en
Feedback
ገድለ ቅዱሳን ዘእለታት

ገድለ ቅዱሳን ዘእለታት

Open in Telegram

ከኢ/ኦ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ላይ የተገኙ የእለቱ የቅዱሳን(የጻድቃን) አባቶቻችን እና የቅዱሳን(የጻድቃን) እናቶቻችን ጽድቅ እና ገድላት ይነገርበታል። በመሀልም ጠቃሚና አስተማሪ ነው የምንላቸውን ታሪኮች ወደእናንተ የምናቀርብ ይሆናል። https://telegram.me/gedlekdusan

Show more
1 206
Subscribers
No data24 hours
+147 days
+2630 days
Posts Archive
​ያ የሕፃንነት ዘመናችን... ብርዱን ሳናስበው፣ ቅዝቃዜው ሳይሰማን በረከቱ ይድረሰኝ ብለን በንጹሕ ልብ በዝናቡና በጸበሉ ስር የምንቆምበት ያ ቅን እምነታችን ...... ​በዓለም ውጣ ውረድና በኃጢአ
​ያ የሕፃንነት ዘመናችን... ብርዱን ሳናስበው፣ ቅዝቃዜው ሳይሰማን በረከቱ ይድረሰኝ ብለን በንጹሕ ልብ በዝናቡና በጸበሉ ስር የምንቆምበት ያ ቅን እምነታችን ...... ​በዓለም ውጣ ውረድና በኃጢአት ጥላሸት የጠቆረውን ልባችንን፣ በሥጋና በነፍስ የቆሸሸውን ማንነታችንን ፈዋሹ መልአክ ቅዱስ ሩፋኤል በምህረቱ ጸበል ይጠብልን። ዛሬ ማደግ ያሳጣንን ያን የሕፃንነት የየዋህነት እምነት ይመልስልን።በፈዋሽ ክንፎቹ ጥላ ስር ሰውሮ ከደዌ ሁሉ ይፈውሰን! ​የቅዱስ ሩፋኤል ምልጃ፣ ፍቅርና በረከት ሁልጊዜም አይለያችሁ!!! እንኳን አደረሳችሁ!

እንኳን ለጳጉሜ 3 ለታላቋ ቀን አደረሳችሁ። የሰማይ ደጆች የሚከፈትበት ታላቅ ዕለት ናት።ሁላችንም ይቺን ለሊት በጸሎት ልናሳልፋት ይገባል።የቻለ እና የበረታ በቤቱ ሊያሳልፍ ይገባል ያልቻለ ደሞ በቤቱ ሆኖ በጸሎት ሊያሳልፍ ይገባል፤እንዲሁም 365 ጊዜ አቡነ ዘበሰማያት በማለት ልንጸልይ ይገባል።አዲሱን አመት በሰላም በፍቅር በመንፈሳዊነት ልናሳልፈው ይገባል።ከመልአኩ ከቅዱስ ሩፋኤል ረድኤት በረከት ያሳትፈን ያድለን። ሰናይ ለሊት https://t.me/gedlekdusan

​​ፈታሔ ማሕፀን ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ " የዘለዓለም ሕይወትን እንዲወርሱ ቅዱሳን መላእክት ምእመናን ለመርዳት ለማገልገል ከእግዚአብሔር የሚላኩ ረቂቃን ፍጥረታት አይደሉምን? ( ዕብ ፩÷፲፬) ብሏል። ቅዱስ ዮሐንስም "የዕጣኑም ጢስ ከቅዱሳን ጸሎት ጋር ከመልአኩ እጅ በእግዚአብሔር ፊት ወጣ"( ራእዩ ለዮሐንስ ፰÷፬) በማለት ተናግሯል። ቅዱሳን መላእክት ያለማያቋረጥ ለፈጣሪያቸው ምስጋና የሚያቀርቡ ረቂቃን ፍጥረታት ናቸው። በሰውና በእግዚአብሔር መካከል ለተልእኮ ይፋጠናሉ። የሰውን ጸሎትና ልመና ወደ እግዚአብሔር ያደርሳሉ፤ የእግዚአብሔርን ቸርነትና ምሕረት ወደ ሰው አድርሰው በእምነት ያጸናሉ። "በእግዚአብሔርም ፊት የሚቆሙትን ሰባቱን መላእክት አየሁ፥ ሰባትም መለከት ተሰጣቸው" (ራእ. ፰÷፪) የሚለው የሚያስረዳን ለተልእኮ መፋጠናቸውን ነው። ሄኖክም “በሰው ሰውነት ላይ የተሾሙ ከከበሩ ፯ቱ ሊቃነ መላእክት ቅዱስ ሩፋኤል አንዱ ነው” (ሄኖ.፮÷፩-፵፪) ብሏል። የሰዎችን ልመና ወደ እግዚአብሔር፣ የእግዚአብሔርን ምሕረት እና በረከት ወደ ሰው የሚወርድባት ዕለት"ርኅወተ ሰማይ” ትባላለች። ይህች ዕለት የሰዎች ሁሉ ጸሎት የሚያርግባት፣ አራተኛው መጋቢ ኮከብ የሚያልፍባት፣ ለሰው ልጆች ከፈጣሪያቸው ጸጋ በረከት የሚሰጥባት ስለሆነች "ርኅወተ ሰማይ-ሰማይ የሚከፈትባት ቀን" ትባላለች። እንዲህ የሚባለው በሰማይ መዘጋት መከፈት ኑሮበት አይደለም። የሰው ልጆችን ልመና ቅዱሳን መላእክት የሚያሳርጉበት፣ አንድም ቅዱስ ሩፋኤል የዓመቱን የጸሎት መዝገብ የሚከፍትበት ቀን ስለሆነ እንጂ። ቅዱስ ሩፋኤል ልቡናን ደስ የሚያሰኝ፣ ባለ መድኃኒት፣ የጸሎት መዝገብ መክፈቻ ቍልፍ የተሰጠው፣ የሴቶችን ማሕጸን የሚፈታና ሳይጨነቁ እንዲወልዱ ምጥን የሚያቀል መልአክ ነው። "ለሰብእ ወለእንሰ ፈታሔ ማሕጸኖሙ አንተ" እንዲል። የቅዱሳንን ጸሎት ከሚያሳርጉ ወደ ከበረና ወደ ገነነ ወደ እግዚአብሔር ጌትነትም ከሚያገቡ ከከበሩ መላእክት መካከል አንዱ እኔ ሩፋኤል ነኝ "(ጦቢያ ፲፪÷፲፭) የሚለው የሚያስገነዝበው ተራዳኢነታቸውን፣ ባለሟልነታቸውን፣ አማላጅነታቸውን ነው። ጸሎትህና ምጽዋትህ በእግዚአብሔር ፊት ለመታሰቢያ እንዲሆን ዐረገ"(ሐዋ. ፲÷፬) የሚለው የመላእክትን አገልግሎት የሚገልጥ ነው። መላእክት ሰዎችን ይራዳሉ፣ የሰውን ጸሎት ያሳርጋሉ፣ ያማልዱሉ፣ ሰዎችን ከመከራ ነጥቀው ያወጣሉ። "የእግዚአብሔርም መልአክ መልሶ። አቤቱ፥ የሠራዊት ጌታ ሆይ፥ እነዚህን ሰባ ዓመት የተቈጣሃቸውን ኢየሩሳሌምንና የይሁዳን ከተሞች የማትምራቸው እስከ መቼ ነው? አለ፣ እግዚአብሔርም መልሶ ከእኔ ጋር ይነጋገር ለነበረው መልአክ በመልካምና በሚያጽናና ቃል ተናገረው። ስለዚህም ከእኔ ጋር ይነጋገር የነበረው መልአክ እንዲህ አለኝ። ስበክ እንዲህም በል። የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል (ዘካ፣ ፩÷፲፪÷፲፬) የሚለው አማላጅነታቸውን የሚገልጥ የማጽናኛ ቃል ነው። ጦቢያና መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል ወደ ራጉኤል ቤት በደረሱ ጊዜ ሣራ ተቀብላ ደስ አሰኘቻቸው። መልአኩም ለጦቢያ አባትህ ከዘመዶችህ ወገን አግባ ያለህን ቃል አስብ አለው። ራጉኤልም ልጁ ሣራን ለጦቢያ አጋባት። ተመግበውም ከጨረሱ በኋላ ጦቢያን ወደ እርሷ አገቡት፤ ወደ እርሷም በገባ ጊዜ የመልአኩ የቅዱስ ሩፋኤልን ነገር አሰበ፤ የዕጣን እራሪ ወሰደ፤ ከዚያም ዓሣ ከልቡና ከጉበቱ ጨምሮ አጤሰው። ሽታውም ያን ጋኔን በሸተተው ጊዜ እስከ ላይኛው ግብፅ አውራጃ ድረስ ሸሸ። መልአኩም ጋኔኑን አሰረው( ጦቢ ፰÷፩) የተባለው የሚያስረዳን የመላእክትን ተራዳኢነት ነው። ጦቢያ የሰርጉን በዓል በጨረሰ ጊዜ ወደ አባቱ ቤት ከሚስቱ ከሣራና ከመልአኩ ከቅዱስ ሩፋኤል ጋር ተመለሱ። ሩፋኤልም አለው፥ "ያባትህ ዐይኖች እንዲበሩ አውቃለሁ፤ አንተ ግን ያን ሐሞት ያባትህ ዓይን ኳለው፤ በተኳለም ጊዜ ብልዙ ከአይኑ ይወጣል በደህናም ያያል። ጦቢያም የአባቱን አይን ኳለው ዓይኑም በራለት”( ጦቢ ፲፩÷፮) ተብሎ እንደተነገረው እግዚአብሔር ከዚህ ክፉ ወረርሽኝ ጠብቆን በሰላም በጤንነት ለሚመጣው ዓመት ያድርሰን። የጦቢትን ዓይን ያበራውን የቅዱስ ሩፋኤልን ዓመታዊ በዓል አክብረን በረከት ለማግኘት ያብቃን።አሜን!! ዲ/ን ተመስገን ዘገየ

