገልጿል። ዩኒቨርሲቲ ከደረሰ በኋላ የትምህርት ማስረጃ ማቅረብ ባለመቻሉ መታወቂያ እና ምዝገባ ማካሄድ አትችልም ተብሎ በዩኒቨርሲቲ ውስጥ መቆየት አትችልም ተብሏል። ይሄው ወጣት፤ ባለው አስቸጋሪ የኢንተርኔት መቆራረጥ ማስረጃውን ከቤተሰብ እንዲላክለት ማድረጉን ጨምሮ ለአዲስ ማለዳ ገልጿል። ታጣቂዎቹ ሾፌሮችን ገንዘብ እንደሚቀበሏቸው የተገለጸ ሲሆን የተወሰኑ መምህራን የሥራ መታወቂያቸውን ደብቀው በነዋሪነት መታወቂያ ማለፍ ችለዋል ተብሏል። ከተለያዩ አካባቢዎች ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሚያቀኑ ተማሪዎች በታጣቂዎች የመታገት፣ የዘረፋ እና ወደመጡበት እንዲመለሱ እየተደረጉ መሆኑን ተማሪዎች ያነሳሉ። በአማራ ክልል በተፈጠረው የጸጥታ ችግር ምክንያት በክልሉ የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች በ2016 የትምህርት ዘመን የመጀመሪያዉ ወሰነ ትምህርት ተማሪዎቻቸውን ለመጥራትና መደበኛ የመማር ማስተማር ስራቸዉን ሙሉ ለሙሉ ለመጀመር አለመቻላቸው አይዘነጋም። ሆኖም የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ፣ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ፣ የአስሩ ዩኒቨርሲቲዎች ፕሬዝዳንቶችና ጉዳዩ የሚመለከታቸው የክልሉ ጸጥታ አካላት ታህሳስ 18 ቀን 2016 አደረጉ በተባለው ምክክር ተቋማቱ ተማሪዎችን እንዲቀበሉ መወሰኑን ትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል። አዲስ ማለዳ በጉዳዩ ላይ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ጌታቸው ቢያዝንን ለማነጋገር ያደረገችው ሙከራ ሳይሳካ ቀርቷል። በውሳኔያቸው ግን “በክልሉ አንጻራዊ ሰላም የተፈጠረ በመሆኑ ዩኒቨርስቲዎቹ ተማሪዎችን መጥራትና ማስተማር ይችላሉ” የተባለ ሲሆን ከጥር 1 ቀን 2016 ጀምሮ ባሉ ሁለት ሳምንታት ጊዜ ውስጥ ዩኒቨርስቲዎቹ ተማሪዎችን ጠርተው የመማር ማስተማር ስራቸውን እንደሚጀምሩ ተገልጾ ነበር። ይሁን እንጂ በክልሉ ያለው ወቅታዊ ሁኔታ መደበኛ የመማር ማስተማር ስራዎች ለመስራት አስቸጋሪ ስለመሆኑ ለአዲስ ማለዳ የደረሱ መረጃዎች ያመለክታሉ። የሚኒስቴሩን ውሳኔ የአማራ ክልል ተማሪዎች ማህበር በክልሉ ያለው የፀጥታ ችግር ባለበት እንደቀጠለ መሆኑ እየታወቀ የትምህርት ሚኒስቴር ትምህርት ይጀምሩ ማለቱ ትክክል አይደለም በማለት ተቃውሞ ነበር። ከምንም ነገር በላይ የተማሪዎቹን ደህንነት መጠበቅ የሚቀድም በመሆኑ ማህበሩ እንደ ተቋም ከሚኒስቴሩና ከትምህርት ተቋማት ጋር በመነጋገር ውሳኔውን ለማስቀልበስ የበኩሉን ጥረት እንደሚያደርግም አስታውቋል። @ethio_new_information @ethio_new_information

ጎንደር ዩንቨርስቲ ተማሪዎች ከጥር 27 - 30 ይገባሉ ማለቱ የሚዘነጋ አይደለም:: ይሄ በእንዲህ እንዳለ ዩንቨርስቲው እስካሁን በ television ም ሆነ በ radio የ ጥሪ ማስታወቂያ አላወጣም ስለሆነም ተማሪዎች ምን ያህል እርግጠኛ ሆነን ticket እንቁረጥ እያሉ ጥያቄ እያቀረቡ ይገኛሉ እኛም ይሄንን ጥያቄ ለ ዩንቨርስቲው የበላይ ጠባቂዎች የምናደርስ ሲሆን  ምላሹን የምናሳውቃቹ ይሆናል :: @ethio_new_information @ethio_new_information

