en
Feedback
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

Channel የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 14 430 subscribers, ranking 6 084 in the Religion & Spirituality category and 2 336 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 14 430 subscribers.

According to the latest data from 27 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 543 over the last 30 days and by 21 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 36.43%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects N/A% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 5 252 views. Within the first day, a publication typically gains 0 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 33.

📝 Description and content policy

Channel description not provided.

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 28 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

14 430
Subscribers
+2124 hours
+1247 days
+54330 days
Posts Archive
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ ተጠናቀቀ 16/03/2016 ዓ.ም (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) ከትላንት ጀምሮ ለሁለት ተከታታይ ቀናት ሲካሄድ የነበረው የአዲስ አበባ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤውን በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት መሰብሰቢያ አዳራሽ ተጠናቀቀ። በጉባኤውም ላይ ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ የደቡብ ኦሞ እና የአሪ ዞኖች ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ የበላይ ጠባቂ ፣ መጋቤ ሐዲስ ጸጋ ወልደ ትንሳኤ የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ምክትል ኃላፊ ፣ መልአከ ብርሃናት ቀሲስ ተክለርትዕ ገብረ ወልድ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ጸሐፊ ፣ መምህር ደምስ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ክፍል ዋና ኃላፊ ፣ ጥሪ የተደረገላቸው አንግዶች ፣ የሀገር አቀፍ እና የአዲስ አበባ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ሥራ አመራር አባላትና የአጥቢያ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ሊቃነ መናብርት ተገኝተዋል። ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ ባስተላለፉት አባታዊ ምክር "መልካም አገልጋይ በንጉሡ ይወደዳል።" በሚል መነሻ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ትውልድን በመቅረጽ የሚያገለግሉት አገልግሎት በንጉሥ እግዚአብሔር ዘንድ የተወደደ ሊሆን እንደሚገባው መክረዋል። በጉባኤው የጠዋት ውሎው በ5 የትኩረት አቅጣጫ ላይ ትኩረቱን ያደረገውን የ2016 ዓ.ም የመጪው የ6 ወር ዕቅድ ቀርቦ ውይይት የተደረገበት ሲሆን ከተሳታፊዎች ብዙ ግብአቶች የተገኘ ሲሆን ለተነሱትም ጥያቄዎች ላዕከ ኄራን መንክር ግርማ እና መምህር አንተነህ መልስ ሰጥተውባቸዋል። በከሰዓቱም መርሐ ግብር የሰንበት ትምህርት ቤቶች አባላትና ምዕመናን በቃለ አዋዲው በተሰጣቸው የመወሰን ድርሻና የአንድነቱን አወቃቀር ሥልጣንና ኃላፊነት የሚዳስስ ጥናታዊ ጽሑፍ ቀርቦ ውይይ ተደርጓል። ጉባኤው የኃላፊነት ጊዜያቸውን ያጠናቀቁትን ሥራ አመራሮች በጸሎተ ማርያም ሸኝቶ አዲሱን ሥራ አመራር በመምረጥ እንዲሁ አገልግሎታቸው የተቃና እንዲሆን በብፁዕ አቡነ ፊልጶስ ጸሎተ ማርያም ተደግሞላቸው የሥራ መመሪያ ተሰጥቷቸዋል። በመጨረሻም የአቋም መግለጫ በማውጣት ጉባኤው ተጠናቅቋል። (የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት) ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Tiktok👇 https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion

የአሥራ ሁለተኛ ክፍልን አጠናቅቀው ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ለሚገቡ ኦርቶዶክሳዊያን ተማሪዎች የሽኝት መርሐ ግብር ተከናወነ። 16-03-2016 ዓ.ም (የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት) በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነትና ማኅበረ ቅዱሳን በመተባበር ያዘጋጁት የአሥራ ሁለተኛ ክፍልን አጠናቅቀው ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ለሚገቡ ኦርቶዶክሳዊያን ተማሪዎች የሽኝት መርሐ ግብር ተከናወነ። በመርሐ ግብሩም ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ የደቡብ ኦሞ እና የአሪ ዞኖች ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ሊቀ ጳጳስ ፣ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ተቀዳሚ ምክትል ሰብሳቢ ዲ.ን ስንታየሁ ምስጋናው ፣ የማኅበረ ቅዱሳን ዋና ሰብሳቢ ቀሲስ ዶክተር ሙሉጌታ ስዩም ፣ ቀሲስ ሙሉቀን ብርሃኑ የማኅበረ ቅዱሳን ሕዝብ ግንኙነትና ትብብር አገልግሎት ማስተባበሪያ ምክትል ኃላፊ ፣ የ12ኛ ክፍልን ያጠናቀቁ ተማሪዎችና ወላጆቻቸው ተገኝተዋል። በመርሐ ግብሩም ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ ባስተላለፉት አባታዊ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ "የእርሱ ተማሪ አደረገኝ" በሚል የቅዱስ ቀለሜንጦስን ቃል መነሻ አድርገው "ዓለማዊ ትምህርታቸውን ከመንፈሳዊ አገልግሎታቸው ጋር አስተባበረው በመያዝ በዩኒቨርስቲም ቆይታቸው መንፈሳዊ ተማሪዎች ፣ መንፈሳዊ አገልጋዮች ከመሆን የሚያግዳድ የሚከለክላችሁ ነገር የለም" ብለዋል። ከፍተኛ ነጥብ ያስመዘገቡ ተማሪዎችም ከብፁዕ አባታችን እጅ የማበረታቻ ሽልማት ተቀብለዋል። (የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት) ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Tiktok👇 https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion

"ወደ ሕይወት መግባት ብትወድ ግን ትእዛዛትን ጠብቅ አለው።" ማቴ 19፡18 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! መልካም ዕለተ ሰንበት! ✍️YouT
"ወደ ሕይወት መግባት ብትወድ ግን ትእዛዛትን ጠብቅ አለው።" ማቴ 19፡18 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! መልካም ዕለተ ሰንበት! ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu

የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ ተጀመረ። 15-03-2016 ዓ.ም (ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት) በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ  የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን የሀገር አቀፍ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ተቀዳሚ ምክትል ሰብሳቢ ቀሲስ ጥላሁን ደሲሳ ፣ ምክትል ሰብሳቢ ዲ.ን ስንታየሁ ምስጋናው ፣ የአንድነቱ የሥራ አመራር ኮሚቴዎች እንዲሁም የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ተቀዳሚ ምክትል ሰብሳቢ ላዕከ ኄራን መንክር ግርማ ፣ መምህር አንተነህ አወቀ የአንድነቱ ጸሐፊና ሥራ አመራሮች እንዲሁም የአጥቢያ ሰንበት ት/ቤቶች ሰብሳቢዎች በተገኙበት የመጀመሪያ ቀን ጉባኤ ዛሬ ኅዳር 15 ቀን በአ.አ ሀገረ ስብከት አዳራሸ ተካሂዷል። በጠቅላላ ጉባኤውም የ 6ወር የዕቅድ አፈጻጸምና አጠቃላይ የ3ዓመት የሥራ ትግበራ ሪፖርቶች ቀርበዋል። በሪፖርቱም ትኩረት ተደርጎ ሲሰራባቸው የነበሩ አምስት አብይት ጉዳዮች ፤ የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት በፐርሰንት፤ ያጋጠሙ ተግዳሮቶችና ቀጣይ ሊሰራባቸው የሚገቡ የትኩረት አቅጣጫዎች ተመላክተዋል። የ አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በያዝነው ዓመት የአመራር ዘመኑ በሚያበቃው ሥራ አመራር በ 3ዓመታት ውስጥ ጽሕፈት ቤት 85 በመቶ ፣ ልማት ክፍል 71 በመቶ ያሳካ ሲሆን በሪፖርቱ መሠረት የመረጃና ግንኙነት ክፍል ዝቅተኛ አፈጻጸም እንደነበረው ተገልጿል። የበጀት እጥረት መኖር ፣ በአንድነቱ ስም የተከፈተ የባንክ አካውንት አለመኖር ፣ አጥቢያ ሰንበት ት/ቤቶች ለአንድነቱ ትኩረት አለመስጠት እንደ ተግዳሮት የተነሱ ሲሆን ሥርዓተ ትምህርቱን ከዓመት ወደ ዓመት በሁሉም ሰንበት ት/ቤቶች እንዲተገበር ማስቻል በዚህም ከ57 ሰንበት ት/ቤቶች ተነስቶ በዘንድሮው ዓመት 208 ሰንበት ት/ቤቶች መተግበራቸውን፣  ከ300 በላይ ተተኪ መምህራንን ማፍራት እንዲሁም ለ600 ሰንበት ተማሪዎች በኢኮኖሚና ራስን ማስቻል ሥልጠና በመስጠት 50 ሰዎች የብድር ፍቃድና 5 ሰዎች ደግሞ ብድር ወስደው የስራ ትግበራ ላይ መግባታቸውን  እንዲሁም በቤተ ክርስቲያናችን ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ በንቃት ሲሳተፍ ነበር የሚሉት ጉዳዮች በስፋት ተገልጸዋል። የስድስት ወር ዕቅድ ትግበራ በአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ዕቅድና ክትትል ኃላፊ ተስፋዓለም ከተማ የ3 ዓመታት ሥራ አፈጻጸም ትግበራ ደግሞ በአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ሰብሳቢ ላዕከ ኄራን መንክር ግርማ ቀርቧል። ጉባኤው በነገውም ዕለት ቀጥሎ የሚውል ሲሆን  የሰንበት ት/ቤቶች ድርሻ በቤተ ክርስቲያን የውስጥ አስተዳደር ጉዳይ ላይ ይመክራል የጋራ አቋምም ይይዛል ተብሎ ይጠበቃል። (የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት) ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Tiktok👇 https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion

"በጾምና በጸሎትም ሌሊትና ቀን እያገለገለች ከመቅደስ አትለይም ነበር።" ሉቃ 2፡37 እንኳን ለጾመ ነቢያት በሰላም አደረሳችሁ! ጾሙ የዲያብሎስ ድል መንሻ የመንግሥተ ሰማያት መውረሻ ያደርግልን ዘንድ
"በጾምና በጸሎትም ሌሊትና ቀን እያገለገለች ከመቅደስ አትለይም ነበር።" ሉቃ 2፡37 እንኳን ለጾመ ነቢያት በሰላም አደረሳችሁ! ጾሙ የዲያብሎስ ድል መንሻ የመንግሥተ ሰማያት መውረሻ ያደርግልን ዘንድ የአምላካችን ቅዱስ ፈቃድ ይሁንልን! የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu

የመርሐ ግርብር ማስተካከያ!!! ኅዳር 11 ቀን 2016 ዓ.ም ቋሚ ቅዱስ ሲኖዶስ የጸሎትና የምሕላ አዋጅ መግለጫ ማውጣቱ ይታወሳል፡፡ በመግለጫው፡- ታቦታት ይወጣሉ ተብሎ የነበረ መሆኑ ይታሳል፡፡ ይህ
የመርሐ ግርብር ማስተካከያ!!! ኅዳር 11 ቀን 2016 ዓ.ም ቋሚ ቅዱስ ሲኖዶስ የጸሎትና የምሕላ አዋጅ መግለጫ ማውጣቱ ይታወሳል፡፡ በመግለጫው፡- ታቦታት ይወጣሉ ተብሎ የነበረ መሆኑ ይታሳል፡፡ ይህንንም በተመለከተ ኅዳር 13 ቀን 2016 ዓ.ም የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ መልእክት አስተላልፈዋል፡፡ባስተላለፉት መልእክትም ከኅዳር 15 እስከ 21 ቀን ባለው የጸሎት መርሐ ግብር ታቦት ሳይወጣ ልብሰ ተክህኖ በመልበስ ብቻ ቅዳሜ እና እሁድ ከቅዳሴው በኋላ በአውደ ምሕረት ምህላ ተደርጎ ሰርሖተ ህዝብ ይሆናል ትምህርት አይሰጥም። በማታው መርሐ ግብር 11 ሰዓት ላይ ልብሰ ተክህኖ በመልበስ ጸሎትና ምሕላ ብቻ ተደርጎ ስንብት ይደረጋል፡፡ ትምህርት አይሰጥም፡፡ ከኅዳር 22 ጀምሮ እስከ ታኅሳስ 28 ቀን 2016 ዓ.ም ጸሎትና ምሕላው ከትምህርተ ወንጌል ጋር ይቀጥላል፡፡ እንደየሁኔታው ከቅዱስ ሲኖዶስና ከመንረ ፓትርያክ በየውቅቱ ማሳሰቢያ ይሰጣል ሲሉ ብፁዕነታቸው ባስተላለፉት መልእክት ገልጸዋል፡፡ የቅዱስ ሲኖዶስ ጽሕፈት ቤት

