en
Feedback
Grace & Truth Ministry

Grace & Truth Ministry

Open in Telegram

እንኳን ወደዚህ ቻናል በሰላም መጡ ከእግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ፀጋና ሰላም ይብዛላችሁ በእውነት ቃልና በፀጋው መንፈስ ይታነፁ

Show more
1 029
Subscribers
No data24 hours
-77 days
-2030 days
Posts Archive
ክፍሉን ማወቄ ሳይሆን እምነት ነው በጠራራ ጸሃይ መርከብ የሚያሰራኝ ክፍሉን ማወቄ ሳይሆን እምነት ነው ከዑር ከለዳውያን የሚያወጣኝ ክፍሉን ማወቄ ሳይሆን እምነት ነው ከግብጽ ይልቅ ምድረ በዳን እንድ
ክፍሉን ማወቄ ሳይሆን እምነት ነው በጠራራ ጸሃይ መርከብ የሚያሰራኝ ክፍሉን ማወቄ ሳይሆን እምነት ነው ከዑር ከለዳውያን የሚያወጣኝ ክፍሉን ማወቄ ሳይሆን እምነት ነው ከግብጽ ይልቅ ምድረ በዳን እንድመርጥ የሚያደርገኝ ክፍሉን ማወቄ ሳይሆን እምነት ነው በምድረ በዳ ጸንቼ እንድቆም የሚያደርገኝ ክፍሉን ማወቄ ሳይሆን እምነት ነው በጎልያድ ፊት የሚያቆመኝ ክፍሉን ማወቄ ሳይሆን እምነት ብቻ ነው በውሃው ላይ እንድራመድ የሚያደርገኝ አሁንም ቢሆን የሆነ ጥቅስ ማወቄ ሳይሆን እምነት ነው እግዚአብሔርን እንዳስብና በእርሱ መንገድ እንድሄድ የሚያደርገኝ እምነት የፈሪዎች ሳይሆን የደፋሮች ነው፡ በስሜታችን ከምናውቀውና ከምንረዳው ነገር በላይና አልፎ መሄድን ይጠይቃል። እምነት ሐሳብ ሳይሆን ተግባር ነው: እምነት ቀመር የለውም: ካለውም ተግባር ብቻ ነው::

ክፍሉን ማወቄ ሳይሆን እምነት ነው በጠራራ ጸሃይ መርከብ የሚያሰራኝ ክፍሉን ማወቄ ሳይሆን እምነት ነው  ከዑር ከለዳውያን የሚያወጣኝ ክፍሉን ማወቄ ሳይሆን እምነት ነው ከግብጽ ይልቅ ምድረ በዳን እንድመርጥ የሚያደርገኝ ክፍሉን ማወቄ ሳይሆን እምነት ነው በምድረ በዳ ጸንቼ እንድቆም የሚያደርገኝ ክፍሉን ማወቄ ሳይሆን እምነት ነው በጎልያድ ፊት የሚያቆመኝ ክፍሉን ማወቄ ሳይሆን እምነት ብቻ ነው በውሃው ላይ  እንድራመድ የሚያደርገኝ አሁንም ቢሆን የሆነ ጥቅስ ማወቄ ሳይሆን እምነት ነው እግዚአብሔርን እንዳስብና በእርሱ መንገድ እንድሄድ የሚያደርገኝ እምነት የፈሪዎች ሳይሆን የደፋሮች ነው፡ በስሜታችን ከምናውቀውና ከምንረዳው ነገር በላይና አልፎ መሄድን ይጠይቃል። እምነት ሐሳብ ሳይሆን ተግባር ነው: እምነት ቀመር የለውም: ካለውም ተግባር ብቻ ነው::

"በዚያም ከስምንት ዓመት ጀምሮ በአልጋ ላይ ተኝቶ የነበረውን ኤንያ የሚሉትን አንድ ሰው አገኘ፤ እርሱም ሽባ ነበረ። ጴጥሮስም ኤንያ ሆይ፥ ኢየሱስ ክርስቶስ ይፈውስሃል፤ ተነሣ ለራስህም አንጥፍ አለው
"በዚያም ከስምንት ዓመት ጀምሮ በአልጋ ላይ ተኝቶ የነበረውን ኤንያ የሚሉትን አንድ ሰው አገኘ፤ እርሱም ሽባ ነበረ። ጴጥሮስም ኤንያ ሆይ፥ ኢየሱስ ክርስቶስ ይፈውስሃል፤ ተነሣ ለራስህም አንጥፍ አለው። ወዲያውም ተነሣ። በልዳና በሰሮናም የሚኖሩ ሁሉ እርሱን አይተው ወደ ጌታ ዘወር አሉ።(ሐዋ 9:34-35) #ዛሬ ኢየሱስን ፈዋሽ አድርጎ ለአለም ማሳየት ላይ የክርስቶስ አካል የወደቀች የሚመስል ሁኔታ ውስጥ አለን.. ሰበባ ሰበብ እንፈጥራለን፣ በአስተምህሮ እንከለላለን.. ወይም የሚፈጠሩ ስሕተቶችን ፍራቻ ፅንፈኛና ተቃራኒ እንሆናለን። በነገራችን ላይ ኢየሱስ ፈውስን በሰጠበት ቦታ ሁሉ ፈሪሳውያን (ለእግዚአብሔር በጣም የቀረቡና ከእነሱ በላይ ለአሳር የሚል መረዳት ያለቸው ) የሰው መፈታትና ከደዌ መላቀቅ ምንም ነፃነት አይሰጣቸውም ነበር። ዛሬ ሁሉንም አይነት ነገር ለሰው ጭንቅላታዊ ነገር እየተውን ነው፣ ሰዎች ለአካላዊ በሽታ ፣ ለስሜታዊ ጥቃትና አእምሮዊ መታወክ ደርሶባቸው ቢመጡብን.. ወደ ሕክምና ቦታ እንጦቅማለን(ችግር አለው እያልኩ አይደለም) በልብህ ግን ለፈውስ ማመን እያቃተህ ስላለ ፍራቻህን እየተቃወምኩ ነው! የክርስቶስ አካል ከመንፈስ ቅዱስ የኃይል መግለጥ ራሷን እያገለለች ከመጣች "የፍልስፍና ማዕከል" ልትሆን ትችላለች፣ ትልልቅ የስነ-መለኮት ርዕሶች መናኸሪያ ልትሆን ትችላለች! 👉 " እምነታችሁም በእግዚአብሔር ኃይል እንጂ በሰው ጥበብ እንዳይሆን፥ ቃሌም ስብከቴም መንፈስንና ኃይልን በመግለጥ ነበረ እንጂ፥ በሚያባብል በጥበብ ቃል አልነበረም።" (1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 2:4-5) የትኛውም ስም ያለው በሽታና ደዌ ሁሉ ኢየሱስ ፈዋሽ ነው 💒 #ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ💒 ወደ ቴሌግራም ቻናላችን ለመቀላቀል ሁለት ጊዜ ብቻ ይኼንን ሊንክ ይንኩ 👉@biruk351