በባህርዳር ዩኒቨርሲቲ በዘንዘልማ ካምፓስ ሰሞኑን ማታ ማታ ሲቪል የለበሱ ሰዎች ተኩስ ከፍተው እንደነበር የግቢው ተማሪዎች ተናገሩ ። ጥር 15 ቀን 2016 ዓ/ም ምሽት በግቢያቸው ተኩስ ተከፍቶ እንደነበር ገልጿል። በአካባቢው የቦንብ ፍዳታም እንደነበር ተናግረዋል ። ተማሪዎች እንዳሉት" በዘንዘልማ ካምፓስ ተኩስ አዲሳችን አልነበረም " ሲል ገልጾ ከትላንት በስቲያ ግን በአጥር ዘለው የገቡ አካላት ጥይት እየተኮሱ እስከ ዋና መግቢያ በር መሄዳቸውን ጠቁሟል። በጊቢው ማስታወቂያ መሰረት የገባን ቢሆንም አብዛኛው ተማሪዎች እንዳልገቡ እና የገቡት ተማሪዎችም ከ 100 እንደማይበልጡ ተናግረዋል ። ጥር 16 ቀን 2016 ዓ/ም በተጨማሪ ማብራሪያ የሰጠ አንድ የግቢው ተማሪ ፤ በዘንዘልማ ያለው ሁኔታው ስለሚያሰጋ ወደ ዋናው ካምፓስ  መሄዱንና የቀሩት ጓደኞቹ በሁኔታው መጨነቃቸውን እንደገለፁለት ተናግሯል። " እስከ 18 ድረስ ግቢውን ለቃችሁ ውጡ " የሚል ወረቀቶችም መበተኑን ከጓደኞቹ ዘንድ እንደሰማ በመግለፅ ያለንበትን ሁኔታ የሚመለከተው አካል ይወቅልን ብሏል። ፨ዩኒቨርሲቲው የተማሪዎችን የመግቢያ ቀን የመግቢያ ቀኑ ሊደርስ 3 ቀን ሲቀረው ዛሬ ላልተወሰነ ጊዜ ያራዘመ መሆኑን ማሳወቁ ይታወቃል። ምንጭ ።(መናኸሪያ ራዲዮ) @ethio_new_information @ethio_new_information

#BahirDarUniversity ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በ2016 ዓ.ም አዲስ ለተመደባችሁ የጀማሪ መርሐግብር (Freshman) ተማሪዎች እና ለአቅም ማሻሻያ (Remedial) መርሐግብር ተማሪዎች እንዲሁም በ2015 ዓ.ም የአቅም ማሻሻያ (Remedial) መርሐግብር ወስዳችሁ የማለፊያ ውጤት ያላችሁ ተማሪዎች አድርጎት የነበረውን ጥሪ ላልተወሰነ ጊዜ አራዝሟል፡፡ ዩኒቨርሲቲው ከላይ የተገለፁት ተማሪዎች ከጥር 21 እስከ 23/2016 ዓ.ም ምዝገባ እንዲያደርጉ ጥሪ ማስተላለፋ ይታወቃል፡፡ ይሁን እንጂ ምዝገባው ላልተወሰነ ጊዜ የተራዘመ መሆኑን የገለፀው ዩኒቨርሲቲው ፤ ወደፊት ጥሪ እስከሚደረግ ድረስ ተማሪዎች በትዕግስት እንዲጠብቁ ጠይቋል፡፡ @ethio_new_information @ethio_new_information

#JimmaUniversity በ2016 ዓ.ም ጅማ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ አዲስ የሪሚዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች ምዝገባ ጥር 27 እና 28/2016 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል። የምዝገባ ቦታ፦ የተፈጥሮ ሣይንስ ተማሪዎች በአጋሮ ካምፓስ (አጋሮ ከተማ) እና የማኅበራዊ ሣይንስ ተማሪዎች በጅማ ግብርናና እንስሳት ሕክምና ኮሌጅ (ጅማ ከተማ) ወደ ተቋሙ ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፡- ➢ የ12ኛ ክፍል ሰርተፍኬት ዋናውና ኮፒው፣ ➢ ጉርድ ፎቶግራፍ፣ ➢ ብርድ ልብስ፣ አንሶላ፣ ትራስ ጨርቅ እና የስፖርት ትጥቅ። @ethio_new_information @ethio_new_information