"ጾምን ቀድሱ፥ ጉባኤውንም አውጁ፤ ሽምግሌዎችንና በምድር የሚኖሩትን ሁሉ ወደ አምላካችሁ ወደ እግዚአብሔር ቤት ሰብስቡ፥ ወደ እግዚአብሔርም ጩኹ።" ኢዩ 1፡14 እንኳን ለጾመ ነቢያት በሰላም አደረሳች
"ጾምን ቀድሱ፥ ጉባኤውንም አውጁ፤ ሽምግሌዎችንና በምድር የሚኖሩትን ሁሉ ወደ አምላካችሁ ወደ እግዚአብሔር ቤት ሰብስቡ፥ ወደ እግዚአብሔርም ጩኹ።" ኢዩ 1፡14 እንኳን ለጾመ ነቢያት በሰላም አደረሳችሁ! ጾሙ የዲያብሎስ ድል መንሻ የመንግሥተ ሰማያት መውረሻ ያደርግልን ዘንድ የአምላካችን ቅዱስ ፈቃድ ይሁንልን! የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu

https://youtu.be/2SMEAnVDiWI?si=O0-7yEyeYUHlKWJU የሃይማኖት አባቶች እየተፈጠሩ ያሉ ችግሮችን በጾምና በጸሎት ለመፍታት ጥረት ሲያደርጉ መንግሥትና ፖለቲከኞች ደግሞ በመቻቻል አገራቸውን የሚያስቀጥል፣ ትውልዱን ከመከራ የሚታደግ፣ ኋላ ቀርነትን የሚያስወግድ ተግባር ለመፈጸም መተባበር ይኖርባቸዋል ... በዕለቱ በዝርዝር ከምንመለከታቸው ዜናዎቻችን መካከል አንዱ ነው። ዜና ፈለገ ጥበብ ሳምንታዊ የዜና መርሐ ግብር ከ2፡00 ጀምሮ በሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ፈለገ ጥበ ብ ሚዲያ ይከታተሉን።

የሰላም ዋጋው ስንት ነው? ሰላም የሚለው ቃል ሲጠራ ቀላል ቢመስልም ዋጋው ግን በገንዘብ ከመተመን በላይ ነው፡፡ ሰላም እንኳን ለሰው ልጅ ለእንስሳት፣ ለአራዊት እና በጠቅላላው ለሥነ ፍጥረት በጣም አ
የሰላም ዋጋው ስንት ነው? ሰላም የሚለው ቃል ሲጠራ ቀላል ቢመስልም ዋጋው ግን በገንዘብ ከመተመን በላይ ነው፡፡ ሰላም እንኳን ለሰው ልጅ ለእንስሳት፣ ለአራዊት እና በጠቅላላው ለሥነ ፍጥረት በጣም አስፈላጊ ነገር ነው፡፡ ሰላም ከሌለ ማንም ወጥቶ መግባት፣ ነግዶ ማትረፍ፣ አርሶ መብላት፣ ደግሶ መዳር አይችልም፡፡ ሠርቶ የመለወጥን ተስፋም ያመነምናል፡፡ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በጸሎተ ቅዳሴዋ “እግዚአብሔር በይቅርታው አንድ ያደርገን ዘንድ ስለ ሰላም እንማልዳለን፤ በዘመኑ ሁሉ ፍጹም ሰላምን እግዚአብሔር ይሰጣት ዘንድ እግዚአብሔርን ስለምትወድ ስለ አገራችን ኢትዮጵያ እንማልዳለን” በማለት ዕለት ዕለት ፈጣሪዋን የምታሳስበው ያለ ምክንያት አይደለም - ሰላም የሁሉ ነገር መሠረት ስለሆነ እንጂ፡፡ እንኳን ሰማያዊ ለሆነው ሃይማኖት ለምድራዊ ኑሮም ቢሆን ዓለም የምትሸልመው ሳይታክቱ ለሰላም የደከሙትን ነው፡፡ ማንበብ ይቀጥሉ ... https://eotc-gssu.org/a/የሰላም-ዋጋው-ስንት-ነው/ የሰላም ዋጋው ስንት ነው? ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Tiktok👇 https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion