en
Feedback
Grace & Truth Ministry

Grace & Truth Ministry

Open in Telegram

እንኳን ወደዚህ ቻናል በሰላም መጡ ከእግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ፀጋና ሰላም ይብዛላችሁ በእውነት ቃልና በፀጋው መንፈስ ይታነፁ

Show more
1 029
Subscribers
No data24 hours
-77 days
-2030 days
Posts Archive
#ምስክሮቼ_ትሆናላችሁ_ ማናችንም ያለመንፈስ ቅዱስ ኅይል የክርስቶስ ምስክር መሆን አንችልም፡ ያለ መንፈስ ቅዱስ ቅዱሳት መጻህፍትን ላንበለብላቸው እችላለሁ፣ የሕያው ክርስቶስ ምስክር መሆን ግን አልችልም፡ ምስክርነት የምንሰጠው ስለ ሕያው ክርስቶስ ነው፣ ለዚህ ምስክርነት የሚያበቃን ደግሞ የእርሱ መንፈስ ብቻ ነው። ስለ ማንዴላ፣ ስለ ሼክስፒር፣ ስለ ማዘር ቴሬሳ፣ ወይም ስለ ጆን ኤፍ ኬኔዲ ምስክር መሆን ይቻላል፡ በተለመደው መልኩ ግን ለክርስቶስ ምስክር ሆኖ ለመቆም አይቻልም፡ ለክርስቶስ ምስክርነት የሚያበቃው መንፈሱ ብቻ ነው: No Spirit No Christ! እንደ ሐዋርያት ሥራ 1 ፡ 8 ጥቅስ መሰረት ኢየሱስ ለደቀመዛሙርቱ የተናገረው ነገር የሚገርም ነው፡ የሚያውቁትንና ወደ ሦስት አመታት አብረውት የነበሩትን ሰዎች ያለ አንድ ነገር ምሥክሮቼ መሆን አትችሉም ይላቸዋል: "ነገር ግን መንፈስ ቅዱስ በእናንተ ላይ በወረደ ጊዜ ኃይልን ትቀበላላችሁ፥ በኢየሩሳሌምም በይሁዳም ሁሉ በሰማርያም እስከ ምድር ዳርም ድረስ ምስክሮቼ ትሆናላችሁ አለ" የሦስት አመታት “የስራ ልምዳቸው / resume” የኢየሱስ ምስክር ለመሆን ብቁ አያደርጋቸውም ማለት ነው? እንደ ሐዋርያት ሥራ መሰረት መልሱ አዎ አያደርጋቸውም የሚል ነው። ማንም ሰው ያለ መንፈስ ቅዱስ ኅይል የክርስቶስ ምስክር መሆን አይችልም፡ የትኛውም ያጠራቀምሁት እውቀት፣ የተማርሁት ትምህርት፣ ያነበብኋቸው መጻህፍት፣ የትኛውም ኮሜንታሪና ዲክሽነሪ የክርስቶስ ምስክር ሊያደርገኝ አቅም የለውም፡፡ የክርስቶስ ምስክር መሆን የምችለው በተሞላሁት መንፈስ ኅይል እንጂ ባጠራቀምሁት እውቀት አይደለም ፡ ያጠራቀምሁት የመጽሐፍት እውቀት ምን ያህል እንዳነበብሁ ወይም ምን ያህል እንደማውቅ ይገልጻል እንጂ ክርስቶስን አይገልጽም፡ በዋነኛነት ክርስቶስ የሚገለጠውና የክርስቶስ ምስክር የምንሆነው እኛ በምንገለጥበት ያጠራቀምነው እውቀት ሳይሆን ክርስቶስ በእኛ በሕይወት ስርዓት በሚገለጥበት በመንፈሱ ብቻ ነው፡፡ ያለዚህ መንፈስ “ቸርች ቸርች” መጫወት ይቻላል፣ የክርስቶስ ምስክር መሆን ግን አይቻልም፡ ያለዚህ መንፈስ በግሪኩ በዕብራይስጡ፣ ታሪካዊ ዳራ፣ ስነ-አፈታት ምናምን ማለት ይቻላል፣ የክርስቶስ ምሥክር መሆን ግን አይቻልም፡ ያለዚህ መንፈስ ወንጌላዊ፣ መጋቢ፣ ነብይ ፣ ዘማሪ፣ ዐቃቢ ወዘተረፈ መባል ይቻላል የክርስቶስ ምስክር መሆን ግን አይቻልም። ሕይወቱና ኅይሉ እንጂ ስልቱና ብልጠቱ አልጠፋብንም፡፡ ኢየሱስ “ምስክሮቼ ትሆናላችሁ” አላቸው፡ መቼ? መንፈስ ቅዱስ በእናንተ ላይ በወረደ ጊዜ፡ መንፈሱ ካልመጣ እንኳን እስከ ምድር ዳር ድረስ አይደለም: ሰፈራቸው ኢየሩሳሌም እንኳን ምስክር መሆን አይችሉም፡፡ ጉዳዩ የችሎታ ወይም የእውቀት አይደለም፡ ጉዳዩ የመንፈስ አሰራር ነው፡ ስለዚህ ትልቁ ጥያቄ ምን ያህል እናውቃለን የሚለው ሳይሆን መንፈሱ ምን ያህል እየተገለጠብን ነው የሚለው ነው። የኢየሱስን ታሪክ ማስተማርና ክርስቶስን ማስተማር ይለያያሉ፡ ያኛውን ካነበበና መረጃ ከሰበሰበ ማንም ሊያደርገው ይችላል፤ ይሄኛውን ግን ማንም ሰው ያለመንፈስ ቅዱስ ኅይልና ርዳታ አይችልም። ምስክር የምንሆነው ለክርስቶስ ነው፣ ለምስክርነት የሚያበቃን ደግሞ የክርስቶስ መንፈስ ብቻ ነው፡፡ መንፈስ ቅዱስ ሆይ ስለ ክርስቶስ በይበልጥ ግለጥልኝና ምስክርነትህን በሕይወቴ ፣ በአገልግሎቴ አብዛው፣ መንፈስ ቅዱስ ሆይ ያለ አንተ አይቻለኝም ሁለንተናዬን በኃይልህ ችሎት ተቆጣጠረው በኢየሱስ ስም አሚን 🙏 #ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ ወደ ቻናላችን ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለት ጊዜ ብቻ ይንኩ👉@biruk351

ሰላማችሁ ይብዛ ጅማ የምትኖሩና በተለያዩ የበሽታ ደዌ የምትሰቃዩ ሰዎች ከዚህ በታች ባለው ሊንክ ያናግሩኝ : ቅዳሜ የፈውስና የነፃ መውጣት ፀሎት ይኖረናል : #ፀጋ_ይብዛላችሁ ይኼው ሊንኬ 👉 @lejbiruk

#ጸጋ ለሚፈላሰፈው ትርጉም የለሽ ነው!!! ፀጋ ለዳኛ ኢ-ፍትህዊ ነው!!! ፀጋ ሰርቶ መብላት ለለመደው ሞኝነት ነው! ፀጋ ራሱን ለሚወድ ብክነት ነው!!! ፀጋ ለሚያምን ስህተት ነው!!! ፀጋ ለሀይማኖተኛ ሀፍረት ነው!!! ፀጋ ግን ለተጠሙት የውሀ የምንጭ ነው!! ለታሰሩት ነጻነት ነው!!! ለሞቱት ሕይወት ነው!!! ለደከሙት እረፍት ነው!!! ለወደቁት ዳግም ዕድል ነው!!! ለጠፋው መንገድ ነው!!! በሩን ለሚያዩት መግቢያ ነው!!! #ስቲቭ_ማክቬይ_ #ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ ወደ ቻናላችን ለመቀላቀል ይኼን ሊንክ ሁለቴ ብቻ ይንኩ👉@biruk351 #ሼር_ያደርጉ❤🙏

**በቅዳሜ በነበረን ፕሮግራም እግዚአብሔር ድንቅ ጊዜ የሰጠን ሲሆን በጊዜው HIV**፣ ካንስር ፣ **ግፊት** ፣ **ነርቭ** ፣ **የእግርና የወገብ ሕመም** ፣..... **ሕመምተኞች ለነበሩ በአካ
+8
**በቅዳሜ በነበረን ፕሮግራም እግዚአብሔር ድንቅ ጊዜ የሰጠን ሲሆን በጊዜው HIV**፣ ካንስር ፣ **ግፊት** ፣ **ነርቭ** ፣ **የእግርና  የወገብ ሕመም** ፣.....  **ሕመምተኞች ለነበሩ በአካል ተገኝተው  የእምነት ፀሎት የተደረገ ሲሆን እንደ እምነታችሁ መጠን ተዓምራቶቻቸውን ተቀብለዋል**... **አሁን ቅዳሜ ድንቅ ይሆናል** 🔥🔥🔥 #ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን

ታላቅ የምስራች በጅማና አከባቢዋ ለምትኖሩ በተለያዩ ሀይማኖት ውስጥ ላላችሁም የተዘጋጀ ከሰማይ ለሰው ልጆች የተዘጋጀ የፈውስ ማዕድ 🔥🔥 ከፊታችን ቅዳሜ ይጀምራል ከዚህ ቀደም እግዚአብሔር ብዙ ከተ
+2
ታላቅ የምስራች በጅማና አከባቢዋ ለምትኖሩ በተለያዩ ሀይማኖት ውስጥ ላላችሁም የተዘጋጀ ከሰማይ ለሰው ልጆች የተዘጋጀ የፈውስ ማዕድ 🔥🔥 ከፊታችን ቅዳሜ ይጀምራል ከዚህ ቀደም እግዚአብሔር ብዙ ከተፈጥሮ ችሎት በላይ የሆኑ ነገሮችን ሲሰራ አይተነዋል አሁን ደግሞ ለብዙዎች ይደርስ ዘንድ ከእኛ የሚጠበቀውን ሁሉ አዘጋጅተናል ❤ ኢየሱስ ፈዋሽ ነው #በፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ **ሼር ያድርጉ**🙏 **ወደ ቻናላችን ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለት ጊዜ ብቻ ይንኩ**👉@biruk351

አለማመንን መጋፈጥ part4.mp357.70 MB

አለማመንን መጋፈጥ part3.mp349.36 MB

ሰላማችሁ ይብዛ የፀጋና እውነት ሚኒስትሪ የቻናል ተከታታዮች ላለፉት ጊዜያት ያለማቋረጥ ፁህፎች ኦድዮች ያለማቋረጥ ወደ እናንተ ይደርሱ እንደነበር ይታወሳልሆኖም ከዚህ በኋላ አንዳንድ ነገሮችን እስካስተካክል ላልተወሰነ ጊዜያት በዚህ ቻናል የሚለቀቁ ነገሮች አይኖሩም(ምናልባት አንድ ወንድም ቻናሉን ክፍት አርጌለት የሚለቀው ነገር እንዲመቻች ለማድረግ እሞክራለው) እስከምንገናኝ ፀጋና ሰላም በያላችሁበት ይብዛ እያልሁ ቸር እንዲያገናኘን አምናለሁ.. ለመጨረሻ ጊዛ በኦዲዮ የተዘጋጀ 2 በእምነት ዙሪያ የተዘጋጁ ስብከቶችን እለቃለሁመልካም ቆይታ 🙏

#በእምነት_መኖር!? የዛሬውን መልዕክት በተረጋጋ መንፈስ ቆም ብላችሁ ብታዩ መንፈስ ቅዱስ ትልቅ ነገር እንደ ሚያስተምራችሁ አልጠራጠርም! ሁላችንም እምነት ውስጥ ነው የምንኖረው: የስህተት እምነት አልያም ትክክለኛ እምነት ውስጥ እየኖርን ነውየሕይወት እምነት አልያም የሞት እምነት ውስጥ እየተመላለስን ነውአዳምን ወደ ሞት የመራው ሄዋን ከሰይጣን በሰማቹ ቃል ላይ በነበረው እምነት ነው። ሮሜ 10:17 "#እምነት_ከመስማት_ነው" የምንሰማቸው ነገሮች ወደድንም ጠላንም በውስጣችን እምነት መመስረቱ የማይቀር ነው:#ምክንያቱም_መርሑ_መስማት_ነውና! በተለይም ደጋግመን የምንሰማቸው ነገሮች ላይ እምነት እንመሰርታለን እንደሰማነው ነገር ፍሬው ደግሞ ወደ ሕይወት አልያም ሞት ይነዳናል(ሞት ስል ስለ አካላዊ ብቻ አታስቡ ድብርት ጭንቀት ኩነኔ ሀዘን ፍርሃት ጥርጥር እነዚህ የሞት ሌላ ገፅታዎች ናቸው) "#የስህተት_እምነት" የስህተት እምነት ማለት እግዚአብሔር ከነገረን ውጪ የሄድንበት መንገድ አልያም እግዚአብሔር ከሚያየው እይታ ውጪ ያየንበት ማለት ነውውደዱ ሲለን የጠላንበትአፍቅሩ ሲለን ላለማፍቀር ምክንያት የደረደርንበትስጡ ሲለን የሰሰትንበትአጥኑ ሲለን ፊልም ያየንበትታላላቆችን አክብሩ ሲለን የናቅንበትክፉን በክፉ  አትመልሱ ሲለን የመለስንበትጊዜያቹን በማይጠቅም ነገር አታባክኑ ሲለን ያባከንበትስሩ ሲለን የሰነፍንበት...ብዙ ብዙ። እግዚአብሔር የነገረንን ነገሮች ማድረግ ያቃተን ደግሞ እርሱን መስማት ላይ ራሳችንን ስለማናስማርክ ነው: ለእግዚአብሔር ጊዜ ስላልሰጠን እና አብዛኞቻችን ከነ ጭራሹ ለእግዚአብሔር ጊዜ ስለሌለን ነውቀኖቻችን በሙሉ በማይጠቅሙን ነገሮች የተጠመዱ ናቸውእግዚአብሔርን ለመስማት ከ እግዚአብሔር ለመማር ከ እግዚአብሔር የሰማነውን ነገር ለማሰላሰል እና በልባችን ለመያዝ ጊዜ የለንም😥 ። በሌሎች ለተሳሳተ እምነት ለሚያጋልጡን ለብዙ ነገሮች ተጠምደናልምርኮኞች መስለናልእግዚአብሔር በክርስቶስ ናችሁ ብሎ በቃሉ በሚነግረንና እኛ በትክክል ባለንበት ሁኔታ መካከል ያለው አስደንጋጭ ልዩነት አሳስቧችሁ አያውቅም?😥፣ እግዚአብሔርን ከመስማት ታቅበን በሌሎች ነገሮች ስለተጠመድን በተሳሳተ እምነት ተዘፍቀን እግዚአብሔር ያየልንን ሕይወት መኖር አልቻልንም!። እግዚአብሔር ያየልን ሕይወት እንከን አልባ ፍጹም የሆነ ሕይወት ነውከእግዚአብሔር ጋር በመጣበቅ ሕብረት ማድረግና ደጋግመን መስማት ያስፈልገናል: እግዚአብሔርን ደጋግመን ስንሰማ ነው ከስህተት እምነት ወጥተን ወደ ትክክለኛው የ እግዚአብሔር አይነት እምነት የምንገባውለእግዚአብሔር ጊዜ ስጡ ሕይወት ይሆንላችዋል በብዙ ታተርፋላቹ: እግዚአብሔር ጊዜያቹን የሚጠይቃቹ ለእናንተው ጥቅም ነው። ዘዳግም 6:6-9 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ እኔም ዛሬ አንተን የማዝዘውን ይህን ቃል በልብህ ያዝ:ለልጆችህም አስተምረውበቤትህም ስትቀመጥበመንገድም ስትሄድስትተኛም ስትነሣም ተጫወተውበእጅህም ምልክት አድርገህ እሰረውበዓይኖችህም መካከል እንደክታብ ይሁንልህበቤትህም መቃኖች በደጃፍህም በሮች ላይ ጻፈውይህቺኛዋ አለም የተረዳችው ነገር አለ : ሰው የሚኖረው ያመነውን ያህል ነው ( #እምነት_ማለት_የልብ_እርግጠኝነት_ነው) ይሄን ስላወቀች ባገኘችው አጋጣሚ ሁሉ የተሳሳተ እምነትን የሚፈጥሩ እውቀትን ትለቅብናለችያለማቋረጥ እንድንሰማት አምስቱ የስሜት ሕዋሳችንን እየገዛቹ አለች: ዓለም ሲባል እሩቅ አትሂዱ..    ከላይ ዘዳግም 6:6-9 ላይ የተጻፈውን አነበባችሁት? "#ዘዳግም" የሚለውን "#ዓለም" በሚል ቀይሩና አንብቡት ዓለም፦ 6:6-9 እኔም ዛሬ አንተን የማዝዘውን ይህን ቃል በልብህ ያዝ ለልጆችህም አስተምረውበቤትህም ስትቀመጥበመንገድም ስትሄድስትተኛም ስትነሣም ተጫወተውበእጅህም ምልክት አድርገህ እሰረውበዓይኖችህም መካከል እንደክታብ ይሁንልህበቤትህም መቃኖች በደጃፍህም በሮች ላይ ጻፈውእግዚአብሔር ለሕይወት ጥቅም በሚመክርህ ልክ  ዓለምም ትመክርሀለችመምከር ብቻ አይደለም  የምትመክርህን ቃል በልብህ እንድትይዝ ለልጆችህ እንድታስተምረው በቤትህ ስትቀመጥ በመንገድ ስትሄድ ስትተኛ ስትነሳም እንድትጫተው...በብዙ አማራጮች በስልክ በቲቪ በመንገድ በታክሲ በቡና ጠጡ...በእልፍ አማራጮች በፊትህ አቅርባልሀለችየዓለም ቃል ሞትን ይዟል የ እግዚአብሔር ቃል ሕይወትን ይዟል መርጠህ መታዘዝ የአንተ ድርሻ ነውአጥብቀህ ልብህን ጠብቅ(#የእግዚአብሔር_ድርሻ_አይደለም_!) #የሕይወት_መውጫ_በእርሷ ነውና_!! #ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ 💒 ወደ ቻናላችን ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለቴ ብቻ ይንኩ👉@biruk351 #ሼር_ስለሚያደርጉ_እናመሰግናለን ❤🙏

በምንም አይነት ሁኔታ ውስጥ ብትሆኑና ሁኔታዎች እናንተን ተስፋ ለማስቆረጥ ቢታገሉ እነዚህን ሶስት ነገሮች አስቡ 👉 ከዚህ ቀደም እግዚአብሔር ከእናንተ ጋር እንደነበር 👉አሁንም ምንም ባይሰማችሁ ከእናንተ ጋር እንዳለና 👉ሁልጊዜም ከእናንተ ጋር እንደሚሆን በተስፋ መቁረጥ ስንፈተን እርሱ ትክክለኛው ተስፋችን ነውቀናቶች የጨላለሙ ሲመስሉን እርሱ ብርሃናችን ነውከአቅማችን በላይ ሆኖ ስንደካክም እርሱ ብርታታችን ነው! እግዚአብሔር መታመኛው ያደረገ አያፍርም! ሰዎች ይቀያየራሉ ፣ ሁኔታዎች ይለዋወጣሉ ፣ ሳታስቡት ሰዎች በተሳሳተ መንገድ ይረዷችኋል ፣ እናም በረሃ ውስጥ ያላችሁ ያህል ይሰማችኋል..በዚህ ሁሉ ግን በወደዳችሁ በእርሱ ከአሸናፊዎች ትበልጣላችሁ ልባችሁ በእርሱ አበርቱ #ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ ወደ ቻናላችን ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለቴ ብቻ ይንኩ 👉@biruk351 #ሼር_ስለሚያደርጉ_እናመሰግናለን ❤🙏

ለረጅም ጊዜ ለፀሐይ የተጋለጠ አንድ ነገር ፣ ከፀሐዩ ብርሃን የተነሳ መጥቆሩ ፣ ቀለሙን መልቀቁ የማይቀር ነው። እምነት የሚለው ቃልም እንዲሁ አደጋ ያንዣበበት ቃልና ትርጓሜ የያዘ እየመሰለ ነው። እ
ለረጅም ጊዜ ለፀሐይ የተጋለጠ አንድ ነገር ፣ ከፀሐዩ ብርሃን የተነሳ መጥቆሩ ፣ ቀለሙን መልቀቁ የማይቀር ነው። እምነት የሚለው ቃልም እንዲሁ አደጋ ያንዣበበት ቃልና ትርጓሜ የያዘ እየመሰለ ነው። እምነት አግባብ ያለውን ጠቃሜታ የጎላ ቢሆንም አሁን አሁን ግን ጥቅሙ ተለይቶ ሊታወቅ እስከማይችል ድረስ የመቀየጥ አዝማሚያ ይታይበታል። በሌላ ጎኑ መፅሐፍ ቅዱስ ከሚሰጠን የእምነት ቁልፍ ውጭ ተመሳስለው የተሰሩ የእምነት ቁልፎች መብዛታቸው ነገሩን አምታቶታል። ብዙ ጊዜ እምነት ተብሎ የሚበየኑ ነገሮችም ፦ በምኞት የተሞላ ሀሳብ፣ ወይም ራስ-ወዳድ ፍልጎት ፣ ወይም አዎንታዊ አስተሳሰብ(positive thing) ፣ ወይም እውነታን መካድ ፣ ወይም ጭራሽ የአእምሮን አስፈላጊነት ማጣጣል.. እነዚህ ሁሉ ተመሳሳይ ቁልፎች በመሆናቸው በእምነት መኖር የሚል የመፅሐፍ ቅዱስ ትዕዛዝ ላይ ግልፅ የሆነ ገለልተኝነትና ጥቃት ደርሶብናል። እውነተኛ እምነት መፅሐፍ ቅዱስ የሚነግረን እግዚአብሔርን የሚያከብር እኛንም በደስታ የሚሞላና በሌሎች ዘንድም ምስክርነትን የሚያተርፍ ሲሆን መንገዱም እውነቱም የእምነት ሕይወቱም ራሱ ኢየሱስ ክርስቶስን ማዕከል ያደረገ ነው። እምነት አሁን አንድ ነገር አሊያም በውጭ ያለ የሆነ አመለካከት አይደለም! እምነት ስብዕና ያለው ማንነት ነው ፣ የእምነታችን ጀማሪና ፈፃሚ የሆነው ክርስቶስ በእኛ ውስጥ ያለው የራሱ ሰማያዊ የሕይወት ስርዓት ነው! #ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ 💒

(የያዕቆብ መልእክት ምዕራፍ 2) ---------- 17፤ **እንደዚሁም ሥራ የሌለው እምነት ቢኖር በራሱ የሞተ ነው**። 18#ነገር_ግን_አንድ_ሰው። **አንተ እምነት አለህ እኔም ሥራ አለኝ**፤ **
(የያዕቆብ መልእክት ምዕራፍ 2) ---------- 17፤ **እንደዚሁም ሥራ የሌለው እምነት ቢኖር በራሱ የሞተ ነው**። 18#ነገር_ግን_አንድ_ሰው። **አንተ እምነት አለህ እኔም ሥራ አለኝ**፤ **እምነትህን ከሥራህ ለይተህ አሳየኝ**፥ **እኔም እምነቴን በሥራዬ አሳይሃለሁ ይላል**። #ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ 💒 **ወደ ቻናላችን ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለት ጊዜ ብቻ ይንኩ**👉@biruk351

#በእውነት_ይኼንን_ቃል_እናምነዋለን_ወይ_? "በእኔ ብትኖሩ ቃሎቼም በእናንተ ቢኖሩ የምትወዱትን ሁሉ ለምኑ ይሆንላችሁማል።" (የዮሐንስ ወንጌል 15:7) ወይ ወንጌላዊዉ ዮሃንስ ኢየሱስ ያላለውን አለ ብሎ እየነገረን ነው አልያም እኛ በክርስቶስ ውስጥ ብንኖርም ቃሎቹ በእኛ ውስጥ በሕያውነት አይኖሩም ማለት ነው:: 👉# ኢየሱስም_ያመኑትን_አይሁድ_እናንተ በቃሌ ብትኖሩ በእውነት ደቀ መዛሙርቴ ናችሁእውነትንም ታውቃላችሁ እውነትም አርነት ያወጣችኋል አላቸው (ልብ በል ካመኑት በኋላ ቃሎቹ በእነርሱ ውስጥ እንዲኖር እየጋበዛቸው ነበር ኢየሱስ ዮሐ8:31-32) ......እውነታው ግን ዮሃንስም እየዋሸን አይደለም: ጌታችንም የሚሆነውን እውነቱን ነው የተናገረው: ጥያቄው እኛ ጋር ነው:- #በእውነት_በክርስቶስ_እንኖራለን? #ቃሎቹስ_በእኛ_ኖረው_ይገዙናል? ለምንድነው ሰሞኑን ትንቅንቅ ያለበት ሞጋች ሀሳቦችን የማቀርበው?: ክርስትናችን ሕያው የመሆን አቅሙ እየተዳከመና ሀይማኖታዊ መልክ በመያዝ ከኃይሉ እየራቅን ያለንበት ዘመን ውስጥ እንዳለን እየታወቀኝ ስላለ ነውክርስትና በሆኑ ግሩፖች መታጠርና የሆነ ቸርች አባል በመሆን መመፃደቅ አይደለም!: ክርስትና በግልህ በመንፈስ ቅዱስ በኩል በክርስቶስ በሆንከው እውነት በአብ ጋር ያለ አሁናዊ መስተጋብር ነው!!! ጌታ ግን የሚገርም የተስፋ ቃል ነው የሰጠን!? #ቃሉ_እኮ_እንዲህ_ነው_ የሚለው:- #የምትወዱትን_ሁሉ_ለምኑ:: #የምትወዱትን_ሁሉ_? አዎ የምትወዱትን ሁሉ! ጌታችን ቸር አይደል!? #ሆኖም_ግን_ይህን "የምትወዱትን ሁሉ ለምኑ ይሆንላችሁማል" የሚለውን የከበረ ተስፋ ስናስብ ሁለት እውነቶችን አብረን ማሰብ አለብን: #አንድ በእውነት ይህን ቃል እናምነዋለን ወይ? በእውነት ቤተክርስትያን ይህን ቃል ታምናለች ወይ? #ትርጉሙንና_አውዱን_ማወቅ_ማመን #አይደለም: ልባችን ውስጥ ተተክሏል ወይ የሚለው ነው ጉዳዩ:: #ሁለት በክርስቶስ ውስጥ"#ብንኖርም" ቃሎቹስ ነግሰውብናል ወይ? ቃሉን ማወቅና ለቃሉ እውቅና ሰጥቶ መገዛት ይለያያል::(ቃሉን ሰሚዎች ብቻ አትሁኑ አድራጊዎችም የተባልነው ለዚህ ነው) ቃሉን አምነኸው በክርስቶስ ከኖርክና ቃሎቹም በአንተ ከኖሩ የምትወደውን ሁሉ ለምን #ይሆንልሃል:: #ትኩረት_የሚሻ_መረዳት_ልስጥህ፦ የምትወደው ሁሉ ስለተባለ አሰስ ገሰሱን ዝም ብሎ የሚነሽጥህን ሁሉ ስለማለት አይደለም። #በክርስቶስ_ስንኖርና_ቃሎቹም_በእኛ_ሲኖሩ #ጌታ_ከሚወደው_ውጪ_ምንም_ነገር_አንወድም:: ክርስትና ቀልድ ወይም ከሃይማኖቶች መካከል አንዱ አይደለም: በአማኝ ሕይወት የክርስቶስ ስልጣን መለገጥ ነው: በክርስቶስ ኑር ቃሎቹም በአንተ ይኑሩ እንጂ የክርስቶስን ፈቃድ በምድር ላይ ታስፈፅማለህ:: ክርስቶስን ወክለንና የእርሱን ስልጣን ይዘን እዚህ እንዳለን መርሳት የለብንም: ክርስትናን አናድበስብሰው ኧረ አናሳንሰው: በክርስቶስ እንኑር ቃሎቹም በእኛ ይኑሩ እንጂ ክርስቶስን አሁንና እዚሁ እንገልጠዋለን: ክርስትና ከዋናው ከቆጣሪው ጋር መነካካት ነው: እርሱን ነክተነው በእርሱ ስልጣን አለመገለጥ አንችልም: ክርስትና ክርስቶስን መንካትና ክርስቶስን መግለጥ ነው: በክርስቶስ ኖሮ የእግዚአብሔር ሕይወት ወይ በብዙ ወይ በጥቂት አለመግለጥ አይቻልም! ፡**የተወደዳችሁ ቅዱሳን ክርስትናን ወደ ሀይማኖታዊ እስራትና ወግ ወስዳችሁ አትታገሉ አትድከሙም! ወይ እምኑ ወይ ደግሞ አትመኑ ይኼው ነው። #ታምናለህ? #ታምኛለሽ? #እናምናለን? #ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ 💒 ወደ ቴሌግራም ቻናላችን ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለት ጊዜ ብቻ ይንኩ👉 @biruk351 #ሼር_ስለሚያደርጉ_እናመሰግናለን 🙏❤

#በእኔ_የሚያምን ከሌሎቹ ወንጌላውያን በተለየ መልኩ ወንጌላዊው ዮሃንስ ወንጌሉን የጻፈበትን ምክንያት ግልጽ ያደርጋል፡ ያም ምክንያት አንባቢዎቹ (እንደሩቅ ተደራስያን እኛንም ጨምሮ) #ኢየሱስ_እርሱ “ክርስቶስእንደሆነ በማመን ሕይወት ይሆንላቸው ዘንድ ነው። ከዚሁ በክርስቶስ ከማመን ጋር በተያያዘ መልኩ ዮሃንስ: ክርስቶስ በአማኞች ሕይወት ውስጥ አሳብ / idea / logy ሳይሆን  ever-present experiential reality መሆኑን አበክሮ ያወሳል፡ ይህንንም እውነት ሲናገር በእርሱ ወንጌል ውስጥ ልዩ የሆነውን የጌታ የኢየሱስን “በእኔ የሚያምን” የሚሉትን ሁለቱን ቃላት በማስቀደም ነው፡ በዮሃንስ ወንጌል ውስጥ ጌታችን “በእኔ የሚያምን” ብሎ የተናገራቸው በዛ ያሉ አሳቦች አሉ። #ለምሳሌ ያህል በእርሱ የሚያምን ከፍርድ እንዳመለጠቢሞት እንኳን ሕያው እንደሚሆንየዘላለም ሕይወት ውሃ ከሆዱ እንደሚፈልቅ ተናግሯል፡ #ከእነዚህ “በእኔ የሚያምን” ንግግሮች መካከል አሳቤን የገዛው ግን የሚከተለው ነው፦                      #እውነት_እውነት_እላችኋለሁ፥ በእኔ የሚያምን                       #እኔ_የማደርገውን_ሥራ_እርሱ ደግሞ ያደርጋል፤                  #ከዚህም_የሚበልጥ ያደርጋል።                                       (ዮሃንስ 14 ፡ 12) እንደዚህ ክፍል እጅግ የሚገርምና የሚያስደነግጥ ይኖር ይሆንን?: አዎ ንቀተ-እምነታችንን የሚበረብር ክፍል ነው። መጽሃፍ ቅዱሳችን ውስጥ እንዳለ ብናውቅም ነገር ግን ምን ያህል ከክፍሉ ጋር የተጣበቀ ዝምድና እንዳለን አላውቅምአሳቡ በዮሃንስ ወንጌል ውስጥ እንዳለ ብናውቅም ነገር ግን ስንት ጊዜ ከመድረክ ላይ ሲሰበክ እንደሰማነው ወይም ስንት ጊዜ እኛ እንደሰበክነው እኛና እኛ ብቻ እናውቃለንበእኔ የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው የሚለውን “#እናምናለን” ደግመንም ደጋግመንም እንሰብከዋለን፡ በእኔ የሚያምን  የዘላለም ሕይወት ውሃ ከሆዱ ይፈልቃል የሚለውን “#እናምናለን” ደግመን ደጋግመንም እንሰብከዋለንበእኔ የሚያምን እኔ የማደርገውን ሥራ እርሱ ደግሞ ያደርጋልከዚህም የሚበልጥ ያደርጋል የሚለውን “#ብናምነውም” (ማመናችንን እኛና ጌታ ብቻ ነው የምናውቀው) ለመስበክ ግን አንደፍርም። “#ጥያቄው_አሁን_ነው_የሚመጣው_፦ “#አምነን” የዘላለም ሕይወት እንዳለን “#ካወቅን” ወይም እርግጠኛ ከሆንን አምነን ጌታ ካደረገው በላይ ማድረግ ያልቻልን ስለምንድን ነው?: አንዳንዶች ይኼንን ጥያቄ ለመኮነንና ዋጋ ቢስ የመሆን ስሜት ውስጥ ለመጣል እየፈጠርኩ ያለ አርጋችሁ ታስቡ ይሆናልይኼ ለእኔ ጉዳዬ አይደለም እግዚአብሔር ልቤን ያውቃልና! #በእርግጠኝነት_ማናችንም_በነፍስ_ወከፍ “የዘላለም ሕይወት እንዳለህ እንዴት አወቅህ?ተብለን ብንጠየቅ በልበ ሙሉነት “#ምክንያቱም_በክርስቶስ_ ስላመንሁ” የሚል እንደሚሆን ምንም ጥርጥር የለኝም፡ “ ታዲያ ለምን እርሱ ካደረገው በላይ አታደርግም?የሚል ጥያቄ ተከትሎ ቢቀርብልን ግን መልሳችን ምን ይሆን?: ወደድንም ጠላንም ለዚህ ጥያቄ የምንሰጠው መልስ በዮሃንስ ወንጌል ውስጥ ለተገለጹት“#በእኔ_የሚያምን” መልዕክቶች በሙሉ ያለንን ግንዛቤ የሚያሳብቅ ነው። #ጌታ_ይህን_አሳብ_የተናገረው “እውነት እውነት እላችኋለሁ” #ብሎ_በማስረገጥ ነው፡ ፈጽሞ ጥርጥር የሌለበት ጉዳይ ነውበእርሱ የሚያምኑ እነርሱ በእውነት በእርሱ ይመኑ እንጂ እርሱ ካደረገው በላይ ማድረግ ይችላሉበክርስቶስ አምነን የዘላለም ሕይወት እንዳለን ካመንን በክርስቶስ በማመን ከእርሱ የበለጠ ስራ መስራት እንደምንችልም ማመም አለብን!አለበለዚያ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረን “#አምነናል” የሚለውን ነገር መጠርጠር አለብን፣ #ካልሆነም_ዮሃንስ “እየዋሸን” ነው፣ ካልሆነ ካልሆነ ደግሞ ክፍሉ የሚለውን አይልም ማለት ነውየኔ አላማ ፈጽሞ ተስፋ እንድንቆርጥ ሳይሆን  ዮሃንስ በወንጌሉ ምን ያህል ጥልቅና ተራክቦአዊ ወደሆነ ሕይወት እንደጠራን ለማሳየት ነውክርስትና ወይም በክርስቶስ ማመን ድንቅ ነውበራሱ ተአምር ነውበክርስቶስ ማመን የሆነ የፍልስፍና School of Thought መከተል አይደለምታምራታዊ የሆነ የራሱን የጌታን ሕይወት መቀበልና በእርሱ ስልጣን መመላለስ ማለት ነው። #እውነት_እውነት_እላችኋለሁ_ክርስትና_ይኼው_ነው። ዮሃንስ ወደ ዶክትሪን ሳይሆን እንደ ውቅያኖስ ሰፊና ጥልቅ ወደሆነ የክርስቶስ ሕይወት ነው እየጠራን ያለውበራሱ በክርስቶስ ስልጣን በመኖር እርሱ እንዳደረገው ለማድረግአስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ ደግሞ እርሱ ካደረገው በላይ ወደማድረግ የላቀ ሕይወት ነው የተጠራነው፡፡ #ታምናለህ? #ታምኛለሽ? አደራህን ያ ክፍል እኮ ለደቀመዛሙርቱ ብቻ ነው እንዳትለኝቤተክርስትያን የእግዚአብሔርን ሕይወት ከመለማመድ ስትወድቅ የፈበረከችው መልስ ነው፡ "በእኔ የሚያምን" ነው እንጂ የሚለው "#እናንተ_ደቀመዛሙርቶቼ_ብቻ" አይደለም የሚለው፡ እኔ በግሌ እንደዚህ  ከማስብ ሙሉዉን መጽሃፍ ቅዱሱን አስቀምጬ ባዶ እጄን መቅረትን እመርጣለሁ፡ 😥 “#ለደቀመዛሙርቱ_ነውማለት ከጀመርን ከረጅም ተራራ ላይ ቁልቁል መሮጥ ጀምረናል ማለት ነው**፡😥 #ማቆሚያ_የለውም። ከዚህ አይነት አፈራርሶን ከሚጥለን እሳቤ ይልቅ የሚያዋጣን እንዴት ነው ዮሃንስ ወደሚጠራን ወዲዚህ ጥልቅና ተራክቦአዊ ሕይወት መግባት የምንችለው ወይም የምንለማመደው ብሎ መጠየቅና በጸሎት የተናጋሪውን ጌታ ፊት መፈለግ መልካም ነው፡፡ ጌታ ካደረገው በላይ ስለማድረግ ከማመናችን በፊት እርሱ ያደረገውን ማድረግ ቢቀድም መልካም ነው! መጀመሪያ ከትንሹ ጀምር ከዚያ ወደ ትልቁ ልምምድ ትወጣለህ! ሂድ መጀመሪያ ካመንክ ወንጌል ስበክሂድ በኩነኔ ላሉ የፅድቅ ቃል ስበክሂድ በአጋንንት እስራት ላሉ መንግሥቱን እግዚአብሔር በክርስቶስ እንዳፈረሰ አውጅሂድ የታመሙት ላይ ከወንጌል በኋላ እጅህን ጫንሂድ በሽተኞች መፈወስ እንደሚችሉ አውጅ ይኼን እያደረክ ወደ ትልልቅ ድሎች መግባት የምትችልበትን መንገድ መንፈስ ቅዱስ ያበራልሃል። 🔥🔥🔥 #ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ 💒 ወደ ቻናላችን ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለት ጊዜ ብቻ ይንኩ👉@biruk351 #ሼር_ስለሚያደርጉ_እናመሰግናለን ❤🙏

#ለሚያምን_ሁሉ_ይቻላል_ በግሪኩ ወይም በላቲኑ ብለን ምንም አንጨምርበትም አንቀንስበትምም:: #ስትፈልጉ "የእምነት ቃል" ወይም "የቃል እምነት" #በሉት_አንድ_ነገር_ግን #እናውቃለን_ለሚያምን_ሁሉ_ይቻላል:: ይኼ እንዴት አይነት ያልተለመደ አገላለፅ ነው?በመፅሀፍ ቅዱስ እግዚአብሔር ሁሉን እንደሚችል ተገልጿል!: በዚህ ቦታ ደግሞ ይኼንን እግዚአብሔር ለሚያምን ሁሉ ይቻልለታል እየተባልን ነውለኔ ወይም ለአንተ አይደለም ነገር ግን👉 ለሚያምን ለእርሱ ጌታ በእርሱ ውስጥ ይችላል  #እንደማለት_ነው።  እንደዚህ አይነት ሕይወት እኛ ስላላወቅነው ወይም ስላልደረስንበት ስህተት ነው ማለት አይደለም:: ከሰው አስተያየትና ከሰው ልምምድ በላይ የምንሰማውና የምናምነው የእግዚአብሔርን ቃል ነው: ፀሎታችንም እግዚአብሔር በመንፈሱ ወደዚህ አይነት የሕይወት ከፍታና ልምምድ እንዲያስገባን ነው:: #የእግዚአብሔር_ሰው_በእምነት /በማመን / #በመደገፍ_እንጂ "በቀመር" #ወይም_በሞላ_ጎደለ አይኖርም:: በተለይ ጥቅስ እያዋቀርን ለምንፅፍም ሆነ ለምንሰብክ ሰዎች "#እምነት" ዘወትር መፈተሽ ያለበት ጉዳይ መሆኑን ደጋግሜ ሳስታውስ እኔን አይታክተኝም!: ምክንያቱም ሁል ጊዜ ታምነን በእምነት እንድንመላለስ መፅሀፍ ቅዱስ አጠንክሮ ስለሚናገር!: ጥቅሶችን ማወቃችንና አዋቅሮ መፃፍ መቻላችን እምነታችን ሙሉ እንደሆነ አድርጎ ሊሸውደን አይገባም: ወይም በእምነት የመኖራችን መገለጫ ሊሆን አይችልም! **መፅሀፍ ቅዱስ እምነትን በተመለከተ የሚሰጠውን ፍንጭ በስሱ እንይና ራሳችንን በቃሉ በማረም አለማመናችንን በአጭሩ ስር ሳይሰድ እንቅጨው!! "#ባለማመናቸው_ጠንቅ_ሊገቡ እንዳልተቻላቸው እናያለን" "#በእናንተ_በአንዳችሁም_ክፉና_የማያምን ልብ እንዳይኖር ተጠንቀቁ" "#የሰሙት_ቃል_ከሰሚዎቹ_ጋር_በእምነት ስላልተዋሃደ አልጠቀማቸውም" "#እርሱ_የላከውን_እናንተ_አታምኑምና_ በእናንተ ዘንድ የሚኖር ቃሉ የላችሁም" " #ኋላም_በማዕድ_ተቀምጠው_ሳሉ_ለአሥራ #አንዱ_ተገለጠ_ተነሥቶም_ያዩትን ስላላመኑአቸው አለማመናቸውንና የልባቸውን ጥንካሬ ነቀፈ" " #እርሱም_እናንተ_የማታስተውሉ_ነቢያትም የተናገሩትን ሁሉ ልባችሁ ከማመን የዘገየ" (ኢየሱስ የኤማውስ መንገደኞችን ሲነቅፍ) "#ያመንህ_እንጂ_ያላመንህ_አትሁን" "#እናንተ_እምነት_የጎደላችሁ_" "#ስለምን_ተጠራጠርህ_?_" "#ማንም_በልቡ_ቢያምን_ሳይጠራጠርም...." "#በመንገዱ_የሚወላውል_ከእግዚአብሔር ዘንድ አንዳች የሚያገኝ አይምሰለው" "#ያለእምነት_እግዚአብሔርን_ደስ_ማሰኘት አይቻልም" " ዳሩ ግን ሁሉን አንድ ጊዜ ፈጽሞ ምንም የተማራችሁ ብትሆኑ ጌታ ከግብፅ አገር ሕዝቡን አድኖ #የማያምኑትን_በኋላ_እንዳጠፋቸው ላሳስባችሁ እወዳለሁ።" (የይሁዳ መልእክት 1:5) ከፅሁፋችን ከስብከታችን ከሚኒስትሪያችን በላይ የሰናፍጭ ቅንጣት የምታክል እምነታችንን መጠቀም  ትልቅ ዋጋና ብድራት አላትና በፀጋው የተሰጠንን እምነት እንጠቀም እላለሁ 🙏 "አቤቱ በዚህ ስጋዊነቴ ውስጥ ያለውን በመንፈሳዊ ነገር ተቃርኖ የሚቆመውን ተፈጥሮአዊውን  አለማመኔን እርዳ" ፣ አቤቱ በመንፈሴ ውስጥ አንተን እንዲሁ የማመን ተፈጥሮ በዳግም ልደት ስላካፈልከኝ ያንን ተፈጥሮዬን በቃልህ በኩል እንዳሳድገው መንፈስህ ይግዛኝ አሚን 🙏 #ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ ወደዚህ ቻናል ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለት ጊዜ ብቻ ይንኩ👉@biruk351

#ለሚያምን_ሁሉ_ይቻላል_ በግሪኩ ወይም በላቲኑ ብለን ምንም አንጨምርበትም አንቀንስበትምም:: #ስትፈልጉ "የእምነት ቃል" ወይም "የቃል እምነት" #በሉት_አንድ_ነገር_ግን #እናውቃለን_ለሚያምን_ሁሉ_ይቻላል:: ይኼ እንዴት አይነት ያልተለመደ አገላለፅ ነው?: በመፅሀፍ ቅዱስ እግዚአብሔር ሁሉን እንደሚችል ተገልጿል!: በዚህ ቦታ ደግሞ ይኼንን እግዚአብሔር ለሚያምን ሁሉ ይቻልለታል እየተባልን ነውለኔ ወይም ለአንተ አይደለም ነገር ግን👉 ለሚያምን ለእርሱ ጌታ በእርሱ ውስጥ ይችላል #እንደማለት_ነው። እንደዚህ አይነት ሕይወት እኛ ስላላወቅነው ወይም ስላልደረስንበት ስህተት ነው ማለት አይደለም:: ከሰው አስተያየትና ከሰው ልምምድ በላይ የምንሰማውና የምናምነው የእግዚአብሔርን ቃል ነው: ፀሎታችንም እግዚአብሔር በመንፈሱ ወደዚህ አይነት የሕይወት ከፍታና ልምምድ እንዲያስገባን ነው:: #የእግዚአብሔር_ሰው_በእምነት /በማመን / #በመደገፍ_እንጂ "በቀመር" #ወይም_በሞላ_ጎደለ አይኖርም:: በተለይ ጥቅስ እያዋቀርን ለምንፅፍም ሆነ ለምንሰብክ ሰዎች "#እምነት" ዘወትር መፈተሽ ያለበት ጉዳይ መሆኑን ደጋግሜ ሳስታውስ እኔን አይታክተም ነው: ምክንያቱም ሁል ጊዜ ታምነን በእምነት እንድንመላለስ መፅሀፍ ቅዱስ አጠንክሮ ስለሚናገር!: ጥቅሶችን ማወቃችንና አዋቅሮ መፃፍ መቻላችን እምነታችን ሙሉ እንደሆነ አድርጎ ሊሸውደን አይገባም: ወይም በእምነት የመኖራችን መገለጫ ሊሆን አይችልም! **መፅሀፍ ቅዱስ እምነትን በተመለከተ የሚሰጠውን ፍንጭ በስሱ እንይና ራሳችንን በቃሉ በማረም አለማመናችንን በአጭሩ ስር ሳይሰድ እንቅጨው!! "#ባለማመናቸው_ጠንቅ_ሊገቡ እንዳልተቻላቸው እናያለን" "#በእናንተ_በአንዳችሁም_ክፉና_የማያምን ልብ እንዳይኖር ተጠንቀቁ" "#የሰሙት_ቃል_ከሰሚዎቹ_ጋር_በእምነት ስላልተዋሃደ አልጠቀማቸውም" "#እርሱ_የላከውን_እናንተ_አታምኑምና_ በእናንተ ዘንድ የሚኖር ቃሉ የላችሁም" " #ኋላም_በማዕድ_ተቀምጠው_ሳሉ_ለአሥራ #አንዱ_ተገለጠ_ተነሥቶም_ያዩትን ስላላመኑአቸው አለማመናቸውንና የልባቸውን ጥንካሬ ነቀፈ" " #እርሱም_እናንተ_የማታስተውሉ_ነቢያትም የተናገሩትን ሁሉ ልባችሁ ከማመን የዘገየ" (ኢየሱስ የኤማውስ መንገደኞችን ሲነቅፍ) "#ያመንህ_እንጂ_ያላመንህ_አትሁን" "#እናንተ_እምነት_የጎደላችሁ_" "#ስለምን_ተጠራጠርህ_?_" "#ማንም_በልቡ_ቢያምን_ሳይጠራጠርም...." "#በመንገዱ_የሚወላውል_ከእግዚአብሔር ዘንድ አንዳች የሚያገኝ አይምሰለው" "#ያለእምነት_እግዚአብሔርን_ደስ_ማሰኘት አይቻልም" " ዳሩ ግን ሁሉን አንድ ጊዜ ፈጽሞ ምንም የተማራችሁ ብትሆኑ ጌታ ከግብፅ አገር ሕዝቡን አድኖ #የማያምኑትን_በኋላ_እንዳጠፋቸው ላሳስባችሁ እወዳለሁ።" (የይሁዳ መልእክት 1:5) ከፅሁፋችን ከስብከታችን ከሚኒስትሪያችን በላይ የሰናፍጭ ቅንጣት የምታክል እምነታችንን መጠቀም ትልቅ ዋጋና ብድራት አላትና በፀጋው የተሰጠንን እምነት እንጠቀም እላለሁ 🙏 "አቤቱ በዚህ ስጋዊነቴ ውስጥ ያለውን የመንፈሳዊ ነገር ተቃርኖ የሚቆመውን ተፈጥሮአዊውን አለማመኔን እርዳ" ፣ አቤቱ በመንፈሴ ውስጥ አንተን እንዲሁ የማመን ተፈጥሮ በዳግም ልደት ስላካፈልከኝ ያንን ተፈጥሮዬን በቃልህ በኩል እንዳሳድገው መንፈስህ ይግዛኝ አሚን 🙏 #ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ ወደዚህ ቻናል ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለት ጊዜ ብቻ ይንኩ👉@biruk351

#በእምነት_እኖራለሁን_? በእምነት መሆናችሁን ለማወቅ ራሳችሁን መርምሩ፤ ራሳችሁን ፈትኑ...(2ኛ ቆሮ13:5) አንዳንድ ጊዜ የማምናቸውንና ቀጥሎ ደግሞ እምነት የማጣባቸውን ነገሮች ሳስብ እውን ድሮስ ቢሆን የማምናቸውን ነገሮች አምናቸዋለሁ ወይ ብዬ እጠይቃለሁለመቶ ብር  አምኜ ለድንቡሎ ሲሆን አለማመን ወይም ጥርጣሬ ሊነግስብኝ ይችላል ወይ ብዬ እጠይቃለሁለድንቡሎ አለማመኔ ለመቶ ብር አለኝ የምለውን እምነቴን አያፋልስብኝም ወይ ብዬ አስባለሁ፣ #ደግሞም_አሰጋለሁ። መቼም ፍጥረትን ሁሉ የፈጠረበሁሉ የሚኖርሁሉን የሚችልናሁሉን የሚያውቅ አምላክ አለ ብሎ ማመን ከፍተኛ የሆነ እርምጃ እንደሆነ ማናችንም አንጠረጥርምበአካል ያላገኘነውንና በአብዛኛው መጽሃፍ ቅዱስ ላይ ብቻ አንብበን: “#ያወቅነውን” እግዚአብሔርን ሁሉን ፈጥረሃልዘላለማዊ ነህበሁሉም አለህሁሉን ታውቃለህና ሁሉን ትችላለህ ብሎ ማመን በዚህ አፅናፈ ዓለም ውስጥ የምንራመደው ትልቁ እርምጃ ነውጥያቄው ግን ይሄንን ሁሉና እንዲህ አይነት አምላክ አምኜ ለአንድ የጸሎት ርዕስ ላላምነው ወይም ልጠረጥረው ከእምነትም ዞር ብዬ ባለማመን ፀሎቴን ልተው እችላለሁ ወይ የሚለው ነውበእንደዚህ አይነት እጅግ ምጡቅ በሆኑ እግዚአብሔራዊ ባሕርያት አምኜና እግዚአብሔርንም በመዝሙሬም ሆነ በስብከቴ አንተ እንደዚህ ነህ ብዬውከዛም አልፎ ለሰዎችም እግዚአብሔር እንደዚህ ነው ብዬ አንበልብዬም ተንበልብዬም ሳበቃ ለአንድ ከግል ሕይወቴ ጋር ለተገናኘች “#ሚጢጢዬ” #የጸሎት_ርእስ_ላላምነው #እችላለሁን?_እንደዚህስ_ከሆነ፣ ማለትም ለአንድ ብር አለማመኔ ለእልፍ ብር አምንሃለሁ የሚለውን እሳቤዬን አይንድብኝምን? #እውነት_ግን_አምንሃለሁ_ስለው_አምነዋለሁ? *እግዚአብሔር ከሞትሁ በኋላ ያስነሳኛል ለዘላለምም ከእርሱ ጋር ያኖረኛል የሚለው ሐሳብ በመዝሙሮቼም ሆነ በስብከቶቼ ውስጥ እንደ ሰንደቅ ከፍ ብለው ይውለበለባሉ፡ #ነገር_ግን “ወገቤንየሚያሰኘው ዱብዕዳ ሲገጥመኝ ለዘላለም ከእርሱ ጋር ለመኖር ከሞት ያስነሳኛል ብዬ የማምነውን እግዚአብሔርን: ለአንድ ቀን ያኖረኛል ብዬ አምነዋለሁ ወይ የሚለው ነው*፡ ዘላለም ለሚባል እድሜና ለዘላለም ጉዳይ ያመንሁትን ያንኑ እግዚአብሔርን#ለእለት_እንጀራአምነዋለሁ ወይ የሚለው ጥያቄ እስከ አጥንት ድረስ ዘልቆ የሚሰማ ነው**። #እውን_ለዘላለም_ሕይወት_የማምነውን #እግዚአብሔርን_ለአሁን_አምነዋለሁ_? እግዚአብሔር አንድያ ልጁን ለሃጢአቴ እንደ ሰጠውና ከፍርድና ከኩነኔ ሁሉ እንዳዳነኝ አምናለሁነገር ግን ይሄው ልጁን ስለ እኔ እስከሞት ድረስ አሳልፎ እንደ ሰጠኝ በየመድረኩና በየፌስቡኩ የማውጅለትን እግዚአብሔርን ለአንድ ዳቦ አምነዋለሁ ወይ የሚለው ጥያቄ ቆም ብዬ ስለ እርሱ አለኝ ብዬ የማስበውን እምነቴን ሁሉ እንድጠይቅ ያስገድደኛልእውነት ሳላይና ባልነበርኩበት አውድ ውስጥ ንጹህ ልጅህን ሰጥተኸኛል ብዬ የማምነውን እግዚአብሔርን ለአንድ ቀን ኑሮዬ ወይም እንጀራዬ አምነዋለሁ?: እውነት ለትዳሬ አምነዋለሁ?እውነት ለልጆቼ አምነዋለሁ?እውነት ለስራዬ አምነዋለሁ?እውነት በአገልግሎቴ አምነዋለሁ?እውነት ለጀመርኩት ትምህርት መጠናቀቅ አምነዋለሁ? (ራሳችሁን በምትፈልጉበት አቅጣጫ እውነት አምነዋለሁ እያላችሁ ጠይቁበት?) እውነት ይህን ለዘላለም ሕይወት ያመንሁትን የዘላለም አምላክ ለእለት ጉዳዬ አምነዋለሁ? ለነገ አምነዋለሁ?በስተርጅናም ተገኔ ነህ ብዬ አምነዋለሁ?: አለበለዚያማ እንዴት አድርጌ ነው ለዘላለም ሕይወት የማምነው? እንዴት አድርጌ ነው አንተ ዘላለማዊ ነህ ብዬ የማምነው? ለዕለት እንጀራ ከጠረጠርሁት ለዘላለሙ ማመኔን ከንቱ አያደርግብኝም ወይ? : ለዘላለም ሕይወት አምኜው ለዕለት እንጀራ ልጠረጥረው እችላለሁ ወይ? ሳልወድህ ወደኸኛልጠላትህ ሳለሁ በልጅህ ሞት ከራስህ ጋር አስታርቀኸኛል ብዬ የማምነውን እግዚአብሔርን ከጎኔ ያለውን ወንድምና ከጎኔ ያለችውን እህትስ ለመውደድ አምነዋለሁ? : ወንድሞችና እህቶችን ለመውደድስ አምነዋለሁ ወይ የሚለው ነው?:: #እውነት_እምነቴ_እውነት_ነው°? Is it genuine? #ሐዋርያው_ጳውሎስ_እንዲህ_ይላል፦ ለገዛ ልጁ ያልራራለት ነገር ግን ስለ ሁላችን አሳልፎ የሰጠውያው ከእርሱ ጋር ደግሞ ሁሉን እንዴት አይሰጠንም?(ሮሜ8:32) #ሃሌሉያ!🔥 ልጁን ለመስጠት የታመነኝ ጌታ እንዴት ለሌላው አይታመነኝም?!: ልጁን ያልሰሰተልኝ አምላክ እንዴት ነው የእለት እንጀራ የሚነፍገኝ?!  የፍቅሩን የመጨረሻ ጥግ ያሳየኝ አምላክ እንዴት ነው ለሰባና ሰማኒያ ዓመት እንዳልታመነች ምንጭ የሚሆንብኝ?! ጥርጣሬአችንን የአባታችን ታማኝነት በቃሉ በኩል በማየትና በመስማት እንድናስወግደው እንጂ ስለ ጥርጣሬአችን ጥግ ድረስ ራስን እስከ መጥላት ራሳችንን እንድንኮንን ይኼ መልዕክት አልተዘጋጀም!!! : ኢየሱስ በስጋ ወራቱ ያለማመን አይሎባቸው ሲያይ አይለሳለስም ነበር ቆጣ ብሎ እምነታቸውን እንዲጠቀሙ ያነቃ ነበር በእኔም እንደዚያው ነውበልጁ የታመነኝ ጌታ ለዛሬም ለዘላለምም ታማኝ ነውና ጌታ ሆይ አለማመኔ እርዳ🙏 #ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ 💒 ወደ ቴሌግራም ቻናላችን ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለት ጊዜ ብቻ ይንኩ👉@biruk351