photo content
+1

#WolaitaSodoUniversity  በ2016 ዓ.ም. ወደ መላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ አዲስ የሪሜዲያል/የማሻሻያ ተማሪዎች የምዝገባ ጊዜ👉 ከጥር 23-24/2016 ዓ.ም. ለሁለት ተከታታይ ቀናት ብቻ መሆኑን እያሳወቅን ከተጠቀስዉ ጊዜ ቀድሞም ሆነ ዘግይቶ የሚመጣ ተማሪ ዩኒቨርሲቲዉ የማያስተናግድ መሆኑን እናሳስባለን፡፡ 💥ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲ ስትሄዱ 1. የ8ኛ ክፍል ስርተፍክት: ከ9ኛ - 12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት እና የ12ኛ ክፍል ሰርተፊኬት ዋናዉን እና ፎቶ ኮፒ ይዛችሁ እንድትመጡ፤ 2. አንሶላ፣ብርድልብስ፣ትራስ ጨርቅ እና የስፖርት ትጥቅ ይዛችሁ መምጣት ይኖርባችኋል፡፡ @ethio_new_information @ethio_new_information

photo content

🔥የመውጫ ፈተና መመዝገቢያ ጊዜ ተራዝሟል! ✅በ2016 ዓ.ም የመውጫ ፈተና ለመፈተን የምዝገባ ጊዜው ጥር 08/2016 ዓ.ም ጀምሮ ጥር 15/2016 ዓ.ም እንደሚጠናቀቅ መጠቀሱ የሚታወሰ ነው። ✅ይሁን እንጂ ትምህርት ሚኒስቴር በተፈታኞች ጥያቄ መሰረት የምዝገባ ጊዜው እስከ ጥር 20/2016 ዓ.ም የተራዘመ መሆኑን ገልጿል። ✅ሌሎች ሁኔታዎች ግን ቀደም ሲል በተገለጸው አግባብ የሚከናወኑ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አሳስቧል @ethio_new_information @ethio_new_information

በማንኛውም ጊዜ የፀጥታ ችግር ቢከሰት ሃላፊነቱን አልወስድም‼️ (ደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ) በአሁኑ ወቅት አንፃራዊ ሰላም በአከባቢዉ ቢስተዋልም ባለው ነባራዊ ሁኔታ አስጊ የሆነ የፀጥታ ችግሮች አሁንም በስጋትነት ያሉ በመሆኑ በማንኛውም ወቅት የፀጥታ ችግር ቢከሰት ሃላፊነቱን እንደማይወስድ ደብረ ብርሃን ዩንቨርስቲ አስታውቋል፡፡ የ2016ዓ.ም የመማር የማስተማር ሂደት በአማራ ክልል ባለው የፀጥታ ስጋት ምክንያት የተስተጓጎለ መሆኑን የሚገልጹት የዩኒቨርሲቲው የኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ አህመድ ሞሃመድ መስከረም ወር መጨረሻ 2016ዓ.ም የጤና ተማሪዎችን እና የ2016ዓ.ም ተመራቂ ተማሪዎችን እንዲሁም ጥቅምት መጨረሻ የ2015ዓ.ም የመጀመሪያ አመት ተማሪዎች የ2ኛ ሲሚስቴር ትምህርታቸ እንዲቀጥሉ ጥሪ በተደረገላቸው  መሰረት 99 በመቶ የሚሆኑ ተማሪዎችን ተቀብሎ እያስተማረ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ሌሎች ቀሪ ነባር ተማሪዎች እና አዳዲስ ተማሪዎች ከጥር 23ቀን 2016ዓ.ም ጀምሮ የሚገቡ ሲሆን ግጭቶች ካሉባቸው ቦታዎች የሚመጡ ተማሪዎች አማራጭ መንገዶች እንዲጠቀሙም ጠይቀዋል፡፡   ከዚህ ከቀደም ዩንቨርስቲው ከአዲስ አበባ እና ባቅራቢያው ካሉ አካባቢዎች ለሚመጡ ለአዳዲስ ተማሪዎች መጓጓዣ ያዘጋጅ የነበረ ቢሆን በዚህኛው አመት ለሚገቡ ተማሪዎች ግን ይህን ማድረግ አለመቻሉን አስታዉቀዋል፡፡ [ይህ ዘገባ የመናኸሪያ ሬዲዮ ጣቢያ ነው! @ethio_new_information @ethio_new_information

