Grace & Truth Ministry
Open in Telegram
እንኳን ወደዚህ ቻናል በሰላም መጡ ከእግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ፀጋና ሰላም ይብዛላችሁ በእውነት ቃልና በፀጋው መንፈስ ይታነፁ
Show more1 029
Subscribers
No data24 hours
-77 days
-2030 days
Posts Archive
#መለኮታዊ_እሳት/Devine Fire🔥🔥
"በምድርም ላይ እሳትን ልጥል መጣው ፥ አሁንም የነደደ ከሆነ ዘንድ ምን እፈልጋለሁ?" (ሉቃ 12:49)
መለኮታዊ እሳት ምንድነው?
👉 መለኮታዊ እሳት ማለት፦ ከእግዚአብሔር መገለጫዎች መካከል አንዱ የእግዚአብሔር ህልውና ነው የመገኘቱም መታወቂያ ነው።
"በቀንና በሌሊትም ይሄዱ ዘንድ ፥ መንገድ ሊያሳያቸው ቀን በደመና አምድ ፥ ሊያበራላቸውም ለሊት በእሳት አምድ እግዚአብሔር በፊታቸው ሄደ። የደመና አምድ በቀን ፥ እሳት አምድ በለሊት ከህዝቡ ፊት ከቶ ፈቀቅ አላለም።"
_ ዘፀ13:21~22
∞ መለኮታዊ እሳት ማለት፦ የአማኞች የውስጥ ሰውነት / እውቀት ፈቃድ ስሜታቸው/ እንዳይበርድ ሁልጊዜ የነቃና የተቀጣጠለ እንዲሆን የሚያደርግ የእግዚአብሔር መንፈስ ነው።
"ለስራ ከመትጋት አትለግሙ ፤ በመንፈስ የምትቃጠሉ ሁኑ ፤ ለጌታ ተገዙ፤
_ሮሜ 12:11
∞ መለኮታዊ እሳት ማለት፦ በአማኞች ልብ ውስጥ የሚነድ የእግዚአብሔር ቃል ማለት ሲሆን በልባቸው የሚቀጣጠለውን የእግዚአብሔርን ቃል በተግባር እንዲያረጉ የሚያደርግ የእግዚአብሔር ኃይል ነው።
"በውኑ ቃሌ እንደ እሳት ፥ ድንጋዩንም እንደሚያደቅቅ መዶሻ አይደለችምን? ይላል እግዚአብሔር። "
_ኤር23:29
* በዚህ ቃል እውነት አንተ ትውልድ እንዲህ ልባርክህ......
~ ከዚህ ቀን ጀምሮ በጌታ በኢየሱስ ስም ከእግዚአብሔር መገኘት የተነሳ በዙሪያቹ የህልውናው ሙቀት ይክበባችሁ።
~ ውስጣችሁ ዘወትር እንዳይበርድ የእግዚአብሔር መንፈስ መንፈሳችሁን ያቀጣጥለው ከዚህ የተነሳ መንፈሳዊ መነቃቃታችሁ የተገለጠ ይሁን።
~ በልባችሁ ያለው የእግዚአብሔር ቃል በድንቅና በተአምራት ከዚህ ቀን ጀምሮ በኢየሱስ ስም መንደድ ይጀምር ከዚህ የተነሳ ማንኛውም ጨለማ ከቃሉ እሳትነት የተነሳ የታገደ ይሁን።
#በኢየሱስ_ስም_ተፈፀመ
(ምንጭ ማሪማዊት)
#ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ 💒
ወደ ቻናላችን ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለት ጊዜ ብቻ ይንኩ👉@biruk351
#ሼር_ስለሚያደርጉ_እናመሰግናለን ❤🙏
ማሰላሰልና ቃሉን መታዘዝ
#በሁሉ_ነገር_የማደጋችን_መገለጫ_ቁልፉ፦
ሁሉም ሰው ቢጠየቅ በእግዚአብሔር ቃል ውስጥ የእርሱ ስኬት ተሰውሮ እንደተቀመጠለት እርግጠኛ ነው፤ ያንን ስኬት ለማግኘት ከቃሉ ጋር የተሰፋ ህይወት ባይኖረውም ለቃሉ ጊዜ ባይሰጥም በውስጡ ግን ይሄንን እንዲሁ በመንፈስ ይረዳል ነው።
ጠይቃችሁ አታውቁም ስኬታችን ያለው በእግዚአብሔር ቃል ውስጥ ከሆነ: ለምን ከቃሉ ጋር ጊዜ አላሳልፍም ወይም ሰዎች ብዙ ጊዜ ከቃሉ ጋር ለምን አያሳልፉም ብላችሁ?
#መልሱ_ይህ_ነው_የመጀመሪያው_ነገር_ከዚህ፡ በፊት ደጋግሜ እንዳልኩት ብዙ ሰዎች ስኬትን የተረዱት ከእግዚአብሔር አለም (#ከእግዚአብሔር_ቃል) አንፃር ሳይሆን የዚህ አለም ሰዎች በተረጎሙበት መተርጎሚያ ነው። ስለዚህም ይሄን ተከትሎ የዚህ አለም ገዢ ባገኛቸው አጋጣሚዎች ሁሉ ለነፍሳችን ቃሉን ማጥናት ማሰላሰል እና ከቃሉ ጋር ጊዜ ማሳለፍ: ለመንፈሳዊው አለም ንቁ ብቻ እንደምንሆን እንጂ በሌሎች ዘርፎች ለስኬታማነታችን አስተዋፅኦ እንደሌለው ይነግረናል፤ በማስረጃም በማስደገፍ ቃሉን በመንፈስ ቅዱስ ብርሀን ሳይሆን: ለታሪክነት በቲዎሎጂም ሆነ በእውቅ አስተማሪዎች: በተለያዩ መንገዶች ሙሉውን የእግዚአብሔር ቃል የሸመደዱ: ነገር ግን ቃሉን ለህይወት ሳይሆን ለዕውቀት ያነበቡ ሰዎችን: በመዘርዘር እንደ እከሌ ቃሉን የሚያውቅ አለ እንዴ? : እስኪ ህይወቱን ተመልከት ጥቅስ ከመጥቀስ በቀር በእርሱ ህይወት ምን የሚታይ ፍሬ አለው?: ይባላል። እውነትም ነገሩ እንዲህ ነው እንዴ ብለን የእነዛን ሰዎች የሕይወት ምልልስ ስናጠና: እነዛ ሰዎች ቃሉን ሸምድደዋል ግን ቃሉ ህይወት የለውም!: በሌላ አማረኛ የሐይማኖት መልክ አላቸው ሀይሉን ግን ክደዋል።
ነገር ግን የተሳሳትነው ትልቁ ነገር የመጀመሪያውና ዋናው ስኬት ቃሉን በመንፈስ ቅዱስ ብርሀን የግላችን የህይወታችን ክፍል ማድረጉ ነው ስኬት ማለት። ቃሉ በመንፈስ ቅዱስ አማካኝነት ወደ ህይወታችን ከመጣ: ያን ቃል ካሰላሰልነውና ከታዘዝነው ለእኛ ህይወትም በረከትም ይሆንልናል: ልክ ከዚህ ህይወት እና በረከት ከሆነ ቃል ጋር ጊዜ ባሳለፍን እና ማሰላሰል በጀመርን ቁጥር : ያኔ እግዚአብሔር አለም ሳይፈጠር በፊት በእኛ ሊሰራው አቅዶ: እኛን ወደዚህኛው ወደሚዳሰሰው አለም ያመጣበትን አጀንዳ : መንፈስ ቅዱስ ይገልጥልናል: ምክንያቱም ቃሉ የህይወት ምንጭ ካንተ ዘንድ ነውና በብርሀንህ ብርሀንን እናያለን ስለሚል: በመንፈስ ቅዱስ አማካኝነት ለእኛ ብርሀን የሆነው ያው ቃሉ ደግሞ ለእኛ ደግሞ በመንፈስቅዱስ በኩል የተፈጠርንበት አጀንዳ ምን እንደሆነ ያበራልናል። ያን ጊዜ የሚሆነው ይህ ነው፦
“ማደግህ በነገር ሁሉ እንዲገለጥ ይህን አስብ፥ ይህንም አዘውትር።”
— 1ኛ ጢሞቴዎስ 4፥15
“Meditate upon these things; give thyself wholly to them; that thy profiting may appear to all.” 1 Timothy 4:15 (KJV)
እግዚአብሔር እኛን የፈጠረበት አላማው አጀንዳውን ለማስፈፀም የሰጠንን መንፈስቅዱስ ስናስብ: በዚህ በመንፈስ ቅዱስ አማካኝነት ደግሞ በህይወታችን ያለው አጀንዳ ማስፈፀሚያ ይሆን ዘንድ: መንፈሱ የሚሰጠንን ፀጋ ሀይል አቅም እና ጥበብ ተጠቅመን: በእኛ ላይ ያለው የከበረ አላማ ወደ መታየት ወደ መገለጥ ይመጣል ማለት ነው። ማደጋችንን ከጅማሬያችን ጀምሮ ልክ እንደ ቃሉ ስላደረግነው: የምናደርገው ጉዞ ሁሉ በመንፈስ በነፍስ በስጋ በጥበብ በቁመት በሞገስ እየተገለጠ በሁለንተናችን ያለ አንደች ነቀፋ ዕድገታችን ይታያል።
#ፀጋ_ይብዛልን
የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ፀጋ: የእግዚአብሔርም ፍቅር: የመንፈስ ቅዱስም ህብረት ከሁላችሁ ጋር ይሁን!
#ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ💒
ወደዚህ ቻናል ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለቴ ብቻ ይንኩ👉@biruk351
#ሼር_ስለሚያደርጉ_እናመሰግናለን ❤🙏
ፍርሀት ወይም እምነት
- መዝ 56: 1-7
ፍርሃት በመጀመሪያ ከታዩት የኃጢአት በሽታ ምልክቶች መካከል አንዱ ሲሆን፣ እግዚአብሔር አዳምና ሔዋንን ለማናገር ወደ ኤደን ገነት በመጣ ጊዜ ከመተላለፋቸው የተነሳ ፈርተው ተደበቁ (ዘፍ. 3)።ከዚያን ጊዜ ጀምሮ የሰው ልጅ ከተለያዩ ነገሮች የተነሳ ፍርሃትን ሲያስተናግድ ኖሯል።
ፍርሃት እንደ ጨለማ ነው።ከኃጢአት የተነሳ አለማችን እንዲሁም በዚህች አለም የምንኖር የሁላችንም ሕይወት በዚህ ጨለማ ተከቧል። “ለምን ፍርሃት ተሰማኝ? ብለን ራሳችንን ብንወቅስ ወይም ብንኮንን“ለምን ጨለማ ኖረ?” እንደማለት ነው።ጨለማውን መርገም ጨለማውን እንደማያሸሸው ሁሉ፣እኛም የከበበን የፍርሃት ጨለማ ምንም ያህል ብንጠላው አንድ ስንዘር ከእኛ ፈቀቅ አያደርገውም።
ይልቁም ልክ ጥቅጥቁ ጨለማ በትንሿ ብርሃን እንደሚወገድ የፍርሃታችን ጨለማም ሊወገድ የሚችለው በእምነት ብርሃን ብቻ መሆኑን እናስተውል።
የእምነት ብርሃን ሲደበዝዝ የፍርሃት ጨለማ ይነግሳል።በተቃራኒው ደግሞ የእምነት ብርሃን ሲፈነጥቅ የፍርሃት ጨለማ ይገፈፋል።
ለዚህ ነው መዝሙረኛው፦
“ፍርሀት በሚይዘኝ ጊዜ፣
እምነቴን በአንተ ላይ አደርጋለሁ።“ መዝ56:3
እኛም ተመሳሳዩን እርምጃ ልንወስድ ይገባል። ሕይወታችን በፍርሃት ጨለማ ተውጦብን ቢሆን፣እምነታችንን በታማኙ ጌታ ላይ እናድርግ። ያን ጊዜ እርሱን የፍርሃትን ጨለማ የሚገፍፍ ብርሃን በሕይወታችን ያበራልናል።
ጴጥሮስ በወጀብ በሚናወጠው ባሕር ላይ እየተራመደ ወደ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲሄድ “የወጀቡን ኃይል ባየ ጊዜ ፈራ፤ መስጠምም ጀመረ”ይለናል። የፍርሃት ጨለማ ዋጠው። ነገር አይኑን ወደ ጌታችን ሲመልስ የፍርሃት ጨለማውን የሚገፍ የእምነት ብርሃን በራለት።
ወደ ቻናላችን ለመግባት ይኽንን ሊንክ ሁለቴ ብቻ ይንኩ👉 @biruk351
#የቀጠለ
..................................
ከልምምድ የተለየ የሃይማኖት መግለጫም ሆነ ሃይማኖት ወይም ነገረ-መለኮት ልክ በመግነዝ እንደተገነዘውና ሕይወት እንደሌለበት አላዛር ነው።
ለአብርሃም ከሰማይ በሚያማምሩ ቃላት የተዋበ የሃይማኖት መግለጫ ሳይሆን የተወረወረለት “#ውጣ” የሚልና ነገር ግን የሚያም ድምጽ ነው የመጣለት፡ ከዛም በብዙ ጥበቃ ያገኘውን ይሥሐቅን “#ሰዋው” ነው የተባለው፡ የፈለገ ቢመጣ አብርሃም እንዲህ አይነቱን እግዚአብሔርን አይረሳውም - ምክንያቱም ሸምድዶት ሳይሆን ቆስሎ ነው የተማረው፡ ያዕቆብ የፈለገ ቢመጣ ያስነከሰውንና ስሙን የቀየረበትን እግዚአብሔርን አይረሳውም - ምልክቱን በሥጋው ተሸክሞአላ!
እነዚህ ሰዎች እግዚአብሔርን በመግለጫ ወይም በነገረ-መለኮት ከመቀመራቸው በፊት በሕይወታቸው የተጨመቁ ሰዎች ናቸው፡ ከነገረ-መለኮታቸው በፊት ከእግዚአብሔር ጋር ያላቸው ተራክቦ ይቀድም ነበር፡ እግዚአብሔርን በሆነ የአመለካከት ቋት ውስጥ ከማስገባታቸው በፊት በማይረሱት መልኩ የተገኙና የተጨመቁ ሰዎች ናቸው፡ እግዚአብሔርን formulate ከማድረጋቸው በፊት እነርሱ ራሳቸው በእግዚአብሔር formulate የተደረጉ ሰዎች ነበሩ፡ ነገረ-መለኮታቸው ከእግዚአብሔር ጋር ከነበራቸው ተራክቦ ውስጥ ወጣ እንጂ እግዚአብሔራቸው ከነገረ-መለኮታቸው ውስጥ አልወጣም። ነገረ መለኮታቸው የልምምዳቸው ተጎታች እንጂ ልምምዳቸው የነገረ-መለኮታቸው ተጎታች አልነበረም፡ ነገረ-መለኮታቸው የልምምዳቸው ጭማቂ እንጂ ልምምዳቸው የነገረ-መለኮታቸው ጭማቂ አልነበረም፡ የሚናገሩት ልምምዳቸውን፣ ርሃባቸውን፣ ቁስላቸውን ህመማቸውን፣ ጥማታቸውን እንጂ የሸመደዱትን ቀመር አልነበረም፡ እግዚአብሔርን ይራቡት የነበረው ስለቀመሱት እንጂ የሆነ ነገር ስለሸመደዱ አልነበረም፡ “#ክብርህን_ሳይ እጠግባለሁ ያሉት ክብሩን ስላዩትና ክብሩ እንዴት እንደሚያደርግ ስለሚያውቁ እንጂ: “#ክብር” ስለሚባል ነገር የሰሩት ነገረ-መለኮት ስለነበር አይደለም፡ ሁሉ ነገራቸው ከልምምዳቸው ነበር የሚወጣው፡ እግዚአብሔር ከሕይወታቸው ጋር የተጋባ ነበር፡፡
በሕይወታችን የማንለማመደው ነገር ግን በሃይማኖት መግለጫ የምንሸመድደው እግዚአብሔር ልክ ጥቁር ሰሌዳ ላይ እንደተሳለ ቪላ ቤት ነው - ሃሳብ ወይም ምናብ ብቻ፡፡
“እግዚአብሔር ይረዳኛል በእርሱም እታመናለሁ : እርሱም ከመከራዬ በእውነት ያድናኛል: የእግዚአብሔር ስም የተባረከ ይሁን” ማለት በነገረ-መለኮት ሽምደዳ ሳይሆን በሕይወት ልምምድ የሚመጣ ህመም ነው።
ለመጽሐፍ ቅዱስ ሰዎች የመጽሐፍ ቅዱሱ እግዚአብሔር የሚፈላሰፉበት የሆነ ነገር ሳይሆን እንባ በእንባ፣ ላብ በላብና፣ ደም በደም የሚያደርጋቸው በሕይወታቸው የሚገለጥ የአሁንነት መስተጋብር ነው፡ ለዚህ ነው መጽሐፍ ቅዱሳችን የፍልስፍና ሳይሆን እግዚአብሔርና ሰዎች የነበራቸውን መስተጋብር የሚገልጽ መጽሐፍ የሆነው፡ ሰዎችና እግዚአብሔር “#ሲጋጩ” ምን እንደሚሆን የሚናገር መጽሐፍ እንጂ እኛ የምንፈልጋቸውን የፍልስፍናና የሳይንስ አሳቦች እያነሳ የሚተነትን መጽሐፍ አይደለም፡ በዚህ ግጭት ውስጥ እግዚአብሔርን ያውቁታል፡ ከዚህ ግጭት ውስጥ ነገረ-መለኮታቸው ይቀዳል፡ ስለዚህም ከላይ እንዳልነው ከነገረ-መለኮታቸው በፊት “#ግጭታቸው” ወይም ልምምዳቸው ይቀድማል፡ በሕይወታቸው የተገለጠውን እግዚአብሔርን ይነግሩናል እንጂ እግዚአብሔር እንዲሆንላቸው የሚፈልጉትን ምናባዊ “#እግዚአብሔር” አይነግሩንም፡ በቤተመንግስት ዙፋን ላይ በመቀመጥም ይሁን ከቤርሳቤህ ጋር ወድቆ በመያዝ፣ #ከዑር “#ውጣ” በመባልና የሚወዱትን ይስሐቅን ደግሞ “#አምጣ” በመባል፣ ሕዝብን ከግብጽ ይዞ ወጥቶ ከዛም ወደ ከነዓን “#አትገባም” በመባል የሚያውቁትን እግዚአብሔርን እንጂ የሸመደዱትን እግዚአብሔርን አይደለም የነገሩን**።
ከምናባዊው እግዚአብሔር ይልቅ ተራክቦአዊው እግዚአብሔር ያማል፡ ተረክቦአዊው እግዚአብሔር የምቾት ምንጭ ቢሆንም ምቾት ግን ይነሳል፡ ተራክቦአዊው እግዚአብሔር ያቆስላል ምክንያቱም በፈቃዳችን ላይ እንደ ልቡ ይሮጥበታል፡ ተራክቦአዊው እግዚአብሔር ካለን እኛ የኛ አይደለንም ምክንያቱም ለራሳችን ይገድለናል።
በሚሸመደደው እግዚአብሔር ታዎቂ ልንሆን እንችላለን፣ በተራክቦአዊው እግዚአብሔር ግን እግዚአብሔርን እናውቀዋለን፡ በሚሸመደደው እግዚአብሔር ጭንቅላቴ በመረጃ ሊሞላ ይችላል፣ በተራክቦአዊው እግዚአብሔር ግን ልቤ ይቀልጣል - “ይሄ የእግዚአብሔር ቤት ነው አላወቅሁም ነበር” እላለሁ።
#ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ💒
ወደ ቻናላችን ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለቴ ብቻ ይንኩ👉@biruk351
#ሼር_ስለሚያደርጉ_እናመሰግናለን ❤🙏
#ርዕሱን_ራሳችሁ_አውጡ_😥
እግዚአብሔርን በጥቅስ ብቻ የሚያውቅ ትውልድ እየበዛ ነው : ዘመኑ የእውቀት አብዮት እየፈነዳ ያለበት ወቅት ስለሆነ: ሰዎች ሁሉ በዚህ እሳት ተነክተዋሉ : ጥሩ ጎን እንዳለው ሁሉ መጥፎ ጎኖችም እየታዩ ነው። አንዳንዱ ባዶ ጥቅስ: ጠብ የሚል ሕይወት የሌለበት ሲሆን ፣ አንዳንዱ ደግሞ ባወቀው እውቀት: ራሱን የእውቀት ጥግና መደምደሚያ አድርጎ በትዕቢት ሌላው ላይ የሚሳለቅ ትውልድ እንደ አሸን እየፈላ ነው። ፍቅር መሠረቱ እየተነዳ ያለበት ዘመን ውስጥ ነን! በነገራችን ላይ ለሌሎች ሕይወት የሚፈሰን ከዘፍጥረት እስከ ራዕይ ባጠራቀምነው መፅሐፍ ቅዱሳዊ መረጃ ያህል ሳይሆን : ክርስቶስ የኖረብንና የተገለጠብንን ያህል ነው! ብዙዎቻችን ግን ባነበብነው መፅሀፍና ባጠራቀምነው የስብከተ እውቀት ሰውን ማስደመምና መኮነን እንፈልጋለን 😥
በመፅሐፍ ቅዱስ ውስጥ በተለይ ደግሞ በብሉይ ኪዳን ልብን ከሚገዙት አሳቦች መካከል ለብዙዎች እግዚአብሔር የሚሸመድዱት ወይም የሚያጠኑት አንድ object ሳይሆን በሕይወታቸው የሚለማመዱትና የሚማሩት እውነት መሆኑ ነው፡ ብዙዎች በከፍታቸው በዝቅታቸው፣ በማግኘታቸው ባማጣታቸው፣ በብርታታቸው በድካማቸው፣ በቆሰሉበትና ባነከሱበት ነገር ነው የተለማመዱትና የተማሩት።
እግዚአብሔርን አይረሱትም ምክንያቱም በሕይወታቸው የድካምና የብርታት ጫፎች ላይ የተገለጠ የሕይወታቸው ልምምድ እንጂ የተሸመደደ አንድ ጽንሰ-አሳብ ወይም ነገረ-መለኮታዊ ቀመር አይደለም፡ ብዙዎችን አስደንግጦአቸው፣ ሌሎቹን አስለቅሶአቸው፣ አንዳንዶቹን አስነክሶአቸው፣ ጥቂቶቹን ደግሞ እስከመቼ ከእኔ ርቀህ ትቆማለህ ብለው እርሱን በመራብ እንዲንገበገቡ አድርጎአቸው ነው እርሱን ወደማወቅና ወደ መረዳት ያመጣቸው፡፡
የሚያማምሩና ለአዕምሮ የሚጥሙ የነገረ-መለኮት እሳቤዎችን ወርውሮላቸው ሳይሆን እርሱ ራሱ ያለምንም ከልካይ በሕይወታቸው ገብቶ መሆን የማይፈልጉትን በማድረግና የሕይወት ምርጫቸውን በማዛባት ነው ወደ እርሱ የጎተታቸው፡ እነዚህ ሰዎች ስለ እግዚአብሔር የሚናገሩት የረቀቀ ነገር ሳይኖራቸው በፊት ነው በሕይወታቸው ዘው ብሎ ገብቶ ማንነቱን የተከለባቸው፡ የሚሸመድዱትን አንቀጽ ወይም የሃይማኖት መግለጫ ሳይሆን የሰጣቸው ራሱን ነው የገለጠላቸውና ያስደነገጣቸው፡ አንዳንዶቹን አቆሰላቸው፣ ሌሎቹን ደግሞ አስነከሳቸው፣ የተወሰኑትን ደግሞ ለፈቃዳቸው ገደላቸው፡ ይሄንን አይነት በሕይወት መንገድ ላይ በራሱ ማንነት የተገለጠበትን እግዚአብሔርን ማን ይረሳል? ለዚህ ነው እግዚአብሔርን ሊረሱት የማይችሉት፡ ሲኖርም ሳይኖርም ያውቁታል፡ በሚመስል ግን ባልሆነ እግዚአብሔር አይሸወዱም፡ በሃይማኖት መግለጫ ወይም በሃይማኖር ስርአት አይሸወዱም ምክንያቱም ባለቤቱን ያውቁታል፡ አስነክሶአቸዋላ! አቁስሎአቸዋላ!
