Grace & Truth Ministry
Open in Telegram
እንኳን ወደዚህ ቻናል በሰላም መጡ ከእግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ፀጋና ሰላም ይብዛላችሁ በእውነት ቃልና በፀጋው መንፈስ ይታነፁ
Show more1 029
Subscribers
No data24 hours
-77 days
-2030 days
Posts Archive
#ትምሐርተ_ፀሎት
#ፀሎት_ልዩነት_ይፈጥራል!!!
የመፀለይ እና ያለመፀለይ ውጤት በጌተሰማኒ ታይተዋል: ያለማቋረጥ በፀሎት ሲተጋ የነበረው ጌታችን ኢየሱስ ቀጥሎ ለሚመጣው መከራ ጉልበት ሲኖረው: ለጥቂት ሰዓት እንኳ መፀለይ አቅቷቸው ያንቀላፉት ለረጅም ጊዜ የተከተሉትን ጌታ ክደው እንደሸሹ መጽሐፍ ቅዱሳችን ይናገራል።
👉ኢየሱስ መፀለዩ በእግዚአብሔር ፈቃድ እንዲፀና ሲሆን :ደቀመዛሙርቱ ያለመፀለያቸው ከእግዚአብሔር ፍቃድ እንዲሸሹ አድርጓቸዋል። ፀሎት በየትኛዉም ሁኔታ ውስጥ ስናልፍ በእግዚአብሔር ፍቃድ ውስጥ ፀንተን ወጀቡን፣ ማዕበሉን የምንከለልበት ወይም የምሸሸግበት ክንድ አሊያም ጥላ ነው። በክርስቲያን ህይወት እና አገልግሎት ውስጥ ፀሎት ወሳኝና እንድሁም የድርግቶቻችን ሁሉ መሪ ሊሆን ይገባል።
«ወደ ደቀመዛሙርቱም መጣ ተኝቶውም አገኛቸውና ጴጥሮስን። እንዲሁም ከእኔ ጋር አንዲት ሰዓት እንኳ ልትተጉ አልቻላችሁምን?......
( ማቴዎስ 26፥40)
አንዳንድ ውድቀቶች እግዚአብሔር በፀሎት ውስጥ ያስቀመጠውን ፀጋ ያለመጠቀም ውጤት ነው ፣ አንዳንድ ፈተናዎች ማለፍ ያቃተን በፀሎት ማምለጥ አለመቻላችን ነው ! እና አንዳንድ እያልን ብዙ ነገሮችን መነካካትና መተንተን ይቻላል ዋናው አለመፀለይ የሚያመጣውን ውጤት በማሳየት ማስፈራራትና የመፀለይ ጥቅሞችን በመዘርዘር ለፀሎት ማነሳሳት ሳይሆን : የፀሎትን እውነተኛ ኃይል በመረዳት እንድንፀልይ ያዘዘንን ጌታ: በዚያ በማግኘት ሕብረታችንን በይበልጥ ማጠናከር እንድንችል ነው።
#ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ
#ሼር_ስለሚያደርጉ_እናመሰግናለን 🙏
ወደ ቻናላችን ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለቴ ብቻ ይንኩ👉@biruk351
#ትምህር_ፀሎት(የቀጠለ)
አንድ ጊዜ እማሆይ ቴሬዛ ቃለ መጠይቅ እየተደረገላቸው፤
"ያን ሁሉ ሰአት በፀሎት እግዚአብሔርን ምንድን ነው የሚሉት?"