አለማመን መቃረን. part 2.mp330.63 MB

አለማመንን መቃረን. part1.mp344.36 MB

የእምነት ሕግ ክፍል2.mp352.79 MB

"በወንድማማች መዋደድ እርስ በርሳችሁ ተዋደዱ" /ሮሜ. 12፡10/❤ ✔️ጽድቅ መብቀል ነው፣ ፍቅር ደግሞ ፍሬ ነው። የምንበቅለው በደሙ፣ የምናፈራው በመንፈሱ ሲሆን ፍሬውም ፍቅር ነው። ምን ያህል ታውቃለህ?: ሳይሆን ምን ያህል ማፍቀር ትችላለህ? የሚለው ክርስትናህን ሁሉ ይጠይቃል። ፍቅር ከእውነት ጋር ዘላቂ፣ እውነትም ከፍቅር ጋር ጣዕም አላትእውነትና ፍቅር ሚዛን ላይ ቢወጡ ፍቅር ታሸንፋለች። እውነትህ ብቻ ደርቆ እንዳይሰበር፣ ፍቅርህ ብቻ ረጥቦ እንዳይዝለፈለፍ ፍቅር ያለው እውነት ይሁንልን! ✔️የምናምነው ስለ ፍቅር ከሰማይ በወረደውስለ ፍቅር በአደባባይ ሳያፍር በተሰቀለውስለ ፍቅር የሁላችንን በደል በተሸከመው ነው። አንድ ሰው ንግግሩ ሲማርከን እንደ እርሱ እንናገራለን፣ አረማመዱ ሲማርከንም እንደ እርሱ እንራመዳለን። ልክ እንዲሁ ክርስቶስ ሲማርከንም እንደ እርሱ የፍቅር ሠራዊት እንሆናለን።  እኛስ ግን አሁን ከሰማይ ወረደ እያልን ትንሽ ርቀት ስለ ፍቅር መጓዝ አቅቶን ይሆን?፣  ስለ ፍቅር ተሰቀለ እያልን በወንድሞቻችን ድክመት ጥላቻን አርግዘን ይሁን?አፍረንባቸው ጥግ ድረስ አሽቀንጥረናቸው  ይሆን?የሁሉን በደል ተሸከመ እያልን የሌሎችን በደል መሸፈን አቅቶን ይሆን?👉"ፍቅር የኃጢአትን ብዛት ይሸፍናልና ከሁሉ በፊት እርስ በርሳችሁ አጥብቃችሁ ተዋደዱ(1ኛጴጥ4:8) ✔️መዋደድ ማለት መፈቃቀድ ማለት ነው። እኔ ወንድሜን በሙሉ ልብ መቀበል፣ ወንድሜም እኔን መቀበሉ ነው። ያለመስፈርት የክርስቶስን ደም ዋጋ አድርገን መዋደድ ማለት ነው። ፍቅር ማለት ሌሎች እኛን መውደዳቸው ሳይሆን እኛ ሌሎችን መውደዳችን ነው። ፍቅር ግን የጋራ ነውና ስንዋደድ ጣዕም ይኖረዋል። ✔️ሐዋርያው ለመዋደድ መጠኑን ሲገልጥ በወንድማማች መዋደድ ብሏል። በወንድማማች ፍቅር መዋደድ ምንድነው? መንፈሳዊ ዝምድና ላነሰበት ሰው ይህ ታላቅ ጥሪ ነው። እግዚአብሔርን እንደ አባት የሚቀበል አጠገቡ ያለውን አማኝ እንደ ወንድም መቀበል አይከብደውም። ወንድምነት ፈቃድ ሳይሆን ግድ ነው። ወንድማችን ወንድም የሆነው ፈቅደን ሳይሆን ከአንድ አባት በመወለዳችን ነው። ስለዚህ በፍላጎታችን ይህ ወንድምነት አይሰረዝም። ከዚህ ቀን ጀምሮ ወንድሜ አይደለም ብንል ስሜት እንጂ እውነት አይደለምስሜት እውነትን አያሸንፍምዛሬ ወንድማማች እንደሆንን ባይሰማን እንኳ ወንድማማች መሆናችን የማይሻር ሐቅ ነው። ✔️ጌታ የኢየሱስ ከሕማማቱ በፊት ትልቅ ጥሪ ያደረገው "እርስ በእርሳችሁ እኔ እንደወደዳኳችሁ ተወደዱ" የሚል ነው። ሐዋሪያው ዮሐንስ ይኼ ጉዳይ በጣም ገብቶት ነበርና ፍቅርን መሠረት ያደረገ የወንድማማችነት ዋጋ የት ድረስ እንደሆነ በመልዕክቱ አብራራልን። " እርሱ ስለ እኛ ነፍሱን አሳልፎ ሰጥቶአልና በዚህ ፍቅርን አውቀናልእኛም ስለ ወንድሞቻችን ነፍሳችንን አሳልፈን እንድንሰጥ ይገባናል።" (1ኛ የዮሐንስ መልእክት 3:16) ✔️ አሁን ስለ እኔ ይኼን ማድረግ ትችላለህ? ስለ አገልግሎቴ ይኼንን ማሰብ ትችላለህ? እኔ ስለ አንተ ይኼን አስባለሁ?  ኦ እግዚአብሔር ሆይ ከጭንቅላት እውቀት እያዳንከን ከልባችን ክርስትናችንን ራስህ በእኛ ትኖርበት ዘንድ አሁንም አንተን እናያለን 😥 ፣ **መንፈሳዊ ዝምድና ገና አልገባንናም እባክህን ክርስትናን በዋጋው መጠን እንድኖረው እርዳን😥🙏 እርስ በርሳችን እንዋደድ! #ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ💒 ወደ ቻናላችን ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለት ጊዜ ብቻ ይንኩ👉@biruk351 ሼር ስለሚያደርጉ እናመሰግናለን

"በወንድማማች መዋደድ እርስ በርሳችሁ ተዋደዱ" /ሮሜ. 12፡10/❤ ✔️ጽድቅ መብቀል ነው፣ ፍቅር ደግሞ ፍሬ ነው። የምንበቅለው በደሙ፣ የምናፈራው በመንፈሱ ሲሆን ፍሬውም ፍቅር ነው። ምን ያህል ታውቃለህ?: ሳይሆን ምን ያህል ማፍቀር ትችላለህ? የሚለው ክርስትናህን ሁሉ ይጠይቃል። ፍቅር ከእውነት ጋር ዘላቂ፣ እውነትም ከፍቅር ጋር ጣዕም አላትእውነትና ፍቅር ሚዛን ላይ ቢወጡ ፍቅር ታሸንፋለች። እውነትህ ብቻ ደርቆ እንዳይሰበር፣ ፍቅርህ ብቻ ረጥቦ እንዳይዝለፈለፍ ፍቅር ያለው እውነት ይሁንልን! ✔️የምናምነው ስለ ፍቅር ከሰማይ በወረደውስለ ፍቅር በአደባባይ ሳያፍር በተሰቀለውስለ ፍቅር የሁላችንን በደል በተሸከመው ነው። አንድ ሰው ንግግሩ ሲማርከን እንደ እርሱ እንናገራለን፣ አረማመዱ ሲማርከንም እንደ እርሱ እንራመዳለን። ልክ እንዲሁ ክርስቶስ ሲማርከንም እንደ እርሱ የፍቅር ሠራዊት እንሆናለንእኛስ ግን አሁን ከሰማይ ወረደ እያልን ትንሽ ርቀት ስለ ፍቅር መጓዝ አቅቶን ይሆን?ስለ ፍቅር ተሰቀለ እያልን በወንድሞቻችን ድክመት ጥላቻን አርግዘን ይሁን?አፍረንባቸው ጥግ ድረስ አሽቀንጥረናቸው ይሆን?የሁሉን በደል ተሸከመ እያልን የሌሎችን በደል መሸፈን አቅቶን ይሆን?👉"ፍቅር የኃጢአትን ብዛት ይሸፍናልና ከሁሉ በፊት እርስ በርሳችሁ አጥብቃችሁ ተዋደዱ(1ኛጴጥ4:8) ✔️መዋደድ ማለት መፈቃቀድ ማለት ነው። እኔ ወንድሜን በሙሉ ልብ መቀበል፣ ወንድሜም እኔን መቀበሉ ነው። ያለመስፈርት የክርስቶስን ደም ዋጋ አድርገን መዋደድ ማለት ነው። ፍቅር ማለት ሌሎች እኛን መውደዳቸው ሳይሆን እኛ ሌሎችን መውደዳችን ነው። ፍቅር ግን የጋራ ነውና ስንዋደድ ጣዕም ይኖረዋል። ✔️ሐዋርያው ለመዋደድ መጠኑን ሲገልጥ በወንድማማች መዋደድ ብሏል። በወንድማማች ፍቅር መዋደድ ምንድነው? መንፈሳዊ ዝምድና ላነሰበት ሰው ይህ ታላቅ ጥሪ ነው። እግዚአብሔርን እንደ አባት የሚቀበል አጠገቡ ያለውን አማኝ እንደ ወንድም መቀበል አይከብደውም። ወንድምነት ፈቃድ ሳይሆን ግድ ነው። ወንድማችን ወንድም የሆነው ፈቅደን ሳይሆን ከአንድ አባት በመወለዳችን ነው። ስለዚህ በፍላጎታችን ይህ ወንድምነት አይሰረዝም። ከዚህ ቀን ጀምሮ ወንድሜ አይደለም ብንል ስሜት እንጂ እውነት አይደለምስሜት እውነትን አያሸንፍምዛሬ ወንድማማች እንደሆንን ባይሰማን እንኳ ወንድማማች መሆናችን የማይሻር ሐቅ ነው። ✔️ጌታ የኢየሱስ ከሕማማቱ በፊት ትልቅ ጥሪ ያደረገው "እርስ በእርሳችሁ እኔ እንደወደዳኳችሁ ተወደዱ" የሚል ነው። ሐዋሪያው ዮሐንስ ይኼ ጉዳይ በጣም ገብቶት ነበርና ፍቅርን መሠረት ያደረገ የወንድማማችነት ዋጋ የት ድረስ እንደሆነ በመልዕክቱ አብራራልን። " እርሱ ስለ እኛ ነፍሱን አሳልፎ ሰጥቶአልና በዚህ ፍቅርን አውቀናልእኛም ስለ ወንድሞቻችን ነፍሳችንን አሳልፈን እንድንሰጥ ይገባናል።" (1ኛ የዮሐንስ መልእክት 3:16) ✔️ አሁን ስለ እኔ ይኼን ማድረግ ትችላለህ? ስለ አገልግሎቴ ይኼንን ማሰብ ትችላለህ? እኔ ስለ አንተ ይኼን አስባለሁ? ኦ እግዚአብሔር ሆይ ከጭንቅላት እውቀት እያዳንከን ከልባችን ክርስትናችንን ራስህ በእኛ ትኖርበት ዘንድ አሁንም አንተን እናያለን 😥 ፣ **መንፈሳዊ ዝምድና ገና አልገባንናም እባክህን ክርስትናን በዋጋው መጠን እንድኖረው እርዳን😥🙏 እርስ በርሳችን እንዋደድ! #ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ💒 ወደ ቻናላችን ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለት ጊዜ ብቻ ይንኩ👉@biruk351 ሼር ስለሚያደርጉ እናመሰግናለን

"#በዚህ_ዘመን_መጨረሻ_በልጁ_ተናገረን" ተናጋሪውም እግዚአብሔር ነው የተናገረበትም ድምፅ ልጁ ነው:: ከዚህ ቀደም በብዙ መንገድና ጎዳና ለአባቶች ሲናገር ነበር.. ሁሉም የእርሱን ድሜፅ በሙላት ወይም የድምፁን ግብ መምታት አልቻሉም ነበር። በዘመን ፍፃሜ ላይ ግን ከሕግ በታች በመሆን ከሴት በተለወለደው ልጁ አለምን ሙሉ አናግሯል። "በዚህ ዘመን መጨረሻ በልጁ ተናገረን" ተናጋሪውም እግዚአብሔር ነው የተናገረበትም ድምፅ ልጁ ነው:: እኛ ይህንን የእግዚአብሔርን ድምፅ እንደ ገደል ማሚቶ እናስተጋባዋለን እንጂ አንቀይረውምም አናሻሽለውምም: ከቀየርነው ወይም ካሻሻልነው ያኔ የእግዚአብሔር ድምፅ ሳይሆን የኛ ድምፅ ሆኖአል ማለት ነው: የኛ ድምፅ ከሆነ ደግሞ ማንንም ከእንቅልፉ አይቀሰቅስም አያድንምም ማለት ነው:: እዚህ ድምፅ ውስጥ ድምፃችንን አመሳስለን መጨመር እንኳን አንችልም: በግሪኩና በዕብራይስጡ ብለን እንኳን ልናቀጥነው ወይም ልናወፍረው መብት የለንም: እንደሰማነውና እንደወረደ በመንፈስ ቅዱስ አጋዥነት ብቻ የምናስተጋባው ድምፅ ነው:: Discord የሆነ ድምፅ አይፈቀድም: በራሱ በተናጋሪውና በድምፁ ባለቤት ቅኝት ብቻ የሚነገር ድምፅ ነው:: ይህን ድምፅ ቤተክርስቲያን በመጨመር ወይም በመቀነስ ልታሻሽለው አትችልም: መረረም ጣፈጠም የድምፁ የገደል ማሚቶ መሆን ብቻ ነው የሚጠበቅባት:: የድምፁ መንጠሪያ እንጂ የድምፁ ፈጣሪ አይደለችም: የድምፁ ባለአደራ እንጂ የድምፁ ባለቤት አይደለችም: የድምፁ አድራሽ እንጂ የድምፁ አዛዥ አይደለችም:: ግን ግን እውነት አሁን የምናያት የዘመናችን ቤተክርስቲያን ለእግዚአብሔር ድምፅ megaphone ናት ወይስ የሌሎች ድምፆች ማስተጋቢያ? እግዚአብሔር በልጁ መስዋዕትነት አለምን በራሱ ወጪ አናግሯል : ታላቅ ድግስ ያለበት እራት አዘጋጅቷል :.. ኑ ትላለች ቤተክርስቲያን ፣ በሰማይና በምድር ያለውን ሁሉ ሊጠቀልልበት ያሰበውን ክርስቶስን (#ድምፁን) እንዳናሳንሰው እግዚአብሔር ይርዳን🙏 #ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ 💒 ወደዚህ ቻናል ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለት ጊዜ ብቻ ይንኩ 👉@biruk351

💒💒💒💒💒💒💒💒💒💒💒 ክርስትና እጅግ ከምናስበውና ከምንገምተው በላይ የሚገዝፍብን እግዚአብሔር ምን ያህል ክርስቶስን ያለ ልክ ከፍ ከፍ እንዳደረገው ስንረዳ ነው፡ እግዚአብሔር እንደ ክርስቶስ ያከበረው ወይም ከፍ ከፍ ያደረገው የለም፡ ለዚህም ነው ሐዋርያው ጳውሎስ “ያለልክ ከፍ ከፍ አደረገው” በማለት የሚነግረን፡ ክርስቶስ ከፍ ብቻ ሳይሆን የተደረገው ያለ ልክ ከፍ ከፍ ነው የተደረገው፡ እንደ እርሱ ከፍ ከፍ የተደረገ ሌላ የለም፡ እርሱ ብቻ ነው፡ ምክንያቱም ከዚህ ከፍታ የተነሳ ጉልበት ሁሉ ይንበረከክለታል ምላስ ሁሉ ደግሞ ለእግዚአብሔር አብ ክብር ጌትነቱን ይመሰክርለታል። የክርስቶስ ከፍታ የቤተክርስቲያን ራስ ብቻ በመሆን ሳይሆን የአጥናፈ አለሙም መጠቅለያ በመሆኑ ነው፡ ለዚህም ነው ጳውሎስ እግዚአብሔር በሰማይና በምድር ያለውን ሁሉ በእርሱ ሊጠቀልል እንደወደደ የሚነግረን። በዚሁ ልክና ጥልቀት ደግሞ መጽሐፍ ቅዱሳችን የእኛን ከክርስቶስ ጋር አብሮ መክበር ወይም ለክብር መጠራት አበክሮ ያስተምራልየክርስቶስ ከፍታ የክርስቶስ ብቻ ሳይሆን የኛም ከፍታ ነውየክርስቶስ ክብር የእርሱ ክብር ብቻ ሳይሆን የኛም ክብር ነው፡ ስለዚህም ነው በግልጽ “*የሰጠኽኝን ክብር ሰጥቻቸዋለሁ” ያለው፡ ክብሩ ምንም ይሁን የእግዚአብሔር ነው፡ እግዚአብሔር ለክርስቶስ ሰጠው፡ ክርስቶስ ደግሞ ያለስስት ለእኛ ሰጠን፡ መቼም ይሁን መቼም በኩራችንን ክርስቶስን አንሆንም ነገር ግን በኩራችን ክርስቶስ የገባበት ክብር ውስጥ እንገባለን፡ ክርስቶስ የትም ቢሄድ ስለ እኛ ቀዳሚ ሆኖ ነው የሚሄደው እንጂ እኛን ጥሎን አይደለም የሚሄደው፡ “ብዙ ልጆችን ወደ ክብር ሲያመጣ” እንደ ተባለለት ወደ እዚህ በእርሱ በኩል ወደተጠራንለትና በሰው ልብ ወዳልታሰበ ክብር ለመግባት ነው። ክርስትና ምንም እንኳን በዶክትሪን የታጨቀ ቢሆንም ሃይማኖት ግን አይደለም፡ የዘላለም ሕይወትና የዘላለም ክብር ነው። ክርስቶስን ልንከተለው ብቻ ሳይሆን የተጠራነው ክርስቶስ የገባበት ክብር ውስጥም እንድንገባ ነው። “ለአለቅነትና ለሥልጣንም ሁሉ ራስ በሆነ በእርሱ ሆናችሁ ተሞልታችኋል” ሐዋርያው ጳውሎስ፣ የክርስቶስ ብቻ ነው እንዴ የሚገርማችሁ፣ እናንተም እኮ በእርሱ ሆናችሁ ተሞልታችኋል የሚል ነው የሚመስለው፡ የሐዋርያው ጳውሎስ ነገረ-መለኮታዊ እሳቤ ሁሉ የተነጠለጠለችበት “በእርሱ/ In Him” የምትለዋ ቃል እጅግ መሰረታዊ ናት፡ #በእርሱ አማካኝነት በእግዚአብሔር ፊት ያልሆነውና ያልተሰጠን ምን አለ? ምንስ ቀረን ጎደለን ልንለው እንችላለን? አላየንም ፣ አልተገለጠልንም፣ አልገባንም እንጂ የክብሩ ሙላት መጥለቅለቅ ውስጥ ነን! እግዚአብሔር ከዚህ ስሜታዊ አእምሮ ነፃ ያውጠንና በመረዳት ባለጠግነት ነፍሳችንን በዚህ እውነት ይሙላው 🙏 ክርስትና በዋነኛነት በክርስቶስ በኩል የዚህ ክብር ወይም ሙላት ተቋዳሽ መሆን እንጂ ሃይማኖተኛ መሆን አይደለም፡፡ አመነውም አላመነውም ተቀበልነውም አልተቀበልነውም ኑፋቄ ነው አልነውም አላልነውም በክርስቶስ በኩል የእግዚአብሔር ሙላት ጥሪያችን ብቻ ሳይሆን ግባችንም ነው፡ ለዚህ ነው ክርስትና የአንድ አጥቢያ ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የአጥናፈ አለሙ እንዲሁም የዚህኛውና የሚመጣው ዘመን ጉዳይ የሚሆነው። እግዚአብሔርን መቼም አንሆንም: የእግዚአብሔር ሙላት ሊገለጥብን ግን ተጠርተናል፡ በክርስቶስ በመሆን ክርስቶስ የክብሩ መንጸባረቅ የሆነለትን የማይታየውን አምላክ ክብር እኛም በማይከደን ፊት እናንጸባርቅ ዘንድ ተጠርተናል፡ ለዚህም ነው ሐዋርያው ጳውሎስ ያንን መልክ እንመስል ዘንድ ከክብር ወደክብር እንለወጣለን ብሎ በአጽኖትና በጉጉት የሚናገረው። ወንድሜ የተጠራኸው ሃይማኖተኛ እንድትሆን አይደለም፡ ከሲዖል እንድታመልጥ ብቻ አይደለም፡ ወይም ከሞት በኋላ በተለምዶ እንደምናስበው መንግስተ ሰማይ የሚባል “አገር” ለመግባት ብቻ አይደለም፡ በመጋረጃ በማይከደን ፊት የጌታን ክብር እንደ መስታወት እያብለጨለጭህ መንፈስ ከሚሆን ጌታ እንደሚደረግ ያን መልክ ትመስል ዘንድ ከክብር ወደ ክብር ለመለወጥ ተጠርተሃል፡ ይሄ ነፍሳችንን ሲገዛት ብቻ ነው ስንኖርም ስንሞትም የክርስቶስ መሆናችን የሚገባን። ልጁ በኩር ወደሆነበትና የእግዚአብሔር ክብር ወይም ምሳሌ ወደሚገለጥበት እውነት ተጠርተሃል፡ ክርስቶስ የማይታየው አምላክ ምሳሌ እንደሆነው አንተ ደግሞ በክርስቶስ ሆነህ በክርስቶስ የተገለጠውን ክብርና ምሳሌ ልታብለጨልጭ ተጠርተሃል። ከሃይማኖተኝነት ተፋታ፡ በድካምህና በውስንነትህ የከበረውን እውነት አትጠራጠር፣ እየመረረህም ቢሆን እግዚአብሔር ለእንደ እኔ አይነቱ ሰው እንዲህ ያለ ክብር ለምን ወሰነ? እያልህክ እውነቱን ግን ዋጠው! #ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ ወደ ቴሌግራም ቻናላችን ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለቴ ብቻ ይንኩ 👉 @biruk351 #እናመሰግናለን_ሼር_ያድርጉ ❤🙏

#ዕብራውያን 👉👉ኢየሱስ ክርስቶስ ከሁሉም የተሻለ ነው👈👈 👉በመጀመሪያ ዕብራውያን መጽሐፍ የተጻፈው ለአይሁዳውያን ክርስቲያን ነው። ማለት ከአይሁዳውያን ወደ ክርስትና ለመጡት ነው። 👉ይሄ መልዕክት ሲጻፍ ለአይሁዳውያን ክርስትያኖች: ኢየሱስ ምራፍ 1 ላይ ከአባቶች ከነብያቶች ከመልእክቶች እንደሚበልጥምዕ 2 ይሄ ከአባቶች ከነብያቶች ና ከመልአክቶች የሚበልጥ ኢየሱስ ክርስቶስ በእሱ ብቻ መዳን እንደሚገኝምዕ 3 ከሙሴ እንደሚበልጥምዕ 4 እውነተኛ ሰንበት ቀን ሳይሆን ራሱ ኢየሱስ እንደሆነም5 ከአሮን የተሻለና የላቀ መሆኑንምዕ 6 የተሻለ መልከጼዴቅምዕ 7 የተሻለና የላቀ ዋስ(ከሌዊ ወገን የተሻለ) መሆኑን፣ ምዕ 8 የተሸላና የላቀ ተስፋ ቃል ኢየሱስ መሆኑንምዕ 9 የተሻለና የላቀ ደም ለሀጢአተኛ የኢየሱስ ደም መሆኑን፣ *ምዕ 10 የተሻለና የላቀ መስዋዕት ኢየሱስ መሆኑንምዕ 11 በኢየሱስ ማመን የተሻለና የላቀ መሆኑን( እመኑ) እምነት ለክርስቲያኖች መሠረት መሆኑን ለማሳየት። 👉 ዕብራውያን ጻፍ ትልቁ ቁምነገር ኢየሱስ ከሁሉም የተሻለና የላቀ መሆኑን ለማስረዳት ነው። ለምን❓ ከአይሁዱ የመጡ ክርስቲያኖች በመሆናቸው አንዳንድ ግዜ ኢየሱስ ክርስቶስ መስዋዕትነት ይተውና ወደ አሮጌው ካዳን መስዋዕትነት ይመለሳሉ። ከኢየሱስ ደም ይልቅ የእንስሳት ደም ወደ ማመን ይመለሱ ነበር። ከኢየሱስ ይልቅ ሙሴን ወደ ማመን። ከኢየሱስ ይልቅ አባቶችን ወደ ማመን ይመለሳሉ። ኃጢአት ከሠሩ በኢየሱስ ክርስቶስ መታመን ሲገባቸው በአሮጌው ኪዳን መስዋዕት መታመን ይመለሱ ነበር። 👉ስለዚህ ይሄ ቃል የተጻፈው ጠንቅቀው ሕጋቸውንና ሥራአታቸወን እንዲሁም መስዋአታቸውን ( የግደሮች ደም ደም፣የኮርማዎች ደም) ምን እንደሆነ ለሚያውቁ አይሁዳውያን ነው። እንጂ ከአሕዛብ ወደ ክርስትና ለመጡት ቅዱሳን አይደለም። ይሄ ማለት እኛን አይመለከትም ስለ ማለት አይደለም። ግን ዋናው አይሁዳውያን ክርስቲያኖች ኢየሱስ ክርስቶስ ከሁሉም እነሱ ከሚታመኑበት ነገር የተሻለና የላቀ መሆኑን ለማሳየት ነው። ሁሉንም ኢየሱስ እንደጨረሰ ለማስረዳትና ኢየሱስ ክርስቶስ ሠርቶ በጨረሰው ሥራ አርፎ እንድኖሩ ነው። 👉ዕብ12:1-2 ካየነው :- ዕይታቸውንና አመለካከታቸውን በኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ እንዲያደርጉ አርጎ ይገስፃቸዋል። አይሁዳውያን ክርስቲያኖች ትልቁ ችግራቸው የሆነ ነገር ከደረሰባቸው ወዲያውኑ ወደ አሮጌው ኪዳን ይመለሳሉ። ስለዚህ ምንም ይምጣ፣ምንም ይሁን ዕይታችሁንና አመለካከታችሁን በኢየሱስ ብቻ አድርጉ። በሚደርስባችሁ መከራ ብዛት የተነሳ አይናችሁን ከኢየሱስ አታንሱ: እሱ ከበቂ በላይ ነው፣ የፈለገ ድካም ውስጥ ብትሆኑ ወደ ፀጋው ዙፋን ሽሹ እንጂ ወደ ኩነኔና ወደ ኃጢአት አትሽሹ ፣ እርሱ መሃራኒ የታመነ ሊቀ-ካህናታችሁ ነው ፣ ለሁሉም ነገራችሁ መፍትሄው ያለው ኢየሱስ ጋር ብቻ ነው እያላቸው ነው ። ስለዚህ በኢየሱስ ብቻ መኖራችሁንና መታመናችሁን ቀጥሉ። ከኢየሱስ አይናችሁን አታንሱ። በምንም ሁኔታ እርሱን ተመልከቱ አላቸው። ስለዚህ ክርስትና ትልቁ ሁኔታ ውስጥ ኢየሱስን መመልከትና መመልከት ብቻ ነው። ዛሬም ኢየሱስን ተመልከቱ..  ራሳችሁን ብርታታችሁን ፣ ድካማችሁን ፣ በቂ መሆናችሁንና አለመሆናችሁን አትመልከቱ.  ስሜታዊም ሆነ አካላዊ ፈውስ ያለው ኢየሱስን በመመልከት ነው!    #ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ ወደ ቻናላችን ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለት ጊዜ ብቻ ይንኩ👉@biruk351

ጊታር የመግዛት እንቅስቃሴያችን ከጀመረ ጀምሮ ዘራችሁን እየሰጣችሁ ስላላችሁ ቅዱሳን እግዚአብሔርን አመሠግናለው: አሁንም እንደ ቀጠለ ነው : መጠኑንም አትገድበው የበለጠ በሺህ ቤትም የመስጠት ፍላጎት
ጊታር የመግዛት እንቅስቃሴያችን ከጀመረ ጀምሮ ዘራችሁን እየሰጣችሁ ስላላችሁ ቅዱሳን እግዚአብሔርን አመሠግናለው: አሁንም እንደ ቀጠለ ነው : መጠኑንም አትገድበው የበለጠ በሺህ ቤትም የመስጠት ፍላጎት ያላቸው ይሳተፉ የሚል ምክር ተሰቶኝ በተግባርም ማየት በመቻሌ ደስ ብሎኛል...ቢሆንም አሁንም ከ200 ጀምሮ : 100 ብርም ቢሆን የራሱ አስተዋፆኦ አለውና በንቃት ተሳተፉ ስል የከበረ ጥሪዬን አቀርባለው... እኔም ይኼው በሞባዬል ባንኪንግ ጀምሮ Transfer.. ይጀመር ስል በድጋሚ አስቀምጬአለው። ቤተክርስቲያኒቱ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንት ለመውሰድ ያደረገች ያላቹ ጥረት በአንዳንድ ነገሮች ምክንያት የተስተጓጎለ ሲሆን : በስር ያለው የተጠቀሰው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ : የቤተክርስቲያኒቱ ገንዘብ ያዥ አካውንት ነው። 1000 50503 9355 ንግድ ባንክ 👉 አፈወርቅ አባተ “በተነ ለድኾችም ሰጠ ጽድቁ ለዘላለም ይኖራልተብሎ እንደ ተጻፈው ነውለዘሪ ዘርን ለመብላት እንጀራን የሚሰጥ እርሱ የምትዘሩትን አትረፍርፎ ይሰጣችኋልየጽድቃችሁንም ፍሬ ያበዛላችኋልሁል ጊዜ በልግስና መስጠት እንድትችሉ በሁሉ ነገር ያበለጽጋችኋልልግስናችሁም በእኛ በኩል የሚደርሳቸው ሰዎች እግዚአብሔርን ለማመስገን ምክንያት ይሆናቸዋል" (2ቆሮንቶስ 9:9-11) ፀጋና ሰላም ይብዛላችሁ #ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ እናመሰግናለን ለንቁ ፍቅራችሁ❤🙏

""ከሥጋ የተነሣ ስለ ደከመ.. “ከሥጋ የተነሣ ስለ ደከመ ለሕግ ያልተቻለውን፥ እግዚአብሔር የገዛ ልጁን በኃጢአተኛ ሥጋ ምሳሌ በኃጢአትም ምክንያት ልኮ አድርጎአልና፤ እንደ መንፈስ ፈቃድ እንጂ እንደ
""ከሥጋ የተነሣ ስለ ደከመ.. “ከሥጋ የተነሣ ስለ ደከመ ለሕግ ያልተቻለውንእግዚአብሔር የገዛ ልጁን በኃጢአተኛ ሥጋ ምሳሌ በኃጢአትም ምክንያት ልኮ አድርጎአልና፤ እንደ መንፈስ ፈቃድ እንጂ እንደ ሥጋ ፈቃድ በማንመላለስ በእኛ የሕግ ትእዛዝ ይፈጸም ዘንድ ኃጢአትን በሥጋ ኰነነ።”(ሮሜ 8፥3-4) 🌱ሐዋርያው ጳውሎስ ሕግ ለራሱ መድከሙን ይነግረናል። ምክንያቱም ከሥጋችን የተነሣ። ሕግ ራሱ እንዴትስ ደከመ? ሕግ "አታድርጉ " የሚለውን በተደጋጋሚ በማድረጋችን ሕጉ በተደጋጋሚ እየቀጣን ለራሱ መድከሙን ይነግረናል: ልክ አባት ልጅን ገስጾ አስተምህሮ አታድርግ የሚለውን ልጅ በተደጋጋሚ በማድረጉ ፣አባት በተደጋጋሚ እየቀጣ"ኡፍፍ ይኽንን ልጅ እንዴ ምን ላድርግ'ብሎ እንደ ሚደክም የሚገልጽ ነው። መጽሐፍ “ሕጉ መቅሠፍትን ያደርጋልና፤”(ሮሜ 4፥15)እንደሚል ሕጉ በተደጋጋሚ እየቀሠፈ: ሕዝቡንም እየገደለ: ለራሱ እንደ ደከመ እንረዳለን ። ማለትም የመቅሰፍቱ ውጤት ሞት ነበርና። ሕጉ ሕይወትን ማድረግ ባለመቻሉ መድከሙን ብቻ ሳይሆን:የእኛን አይለወጥበትንም እናያለን ። "ሕግ በሙሴ ተሰቶ ነበርና ፀጋና እውነት ግን በክርስቶስ ኢየሱስ ሆነ"(ዮሐ1:17) ይኼንን በማመናችን አዲስ ፍጥረት ሆንን: ከዚህ በኋላ በቀረልን ዘመን: በድንጋይ ላይ ባለ ሕግ ሳይሆን በመንፈስ ባለ ሕግ የእርሱ ሕይወት በእኛ ይገለጥ ዘንድ ሆነ: ከዚህ በኋላ በሕግ ለመምራት ለመፅደቅ መሞከር በስጋ ማሰብ ነው። “ስለ ሥጋ ማሰብ በእግዚአብሔር ዘንድ ጥል ነውና፤ለእግዚአብሔር ሕግ አይገዛምና፥#መገዛትም_ተስኖታል”(ሮሜ 8፥7)፣እንደሚል ስለ መንፈስ ብቻና ብቻ እንድናስብ፡ እንድናሰላስል እግዚአብሔር በቸርነቱ ይርዳን። #ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ #ወደ_ቴሌ_ግራም_ቻናላችን_ለመቀላቀል_ #ይኼንን_ሊንክ_ሁለቴ_ይንኩ👉@biruk351

...ሁላችንም የእግዚአብሔር ምሕረት የሚገባን ግዞተኞች ነን... እግዚአብሔር በክርስቶስ አስቀድሞ ይቅርታን ሰጠን.. ያ ይቅርታ ከአብ ጋር ዘለአለማዊ ዋስትና ሰጠን.. ምሕረቱ ግን በየዕለቱ ሕይወታች
...ሁላችንም የእግዚአብሔር ምሕረት የሚገባን ግዞተኞች ነን... እግዚአብሔር በክርስቶስ አስቀድሞ ይቅርታን ሰጠን.. ያ ይቅርታ ከአብ ጋር ዘለአለማዊ ዋስትና ሰጠን.. ምሕረቱ ግን በየዕለቱ ሕይወታችን የሚለቀቅ ምግባችን ነው ብል ማጋነናን አይሆንብኝም። ለእኔ አይነቱ ግራ የተጋባ ሰው ምሕረት በየዕለቱ እሻለሁ ፣ ለእኔ አይነቱ በቀላሉ የሚታለል ሰው ምሕረትን እሻለሁ፣ ለእኔ አይነቱ ቶሎ የሚሳሳት ሰው ምሕረትን እሻለሁ. ለእኔ አይነቱ በስጋ ቶሎ የሚሸነፍ ሰው ምሕረትን እሻለሁ.. አቤቱ የአንተ ምሕረት ስቦ ካላወጣኝ ረግረጉ ይይዘኛል ፣ ስጋዬ ያታለኛል.. አንተ ምሕረትን ካላገነንክልኝ ወዳስቀመጥክልኝ ከፍታ እንዴት እወጣለሁ? አቤቱ በልጅ በኢየሱስ በየማለዳው የሚደርሰኝን የምሕረት ስጦታ ተቀብዬ መርካትና በአንተ መታመን ይሁንልኝ.. ምሕረትህ በትላንትናው ቦታዬ እንዳልገኝ አቅሜ ነውና ስለሚበዛልኝ ምሕረት አመሠግናለሁ 🙏 እግዚአብሔር ከብሩኬ ነበር: ምሕረትንም አበዛለት ፣ በዚህ አለም ሰዎችና ቅዱሳን ፊት ሞገስን ሰጠው አሚን 🙏 #ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ #ወደ_ቴሌ_ግራም_ቻናላችን_ለመቀላቀል_ #ይኼንን_ሊንክ_ሁለቴ_ይንኩ👉@biruk351

💟የሚምር ሊቀ ካህናት💟 🖊በዘመነ ብሉይ የነበሩት ካህናት ሕዝቡን በእግዚአብሔር ፊት ማቅረብ እንጂ መማርም ሆነ ማስማር አይችሉም፣ ለራሳቸውም ቢሆን ከሕዝብ ተርታ ተሰልፈው ምህረትን የሚጠብቁ ነበ
💟የሚምር ሊቀ ካህናት💟 🖊በዘመነ ብሉይ የነበሩት ካህናት ሕዝቡን በእግዚአብሔር ፊት ማቅረብ እንጂ  መማርም ሆነ ማስማር አይችሉም፣ ለራሳቸውም ቢሆን ከሕዝብ ተርታ ተሰልፈው ምህረትን የሚጠብቁ ነበሩ።ክርስቶስ ግን የሚምር ሊቀ ካህናት ነው። በሥጋ እንደ እኛው ሰው ሆኖ  ከኃጢያት በቀር በነገር ሁሉ የተፈተነ ስለሆነ ለድካማችን በመራራት ይምረናል።  "፤የአብርሃምን ዘር ይዞአል እንጂ የያዘው የመላእክትን አይደለም። ስለዚህ የሕዝብን ኃጢአት ለማስተስረይ፥ ለእግዚአብሔር በሆነው ነገር ሁሉ #የሚምርና የታመነ ሊቀ ካህናት እንዲሆን፥ በነገር ሁሉ ወንድሞቹን ሊመስል ተገባው። "(ዕብ.2፥16-17) 📝የአይሁድ ካህናት ጠባይ መፍረድ እንጂ መማር አይደለም። እነርሱ እንደ ሕጋቸው አንድ ሰው በኃጢያት ተይዞ በፊታቸው ቢቀርብ ሕግና አንቀጽ ጠቅሰው ለፍርድ መስጠት እንጂ ማስማር እያውቁም ነበር። 📖 በጌታ ዘመን በምንዝር የተያዘችውን ሴት ወደ ጌታ አቅርበው የጠየቁት የሙሴን ሕግ ጠቅሰው ነው።በርግጥ የሙሴ ሕግ ሴቲቱ በድንጋይ ተወግራ ትገደል ይል ነበር። የፍቅር በሆነው የኢየሱስ ሕግ (ሕገ ወንጌል) ግን ለሴቲቱ  "አንቺ ሴት ኃጢያትሽ ተሰርዮልሻል በሰላም ሂጂ" (ዮሐ.8 ፥1-11)ወንድሞቼ/እህቶቼ በኃጢያተኝነት ሰዎች ፈርደውባችሁ ሊሆን ይችላል ፤ ከዚህም የተነሳ የሰው ፊት ላለማየት ተሳቃችሁ ዘመን የፈጀባችሁ ብትሆኑ እንኳ አሁን ግን ወደሚምረው ሊቀ ካህናት ወደ ክርስቶስ ኢየሱስ ቅረቡ እርሱ በፍቅር ይምራችኋል። በዘመነ ብሉይ የነበሩት ካህናት ለማስማር ከበዳዩ ሰው ልዩ ልዩ መስዋዕቶች ይዞ ማምጣት ካልቻለ ካህናቱ ስለ እርሱ በእግዚአብሔር ፊት አይቆምለትም።ክርስቶስ ኢየሱስ ግን ያለ ምንም እንዲሁ በነጻ የወደደን በገዛ ደሙ ስለ በደላችን ወደ ሰማያዊቷ መቅደስ በመግባት ምሕረትን ያሰጠን ጌታ ነው! 👉@biruk351

ኃጢአትን የሚረዱኝ ጓደኞች አያስፈልገኝም፤ትክክለኛውን ነገር እንድሰራ ሚከራከሩኝን ወይም ሚታገሉኝን ጓደኞች ግን እፈልጋለው። (HB CHARLES JR.) " አትሳቱ፤ ክፉ ባልንጀርነት መልካሙን አመል
ኃጢአትን የሚረዱኝ ጓደኞች አያስፈልገኝም፤ትክክለኛውን ነገር እንድሰራ ሚከራከሩኝን ወይም ሚታገሉኝን ጓደኞች ግን እፈልጋለው። (HB CHARLES JR.) " አትሳቱ፤ ክፉ ባልንጀርነት መልካሙን አመል ያጠፋል።" (1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 15:33) ""ከሴሰኞች ጋር እንዳትተባበሩ በመልእክቴ ጻፍሁላችሁ።በጠቅላላው የዚህን ዓለም ሴሰኞችን፥ወይም ገንዘብን የሚመኙትን ነጣቂዎችንም፥ወይም ጣዖትን የሚያመልኩትን አላልሁም፤ ይህስ ቢሆን ከዓለም ልትወጡ ይገባችሁ ነበር። አሁን ግን ወንድሞች ከሚባሉት አንዱ ሴሰኛ ወይም ገንዘብን የሚመኝ ወይም ጣዖትን የሚያመልክ ወይም ተሳዳቢ ወይም ሰካር ወይም ነጣቂ ቢሆን ከእርሱ ጋር እንዳትተባበሩ እጽፍላችኋለሁ፤ እንደነዚህ ካለው ጋር መብል እንኳን አትብሉ።በውጭ ባሉ ሰዎች ላይ መፍረድ ምን አግዶኝ? በውስጥ ባሉ ሰዎች ላይ እናንተ አትፈርዱምን?በውጭ ባሉቱ ግን እግዚአብሔር ይፈርድባቸዋል፣ክፉውን ከመካከላችሁ አውጡት""(1ኛቆሮ5:9-13) ሁል ጊዜ በጓደኞቻችሁ ላይ በጎ ተፅዕኖ ለማሳደር የነቃችሁ ሁኑ። ይሁን እንጂ ወንድሞቻችሁ በክርስቶስ ባላችሁ ንቃት ላይ ምንም አይነት ፍላጎት ከሌላቸው ግንኙነታችሁን እየገደባችሁ ፀልዩላቸው። በግሌ በእምነት የማይራመድ ጓደኛ ጋር እንኳ የጠለቀ ሕብረት አላደርግም። እግዚአብሔርን ለትልቅ ነገር አምኜዋለው: በጥቂቱ ደግሞ በሾመኝ መንገድ በታማኝነት ለማገልገል በእርሱ ፀጋ እተጋለሁ.. ነገር ግን አንዳንድ ጓደኞቼ እግዚአብሔር በትልቅ ነገር እንዳምነው አይፈቅዱም፡ እነርሱ ማመን እያቃታቸው ስላለ ባለማመን ሊያጎሳቁሉኝ ይተጋሉ.. እናም ርቃቸዋለው! አንተ ማመን እያቃተህ ካለ የሚያምኑትን አታጎሳቅላቸው ለእምነታቸው ተዋቸው! #ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ ወደ ቻናላችን ለመቀላቀል ይኼን ሊንክ ሁለት ጊዜ ብቻ ይንኩ👉@biruk351

መፅሐፍ ቅዱስ ፦ እምነት የሚገዛበት ሕግ እንዳለው ይናገራል.. ከእምነት ሕግ አንዱ : እንደ ቃሉ የምትናገረው ነገር መገለጡ የማይቀር መሆኑ ሲሆን : እግዚአብሔርም በምላሳችን ሞትንና ሕይወትን የመናገር ነፃነት አስቀምጧል. ሕይወትን የሚፈቅድ መልካሚቱን ቀን ማየት የሚወድ ማንም ቢኖር ለእምነት ሕግ በመገዛት..እንደ እግዚአብሔር ቃል የመናገር ሕይወትን ማዳበር ይኖርበታል። የእምነት ሕግ ሰምተው ድንቅ ምስክርነት ያትርፉ 🔥🔥🔥 #ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ #ወደ_ቴሌ_ግራም_ቻናላችን_ለመቀላቀል_ #ይኼንን_ሊንክ_ሁለቴ_ይንኩ👉@biruk351 #እናመሰግናለን_ሼር_ያድርጉ ❤🙏

ፃድቅ በእምነቱ በሕይወት ይኖራል!እግዚአብሔር በእምነት ሕይወታችን በውስጥ ሰውነታችን እየበረታን እንድንሄድ ይፈልጋል: ለመበርታት ደግሞ ከእግዚአብሔር አፍ የሚወጣ ቃል ያስፈልገዋል! #የምትሰሙትን_ታምናላችሁ_ያመናችቱትን ደግሞ ትኖራላችሁ ስለዚህ ከእግዚአብሔር ስሙ.. እግዚአብሔር በፀጋ አስቀድሞ የሰጣችሁን ያንን ሕይወት ኑሩ.. ፀጋ ሰጪ ሲሆን እምነት ተቀብሎ ተጓዥ ነው..በስጦታ መጠቅለያ አንዳች ነገር ቀረበላችሁ ፈቶ ማየትና በዛ ስጦታ መደሰት የእናንተ ድርሻ ነው.... እምነታችሁን የመጠቀም ጥበብን መንፈስ ቅዱስ ያበራላችኋልድንቅ ስብከት ሰምተው አለመነካት አለመለወጥ አትችልም። #ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ #ወደ_ቴሌ_ግራም_ቻናላችን_ለመቀላቀል_ #ይኼንን_ሊንክ_ሁለቴ_ይንኩ 👉 @biruk351 #እናመሰግናለን_ሼር_ያድርጉ 🙏❤

እምነትን መጠቀም part1.mp343.30 MB

ፃድቅ በእምነቱ በሕይወት ይኖራል! እግዚአብሔር በእምነት ሕይወታችን እየበረታን እንድንሄድ ይፈልጋል : ለመበርታት ደግሞ ከእግዚአብሔር አፍ የሚወጣ ቃል ያስፈልገዋል! የምትሰሙትን ታምናላችሁ.. ስለዚህ ከእግዚአብሔር ስሙ.. ያን ጊዜ እምነታችሁን የመጠቀም ጥበብን መንፈስ ቅዱስ ያበራላችኋል። ድንቅ ስብከት ሰምተው አለመነካት አለመለወጥ አትችልም። #ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