በተለያየ የሕይወት ገጽታቸው የማይረሱት በተለያየው የሕይወት ገጽታቸው እንዳይረሱት አድርጎ ራሱን ስላስተማራቸው ነው፡ “አቤቱ እስከዚህ ያደረስኸኝ እኔ ማን ነኝ ቤቴስ ምንድን ነው?” ከሚለው የከፍታ ንግግር እስከ “እኔ መተላለፌን አውቃለሁ፣ አንተን ብቻ በደልሁ” የሚያስብል የዝቅታ ንግግር ድረስ ያቆሰላቸውን እግዚአብሔርን አይረሱትም፡ “ዳዊት እልፍ ገደለ ሳዖል ግን ሺህ ገደለ” እየተባለላቸው ቤተ መንግስ ሲገቡም ሆነ፡ እያለቀሱ በባዶ እግር የደብረዘይትን ተራራ ሲወጡ ፡ ያኔ ድሮ አቁስሎ ራሱን ያስተማራቸውን እግዚአብሔርን አይረሱትም፡ ለእነርሱ እግዚአብሔር የሕይወታቸው አካል እንጂ የሃይማኖት መግለጫ ወይም የሚሸመደድ ነገረ-መለኮት አይደለም።
#ይቀጥላል
#ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ💒
ወደዚህ ቻናል ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለቴ ብቻ ይንኩ👉 @biruk351
#ሼር_ያድርጉ ❤🙏
#አብርሃምና_ሎጥ
#ሎጥ_መልካምና_ያማረ_የመሰለው_ነገር ላይ የሚጎዘጎዝና የሚሰፍ የሰው አንጎል ሀሳብ ነው፣ የሚያየውን እና የሚሰማውን የሚያምን ፣ውብ ሲሆን ሰላም የሚመስለው ከተበላሸ ጥፋት የሚመስለው የውስጥ አይን እውርነት ነው።
#ሎጥ_ለአዕምሮው_ያልተስማማውና_ የሚቆረቁረው መንገድ ሁሉ ጥፋትና ውድመት የሚመስለው አዕምሮ ነው።
#ሎጥ_ድሎትና_ምቾትን_በማሳደድ የተጠመደ ሀሳብ ነው፣ጎተራ ከሞላ ረሀብ የለም የሚል፣ ጎተራ ባዶ ሲሆን መጥፊያው እንደቀረበ የሚያስብ አዕምሮ ነው፣ ሎጥ ሰው የተገባውን መንፈሳዊ ልዕልና እና ክብር ፣ መንፈሳዊም ግዝፈትና የሚያሳንስ የውርደት ስፍራ ነው። ሎጥነትን የሚከተል ሁሉ ከተሰጠው ክብር ወድቆ ምኞት ስር ይወድቃል።
#አብርሀም_የአማኞች_መንፈሳዊ_ልዕልና_እና ልህቀት ምሳሌ ነው። ለሎጥ ጥፋትና ውድቀት ፣#ውድመት ፣#ውርደትም በምትመስል በበረሀ መንገድ የሚጓዝ ነገር ግን ለህዝቦች መድህን እና መሰብሰቢያ ጥላ ለመሆን የሚዘረጋ ዋርካ ነው።
#ሎጥ_ግን_ያየውን_ምኞቱን_በልቶ_የሚሞት ነው፣ ሎጥ ውስጣዊ አስተውሎት መሰዊያ ካለበት ድንኳን መሰዊያ አልባ አለምን ወደደ: በሰዶም እግዚያአብሔር የለም ነበር ግን ሎጥ የተሸወደው እዚህ ጋር ነው
“ሎጥም ዓይኑን አነሣ፥ በዮርዳኖስ ዙሪያ ያለውንም አገር ሁሉ ውኃ የሞላበት መሆኑን አየ፤ እግዚአብሔር ሰዶምንና ገሞራን ከማጥፋቱ አስቀድሞ እስከ ዞዓር ድረስ እንደ እግዚአብሔር ገነት በግብፅ ምድር አምሳል ነበረ።” ( ዘፍጥረት 13፥10)
👉ሎጥም አይኑን አነሳ የሚለው ሀሳብ ውስጣዊ አይኑ ሰዶምን የተመለከተበት መንገድ ልክ ሔዋን የወደቀችበት መንገድ መሆኑ ይጠቁመናል: ሴቲቱም ለአይን የሚያምር ሆኖ እንዳየችው ልብ ልንል ይገባናል።
👉ሌላው ሎጥ ያላስተዋለው ነገር የተመለከታት ከተማ ከፊቷ እንደ እግዚአብሔር ገነት ከ ጀርባ ግን በ ግብጽ ምድር አምሳል ነበረች ይለናል። ልብ ብለን ካየነው ቃሉ እያለን ያለው እንደ እግዚአብሔር ገነት የሆነውን ገጽታዋን አሳየቺው ግን ሰዶም በ ባርነት ነፍስን ምታከሳ በግብጽ ምድር አምሳል ነበረች: ግብጽን ስናስብ ከ ባርነት ውጪ ከ ጭንቀት የተነሳ የሚጮህ ጩኽት እንጂ ደስታ እንደሌለበት እናውቃለን።
👉ይህች አለም ሁሌ ምታሳይህ እንደ እግዚአብሔር ገነት የሚመስለውን መልኳን ነው ላስተዋለ ግን በ ግብጽ ምድር አምሳል ናት።
👉 በአብርሃም አለም ግን ከ ሰዶም ይልቅ ህይወት በ ከነዓን ይመቻል : ለምን መሰዊያ ሚባል ህይወት አለ : ከ ጥቂቱ ደስታ የሸሸው አብርሃም እግዚአብሔር የመሰረታት ከተማን በ እምነት እየጠበቀ ነበር: እናም በአእምሮ ይኼንኑ እያሰላሰለም ይኖር ነበር የልቡን አይን በሰማያዊ እውነት ላይ ጠምዶት ስጋዊ አእምሮውን ይቆጣጠረው ነበር።
#ይኼ_በኢየሱስ_ስም_በእኛ_ሕይወት_ይሁን
#ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ
ወደዚህ ቻናል ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለቴ ብቻ ይንኩ👉@biruk351
#ለማስታወስ_ያክል..✍
👉የልማድ ኃጢአት በክርስቲያናዊ ሕይወታችን ላይ ምን ተጽዕኖ ያሳድራል?💣
1.ለመንፈሳዊ ነገሮች ስሜት አልባ እንድንኾን ያደርገናል🥱
2.በህይወታችን እግዚአብሔርን እንዳንታመን ያደርገናል😱
3. እግዚአብሔር የሰጠንን ስጦታ እንዳንጠቀም ያደርገናል🤐
4. ለራሳችን ያለንን መልካም እይታ እንድናጣ ያደርገናል🤯
5. የዕለት ሕይወታችንን የምሬት ያደርገዋ😭
6. *,በሰውም በእግዚአብሔርም ፊት ድፍረት እንድናጣ ያደርገናል**🥺
🗣 እና በሁለንተናዊ አምልኮ ላይ ወይም በመንፈሳዊ ነገር ላይ ለዘብተኛ ያደርገናል።
#መፍትሔው
በቤተክርስቲያን እየተረሳ የመጣዉ አንዱ መሰረታዊዉ ትምህርት :- #ንስሃ_ነው።
ንስሃ የማትገባ ቤተክርስቲያን እየሞተች ያለች ወይም የሞተች ነች !: ንስሐ ስንል ዝም ብሎ የመነፋረቅና ራስን የመርገሚያ ልምምድ አልፎም ሀይማኖታዊ ስርዓት ሳይሆን ሕይወት ለዋጭ የንስሐ መንገዶችን ነው።
ንስሃ በዉስጡ ስድስት መሰረታዊ ነገሮችን ይዟል
1) #ዉድቀትን ( #ሃጢአትን ) ማየት መመልከት ( its not generic rather its specific )
2) #ስለዛ ሀጢአት** (#ዉድቀት_ማዘን
3) #ስለዛ_ሀጢአቱ_መናዘዝ
4) #ስለዛ_ሃጢአት_ማፈር
5) #ያንን_ሃጢአትን_መጥላት
6) #ከሃጢአት_መመለስ / የአቅጣጫ ለዉጥ ማድረግ
' ሜታኖያ' የሚለዉ የግሪክ ቃል የአቅጣጫ እና የኑሮ ዘይቤን መለወጥ ተብሎ ተተርጎሟል!! : ይኼውም በአእምሮ መታደስ በመለወጥ በይበልጥ ራስን በክርስቶስ በመረዳት ወደ ፀጋው ዙፋን በየዕለቱ የመቅረብ ሕይወት ነው
“#እንግዲህ_ንስሐ_ግባ፤ አለዚያ ፈጥኜ እመጣብሃለሁ ” (ራእይ 2፥16
ለኃጢያት የሞተን እኛ በፅድቅ ለመመላለስ እግዚአብሔርም ፀጋውን ያብዛልን 🙏
#ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ
ወደ ቻናላችን ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለት ጊዜ ብቻ ይንኩ👉@biruk351
#ሼር_ስለሚያደርጉ_እናመሰግናለን ❤🙏
#እምቢ_በል
በክርስቶስ መሆን ማለት ሞኝ መሆን ማለት አይደለም: በክርስቶስ መሆን ማለት አላፊ አግዳሚው ሁሉ እየቀጠፈ እንደሚበላው የሽምብራ እሸት ማሳ መሆን ማለት አይደለም: በክርስቶስ መሆን ማለት አዲስ ስብእና ወይም ማንነትን ማግኘት ማለት ነው እንጂ ለሰዎች የመለማመጃ የስእል ደብተር መሆን ማለት አይደለም::
በሕይወትህ "#እምቢዬው" የምትለው ነገር ከሌለህ ሰዎች ዛሬ የስሙኒ፣ ነገ የአምሳ ሳንቲም፣ ከዛም የሰባ አምስት ሳንቲም እየቆነጠሩህ ይጨርሱሃል: ለራስህም ለእግዚአብሔርም ሳትሆን እድሜህ ያልቃል።
ከግብ መድረስ ከፈለግህ እምቢዬው ማለትን ልመድ:
እምቢ ማለት የምትፈልግ ከሆነና እምቢ የማለት አቅሙ ካለህ በሕይወት መንገድ ከተማርኳቸው እምቢዬዎቼ ውስጥ ጥቂቶቹን ላካፍልህ:
፩
ሰዎች ራሳቸው ቀደውህና ሰፍተውህ ቅርፅ እንዲያበጁልህ አትፍቀድላቸው እምቢ በል!
፪
ሰዎች በእነርሱ ዛቢያ እንድትሽከረከር ሊያደርጉህ ሲፈልጉ ለስበታቸው ሕግ አትገዛ እምቢ በል!
፫
ሰዎች የሆነ ነገር እንደጎደለህና ያ የጎደለህ የሚመስልህን ነገር ከእነርሱ ብቻ እንደምታገኘው የሚያደርግ ስሜት ሊፈጥሩብህ ሲፈልጉ ደጅ አትጥናቸው - #እምቢ_በል!
፬
ሰዎች እነርሱ ወደሚፈልጉት የሆነ ቦታ መስፈንጠሪያ ወይም መረማመጃ ሊያደርጉህ ሲፈልጉ አትመቻቸው #እምቢ_በል!