እንኳን ለጳጉሜ 3 ለታላቋ ቀን አደረሳችሁ። የሰማይ ደጆች የሚከፈትበት ታላቅ ዕለት ናት።ሁላችንም ይቺን ለሊት በጸሎት ልናሳልፋት ይገባል።የቻለ እና የበረታ በቤቱ ሊያሳልፍ ይገባል ያልቻለ ደሞ በቤቱ ሆኖ በጸሎት ሊያሳልፍ ይገባል፤እንዲሁም 365 ጊዜ አቡነ ዘበሰማያት በማለት ልንጸልይ ይገባል።አዲሱን አመት በሰላም በፍቅር በመንፈሳዊነት ልናሳልፈው ይገባል።ከመልአኩ ከቅዱስ ሩፋኤል ረድኤት በረከት ያሳትፈን ያድለን። ሰናይ ለሊት https://t.me/gedlekdusan

​​ፈታሔ ማሕፀን ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ " የዘለዓለም ሕይወትን እንዲወርሱ ቅዱሳን መላእክት ምእመናን ለመርዳት ለማገልገል ከእግዚአብሔር የሚላኩ ረቂቃን ፍጥረታት አይደሉምን? ( ዕብ ፩÷፲፬) ብሏል። ቅዱስ ዮሐንስም "የዕጣኑም ጢስ ከቅዱሳን ጸሎት ጋር ከመልአኩ እጅ በእግዚአብሔር ፊት ወጣ"( ራእዩ ለዮሐንስ ፰÷፬) በማለት ተናግሯል። ቅዱሳን መላእክት ያለማያቋረጥ ለፈጣሪያቸው ምስጋና የሚያቀርቡ ረቂቃን ፍጥረታት ናቸው። በሰውና በእግዚአብሔር መካከል ለተልእኮ ይፋጠናሉ። የሰውን ጸሎትና ልመና ወደ እግዚአብሔር ያደርሳሉ፤ የእግዚአብሔርን ቸርነትና ምሕረት ወደ ሰው አድርሰው በእምነት ያጸናሉ። "በእግዚአብሔርም ፊት የሚቆሙትን ሰባቱን መላእክት አየሁ፥ ሰባትም መለከት ተሰጣቸው" (ራእ. ፰÷፪) የሚለው የሚያስረዳን ለተልእኮ መፋጠናቸውን ነው። ሄኖክም “በሰው ሰውነት ላይ የተሾሙ ከከበሩ ፯ቱ ሊቃነ መላእክት ቅዱስ ሩፋኤል አንዱ ነው” (ሄኖ.፮÷፩-፵፪) ብሏል። የሰዎችን ልመና ወደ እግዚአብሔር፣ የእግዚአብሔርን ምሕረት እና በረከት ወደ ሰው የሚወርድባት ዕለት"ርኅወተ ሰማይ” ትባላለች። ይህች ዕለት የሰዎች ሁሉ ጸሎት የሚያርግባት፣ አራተኛው መጋቢ ኮከብ የሚያልፍባት፣ ለሰው ልጆች ከፈጣሪያቸው ጸጋ በረከት የሚሰጥባት ስለሆነች "ርኅወተ ሰማይ-ሰማይ የሚከፈትባት ቀን" ትባላለች። እንዲህ የሚባለው በሰማይ መዘጋት መከፈት ኑሮበት አይደለም። የሰው ልጆችን ልመና ቅዱሳን መላእክት የሚያሳርጉበት፣ አንድም ቅዱስ ሩፋኤል የዓመቱን የጸሎት መዝገብ የሚከፍትበት ቀን ስለሆነ እንጂ። ቅዱስ ሩፋኤል ልቡናን ደስ የሚያሰኝ፣ ባለ መድኃኒት፣ የጸሎት መዝገብ መክፈቻ ቍልፍ የተሰጠው፣ የሴቶችን ማሕጸን የሚፈታና ሳይጨነቁ እንዲወልዱ ምጥን የሚያቀል መልአክ ነው። "ለሰብእ ወለእንሰ ፈታሔ ማሕጸኖሙ አንተ" እንዲል። የቅዱሳንን ጸሎት ከሚያሳርጉ ወደ ከበረና ወደ ገነነ ወደ እግዚአብሔር ጌትነትም ከሚያገቡ ከከበሩ መላእክት መካከል አንዱ እኔ ሩፋኤል ነኝ "(ጦቢያ ፲፪÷፲፭) የሚለው የሚያስገነዝበው ተራዳኢነታቸውን፣ ባለሟልነታቸውን፣ አማላጅነታቸውን ነው። ጸሎትህና ምጽዋትህ በእግዚአብሔር ፊት ለመታሰቢያ እንዲሆን ዐረገ"(ሐዋ. ፲÷፬) የሚለው የመላእክትን አገልግሎት የሚገልጥ ነው። መላእክት ሰዎችን ይራዳሉ፣ የሰውን ጸሎት ያሳርጋሉ፣ ያማልዱሉ፣ ሰዎችን ከመከራ ነጥቀው ያወጣሉ። "የእግዚአብሔርም መልአክ መልሶ። አቤቱ፥ የሠራዊት ጌታ ሆይ፥ እነዚህን ሰባ ዓመት የተቈጣሃቸውን ኢየሩሳሌምንና የይሁዳን ከተሞች የማትምራቸው እስከ መቼ ነው? አለ፣ እግዚአብሔርም መልሶ ከእኔ ጋር ይነጋገር ለነበረው መልአክ በመልካምና በሚያጽናና ቃል ተናገረው። ስለዚህም ከእኔ ጋር ይነጋገር የነበረው መልአክ እንዲህ አለኝ። ስበክ እንዲህም በል። የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል (ዘካ፣ ፩÷፲፪÷፲፬) የሚለው አማላጅነታቸውን የሚገልጥ የማጽናኛ ቃል ነው። ጦቢያና መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል ወደ ራጉኤል ቤት በደረሱ ጊዜ ሣራ ተቀብላ ደስ አሰኘቻቸው። መልአኩም ለጦቢያ አባትህ ከዘመዶችህ ወገን አግባ ያለህን ቃል አስብ አለው። ራጉኤልም ልጁ ሣራን ለጦቢያ አጋባት። ተመግበውም ከጨረሱ በኋላ ጦቢያን ወደ እርሷ አገቡት፤ ወደ እርሷም በገባ ጊዜ የመልአኩ የቅዱስ ሩፋኤልን ነገር አሰበ፤ የዕጣን እራሪ ወሰደ፤ ከዚያም ዓሣ ከልቡና ከጉበቱ ጨምሮ አጤሰው። ሽታውም ያን ጋኔን በሸተተው ጊዜ እስከ ላይኛው ግብፅ አውራጃ ድረስ ሸሸ። መልአኩም ጋኔኑን አሰረው( ጦቢ ፰÷፩) የተባለው የሚያስረዳን የመላእክትን ተራዳኢነት ነው። ጦቢያ የሰርጉን በዓል በጨረሰ ጊዜ ወደ አባቱ ቤት ከሚስቱ ከሣራና ከመልአኩ ከቅዱስ ሩፋኤል ጋር ተመለሱ። ሩፋኤልም አለው፥ "ያባትህ ዐይኖች እንዲበሩ አውቃለሁ፤ አንተ ግን ያን ሐሞት ያባትህ ዓይን ኳለው፤ በተኳለም ጊዜ ብልዙ ከአይኑ ይወጣል በደህናም ያያል። ጦቢያም የአባቱን አይን ኳለው ዓይኑም በራለት”( ጦቢ ፲፩÷፮) ተብሎ እንደተነገረው እግዚአብሔር ከዚህ ክፉ ወረርሽኝ ጠብቆን በሰላም በጤንነት ለሚመጣው ዓመት ያድርሰን። የጦቢትን ዓይን ያበራውን የቅዱስ ሩፋኤልን ዓመታዊ በዓል አክብረን በረከት ለማግኘት ያብቃን።አሜን!! ዲ/ን ተመስገን ዘገየ

✞✞✞✝እንኳን ለርኅወተ ሰማይ: ለቅዱስ ሩፋኤል: መልከ ጼዴቅ: ዘርዓ ያዕቆብና ሰራጵዮን ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። ✞✞✞✝ ✞✞✞✝በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! ✞✞✞✝ ✞✞✞✝ ርኅወተ ሰማይ ✞✞✞✝ ✞✞✞ይህች ዕለት የሰዎች ሁሉ ጸሎት የሚያርግባት: አራተኛው መጋቢ ኮከብ የሚያልፍባት: ለሰው ልጆች ከፈጣሪያቸው ጸጋ በረከት የሚሰጥባት ዕለት ስለሆነች "ርኅወተ ሰማይ-ሰማይ የሚከፈትባት ቀን::" ትባላለች:: አሁን በሰማይ መዘጋት መከፈት ኑሮበት አይደለም:: የሰው ልጆችን ልመና ቅዱሳን መላእክት ያለ ከልካይ የሚያሳርጉበት: አንድም ቅዱስ ሩፋኤል የዓመቱን የጸሎት መዝገብ የሚከፍትበት ቀን ስለሆነ እንዲህ ተባለ እንጂ:: እመቤታችን ድንግል ማርያም ለአጼ ናዖድ እንደ ነገረቻቸው በዚህች ዕለት ሁሉም ቅዱሳን ስለሚታሰቡ: የእግዚአብሔር የምሕረት መዝገቡ ስለሚከፈት: ዕለቷን ክብርት ያሰኛታል:: በቅዱስ ሩፋኤል አበጋዝነት (መሪነት) በዚህች ዕለት ለዓመት የሚበቃ ምሕረት ይገኛል:: ስለዚህም አባቶቻችን በዚህች ሌሊት ሦስት መቶ ስልሳ አምስት አቡነ ዘበሰማያትን ሲጸልዩ ያድራሉ:: በሌላ ወገን ደግሞ የጌታ ዳግም ምጽዓቱ መታሰቢያ እንደ መሆኗ ትልቅ ትኩረትም ይሰጣታል:: ቸሩ ጌታችን ከተከፈተች ገነት ከተነጠፈች ዕረፍት ሁላችንንም ያድርሰን:: ✞✞✞✝ቅዱስ ሩፋኤል ሊቀ መላእክት✞✞✞✝ ✞✞✞ቅዱስ ሩፋኤል በቤተ ክርስቲያን አስተምሕሮ ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት በደረጃው ሦስተኛ ነው:: በመጀመሪያዋ ዕለተ ፍጥረት እግዚአብሔር መቶ ነገደ መላእክትን ፈጥሮ በአሥር ከተማ ሲያኖራቸው የቅዱስ ሩፋኤል ዕድል ፈንታው ራማ ሆነች:: በዚያም "መናብርት" ተብለው ለሚጠሩ አሥሩ ነገድ አለቃ (መሪ) ሆኖ በፈጣሪው ተሹሟል:: በኋላም "መጋብያን" በሚባሉ በሃያ ሦስቱ ነገድ ላይ ሹሞታል:: ይህች ዕለትም በዓለ ሲመቱ ናት:: አንድ ቀን ጌታችን ክርስቶስ በደብረ ዘይት ተቀምጦ ሳለ ሐዋርያቱ ቅዱስ ሩፋኤልን እንዲያስተዋውቃቸው ለመኑት:: ጌታም ሦስቱን ሊቃናት (ሚካኤል: ገብርኤል እና ሩፋኤል) ይመጡ ዘንድ አዘዛቸው:: ቀጥሎም ቅዱስ ሩፋኤልን "ክብርህን ንገራቸው::" አለው:: እርሱም ለጌታ ሰግዶ ለሐዋርያት ብዙ ምሥጢር ነገራቸው:: በተለይ ስሙን ለሚጠሩ: መታሰቢያውን ለሚያከብሩ የሚደረገውን ጸጋ አብራርቶላቸው ዐረገ:: በመጽሐፈ ጦቢት ላይ ተጽፎ እንደምናገኘው ቅዱሱ መልአክ ሰው (አዛርያን) መስሎ: ጦብያን ለትዳር አብቅቶ: ሣራን አስማንድዮስ ከሚባል ሰይጣን አድኖ: የጦቢትን ዓይን አብርቷል:: በገድላተ ቅዱሳን እንደምናየውም ለብዙ ቅዱሳን ረዳታቸው ሆኖ ገድላቸውን አስፈጽሟል:: ታሪክ እንደሚለው ይህች ቀን ለቅዱስ ሩፋኤል ቅዳሴ ቤቱም ናት:: በ4ኛው መቶ ክ/ዘመን በቅዱስ ቴዎፍሎስ ዘእስክንድርያ አማካኝነት ቤቱ ታንጿል:: የሚገርመው ደግሞ የታነጸው በዓሣ አንበሪ ጀርባ: ደሴት ላይ ነው:: በመልአኩ አጋዥነትም ለሦስት መቶ ዓመታት አገልግሏል:: ✞✞✞ቅዱስ ሩፋኤል ¤መስተፍስሒ (ልቡናን ደስ የሚያሰኝ) ¤አቃቤ ሥራይ (ባለ መድኃኒት ፈዋሽ) ¤መዝገበ ጸሎት (የጸሎት መዝገብ መክፈቻ የተሰጠው) ¤ሊቀ መናብርት (በዙፋን ላይ በክብር የሚቀመጡ መላእክት መሪ) ¤ፈታሔ ማኅጸን (የሰውንም ሆነ የእንስሳትን ማኅጸን የሚፈታ) ¤መወልድ (አዋላጅ: ምጥን የሚያቀል) ይባላል:: "ለሰብእ ወለእንስሳ ፈታሔ ማኅጸኖሙ አንተ" እንዲል:: ✞✞✞✝ቅዱስ መልከ ጼዴቅ ✞✞✞✝ ✞✞✞ካህኑ መልከ ጼዴቅን ቅዱስ ጳውሎስ "የትውልድ ቁጥር የለውም: ለዘመኑም ጥንትና ፍጻሜ የለውም::" ይለዋል:: (ዕብ.7:3) ሐዋርያው ይህንን ያለው ለወልደ እግዚአብሔር ምሳሌ ሲያደርገው እንጂ ትውልዱ ከነገደ ካም ነው:: ወላጆቹም "ሚልኪ እና ሰሊማ" ይባላሉ:: ገና ከእናቱ ማኅጸን የተመረጠው ቅዱሱ "ካህነ ዓለም: ንጉሠ ሳሌም" ይባላል:: የዛሬ አምስት ሺ አምስት መቶ ዓመት አካባቢ ሴም ባኖረበት ቦታ (በደብረ ቀራንዮ) ለዘላለም ይኖራል:: ካህኑ መልከ ጼዴቅ ከሰው ወገን እጅግ ክቡርም ነው:: ✞✞✞✝ ዘርዓ ያዕቆብ ✞✞✞✝ ✞✞✞ሃይማኖቱ የቀና ኢትዮጵያዊው ንጉሥ አፄ ዘርዓ ያዕቆብ በኢትዮጵያ በነገሠባቸው ሠላሳ አራት ዓመታት (ከ1426 እስከ 1460 ዓ/ም) ብዙ በጐ ነገሮችን ሠርቷል:: ላለፉት ሰባ ዓመታት ግን አንዳንድ ጥቃቅን ሰብአዊ ስህተቶችን እየነቀሱ ተሐድሶዎቹ ስሙን ሲያጠፉት ኑረዋል:: ዛሬ ዛሬ ደግሞ የእኛ ቤት ሰዎችም ተቀላቅለዋቸዋል:: እነርሱ ያሉትን ይበሉ እንጂ ለእኛ ግን ዘርዓ ያዕቆብ ማለት:- 1.ጣዖት አምልኮን ከሃገራችን ለማጥፋት ብዙ ሺህ ካህናትን አሰልጥኖ አሰማርቷል:: 2.የኑፋቄ ችግሮችን ለመቅረፍ ጉባኤያትን አዘጋጅቷል:: 3.ከአሥራ አንድ ያላነሱ መጻሕፍትን በመንፈስ ቅዱስ አጋዥነት ደርሶ ለአገልግሎት አብቅቷል:: 4.ብዙ መጻሕፍትን ከውጪ አስመጥቶ አስተርጉሟል (በተለይ ተአምረ ማርያምን) 5.ሰው ሁሉ ለእመ ብርሃንና ለመስቀሉ ፍቅር እንዲገዛ ጥረት አድርጓል 6.እመቤታችንን በፍጹም ልቡ ከመውደዱ የተነሳ ዛሬ ድረስ በሃገራችን ድንግል ማርያም "የዘርዓ ያዕቆብ እመቤት" እየተባለች ትጠራለች:: 7.ብዙ አብያተ ክርስቲያናትን አንጾ: ብዙ ሥርዓቶችም በሊቃውንት እንዲሠሩ አድርጐ: ሌሎች ብዙ በጐ ተግባራትንም ፈጽሞ በዚህች ቀን ዐርፏል:: ቤተ ክርስቲያን ስለውለታቸው ዘርዓ ያዕቆብን: እናታቸው ጽዮን ሞገሳን እና አባታቸው ዳዊትን በክብር ታስባለች:: ✞✞✞✝ቅዱስ ሰራጵዮን ዘሰንዱን ✞✞✞✝ ✞✞✞ይህ ቅዱስ እጅግ የበዛ ሃብቱን ለነዳያን አካፍሎ: ወደ ሌላ ሃገር ሔዶ ለባርነት ተሽጧል:: በተሸጠበት ሃገርም በጸሎት ተግቶ ከክህደት ወደ ሃይማኖት መልሷቸዋል:: ክብሩን ሲያውቁበትም በተመሳሳይ ወደ ሌላ ሃገር ሒዶ አሕዛብን አድኗል:: በፍጻሜው ወደ በርሃ ገብቶ በተጋድሎ ኑሮ በዚህች ቀን ዐርፏል:: ✞✞✞አምላከ ቅዱሳን የወዳጆቹን ሁሉ በረከትና ጸጋ ያብዛልን:: ለዓለምም ሰላሙን ይዘዝልን:: ✞✞✞ጳጉሜን 3 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት 1.ርኅወተ ሰማይ (የሰማይ መከፈት) 2.ቅዱስ ሩፋኤል ሊቀ መላእክት 3.ቅዱስ መልከ ጼዴቅ ካህን 4.አፄ ዘርዓ ያዕቆብ ንጉሥ (የእመቤታችን ወዳጅ) 5.ቅዱስ ሰራጵዮን ዘሰንዱን 6.ቅዱስ አኖሬዎስ 7.ቅዱስ ቴዎፍሎስ 8.አባ ዮሐንስ 9.ቅዱስ ጦቢት 10.ቅዱሳን ጦብያና ሣራ ✞✞✞ወርኀዊ በዓላት (የለም) ✞✞✞"እውነት እውነት እላችኋለሁ:: ሰማይ ሲከፈት: የእግዚአብሔርም መላእክት በሰው ልጅ ላይ ሲወጡና ሲወርዱ ታያላችሁ::" ✞✞✞ (ዮሐ. ፩፥፶፪) <<<ወስብሐት ለእግዚአብሔር>>> ከኢ/ኦ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ላይ የተገኙ የእለቱ የቅዱሳን(የጻድቃን) አባቶቻችን እና የቅዱሳን(የጻድቃን) እናቶቻችን ጽድቅ እና ገድላት ይነገርበታል። በመሀልም ጠቃሚና አስተማሪ ነው የምንላቸውን ታሪኮች ወደእናንተ የምናቀርብ ይሆናል። https://telegram.me/gedlekdusan

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! 🙏 እስከ መጨረሻው በማንበብ ይተባበሩን፤ ለሌሎችም ያጋሩት! 🙏 የሚዲያ ክፍላችን ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ እግዚአብሔር በሰጠን አቅም ሁሉ ታላላቅ ሥራዎችን ሲሠራ ቆይቷል። በተለይም በዚህ በዲጂታል ዘመን የቤተክርስቲያንን አስተምህሮ ማዳረስ፣ የእግዚአብሔርን ቃል በጽሑፍም ሆነ በቪዲዮ ተደራሽ ማድረግ ዋነኛውና ውዱ አደራችን ነው። ባለፉት ዓመታት ከቅን ወንድምና እህቶቻችን ስልክ እየተዋስን የተለያዩ ትምህርቶችንና መርሃ ግብሮችን ስናቀርብላችሁ ቆይተናል። ነገር ግን ካቀድነው ትልቅ ራእይ አንጻር ሲታይ እስከ አሁን የሠራነው በጣም ጥቂቱን ብቻ ነው። የእቅዳችን ዋና ዋና ግቦች፦
በዲጂታል ዘመን ቃለ እግዚአብሔርን ማዳረስ፤ በግቢ ውስጥ ያሉትንና ተመርቀው የወጡትን የግቢ ጉባኤያችንን ፍሬዎች የሚያገናኝና ካሉበት ቦታ ሆነው የሚያገለግሉበትን መንገድ በማመቻቸት ቤተሰባዊነታችንን ማጠናከር፤ ከመደበኛ መርሐ ግብራችን በተጨማሪ የጉዞ፣ የምሩቃን ሕብረት፣ የምረቃ መርሃ ግብር (Graduation ceremony)፣ የሃፍ ላይፍ (Half-Life) እና የአዲስ ተማሪዎች መቀበያ (Freshman welcoming event) ፕሮግራሞችን በቪዲዮ መዝግቦ ማሰናዳት እና በዶክመንተሪ መልክ ለእይታ ማብቃት፤
እነዚህን ትላልቅ ሥራዎች አቅደን የተነሳን ቢሆንም የራሳችን የቀረጻ ማቴሪያል አለመኖሩ ዋና ማነቆ ሆኖብናል። እንደሚታወቀው የተውሶ ስልክ በፈለግነው ሰዓት ለማግኘት አዳጋች ከመሆኑም በላይ ለአገልግሎቱ ስፋት በቂ አይደለም። የሚዲያ ቡድናችን ይህንን ችግር ለመቅረፍ በግቢያችን ውስጥ የግራፊክስ ዲዛይን እና ቪዲዮ ኤዲቲንግ ሥልጠና በመስጠት እስከ 40,000 ብር ለመሰብሰብ ጥረት ያደረገ ቢሆንም፣ ለዕቃዎቹ ግዢ አሁንም ገና ብዙ ይቀረናል።
"ሀምሳ ሎሚ ለአንድ ሰው ሸክሙ፣ ለሀምሳ ሰው ጌጡ ነው"
እንደሚባለው እኛም ኦርቶዶክሳውያን ከተባበርን ማንኛውንም ነገር ማሳካት እንችላለን። ይህ ቅዱስ አገልግሎት ሳይቋረጥ እንዲቀጥልና ይበልጥ እንዲስፋፋ ሁላችሁም የበኩላችሁን አሻራ እንድታስቀምጡ በአክብሮት እንጠይቃለን። 📌 በምን በምን መረዳት ይችላሉ? 1️⃣ መረጃ በማጋራት (Share)፦ ለዚህ መርሃ ግብር የተዘጋጀውን ፖስተር በቴሌግራም፣ በኢንስታግራም Story፤ እንዲሁም በቲክቶክ እና በዩቲዩብ የተለቀቁትን ቪዲዮዎች Share በማድረግ ተደራሽነቱን ማፋጠን። 2️⃣ ሰዎችን በመጠቆም፦ ድጋፍ ሊያደርጉልን የሚችሉ ሰዎችን (ለምሳሌ ቲክቶከሮችን) Mention ማድረግ፤ ወይም በገንዘብና በዓይነት ሊረዱን የሚችሉ ኦርቶዶክሳውያንን ካወቃችሁ ስምና ስልክ ቁጥራቸውን ከዚህ በታች በተቀመጠው የጉግል ፎርም ሊንክ ያስቀምጡ፦ https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSc4PIhwq7W2ysKVATYxxuDx3gOxhb4-LdsqyG4d807sPXPPPg/viewform?usp=header 3️⃣ በዓይነት ድጋፍ በማድረግ፦ ለሥራችን አስፈላጊ የሆኑ የቴክኖሎጂ ዕቃዎችን በመስጠት፦ 📷 ካሜራ (Camera) 📐 የካሜራ ስታንድ (Tripod) 🎙 ማይክሮፎን (Microphone) 💾 ኤክስተርናል ሃርድዲስክ (External Hard Drive) 🎥 ጊምባል (Gimbal / Stabilizer) 4️⃣ በገንዘብ ድጋፍ በማድረግ፦ «አነሰ፣ በዛ» ሳያሉ አቅማችሁ የፈቀደውን ያህል በመለገስ የዚህ በረከት ተካፋይ ይሁኑ! 💳 የባንክ እና የስልክ አድራሻዎች፦ CBE (ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ): 1000792257686 (Egzihareya Solomon And/or Arsema) Telebirr (ቴሌብር): 0958313628 (Arsema) 📞 ለበለጠ መረጃ፦ 📱 +251 98 332 9770 📱 +251 90 549 6768 ለምታደርጉት ትብብር ሁሉ እግዚአብሔር አምላክ በረከቱን ያድላችሁ!🙏 ▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰         የአ/አ/ሳ/ቴ/ዩ ግቢ ጉባኤ 📥  @gibigubaeHasabon_bot ጻፉልን 🏷 @aastugibigubae ተከታተሉን 📷 @GGgallery1 የፎቶ ማኅደራችን ▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰ TikTok | Instagram | YouTube

ካለ መወለድ መወለድ ይሻላል።ምክንያቱም መወለድ በሚወደድ ፈጣሪ ልቡና በፍጡርነት አንድ ተብሎ መቆጠር ከመሆኑም ባሻገር ለዘለዓለም ሕይወት መታጨት ነውና።   <<<ሕይወተ ወራዙት>>>

††† እንኳን ለቅዱስ ቲቶ ሐዋርያ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። ††† ††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! ††† ††† ቅዱስ ቲቶ ሐዋርያ ††† ††† የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደቀ መዝሙር ቅዱስ ቲቶ ከሰባ ሁለቱ አርድእት አንዱ ሲሆን በተወሰነ መንገድም ቢሆን የተዘነጋ ሐዋርያ አይደለም:: በተለይ ደግሞ ቅዱስ ጳውሎስ ከጻፋቸው አሥራ አራት መልእክታት መካከል አንዷ የተላከችው ለዚህ ቅዱስ በመሆኗ ታሪኩ እንኳ ባይነገር ስሙ አይረሳም:: ቅዱስ ጳውሎስም በመልዕክታቱ በጐ ስሙን እየደጋገመ ያነሳዋል:: ለመሆኑ ሐዋርያው ቅዱስ ቲቶ ማን ነው? ቅዱስ ቲቶ የተወለደው በ1ኛው መቶ ክ/ዘመን እስያ ውስጥ: ቀርጤስ በምትባል ከተማ ነው:: የዘር ሐረጉ ከእሥራኤልም: ከጽርእም (ግሪክ ለማለት ነው::) ይወለዳል:: አካባቢው አምልኮተ እግዚአብሔር የጠፋበት ስለሆነ እሱም: ቤተሰቦቹም የሚያመልኩት ከዋክብትን ነበር:: መዳን በእውቀት ይመስላቸው ስለ ነበር የአካባቢው ሰዎች የግሪክን ፍልስፍና ጠንክረው ይማሩ ነበር:: ቅዱስ ቲቶም በወጣትነቱ ወደ ት/ቤት ገብቶ የግሪክን ፍልሥፍናና የዮናናውያንን ጥበበ ሥጋ ተማረ:: በጥቂት ጊዜም የሁሉ የበላይ ሆነ:: ቅዱሱ በወቅቱ ምንም እውነተኛውን ፈጣሪ አያምልክ እንጂ በጠባዩ እጅግ ቅንና ደግ ነበር:: ምክንያቱን ሳያውቀው ለእኔ ቢጤዎች ያበላ: ያጠጣ: ይንከባከባቸውም ነበር:: እግዚአብሔር ግን የዚህ ቅን ሰው በጐነቱ እንዲሁ እንዲቀር አልወደደምና አንድ ቀን በራዕይ ተገለጠለት:: በራዕይም አንድ ምንነቱን ያልተረዳው ነገር "ቲቶ ሆይ! ስለ ነፍስህ ድኅነት ተጋደል:: ይህ ዓለም ኃላፊ ነው::" ሲለው ሰማ:: ከእንቅልፉ ነቅቶ በእጅጉ ደነገጠ:: የሚያደርገውንም አጣ:: ያናገራቸው ሁሉ ምንም ሊገባቸው አልቻለም:: ለተወሰነ ጊዜም ለጉዳዩ ምላሽ ሳያገኝለት በልቡ እየተመላለሰ ኖረ:: ድንገት ግን በዚያ ሰሞን ከወደ ኢየሩሳሌም አዲስ ዜና ተሰማ:: "ክርስቶስ የሚሉት ኢየሱስ: እርሱም የባሕርይ አምላክ የሆነ ወደ ምድር ወርዶ: ስለ እግዚአብሔር መንግስትም እየሰበከ ነው::" ሲሉ ለቲቶ ነገሩት:: "ሌላስ ምን አያችሁ?" አላቸው:: "በእጆቹ ድውያን ይፈወሳሉ:: ሙታን ይነሳሉ:: እውራን ያያሉ:: ለምጻሞች ይነጻሉ:: ሌሎች ብዙ ተአምራትም እየተደረጉ ነው::" አሉት:: የወቅቱ የሃገረ አክራጥስ መኮንን ፈላስፋ ነበርና ስለ ክርስቶስ ሲሰማ ሊመራመር ወደደ:: እርሱ መሔድ ስላልተቻለው "ብልህ ጥበበኛ ሰው ፈልጉልኝ::" ብሎ ተከታዮችን ቢልካቸው ከቲቶ የተሻለ በአካባቢው አልነበረምና እርሱኑ አመጡት:: መኮንኑ ቲቶን "ነገሩ ትክክል ወይም ስሕተት መሆኑን በጥልቅ መርምረህ ምላሽ አምጣልኝ::" ብሎ ላከው:: ቅዱስ ቲቶም ፈጥኖ ተነስቶ ወደ ኢየሩሳሌም ገሰገሰ:: ወደ ከተማዋ እንደገባም ጌታችንን አፈላልጐ አገኘው:: 1.ጌታችን ክርስቶስ በሥልጣነ ቃሉ ደዌያትን ሲያርቅ: አጋንንትን ሲያሳድዳቸው ተመልክቶ ይህ ሥራ የፍጡር እንዳልሆነ ተረዳ:: 2.ጌታችን የሚያስተምረው ትምሕርት ከግሪክ ፍልሥፍና እጅግ ርቆና መጥቆ አገኘው:: የግሪክ ፍልሥፍና መነሻውም ሆነ መድረሻው ሥጋዊ ነው:: ጌታ ግን በጣዕመ ቃሉ የሚያስተምረው ሰማያዊ: በዚያ ላይ ዘላለማዊ የሆነ ትምሕርት ነው:: በራዕይ "ስለ ነፍስህ ተጋደል::" ያለው ምሥጢር አሁን ተተረጐመለት:: በዚህ ምክንያትም ጊዜ አላጠፋም:: ወዲያውኑ አምኖ ተከታዩ ሆነ:: ጌታም ከሰባ ሁለቱ አርድእት ደመረው:: የአክራጥስ መኮንን "ምነው ዘገየህ?" ቢለው ያየውን ሁሉ ጽፎ: እንደማይመለስም አክሎ ደብዳቤ ላከለት:: ከዚህ በኋላ ቅዱስ ቲቶ ከጌታችን እግር ለሦስት ዓመታት ተምሮ: በበዓለ ሃምሳ መንፈስ ቅዱስን ተቀብሎ: በመላው እስያ ለስምንት ዓመታት ወንጌልን ሰብኳል:: ቅዱስ ጳውሎስ ባመነ ጊዜ ደግሞ የእርሱ ደቀ መዝሙር ሆኖ ለሃያ አምስት ዓመታት አስተምሯል:: ቅዱስ ጳውሎስ ሰማዕት ከሆነ በኋላ ደግሞ ወደ አክራጥስ ተመልሶ: ሕዝቡን አሳምኖና አጥምቆ: ቤተ ክርስቲያንን አንጿል:: ዕድሜው በደረሰ ጊዜም መምሕራንን: ካህናትን ሹሞላቸው: ባርኳቸውም በዚህች ቀን ዐርፏል:: ††† አምላከ ቅዱስ ቲቶ መልካሙን የሕይወት ምሥጢር ይግለጽልን:: ከሐዋርያውም በረከቱን ያድለን:: ††† ጳጉሜን 2 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት 1.ቅዱስ ቲቶ ሐዋርያ (ከሰባ ሁለቱ አርድእት) ††† ወርኀዊ በዓላት (የለም) ††† "የእግዚአብሔር ባሪያና የኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያ የሆነ ጳውሎስ. . . መድኃኒታችን እግዚአብሔር እንዳዘዘ: ለእኔ አደራ በተሰጠኝ ስብከት ቃሉን ገለጠ: በሃይማኖት ኅብረት እውነተኛ ለሚሆን ልጄ ቲቶ:: ከእግዚአብሔርም አብ: ከመድኃኒታችንም ከጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ምሕረት: ሰላምም ይሁን::" ††† (ቲቶ. ፩፥፩) ††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር ††† ከኢ/ኦ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ላይ የተገኙ የእለቱ የቅዱሳን(የጻድቃን) አባቶቻችን እና የቅዱሳን(የጻድቃን) እናቶቻችን ጽድቅ እና ገድላት ይነገርበታል። በመሀልም ጠቃሚና አስተማሪ ነው የምንላቸውን ታሪኮች ወደእናንተ የምናቀርብ ይሆናል። https://telegram.me/gedlekdusan