ተብለው ተጠየቁ: እንዲህ ብለው መለሱ፤ "ኧረ እኔ ምንም አልለውም:
#ጠያቂው+መልሶ፣ "እሺ እግዚአብሔርስ ምን ይሎታል?" ብሎ አክሎ ጠየቃቸው: እርሳቸውም፤
"#እርሱም_ምንም_አይለኝም" ብለው መለሱ: #ጠያቂው፣ "ታዲያ ያን ሁሉ ሰአት ምን ያደርጋሉ?" ሲላቸው፤
"#ዝም_አላለሁ_አሉ::
ፀሎት መናገር ብቻ ሳይሆን ዝም ማለትም ነው: ልብንም ማፍሰስ ነው: ቃላት ሳይወጣንም መፀለይ ይቻላል: ፀሎት የሚለካው በሚፈስሰው ልብ እንጂ በብዙ ንግግር አይደለም።
አንዳንዴ ቃላት የለም ፣ ቃላት ከውስጣችን ለመውጣት አቅም ያጠረናል ፣ በእግዚአብሔር ፊት የምንናገረውን አተን ውሉ ይጠፋናል፣ ቢሆንም ነፍሳችንን እፊቱ እናፈሳለን .. ውስጣችን በቃላት ከመናገር ይልቅ የሚዋደዱ ሰዎች በመተያየት እንደሚግባቡ ተንበርክከን እንደ መተያየት እንፈዛለን ... ቃላት የለም፣ ድምፅ የለም ፣ ጩኸት የለም ፣ ልሳን የለም ....እንደ ዲዳ እንሆናለን ።
(መዝሙረ ዳዊት ምዕ. 143)
----------
6፤ እጆቼን ወደ አንተ ዘረጋሁ፤ ነፍሴም እንደ ምድረ በዳ አንተን ተጠማች 8፤ ነፍሴን ወደ አንተ አንሥቻለሁና የምሄድበትን መንገድ አስታውቀኝ። አንተ አምላኬ ነህና ፈቃድህን ለማድረግ አስተምረኝ፤ ቅዱስ መንፈስህም በጽድቅ ምድር ይምራኝ።
እግዚአብሔር በፊቱ በሚፈስስ ልብ ይባርከን 🙏
#ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ
#ሼር_ስለሚያደርጉ_እናመሰግናለን
ወደ ቻናላችን ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለቴ ይንኩ👉 @biruk351
#ትምሐርተ_ፀሎት(የቀጠለ)
❖ ልቡናውን ሰብስቦ መጸለይ ያቃተው አንድ ደቀ መዝሙር : አረጋዊውን አባት እንዲህ ሲል ይጠይቃቸዋል.....
"አባቴ ወደ ፀሎት ገብቼ ስጸልይ: ልቦናዬ አይሰበሰብልኝም፤ አፌ ቢያነበንብም ልቡናዬ ግን ይበታተናል፤ እኔ ደግሞ ዝም ብዬ ስለ ፀሎት ከእምነት አባቶች ሳስብ: ቅዱሳን በፍጹም ሐሳባቸው እያሰ'ቡና : እንባንና ጸጸትን እየጨመሩ: እንደፀለዩ ነው : የእኔ ከልብ አለመሆንና በዚያ ልክ አለመፀለዬ ይኮንነኛል። እኔ በልቤ ሌላ እያሰብኩ በአፌ ብቻ ባነበንበው እንደ ገደል ማሚቶ ፊደሉ አፌ ላይ እየነጠረ ይሄዳል እንጅ ጸሎትም አይሆንልኝም፤ ስለዚህ አባቴ የአፍ ብቻ ጸሎቴ ቅድመ እግዚአብሔር የማይደርስ ከሆነ ጸሎቴን ብተወው ይሻላል ወይስ ባልተወው ይሻላል?" ብሎ ጠየቃቸው።
❖ አረጋዊው አባትም እንዲህ ሲሉ አስረዱት
✍️“አየህ ልጄ ዐይነ ስውር ሰው በዘንጉ ምድር እየመታ ሲሄድ ከመንገድ ላይ ያለ እባብ፣ ተናካሽ ውሻ ለጊዜው የበትሩን ድምጽ ሰምቶ ይመታኛል ብሎ ይሸሻል። እንጅ ዐይነ ስውር ነው አላየኝም ብሎ ባለበት አይጠብቀውም፤ ስለዚህ አንተም አስተውለህ ብትጸልይ መልካም ቢሆንም ለጊዜው ግን ጭራሽ ከምታቆመው በአፍህ ውስጥ ያለው የቃለ እግዚአብሔርን መንኳኳት የሚሰሙ አጋንንት መሸሻቸው አይቀርምና መቼም ቢሆን ጸሎትህን አትተው፤ አጋንንትንም ማባረር አንድ ታላቅ ጥቅም ነውና፤ ብዙ መጸለይህም ስትጀምር ልብህ ወደ እርሱ ማስተዋል ያድጋል ።