#WachemoUniversity በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስዳችሁ በ2016 ዓ.ም የሪሚዲያል ትምህርታችሁን እንድትከታተሉ ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ አዲስ የሪሚዲያል ተማሪዎች ምዝገባ የሚካሔደው ጥር 20 እና 21/2016 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል። ወደ ተቋሙ ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፡- ➢ የ8ኛ ክፍል ስርተፍኬት ዋናውና ኮፒው፣ ➢ ከ9ኛ-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ዋናውና ኮፒው፣ ➢ የ12ኛ ክፍል ፈተና ሰርተፍኬት ዋናውና ኮፒው፣ ➢ አንድ 2 x 2 እና ሁለት 3x4 ፎቶግራፍ፣ ➢ አንሶላ፣ ብርድ ልብስ፣ ትራስ ጨርቅ እና የስፖርት ትጥቅ። የምዝገባ ቦታ፦ ስማችሁ ከ A-H የሚጀምር የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎችና እና ስማችሁ ከ A-M የሚጀምር የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ምዝገባችሁ በዋናው ካምፓስ የሚከናወን ሲሆን፤ ስማችሁ ከ I-Z የሚጀምር የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎችና እና ስማችሁ ከ N-Z የሚጀምር የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ምዝገባችሁን የምታደርጉት በዱራሜ ካምፓስ እንደሆነ ከዩኒቨርሲቲው ያገኘነው መረጃ ያሳያል፡፡ @ethio_new_information @ethio_new_information

#MoE ትምህርት ሚኒስቴር በ2016 ዓ.ም በሚሰጡ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የትምህርት አይነቶች ላይ ውሳኔ አሳልፏል። በዚህም በሁለቱም የትምህርት መስኮች እያንዳንዳቸው በስድስት የትምህርት አይነቶች ፈተናው እንዲሰጥ ተወስኗል፡፡ ✅የተፈጥሮ ሣይንስ፦ እንግሊዝኛ፣ ሒሳብ፣ ፊዚክስ፣ ኬሚስትሪ፣ ባዮሎጂ እና ስኮላስቲክ አፕቲቲውድ ቴስት ✅የማኅበራዊ ሣይንስ፦ እንግሊዝኛ፣ ሒሳብ፣ ታሪክ፣ ጂኦግራፊ፣ ኢኮኖሚክስ እና ስኮላስቲክ አፕቲቲውድ ቴስት ለሁሉም ክልሎች እና ለሁለቱ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮዎች የተፃፈው ሰርኩላር፤ የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ዝግጅትንም ያብራራል። በዚህም የኢኮኖሚክስ ፈተና ለ2016 ዓ.ም ከ12ኛ ክፍል ብቻ ፈተናው የሚዘጋጅ ሲሆን ሌሎች የትምህርት አይነቶች ከ9-11ኛ ክፍሎች በነባሩ ሥርዓተ ትምህርት እንዲሁም የ12ኛ ክፍል በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት እንደሚሆን ያትታል። ስኮላስቲክ አፕቲቲውድ ቴስት ወደፊት ጥናት ተጠንቶ እስከሚለይ ድረስ በነበረው አሠራር መሠረት ውጤት ተደምሮ የሚገለጽ መሆኑንም ገልጿል። የፈተና አሰጣጡን በተመለከተ ለተማሪዎች፣ ለወላጆች፣ ለመምህራን እና ለትምህርት ማህበረሰቡ ቅድመ ዝግጅት እንዲያደርጉ ከወዲሁ እንዲያውቁት እንዲደረግ ሚኒስቴሩ አሳስቧል። @ethio_new_information @ethio_new_information

photo content

በወሎ ዩኒቨርስቲ! በወሎ ዩኒቨርስቲ በ2016 ዓም በ Remedial program አዲስ ለተመደባችሁ ተማሪዎች በሙሉ የወሎ ዩኒቨርስቲ በ2016 ዓም በ Remedial program አዲስ ለተመደባችሁ ተማሪዎች ጥር 16 እና 17/05/16 ዓም ጥሪ ማድረጉ ይታወቃል።በመሆኑም የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች በሙሉ ኮምቦልቻ ግቢ የሶሻል ሳይንስ ተማሪዎች በሙሉ ደሴ ግቢ የተመደባችሁ መሆኑን እንገልፃለን።  @ethio_new_information @ethio_new_information

photo content