ኧረ እንዴት ደስ እንደሚል እንደዚህ አይነት ጥያቄዎች ተበራክተዋል ሆኖም ካየሁዋቸው በዚህ ቪድዮ ስር ያሉት ኮሜንቶች ግን በርከት ያሉ ናቸው እና በግሌ እጅግ አስደስቶኛል 😊 አላውቅም ሁሉም ተሳክቶ
ኧረ እንዴት ደስ እንደሚል እንደዚህ አይነት ጥያቄዎች ተበራክተዋል ሆኖም ካየሁዋቸው በዚህ ቪድዮ ስር ያሉት ኮሜንቶች ግን በርከት ያሉ ናቸው እና በግሌ እጅግ አስደስቶኛል 😊 አላውቅም ሁሉም ተሳክቶለት ቢያሳካው ደስ ይለኛል። የእናንተስ እንዴት ነበር ታዲያ? 🤔

ኧረ እንዴት ደስ እንደሚል እንደዚህ አይነት ጥያቄዎች ተበራክተዋል ሆኖም ካየሁዋቸው የዚህ ቪድዮ ኮሜንት እጅግ አስደስቶኛል 😊 አላውቅም ሁሉም ተሳክቶለት ቢያሳካው ደስ ይለኛል። የእናንተስ እንዴት
ኧረ እንዴት ደስ እንደሚል እንደዚህ አይነት ጥያቄዎች ተበራክተዋል ሆኖም ካየሁዋቸው የዚህ ቪድዮ ኮሜንት እጅግ አስደስቶኛል 😊 አላውቅም ሁሉም ተሳክቶለት ቢያሳካው ደስ ይለኛል። የእናንተስ እንዴት ነበር ታዲያ? 🤔

ድንቅ አድርጎልኛል ድንቅ አድርጎልኛል የሠራዊት ጌታ (2) አልረሳኝም አምላክ አነሳኝ ከትቢያ (2) አ.ዝ ========= ድንቅ አድርጎልኛል በደሌን ሳይቆጥር ድንቅ አድርጎልኛል ወደቤቱ ጠራኝ ድንቅ አድርጎልኛል ረክሼ ሳለሁ ድንቅ አድርጎልኛል ልጄ ሆይ ና አለኝ ድንቅ አድርጎልኛል በዳግም ምጻቱ ድንቅ አድርጎልኛል መንግስቱን ሊያወርሰኝ አ.ዝ =========== ድንቅ አድርጎልኛል ከአንበሳ መንጋጋ ድንቅ አድርጎልኛል ከጉድጓድ አወጣኝ ድንቅ አድርጎልኛል በጠላቶቼ ፊት ድንቅ አድርጎልኛል ግርማ ሞገስ ሰጠኝ ድንቅ አድርጎልኛል ምን እመልሳለሁ ድንቅ አድርጎልኛል እንዲ ለወደደኝ አ.ዝ =========== ድንቅ አድርጎልኛል ጠላቶቼ ሁሉ ድንቅ አድርጎልኛል ሲጓደዱብኝ ድንቅ አድርጎልኛል ማን ይደርስለታል ድንቅ አድርጎልኛል እያሉ ሲሉኝ ድንቅ አድርጎልኛል ፈጥነህ ደረስክልኝ ድንቅ አድርጎልኛል ከሞት አዳንከኝ

​​ጳጉሜን ጳጉሜን የሚለው ስያሜዋ “ኤፓጉሜኔ” ከሚለው የግሪክ ቃል የመጣ ሲሆን ትርጉሙ ጭማሪ ማለት ነው፡፡ በግእዝ ተውሳክ ማለት ሲሆን ተውሳክ ማለት ተጨማሪ ማለት ነው፡፡ “ወሰከ - ጨመረ” ከሚለው የግእዝ ግስ የተገኘ ነው፡፡ ከኢትዮጵያ ውጭ ያሉ ሌሎች ሀገሮች ጳጉሜን የወር ተጨማሪ ያደርጓታል፡፡ ይኸውም ይታወቅ ዘንድ እኛ የወርን ቁጠር 30 ስናደርግ እነርሱ 31 ብለው የሚቆጥሩት ወር አላቸው፡፡ ይኹን እንጂ ኢትዮጵያውያን ሊቃውንት ጳጉሜን የወር ተጨማሪ ሳያደርጉ የዓመት ተጨማሪ አድርገዋታል፡፡ ጳጉሜን በዓመቱ መጨረሻ ላይ አምስት ወይም ስድስት ቀን በመሆን ትመጣለች፡፡ በአራት ዓመት አንዴ ማለትም በዘመነ ሉቃስ መጨረሻ በዘመነ ዮሐንስ መግቢያ ጳጉሜን ስድስት ቀን ትሆናለች፡፡ በዚህም ሀገራችን ኢትዮጵያ የአስራ ሦስት ወራት ጸጋ /Thirty months of sunshine/ በመባል ትታወቃለች፡፡ ጳጉሜን ስድስት በምትሆንበትም ጊዜ ጾመ ነቢያት /የገና ጾም/ ህዳር 14 ቀን ይገባና ታህሳስ 28 ቀን ጾሙ ተፈትቶ የልደት በዓል ይከበራል፡፡ በቅድስት ቤተክርስቲያን ካሉት ሁለት የፈቃድ አጽዋማት መካከል አንዱ በዚህ በጳጉሜን ወር የምንጾመው የፈቃድ ጾም ነው። ይህም ጾመ ዮዲት በመባል ይታወቃል፡፡ ይህ ግን እንደ አንደኛው የፈቃድ ጾም /ጽጌ ጾም/ በብዙዎች ዘንድ የታወቀ አይደለም፡፡ የዮዲት ጾም የሚባለውም እርሷ ስለ ጾመችው ነው፡፡ እዚህ ላይ ዮዲት ተብላ የተጠቀሰችው በቤተክርስቲያን ታሪክ ትምህርት ላይ በጥፋት ሥራዋ በተደጋጋሚ የምትጠቀሰው ዮዲት ጉዲት እንዳልሆነች ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡ ወደ ታሪኩ ስንመለስ የፋርስ ንጉስ ናቡከደነጾር በሠራዊቱ ተመክቶ ሹም ጠላት አጥፋ ድንበር አስፋ ካመነው እጅ መንሻ እየተቀበልህ ያላመነውን እያሳመንህ ና ብሎ ለጦር አበጋዙ ለሆሎፎርኒስ ትዕዛዝ ሰጠ፡፡ ዮዲ 2፥2-7፡፡ እርሱም እንደታዘዘው በኃይላቸው የታመኑ 12ሺህ እግረኞችንና በፈረስ የተቀመጡ 12ሺህ ጦረኞችን እየመራ ዘምቶ ካመነው እጅ መንሻ እየተቀበለ ያላመነውን እያሳመነ ብዙ ሀገሮችን እያጠፋ ሲሔድ ከአይሁድ ከተማ ደረሰ በዚህም ብዙ ጥፋት በመድረሱ የእስራኤል ልጆች አለቀሱ፡፡ ዮዲት ባሏ ሞቶባት ከወንድ ርቃ ንጽሕናዋን ጠብቃ በጾም በቀኖና በሀዘን ተወስና ትኖራለች በተፈጠረው ጥፋት ህዝቡ ላይ ለመጣው መከራ ማቅ ለብሳ በራስዋ ላይ ትብያ ነስንሳ ወደ እግዚአብሔር አለቀሰች፡፡ የፍጥረቱን ጥፋት የማይሻ እግዚአብሔር አምላክም ሕዝቡን የሚያድኑበትን መንገድ ለመጠየቅ ሱባኤ በገባች በሦስተኛው ቀን ገለፀላት፡፡ ዮዲ 8፥2፡፡ ከዚህ በኋላ ጠላታቸውን በዮዲት ምክንያት እስራኤላውያን እስከ ዮርዳኖስ እየተከተሉ አጥፍተዋቸዋል፡፡ ዮዲት ጠላቷን ለማጥፋት የቻለችው በጾምና በጸሎት ከእግዚአብሔር አምላክ ኃይል አግኝታ ነው፡፡ ስለዚህ ምዕመናን ጥንተ ጠላታችን ሰይጣንን ፈቃደ ሥጋን ለማሸነፍ በጾም ከፈጣሪያችን ኃይልን መጎናጸፍ አለብን ብለው ጳጉሜን በፈቃድ ይጾማሉ፡፡ የጳጉሜን ወር ዕለተ ምጽአት የሚታሰብባትም ወር ነች፡፡ ይህም ጳጉሜን የዓመታት መሸጋገሪያ ጨለማው የክረምት ወቅት ወደ ማብቂያው የምናልፍባት እንደሆነች ሁሉ ምጽአትም ከጊዜያዊው ወደ ዘላለማዊ ከምድራዊ ወደ ሰማያዊ ከዚህ ዓለም ወደ ወዲያኛው መሸጋገሪያ ነውና፡፡ <<<ወስብሐት ለእግዚአብሔር>>>