፭
ሰዎች በጏደኝነት ስም የራሳቸውን አሳብና አመለካከት ብቻ ሊጭኑብህ ሲከጅሉ በርህን ዝጋ - #እምቢ_በል!
፮
ሰዎች በየትኛውም መልኩ የበታች ሊያደርጉህ ሲፈልጉ በጄ አትበላቸው - #እምቢ_በል!
፯
ሰዎች በክርስቶስ የመሆንህን እውነት እንደ ማጥቂያ መሳሪያ ሊጠቀሙበት ሲፈልጉ አትፍቀድላቸው - #እምቢ_በል!
፰
ሰዎች በክርስቶስ ካለህ ማንነት ያነሰ ትርጉም ሊሰጡህና ሊያራክሱህ ሲፈልጉ ቦታ አትስጣቸው - #እምቢ_በል!
፱
ሰዎች አንተን እንደ ተሳቢ ራሳቸውን ደግሞ ወደፈለጉት እንደሚነዱት እንደ ሳቢ መኪና አድርገው ሊያሳዩህ ከፈለጉ አትስማማ - #እምቢ_በል!
፲
ሰዎች ፍቅርና እርስ በርስ መከባበር የሌለበት ቀጠና ውስጥ ሊከቱህ ሲጎትትሁ አትጎተትላቸው - #እምቢ_በል!
፲፩
ሰዎች ባለህ መረዳትና አመለካከት ሊያሸማቅቁህ ከከጀሉ ስፍራህን አትልቀቅ - #እምቢ_በል!
፲፪
ሰዎች ከሳሎንህና ከእቃ ቤትህ አልፈው በመኝታ ቤትህም ሳይቀር እጃቸውን ሊያሳርፉ ከፈለጉ "#እዛው_በጠበላችሁ_በላቸው - #እምቢ_በል!
፲፫
ሰዎች በአንድ ቀን ስህተትህ እድሜህን ሙሉ ሊቆምሩብህ ካማራቸው ፈፅሞ የእግር መቆሚያ አትስጣቸው #እምቢ_በል!
እነዚህን ሁለት እውነቶች ግን በልብህ አስቀምጥ: ለሰው ኑር በሰው ግን አትኑር: ሰውን ሁሉ ያለ አድልዎ ውደድ አክብር!: (ምንጭ ከፌስቡክ ገፅ)
#ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ
ወደ ቻናላችን ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለቴ ብቻ ይንኩ 👉@biruk351
#ሼር_ስለሚያደርጉ_እናመሰግናለን 🙏❤
ቅርስ ጠባቂም አስጠባቂም ብቻ መሆን እንዴት ይሰለቻል!
"#ሃይማኖት" የቱንም ያህል እድሜው ቢረዝም ምንም አያመጣም!፣ ናፍጣና ቤንዚል የሌለው መኪና ምን መልኩ ቢያምር ፣ ምንም በአይነቱ ጠንካራ ቢሆንም ፣ በዕውቅ ሰዎች የተዋቀረ ቢሆንም በቃ አይሄድም! 😥
ለዚህ አይመስላችሁም ወደ ፊት ከመሄድ ይልቅ ባለህበት ቁም እንደሚል ወታደራዊ ትዕዛዝ ቆመን ያለነው? 😥
የጓደለን ጥቅስ አይደለም! አለም ከጥቅስ በስተቀር ምንም እንደሌለን ክፍተታችን እስክታይ እንደምን እንዲህ ሳትን?😥 የጎደለን ጥቅስ አይደለም የጥቅሱ ባለቤት መንፈሱ እንጂ😥
ክርክር ትችት መከፋፈል መከፋፋት አይደለም የጎደለን - የእግዚአብሔር ጥበብና ኅይል የሆነው ክርስቶስ እንጂ: የጎደለን ስብከትም ዝማሬም ህንፃም የተማሩ ሰዎችም አይደሉም - አላዛርን ጎትቶ የሚያወጣው ክርስቶስ እንጂ:
ቤተክርስቲያን ያለክርስቶስ በዶክትሪንና በዶግማ ብርድልብስ ተሸፋፍና ረጅም አመታትን መቆየት ትችላለች: ይሄ ደግሞ በታሪክ የተረጋገጠ ነው::
ቤተክርስቲያን ሌላ ዶግማና ዶክትሪን ሳይሆን የሚያስፈልጋት የሕይወት ምንጭ የሆነው ክርስቶስ ነው: አለም ብቻ ሳይሆን ቤተክርስቲያንም ጭምር የክርስቶስ ሕይወት በሙላት ተገልጦ ለማየት ርሃብተኛ ናት😥
ዶሮ ወጥ ምን ምን እንደሚሸት ማወቅ ዶሮ ወጥን መብላት አይደለም::
የሰው ልጅ ሆይ በውኑ እነዚህ አጥንቶች በሕይወት ይኖራሉን?
#ጌታ_ሆይ_አንተ_ታውቃለህ::
ወደ ቻናላችን ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለት ጊዜ ብቻ ይንኩ👉@biruk351
#የቤተክርስቲያን_የእኔ_የአንቺ_ሀላፊነት
በዘጸአት መጽሐፍ ውስጥ አንድ አጭር ነገር ግን ብዙ እንድናስብ የሚያደርገን ታሪክ አለ፡
እስራኤል ከግብጽ ወጥቶ በምድረበዳ እያለ አማሌቅ ሊወጋው ይመጣል፡ በዚህ ጊዜ ሙሴ ኢያሱን ጎልማሶች መርጦ ውጊያ እንዲገጥም ያዝዘዋል፡ ኢያሱም ጎልማሶችን ይመርጥና ከአማሌቅ ጋር ለመዋጋት ይወጣል፡ በውጊያው መካከል ሙሴ “የእግዚአብሔርን በትር በእጄ ይዤ በኮረብታው ራስ ላይ እቆማለሁ” ብሎ ነግሮት ነበር።
ነገር ግን የጦርነቱ እጣ ፈንታ፣ ወይም አሸናፊውና ተሸናፊው የሚወሰነው በሙሴ እጅ መዘርጋት ወይም መታጠፍ ነበር፡ ክፍሉ እንዲህ ይላል፤
“ሙሴ እጁን ባነሳ ጊዜ እስራኤል ድል ያደርግ ነበር፣ እጁንም ባወረደ ጊዜ አማሌቅ ድል ያደርግ ነበር”
የእስራኤል ማሸነፍና የአማሌቅ መሸነፍ ከሙሴ እጅ ጋር ምን አገናኘው?
ሙሴ ሰው ነውና የቱንም ያህል እስራኤል እንዲያሸንፍ እጁን ቢዘረጋም ይደክመው ነበር፡ ስለዚህም እጁ ዝሎ ሲወርድ የአማሌቅ ጦር ያሸንፍ ነበር፡ ይህንን የተረዱ አሮንና ሖር ሙሴን ድንጋይ ላይ እንዲቀመጥ ያደርጉትና በግራና በቀኝ ሆነው እጆቹን ይደግፉ ነበር፡ ከዚህም የተነሳ “ፀሐይም እስክትገባ ድረስ እጆቹ ጠነከሩ” #እንዲሁም_አማሌቅ_ተመታ።
እግዚአብሔር ሕዝቡን በሙሴ አማካኝነት ከግብጽ ሲያወጣ ጠላቶቻቸውን ሁሉ እንደሚመታላቸው ቃል ገብቶላቸው አልነበረምን?: የሚያሸንፍላቸው እርሱ አልነበረምን?: አሁን እንዴት ነው የእስራኤል የማሸነፍና የመሸነፍ እጣ ፈንታ በሙሴ እጅ ሊወሠን የቻለው?
ምንም እንኳን እግዚአብሔር ለሕዝቡ ያለው ሐሳብ ማሸነፍ ቢሆንም የሚያሸንፉት ግን ሙሴ እጁን ሳይደክም ቀጥ አድርጎ እስከዘረጋ ድረስ ነው ማለት ነው?: እግዚአብሔር የእስራኤል ሕዝብ እንዲያሸንፍ የሙሴን እጅ ቀጥ ብሎ መዘርጋት ይፈልግ ነበር ማለት ነውን?: ሙሴ እጁን ቀጥ አድርጎ ባይዘረጋ ኖሮ የእስራኤል ሕዝብ ያንን ጦርነት በአሸናፊነት አይወጣም ነበር ማለት ነውን?
እነዚህ ሁሉ ጥያቄዎች መልሳቸው አዎ! ነው፡ ምንም እንኳን እግዚአብሔር የእስራኤል ሕዝብ እንዲያሸንፍ ፈቃዱና ሐሳቡ ቢሆንም የእስራኤል ማሸነፍ ግን ከሙሴ እጅ “#position_ጋር_የተቆራኘ_ነበር"፡ በዚህ ተግባር ብቻ ነው በእግዚአብሔር እቅድ ውስጥ ተሳታፊና የእግዚአብሔርን እቅድ አስፈጻሚ መሆን የሚችለው።
ይሄ ክፍል ምን ያህል “#ሙሴ” በእግዚአብሔር ፕሮግራም ውስጥ ድርሻ እንዳለው ነው የሚያሳየን፡ የእግዚአብሔር ሐሳብ ለሕዝቡ የማሸነፍ ቢሆንም በዛ ማሸነፍ ውስጥ “#የሙሴ_እጅ” ድርሻ ነበራት፡ እግዚአብሔር እስራኤል እንዲያሸንፍ ፍላጎቱም እቅዱም ቢሆን ነገር ግን ያንን እውነት “#ከሙሴ” ጋር ነው ተግባራዊ ማድረግ የሚችለው፡ ይህንን ክፍል ምንም ሳንቀባባው ከተረዳነው በጊዜው እግዚአብሔር ለእስራኤል ሕዝብ የነበረው እቅድ ተፈጻሚነት የሚያገኘው ሙሴ ከሚወስደው እርምጃ አኳያ ነው፡ የእስራኤል ሕዝብ ጦርነቱን እንዲያሸንፍ ከፈለገ የቱንም ያህል እጁን ቢደክመው ከእግዚአብሔር ጋር ነው መወገን ያለበት፡ “#አቦ_ደክሞኛል_የራሱ_ጉዳይ” ማለት አይችልም፡ ሙሴ በእግዚአብሔር እቅድ የነበረ ሰው ብቻ ሳይሆን የእግዚአብሔር እቅድ ተግባራዊ ይሆን ዘንድም ድርሻ የነበረው ሰው ነው፡ ከእግዚአብሔር ጋር ይሰራ ዘንድ የተጠራ ሰው ነው!
ጳውሎስስ ቢሆን “#ከእርሱ_ጋር_አብረን ሰራተኞች ነን አይደል የሚለው፡
ምናልባት ዘንድሮ ቤተክርስቲያን “#የሙሴ_እጅ” ትሆን ይሆን?
#አንድ_ጊዜ_Philip_Yancey_እንዲህ_አሉ፤
“ብዙ ሰው እግዚአብሔር ምን አያደረገ ነው?’ እያለ ሺህ ጊዜ ይጠይቃል፤ ትክክለኛው ጥያቄ መሆን ያለበት ግን ቤተክርስቲያን ምን እያደረገች ነው?’ የሚለው ነው”
#እውነታቸውን_ነው! ቤተክርስቲያን እንደ ሙሴ እጅ ናት፡ አሁን እዚህ ያለችው በእግዚአብሔር እቅድ ውስጥ ስላለች ብቻ ሳይሆን በውክልና የእግዚአብሔርን እቅድ ለማስፈጸምም ነው፡ በእግዚአብሔር እቅድ አስፈጻሚነት ውስጥ ወሳኝ ድርሻ አላት፡ በቃ እግዚአብሔር እንዲህ ሊያደርግና እንዲህ ሊሰራ ወድዶአል፡ ምንም እንኳን ጴጥሮስ ከእስር ቤት እንዲፈታ ፈቃዱ ቢሆንም ቤተክርስቲያን ግን ስለ እርሱ አጥብቃ መጸለይ ነበረባት፡ ቤተክርስቲያን በእግዚአብሔር ሐሳብ እስከተቃኘች ድረስ በእግዚአብሔር እቅድ ውስጥ ድርሻ አላት፡ በዚህ የጨለማ አለም ውስጥ ለጌጥ ሳይሆን ያስቀመጣት የእቅዱ መፈጸሚያም ማስፈጸሚያም ፈጻሚም ትሆን ዘንድ ነው።
ቤተክርስቲያንን ከግሮሰሪ ወይም ግለሰብ ከሚያስተዳድረው አንድ ድርጅት ለይተንና እንደ ክርስቶስ አካል እንዲሁም እንደ እግዚአብሔር ልዑክ የምናስባት ከሆነ ምን ያህል ክቡር እንደሆነች ብቻ ሳይሆን የእግዚአብሔር ፈቃድ ለማስፈጸም ምን ያህል ከፍተኛ ሃላፊነት እንዳለባት እንረዳለን፡ ቤተክርስቲያን የእግዚአብሔር ብቻ ሳትሆን የእቅዱ አስፈጻሚም ናት፡ ቤተክርስቲያን እንደ ሙሴ እጅ ናት፡ የሚከፈለውን ዋጋ በመክፈል “#እጇን” ቀጥ አድርጋ እስከዘረጋች ድረስ የእግዚአብሔር ሐሳብ ተፈጻሚነት ያገኛል፡ ይሄንን ማድረግ ረስታና አንዳንዴም ራሷ ለራሷ በምትሰጠው፤ ሌላ ጊዜ ደግሞ ዓለም በምትሰጣት እግዚአብሔር የለሽ አጀንዳ የምትወሰድ ከሆነ እቅድ አስፈጻሚ አለመሆን ብቻ ሳይሆን ከእቅድ ሁሉ ልትወጣ ትችላለች።(ምንጭ አንድ ወዳጄ)
ወደ ቻናላችን ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለቴ ብቻ ይንኩ 👉 @biruk351
እኔ በክርስቶስ ማነኝ? : የምትለውን ጥያቄ በእውነት ቃል በኩል ማወቅና ማመን "ብዙ መፅሀፍት ከማንበብ ፣ ብዙ አካዳሚካል እውቀት ከመማር ፣ ስለ ብዙ ነገር ኢንፎርሜሽን ከማወቅ እና ብዙ የተቀደሱ መንፈሳዊ ስራን ከመስራት ትበልጣለች!!! ማነኝ ብለህ ባወከው ልክ እምነትህን በሕይወት ትገልጣለህ
#ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ
ወደ ቻናላችን ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለት ጊዜ ብቻ ይንኩ 👉@biruk351
#ሼር_ያድርጉ_ተባርካችኋል 🙏❤
የውሃን ያህል ውስጣችንን በኃይል የጠማው tradition ሳይሆን a new spritual dimension ነው። አለበለዚያማ ያው የለመድነው ስርዓታችንን እየፈፀምን "መታኛታችን አይደል? : እንደ እንቅልፍ እያዳካከመን እያሸለበን አይደለምን?
ደማስቆ ለጳውሎስ ብቻ ሳይሆን ለሁላችንም ይሁን 😥
#ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ
ወደ ቻናላችን ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለቴ ብቻ ይንኩ👉@biruk351
ከጅማ ቪዥነሪ አብያተክርስቲያናት ጋር በመተባበር የተዘጋጀ ኮንፍረንስ መተው ፀጋን ይካፈሉ፣ አድራሻ ኪቶ ስታዲየሙ አጠገብ / በፀሎት ቤቴ ደስ አሰኛችኋለው ያለው ጌታ የታመነ ነው 🔥
#ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ
ሼር ያድርጉ🙏
ወደ ቻናላችን ለመቀላቀል ይኼን ሊንክ ሁለቴ ብቻ ይንኩ 👉@biruk351
#ቃሉን_ይዘን_ከስሜታችን_እንውጣ
እኛ የእግዚአብሔር ቃል እንደሚለን ነን እንጂ ስሜታችንና ሁኔታችን እንደሚነግሩን አይደለንም: ስለዚህ ስሜታችንንና ሁኔታችንን ሳይሆን ቃሉን እንዘምር ቃሉን እንስበክ ቃሉን እንፀልይ:
#እግዚአብሔር_እንደ_ቃሉ_ብቻ_ነው::
ለምንድን ነው ግን ብዙ ስብከቶቻችን፣ #ዝማሬዎቻችንና_ፀሎቶቻችን_ስሜታችንንና ሁኔታችንን እንጂ ቃሉን ያገናዘቡ ያልሆኑት?
#ቃሉን_ነው_የምናምነው_ወይስ_ስሜታችንን?
እግዚአብሔር በክርስቶስ በኩል ኅጢአታችንን ካስወገደና ከራሱ ጋር ካስታረቀን፣
ከማስታረቅም አልፎ "#አባ_አባ" የሚል መንፈስ ሰጥቶ ልጆቹ ካደረገን፣
አርሱ ራሱ አልተውህም አልጥልህም ካለንና "#አዲስ_ኪዳን_ከገባልን"፣
በሞት ላይ ስልጣን ያለውን ዲያቢሎስን በኢየሱስ ሞት ከሻረልን፣
ከእግዚአብሔር ጋር ጠላቶች ሳንሆን በክርስቶስ በኩል ወራሽ ከሆንን፣
በክርስቶስ በኩል ጥበብ ፅድቅ ቅድስናና ቤዛነት ከተደረገልን፣
ኢየሱስ ስለ እኛ "#ተፈፀመ" ካለልን ፣
በክርስቶስ በኩል በሰማያዊ ስፍራ ከተቀመጥን፣
እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ከሆነነና ማንም የሚከሰን ከሌለ፣
ከሙላቱ ከተቀበልን፣
ለምንድን ነው እነዚህ ክቡር የሆኑ የወንጌል እውነቶች ላይ ፀንተን የማንቆመው? ለምንድን ነው ከእነዚህ እውነቶች ይልቅ ስሜታችንን የምናምነው? ለምንድን ነው አሁን ድረስ ፀሎታችን "#አስበኝ" ስብከታችን "ይሰብርልሻል" ዝማሬአችን ደግሞ "#አድቅቅልኝ ስበርልኝ ክፈትልኝ" የሆኑት?