✞✞✞✝ እንኳን ለተባረከ ወር ጳጉሜን እና ለቅዱሳኑ ዮሐንስ መጥምቅ : ዑቲኮስ ሐዋርያና ቀሲስ አባ ብሶይ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። ✞✞✞✝ ✞✞✞✝በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! ✞✞✞✝ ✞✞✞✝ወርኀ ጳጉሜን ✞✞✞✝ ✞✞✞እግዚአብሔር አዝማናትን የፈጠራቸው ለሰው ልጆች ጥቅም መሆኑ ይታወቃል:: እርሱ ባወቀ: በረቂቅ ሥልጣኑ ዓለምን ፈጥሮ: ጊዜያትን እንዲከፍሉ ብርሃናትን (ፀሐይ: ጨረቃ: ከዋክብትን) ፈጥሮልናል:: ጊዜያትንም በደቂቃ: በሰዓት: በቀን: በሳምንት: በወር: በዓመታት: በኢዮቤልዩ: በክፍላተ ዘመናት እንድንቆጥር ያስማረንም እርሱ ነው:: የሰከንድ 540,000 ክፋይ ከሆነችው 'ሳድሲት' እስከ ትልቁ ቀመር (532 ዓመት) ድረስ እርሱ ለወደዳቸው እንዲያስተውሉት ገልጧል:: በየዘመኑም በቅዱስ ድሜጥሮስ: በቅዱስ ዮሐንስ ዘደማስቆ : በቅዱስ አቡሻኽር እና በሌሎቹም አድሮ መልካሙን አቆጣጠር አስተምሯል:: ሃገራችን ኢትዮጵያ ደግሞ የአሥራ ሦስት ወራት የፀሐይ ጸጋ (thirteen months sun shine) ያላት: አራቱ ወቅቶች የተስማሙላት ናት:: ✞✞✞ሌላው ዓለም ወሮችን 31,30,29 (28) እያደረገ ሲጠቀም እኛ ግን እንደ ኖኅ (ዘፍ. 8:1-15) አቆጣጠር ወሮችን በሠላሳ ቀናት ወስነን: ጳጉሜንን ለብቻዋ እናስቀምጣለን:: ጳጉሜን 'ኤጳጉሚኖስ' ከሚል የግሪክ (ጽርዕ) ቃል የተወሰደ ሲሆን ትርጉሙም 'ትርፍ: ጭማሪ' እንደ ማለት ነው:: የወርኀ ዻጉሜን አምስቱ (ስድስቱ) ቀናትም ወደ አዲስ ዓመት መሸጋገሪያ እንደ መሆናቸው ብዙ ምሳሌያት (ምሥጢራት) አሏቸው:: ዋናው ግን በዚህ ጊዜ ዳግም ምጽዓት ይታሠባል:: ጊዜውንም በጾምና በጸሎት ሊያሳልፉት ይገባል:: ግን በፈቃድ ነው እንጂ የግዴታ አይደለም:: ✞✞✞✝ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ ✞✞✞✝ ¤የቅዱሳኑ ዘካርያስና ኤልሳቤጥ ልጅ ¤በማኅጸን ሳለ መንፈስ ቅዱስ የሞላበት ¤በበርኀ ያደገና በገዳማዊ ቅድስና ያጌጠ ¤እሥራኤልን ለንስሐ ያጠመቀ ¤የጌታችንን መንገድ የጠረገ ¤ጌታውን ያጠመቀና ¤ስለ እውነት አንገቱን የተቆረጠ ታላቅ ሰው ነው:: ✞✞✞ስለዚህም ቤተ ክርስቲያን:- ¤ነቢይ: ¤ሐዋርያ: ¤ሰማዕት: ¤ጻድቅ: ¤ገዳማዊ: ¤መጥምቀ መለኮት: ¤ጸያሔ ፍኖት: ¤ቃለ ዐዋዲ ብላ ታከብረዋለች:: ✞✞✞ቅዱሱ በዚህች ዕለት ወደ እሥር ቤት ገብቷል:: ይሕስ እንደ ምን ነው ቢሉ:- ንጉሡ ሔሮድስ የወንድሙን የፊልጶስን ሚስት ሔሮድያዳን በማግባቱና በመሰል ክፋቶቹ ቅዱስ ዮሐንስ ይገስጸው ነበር:: ቅዱስ ዮሐንስ "መምሕርወመገስጽ: ዘኢያደሉ ለገጽ - ፊት አይቶ የማያዳላ" ነውና ገሰጸው:: ሔሮድስ ቅዱሱን ይፈራው: ያከብረውም ነበር:: በኋላ ግን ፈቃደ ሥጋው ስላየለበት: በተለይ ደግሞ ከሰባት ቀናት በኋላ ልደቱን ሲያከብር እንዳይረብሸው በመስጋት በዚህች ቀን በወታደሮቹ አስይዞ እሥር ቤት ውስጥ ጥሎታል:: ለሰባት ቀናት በጨለማ ውስጥ አሥሮ መስከረም 2 ቀን አንገቱን እንዴት እንዳስቆረጠው ዕለቱን ጠብቀን እንመለከታለንና የዚያ ሰው ይበለን:: ✞✞✞✝ቅዱስ ዑቲኮስ ሐዋርያ ✞✞✞✝ ✞✞✞ቅዱሱ ሐዋርያ ጭራሽ ከነስማቸው እንኳ እየተዘነጉ ከሔዱ ሐዋርያት አንዱ ሲሆን ቁጥሩም ከሰባ ሁለቱ አርድእት ነው:: በወጣትነት ዘመኑ የጌታችን ደቀ መዝሙር መሆንን መርጦ ለሦስት ዓመት ከሦስት ወር ምሥጢረ ወንጌልን ጠንቅቆ ተምሯል:: መንፈስ ቅዱስ በወረደ ጊዜም እንደ መጠኑ ተቀብሎ ለአገልግሎት ወጥቷል:: በመጀመሪያ የወንጌላዊው ዮሐንስ ተከታይ ሁኖ ብዙ ምሥጢራትን ተካፍሏል:: ቀጥሎም ቅዱስ ጳውሎስን ተከትሎ ብዙ አሕጉራትን በስብከተ ወንጌል አዳርሷል:: በመጨረሻም በእስያ አካባቢ ለብቻው ተጉዞ: ብዙ ነፍሳትን ማርኮ: ጣዖታትን አጥፍቷል:: ስለዚህ ፈንታም በእሳት: በስለትና በግርፋት ብዙ መከራዎችን አሳልፏል:: በዚህች ቀንም በበጐው እርግና (ሽምግልና) ዐርፏል:: ✞✞✞✝ቅዱስ ብሶይ ቀሲስ ✞✞✞✝ ✞✞✞ከ3ኛው መቶ ክ/ዘመን ካህናት አንዱ የነበረው አባ ብሶይ ለአገልግሎት ወጥቶ ሲመለስ የቤተሰቦቹ ቤት ሰው አልነበረበትም:: "የት ሔዱ?" ብሎ ቢጠይቅ "ወንድምህ አባ ሖር እና እናትህ ቅድስት ይድራ ወደ እስክንድርያ ሔደዋል:: በዚያም ስለ ክርስቶስ ፍቅር ተሰውተዋል::" አሉት:: በማግስቱ የኔ ብጤዎችን ጠርቶ ሃብቱን: ንብረቱን: ቤቱን አካፈላቸው:: ለራሱ ግን አንዲት በትር እና ሦስት የዳቦ ቁራሾች ይዞ ጉዞ ተነሳ:: ወደ እስክንድርያ እንደ ደረሰ አፈላልጐ የቤተሰቦቹን መቃብር አገኘ:: ከፊታቸው ወድቆም የናፍቆት ለቅሶን አለቀሰ:: ወዲያውም እንዲህ አላቸው:- "ፈጥኜ ወደ እናንተ ስለምመጣ ጠብቁኝ:: ደግሞም ጸልዩልኝ::" ከዚያ ተነስቶ በመኮንኑ ፊት ስለ ክርስቶስ የባሕርይ አምላክነት መሰከረ:: በዚህ ምክንያት ብዙ ተሰቃይቶ በዚህች ቀን ሰማዕት ሆኗል:: ከወገኖቹም ጋር ተቀብሯል:: ✞✞✞አምላከ ቅዱሳን ተረፈ ዘመኑን ባርኮ ለአዲሱ ዘመን በቸር ያድርሰን:: ከወዳጆቹም ጸጋ በረከትን ይክፈለን:: ✞✞✞ጳጉሜን 1 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት 1.ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ (የታሠረበት) 2.ቅዱስ ዑቲኮስ ሐዋርያ (ከሰባ ሁለቱ አርድእት) 3.ቅዱስ ብሶይ ቀሲስ (ሰማዕት) 4.አባ ጳኩሚስ /ባኹም (የሦስት ሺ ቅዱሳን አባት) 5.አባ ሰራብዮን /ሰራፕዮን (የአሥር ሺ ቅዱሳን አባት) ✞✞✞ወርኀዊ በዓላት (የለም) ††† "ጌታ ኢየሱስ ለሕዝቡ ስለ ዮሐንስ ሊናገር ጀመረ . . . ምን ልታዩ ወጣችሁ? ነቢይን? አዎን እላችኋለሁ ከነቢይም የሚበልጠውን . . . እውነት እላችኋለሁ ከሴቶች ከተወለዱት መካከል ከመጥምቁ ዮሐንስ የሚበልጥ አልተነሳም . . . ነቢያት ሁሉና ሕጉ እስከ ዮሐንስ ድረስ ትንቢት ተናገሩ:: ልትቀበሉትስ ብትወዱ ይመጣ ዘንድ ያለው ኤልያስ ይሕ ነው:: የሚሰማ ጆሮ ያለው ይስማ::" ††† (ማቴ. ፲፩፥፯-፲፭) <<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>> ከኢ/ኦ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ላይ የተገኙ የእለቱ የቅዱሳን(የጻድቃን) አባቶቻችን እና የቅዱሳን(የጻድቃን) እናቶቻችን ጽድቅ እና ገድላት ይነገርበታል። በመሀልም ጠቃሚና አስተማሪ ነው የምንላቸውን ታሪኮች ወደእናንተ የምናቀርብ ይሆናል። https://telegram.me/gedlekdusan