ቃሉን ነው የምናምነው ወይስ ስሜታችንን?:ልጆች ነን ወይስ ባሮች?
እግዚአብሔር በክርስቶስ ጨለማችንን አላበራውም እንዴ?
ከድቅድቅ ጨለማ ወደሚደነቅ ብርሃን አላመጣንም እንዴ?
ልጁን እስከመስቀል ሞት አሳልፎ በመስጠት ታላቅ ፍቅሩን አልገለፀልንም እንዴ?
ሳንለምነው የሚያስፈልገንን እንደሚያውቅ አልነገረንም እንዴ?
ልመናችሁን አስታውቁ እንጂ አትጨነቁ አልተባልንም እንዴ?
እስከ ዓለም ፍፃሜ ከእኛ ጋር እንደሚሆን ቃል አልገባልንም እንዴ?
በስሙ ስንሰበሰብ በመካከላችን እንደሚገኝስ አላሳሰበንም እንዴ?
ታዲያ ለምንድን ነው ዛሬ ድረስ ፀሎታችን "ጌታ ሆይ ና" እና "ጌታ ሆይ አስበኝ" የሆነው?
በመንፈሱ ውስጣችን አይደል እንዴ ያለው?: በመስቀል ላይ አላሰበንም እንዴ?: ነው ወይስ መስቀሉ ለመታሰብ ብቁ አይደለም?
ለምንድን ነው ከእግዚአብሔር ቃል ይልቅ ስሜታችንን ወይም ሁኔታችንን የምናምነው? ለምንድ ነው ቃሉ የሚለውን ተቀብለንና በቃሉ እውነት ላይ ቆመን ከማመስገን ይልቅ ማልቀስ፣ ማዘንና፣ ማጉረምረም፣ እኔን ትቶኛል፣ አያስበኝም፣ እኔ ልጁ አይደለሁም፣ ውስጥ የምንገባው?
እውነት ከመስቀሉ አለመታሰብንና መረሳትን ነው የምንማረውን?
እስራኤላውያን እንዲህ አይደለምን የሆኑት? :በተስፋ ቃል ከግብፅ ወጥተው ከነዓን እንደሚገቡም በመሃላ ተነግሮአቸው ነገር ግን ከተነገራቸው ከእግዚአብሔር ቃል ይልቅ ስሜታቸውንና ሁኔታቸውን ከማመናቸው የተነሳ ከእግዚአብሔር ጋር እኩል መሄድ ሳይችሉ ቀሩ::
ከምድረ በዳው ከኢያሪኮና ከዮርዳኖስ ወንዝ በላይ ቃል የገባላቸው እግዚአብሔር አቅም የለውምን?: እነርሱን ከነዓን ለማስገባትስ አይችልምን? ይችላል! : ችግሩ ግን ከቃሉ ይልቅ ስሜታቸው ላይ መንጠልጠላቸው ጎዳቸው: ስሜት ደግሞ የሚዋዥቅ ወይም የሚዋልል ጉዳይ እንጂ አስተማማኝ አይደለም::
ስሜታችንና ሁኔታችን ምንም ቢሉን የእግዚአብሔር ቃል እውነትና የፀና ነው: ፀሎታችንም ዝማሬአችንም ስብከታችንም የእግዚአብሔር ቃል ላይ ተደላድለው ያረፉ እንጂ ስሜታችንንና ሁኔታችን ላይ ችክ ያሉ መሆን የለባቸውም::
አንተ የእግዚአብሔር ቃል እንደሚልህ ነህ እንጂ ስሜትህና ሁኔታህ እንደሚነግሩህ አይደለህም: ስለዚህ ስሜትህንና ሁኔታህን ሳይሆን ቃሉን ዘምር ስበክ ፀልይ::
በአዲስ ኪዳን እንደ ብሉይ ኪዳን አንኑር: በእኛና በእግዚአብሔር መካከል እግዚአብሔር ስለኛ ላይተወንና ላይረሳን የማለበት ክርስቶስ መኖሩን አንዘንጋ::
እንዲሁም የምናነበው ቃል በእምነት ከእኛ ጋር ካልተዋሃደ ምንም እንደማይጠቅመን አንዘንጋ: ቃሉን ማንበብ ብቻ ሳይሆን ቃሉን ማመንና በቃሉ መቆምም ይብዛልን::
ቃሉን ይዘን ከምናጉረመርም ቃሉ ላይ ቆመን እናመስግን::
#ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ
ወደ ቻናላችን ለመቀላቀል ይኼን ሊንክ ሁለቴ ብቻ ይንኩ👉 @biruk351
#ዛሬም_በሕያውነትህ_አትነካንምን_? 😥
ዛሬም እቅፍ ውስጥ አታንሸራሽረምን? አቤቱ በአንተ የምንደገፍ ያለ አንተ ባዶ መሆናችንን ታውቃለህና በመንፈስህ ሙላን 😥😥😥 #ንካን_ንካን 😥
ዮሐንስ በጉልበቱ የጣለውን ክብር እንዴት ይረሳል?
ጳውሎስስ በመሬት ላይ ወድቆ "ጌታ ሆይ አንተ ማን ነህ ምንስ አደርግ ዘንድ ትወዳለህ?" ያስባለውን ክብር እንዴት ይረሳል?
ያዕቆብ ሹዳውን ነክቶበት እያነከሰ "ሰውነቴ ድና ቀረች" ያስባለውን ያህዌህን እንዴት ይረሳል?
ያነበበውን አንድ ሚልየን መፅሐፍ ከሚነግርህ ሰው ይልቅ በሕይወቱ ለአንድ ደቂቃ በጉልበቱ የጣለውን የእግዚአብሔርን ክብር የሚነግርህ ሰው ያንፅሃል:: እግዚአብሔር ስለ መፅሐፍ ቅዱስ ይባረክ🙏 መፅሐፍ ቅዱስ እግዚአብሔር እንደሚገለጥ ፣ እንደሚነካ፣ እንደሚጠራ ፣ እንደሚያናግር መመሪያም ነው እንጂ እንዳቆመ መማሪያ አይደለም!!!
እግዚአብሔር በሁሉ ነገራችን ተስፋ ያስቆርጠንና ክብሩን ብቻ እንድንናፍቅና እንድንፈልግ ያድርገን: ያኔ ብቻ ከስማ በለውና ሕይወትና ኃይል ከሌለበት ከልማዳዊ የተብሎ ተፅፎአል ሕይወት ነፃ እንወጣለን::
Without the power of God Christianity is only a philosophy.
#ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ
ወደዚህ ቻናል ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለቴ ብቻ ይንኩ👉@biruk351
ጌታ ሆይ የምትወዳት አላዓዛር (#ቤተክርስቲያንህ) ታማለች 😥 ሕያውነታችንን በሙቱ አለም ላይ አታጎላውምን?😥
አላዛርን የሚወዱት እህቶቹና ጎረቤቶቹም ከሞት ሊያስመልጡት አልቻሉም: ምንም እንኳን ቢወዱትና ከመቃብሩ ደጅ ሆነው ቢንጫጩም አላዛር የአንዳቸውንም ድምፅ መስማት አይችልም: አንድ ድምፅን ግን አለመስማት አይችልም - የክርስቶስን::
ክርስቶስ "አላዛር ሆይ ወደ ውጭ ና" ብሎ ሲጮህ አላዛር ለዚህ ድምፅ "ጆሮ ዳባ ልበስ" ማለት አይችልም: ሳይወድ በግዱ ይሰማል: መስማት ብቻ አይደለም ከመቃብሩ ይወጣል::
ይሄ የክርስቶስ ድምፅ የነፍስ ሁሉ ተስፋና ስውር ረሃብ ነው: ቤተክርስቲያን ደግሞ የዚህ ድምፅ አስተጋቢ Megaphone ናት: ይሄ ድምፅ ከቤተክርስቲያን ሲጠፋ አላዛር የማይሰማቸው ደግሞም ሊሰማቸው የማይችላቸው የነብሩክ ድምፅ ይበረክታሉ: በነብሩክና አይነቶቹ ድምፅ ደግሞ ማንም ከመቃብሩ ዘሎ አይወጣም: እንደውም ሞቱ ይመቸዋል😥::
የክርስቶስ ድምፅ መገለጫ ወይም ማስተጋቢያ ከሆነችው ቤተክርስቲያን ውስጥ የክርስቶስ ድምፅ ሲጠፋ የሰው ወግና የሰው ድምፅ ይነግሳል: ነገር ግን ሕይወት የሌለው ወግና ጫጫታ ነው: በመንጫጫት ሳይሆን ለክርስቶስ ድምፅ ቦታ በመስጠትና የክርስቶስ ድምፅ ማስተጋቢያ በመሆን ብቻ ነው ቤተክርስቲያን በሙታን አለም ውስጥ የእግዚአብሔር ደውል መሆን የምትችለው::
ከክርስቶስ ድምፅ የተለየች ቤተክርስቲያን እንኳን የሞተን ልትቀሰቅስ አይደለም እርሷ ራሷ እንደ ሎዶቂያ ቤተክርስቲያን ስም እያላት የሞተች ልትሆን ትችላለች::
ቤተክርስቲያን የክርስቶስ ድምፅ መገለጫ እንጂ የማሪያምና ማርታ እንዲሁም የሰፈር ሰዎች ሁሉ የሚንጫጩባት ቦታ አይደለችም: የቤተክርስቲያን ውበቷም ሆነ ተሰሚነቷ የክርስቶስ ድምፅ መገለጫ መሆኗ ብቻ ነው: ከዚህ ድምፅ ውጭ የተውኔት ቤት ብቻ የመሆን እድል ነው ያላት::
ከዚህ ድምፅ ውጭ የነብሩክ ድምፅ ብቻ ነው ጎልቶ የሚሰማው: ይሄ ድምፅ ደግሞ የክርስቶስን ድምፅ ከማቀጨጭ ውጭ ምንም አስተዎፆ የለውም:😥
በቤተክርስቲያን ውስጥ የእግዚአብሔር ድምፅ የሆነው ክርስቶስ ሲናገር ይሰማ ዘንድ ከመቃብሩ ደጅ የሚንጫጩት ሌሎች ድምፆች ሁሉ ፀጥ ማለት አለባቸው - says the Lord.