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! 🙏 እስከ መጨረሻው በማንበብ ይተባበሩን፤ ለሌሎችም ያጋሩት! 🙏 የሚዲያ ክፍላችን ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ እግዚአብሔር በሰጠን አቅም ሁሉ ታላላቅ ሥራዎችን ሲሠራ ቆይቷል። በተለይም በዚህ በዲጂታል ዘመን የቤተክርስቲያንን አስተምህሮ ማዳረስ፣ የእግዚአብሔርን ቃል በጽሑፍም ሆነ በቪዲዮ ተደራሽ ማድረግ ዋነኛውና ውዱ አደራችን ነው። ባለፉት ዓመታት ከቅን ወንድምና እህቶቻችን ስልክ እየተዋስን የተለያዩ ትምህርቶችንና መርሃ ግብሮችን ስናቀርብላችሁ ቆይተናል። ነገር ግን ካቀድነው ትልቅ ራእይ አንጻር ሲታይ እስከ አሁን የሠራነው በጣም ጥቂቱን ብቻ ነው። የእቅዳችን ዋና ዋና ግቦች፦
በዲጂታል ዘመን ቃለ እግዚአብሔርን ማዳረስ፤ በግቢ ውስጥ ያሉትንና ተመርቀው የወጡትን የግቢ ጉባኤያችንን ፍሬዎች የሚያገናኝና ካሉበት ቦታ ሆነው የሚያገለግሉበትን መንገድ በማመቻቸት ቤተሰባዊነታችንን ማጠናከር፤ ከመደበኛ መርሐ ግብራችን በተጨማሪ የጉዞ፣ የምሩቃን ሕብረት፣ የምረቃ መርሃ ግብር (Graduation ceremony)፣ የሃፍ ላይፍ (Half-Life) እና የአዲስ ተማሪዎች መቀበያ (Freshman welcoming event) ፕሮግራሞችን በቪዲዮ መዝግቦ ማሰናዳት እና በዶክመንተሪ መልክ ለእይታ ማብቃት፤
እነዚህን ትላልቅ ሥራዎች አቅደን የተነሳን ቢሆንም የራሳችን የቀረጻ ማቴሪያል አለመኖሩ ዋና ማነቆ ሆኖብናል። እንደሚታወቀው የተውሶ ስልክ በፈለግነው ሰዓት ለማግኘት አዳጋች ከመሆኑም በላይ ለአገልግሎቱ ስፋት በቂ አይደለም። የሚዲያ ቡድናችን ይህንን ችግር ለመቅረፍ በግቢያችን ውስጥ የግራፊክስ ዲዛይን እና ቪዲዮ ኤዲቲንግ ሥልጠና በመስጠት እስከ 40,000 ብር ለመሰብሰብ ጥረት ያደረገ ቢሆንም፣ ለዕቃዎቹ ግዢ አሁንም ገና ብዙ ይቀረናል።
"ሀምሳ ሎሚ ለአንድ ሰው ሸክሙ፣ ለሀምሳ ሰው ጌጡ ነው"
እንደሚባለው እኛም ኦርቶዶክሳውያን ከተባበርን ማንኛውንም ነገር ማሳካት እንችላለን። ይህ ቅዱስ አገልግሎት ሳይቋረጥ እንዲቀጥልና ይበልጥ እንዲስፋፋ ሁላችሁም የበኩላችሁን አሻራ እንድታስቀምጡ በአክብሮት እንጠይቃለን። 📌 በምን በምን መረዳት ይችላሉ? 1️⃣ መረጃ በማጋራት (Share)፦ ለዚህ መርሃ ግብር የተዘጋጀውን ፖስተር በቴሌግራም፣ በኢንስታግራም Story፤ እንዲሁም በቲክቶክ እና በዩቲዩብ የተለቀቁትን ቪዲዮዎች Share በማድረግ ተደራሽነቱን ማፋጠን። 2️⃣ ሰዎችን በመጠቆም፦ ድጋፍ ሊያደርጉልን የሚችሉ ሰዎችን (ለምሳሌ ቲክቶከሮችን) Mention ማድረግ፤ ወይም በገንዘብና በዓይነት ሊረዱን የሚችሉ ኦርቶዶክሳውያንን ካወቃችሁ ስምና ስልክ ቁጥራቸውን ከዚህ በታች በተቀመጠው የጉግል ፎርም ሊንክ ያስቀምጡ፦ https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSc4PIhwq7W2ysKVATYxxuDx3gOxhb4-LdsqyG4d807sPXPPPg/viewform?usp=header 3️⃣ በዓይነት ድጋፍ በማድረግ፦ ለሥራችን አስፈላጊ የሆኑ የቴክኖሎጂ ዕቃዎችን በመስጠት፦ 📷 ካሜራ (Camera) 📐 የካሜራ ስታንድ (Tripod) 🎙 ማይክሮፎን (Microphone) 💾 ኤክስተርናል ሃርድዲስክ (External Hard Drive) 🎥 ጊምባል (Gimbal / Stabilizer) 4️⃣ በገንዘብ ድጋፍ በማድረግ፦ «አነሰ፣ በዛ» ሳያሉ አቅማችሁ የፈቀደውን ያህል በመለገስ የዚህ በረከት ተካፋይ ይሁኑ! 💳 የባንክ እና የስልክ አድራሻዎች፦ CBE (ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ): 1000792257686 (Egzihareya Solomon And/or Arsema) Telebirr (ቴሌብር): 0958313628 (Arsema) 📞 ለበለጠ መረጃ፦ 📱 +251 98 332 9770 📱 +251 90 549 6768 ለምታደርጉት ትብብር ሁሉ እግዚአብሔር አምላክ በረከቱን ያድላችሁ!🙏 ▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰         የአ/አ/ሳ/ቴ/ዩ ግቢ ጉባኤ 📥  @gibigubaeHasabon_bot ጻፉልን 🏷 @aastugibigubae ተከታተሉን 📷 @GGgallery1 የፎቶ ማኅደራችን ▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰▰ TikTok | Instagram | YouTube

ሰዎች ስለ ክርስቶስ ከእንግዲህ መስማት አያስፈልጋቸውም፣ በቂ ሰምተዋል። ይልቁንም ክርስቶስን በእኛ ውስጥ ማየት ያስፈልጋቸዋል። Fr Pishoy Kamel https://t.me/gedlekdusan
ሰዎች ስለ ክርስቶስ ከእንግዲህ መስማት አያስፈልጋቸውም፣ በቂ ሰምተዋል። ይልቁንም ክርስቶስን በእኛ ውስጥ ማየት ያስፈልጋቸዋል። Fr Pishoy Kamel https://t.me/gedlekdusan