ሰው ፀጥ ያለውን ያህል ነው በቤተክርስቲያን ውስጥ ክርስቶስ የሚሰማው!::
በቤተክርስቲያን ውስጥ ሰዎች የክርስቶስን ድምፅ መስማት ካልቻሉና ብዙ "ነፍሶች" ከመቃብራቸው ካልወጡ ከክርስቶስ ድምፅ ይልቅ የብሩክ ድምፅ ስለጎላ ነው - ቀባሪዎቹ ስለሚንጫጩ ነው::😥
አላዛር በክርስቶስ ድምፅ እንጂ በቀባሪዎቹ ጫጫታ አይነቃምና ከቀባሪዎቹ ጫጫታ ይልቅ ሕይወት የሚሰጥ የክርስቶስ ድምፅ ይብዛልን🙏
ወደ ቻናላችን ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለቴ ብቻ ይንኩ👉@biruk351
ዛሬም ልክ እንደ አቻምናው ልባችን የእግዚአብሔር ይሁን😪
እግዚአብሔር ለሰለሞን ብዙ አድርጎለታል፡ በአባቱ ዙፋን ላይ አስቀምጦታል፣ አባቱ እንዳይሰራ የተከለከለውን የእግዚአብሔርን ቤት እንዲሰራ ፈቅዶለታል፣ #በጥበብ፣ #በማስተዋል፣ #ብሩም_እንደ_ድንጋይ_እስኪሆን_ድረስ #በሃብት_ባርኮታል፣ በተጨማሪም ከጦርነት ሁሉ አሳርፎ ሰላማዊ መንግስትን ሰጥቶት ነበር።
ሰለሞን ግን በአባቱ “ሽበቱን በደም ወደ መቃብር ሸኘው” በሚል የበቀል ምክር የጦር አለቃውን ኢዮአብን (ምንም እንኳን ሸሽቶ የመሰዊያውን ቀንድ ቢይዝም) ገደለው፤ በማስከተል የገዛ ወንድሙ አዶንያስን ገደለ፣ አብያታርን ከክህነት አባረረ፣ ሳሚን በማይረባ ምክንያትና ለአባቱ በመበቀል መንፈስ ገደለው።
ከሁሉ ከሁሉ የሚያሳዝነው ግን እግዚአብሔር ይህን ሁሉ አልፎትና መቅደሱን እንዲሰራ እድል ሰጥቶት ሳለ ሰለሞን ግን አንዴ የሳተባትና ያገባት የፈርዖን ልጅ ሳታንሰው በሞዓባውያንና፣ በአሞናውያን፣ በኤዶማውያንም፣ በሲዶናውያንና በኬጢያውያን ሴቶች ፍቅር ተነደፈ፤ #ከእነርሱም_ጋር_በፍቅር_ተጣበቀ።
#ተነደፈ #ተጣበቀ
አደገኛ ቃላቶች ናቸው::
ጉዳዩ ቀላል አለመሆኑንና ምን ያህል ስር እንደ ሰደደ ነው የሚነግሩን - ሰለሞን በቀላሉ እንዳይነቀል ሆኖ ነበር ስር የሰደደው፣ ለዛም ነው ከዛ በኋላ እንኳን በሚስቶችና በቁባቶች የተከበበው: ልቡን ሰረቁትና ንቦች ንግስት ንብን እንደሚከቡት እንግዶች ንጉስ ሰለሞንን ከበቡት - ሽበትም ወጣበት አላወቀም ጉልበቱንም በልተው አደከሙት::
መነደፍም መጣበቅም የሚገባው ከያህዌህ ጋር ነበር፣ ነገር ግን የእንግዳ ሴት ልጆች ፍጻሜው እንዳያምር አደረጉት።
ዋናውን ወስደውበት ከዋናው ለያዩት: ልቡን በመስረቅ ከባልቦላው አጠፉት::
ከእግዚአብሔር ጋር ብቻ ይጣበቅ ዘንድ የሚገባውን ልቡን ሰረቁበት።
ሲጀምርም የቃል ኪዳኑ አምላክ ያህዌህ ከእንደዚህ አይነት ሰዎች ጋር አትግጠሙ ያላቸው ለዚሁ ልብን የማነውለልና የመስረቅ አቅማቸው ነበር፡
ያህዌህ ይህን ሕዝብ ስለሚጠላው አልነበረም ከእነርሱ ጋር አትግጠሙ ያላቸው ልባቸውን ስለሚሰርቁባቸው እንጂ፤ ለእግዚአብሔር ብቻ ሊሰጡት ከሚገባቸው አምልኮ አንሸራተው ስለሚጥሏቸው እንጂ፡ ሰለሞን ተንሸራተተ፤ መመለሻም አልነበረውም፡
ፀሃፊው፣ ሰለሞን በእንግዳ ሴቶች ተነደፈ ተጣበቀ ብቻ ብሎ ሳይሆን የሚነግረን ጨምሮ ሌሎችን አማልክት ይከተል ዘንድ ልቡን #አዘነበሉት ይለናል: ታዲያ ሰለሞን አያሳዝንም!!
በእንግዳ ሴቶች አማካኝነት እንግዶች አማልክትን እንዲያመልክ ተጠመደ: “አምላክን” አይደለም የሚለው “አማልክቶችን” እንጂ - አስታሮትን ሚልኮምን - #ተከተለ: በሚያሳዝን መልኩ ለካሞሽና ለሞሎክ መስገጃን #ሰራ: ይህን ለእንግዶች አማልክት የሚሆን መሰዊያ የት እንደሰራ ማሰቡ ደግሞ ሌላ ራስ ምታት ነው: ፀሃፊው እንዲህ ብሎ ይነግረናል:-
"በኢየሩሳሌም ፊት ለፊት ባለው ተራራ ላይ"
የያህዌህን መቅደስ በገነባበት ኢየሩሳሌም ከተማ ፊት ለፊት ለባእድ አማልክት መሰዊያን ሰራ::
ፍፃሜዬን አሳምረው ማለት እንዲህ አይነቱ ላይ ነው😪::
ሰለሞን እንዴት ነው ለያህዌህ ቤተ መቅደስ መታነፅ ያወጣውን ያንን ሁሉ የገንዘብና የሰው ኃይል ፈፅሞ ሊረሳው የቻለው?: እንዴት ነው ቤተ መቅደሱ ታንፆ ባለቀ ጊዜ ተንበርክኮና እጁን ወደ ሰማይ አንስቶ የፀለየውን ፀሎት የረሳው? : እንዴት ነው ከወረደው ክብር የተነሳ ካህናት ማገልገል እስኪሳናቸው ያደረሳቸውን ክስተት አንጠፍጥፎ ከአዕምሮው የጣለው? 😥
አዎ ሰለሞን ያሳዝናል!!
እነዚህን ቃላቶች ልብ በሏቸው:-
#ተነደፈ
#ተጣበቀ
#አዘነበሉት
#ተከተለ
#ሰራ
ዘንድሮ ልብን የሚሰርቅ ነገር በየአይነቱና በየፈርጁ ነው፡
ቅዱሳን የልብ ሌባ ብዙ ነውና ልባችሁን ጠብቁ!
ለነገሩ፦
“አጥብቀህ ልብህን ጠብቅ
የሕይወት መውጫ ከዛ ነውና”
ብሎ ያለው ራሱ ሰለሞን አልነበረምን?
የራሱን መጠበቅ አቃተው እንጂ
የራሱን አሰረቀ እንጂ😥
ወደ ቻናላችን ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለት ጊዜ ብቻ ይንኩ👉@biruk351