❖ የፀሎት ልምድህን እንዳታቆመው፤ አሁን አንዱን ይዘሃል እርሱ ደግሞ ድካምህን እያገዘ ይሄዳል: ወደፊት ደግሞ ሁለቱንም ለማገናኘት መጣር ይኖርብሃል።
አንድ ነገር ልነግራችሁ ዝም ብላችሁ ፀልዩ 👉 "እንዲሁም ደግሞ መንፈስ ድካማችንን ያግዛል፤ እንዴት እንድንጸልይ እንደሚገባን አናውቅምና፥ ነገር ግን መንፈስ ራሱ በማይነገር መቃተት ይማልድልናል፤"
(ወደ ሮሜ ሰዎች 8:26)
#ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ
ወደ ቻናላችን ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለት ጊዜ ብቻ ይንኩ👉@biruk351
#ሼር_ስለሚያደርጉ_እናመሰግናለን 🙏
#የሳምንቱ_ምርጥ_ምስል_
#ትምህርተ_ፀሎት
ከፍ እንዳትል ያደረገህ አፍህ ነው:#ችግሩ!!!
እግዚአብሔር ባዘጋጀልህ የድል መንገድ ላይ: ወደ ከፍታህ መሰላል እንዳትወጣ የያዘህ ከአፍህ የወጣ ዘር ነዉ። እየከለከለህ መላ እንቅስቃሴህን የተቆጣጠረው ምላስህ ነው።
#ስትፀልይ_እግዚአብሔር_ጋር ታወራለህ : እግዚአብሔርም በነገሩ ፊት ጠንካራና ጠቢብ ሊያደርግህ ቃሉን ይሰጥሃል : ቢሆንም አፍህ ችግር አለበት*,፤ እግዚአብሔር የሚናገረውን አይናገርም ስሜቱን አሁናዊ ነበራዊ ሁኔታውን ያውጃል!!: እናም አፍህ የራስህ የፀሎትህ ጠላት ሆኖሃል።#ትፀልያለህ_ግን_ በሰዎች ፊት ስለሰው ፣#ስለመንፈሳዊ_ነገር ፣ #ስለቤተክርስቲያን_አገልጋዮች፣ ስለ ቅርብና ሩቅ ሰዎች ሳይቀር በማይመለከትህ ነገር በአፍህ ትፈርዳለህ፣ በድካማቸው በአፍህ እንደ ድካም አልባ ታሽሟጥጣለህ.. ጠላትህ አፍህ ሆኖሃል ፣ አንተ ጎበዝ የፀሎትህን መልስና የተዘጋጀልህን ክብር እየመለሰና እያሳነሰህ ያለው አፍህ እንደሆነ ማን በነገረህ?: ምነው ጥበብ ብትመክርህ?! ።
አፍህን በማይመለከትህና ለአንተ ባልተሰጠ ነገር ላይ መክፈትህን አቁምና የፀሎትህን መልስ ተቀበል!!
#ፀሎት
ጌታ ኢየሱስ ሆይ አፌ በአንተ የማዳን ስራ ብቻ የተሞላ ይሆን ዘንድ ልቤን ለቃልህ ፣ ለምክርህ አሳልፌ እሰጣለው ፣ መንፈስ ቅዱስ ሆይ ለእውነተኛ መንፈሳዊነት ራሴን ለማሰልጠን አለህልኛና በጥበብህ አንቃኝ AMEN 🙏
#ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ
ወደ ቴሌግራም ቻናሌ ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለቴ ብቻ ይንኩ👉@biruk351
#ትምህርተ_ፀሎት
#በዚህ_ምድር_ላይ_ሳላችሁ: በቀላሉ ልትደራደሩትና፡ ልታሸንፉት የምትችሉት ብቸኛ አምላክ አለ! : ከእናንተ ልብ የምትወጣ: እውነተኛ የነፍስ ሲቃ: እውነተኛ አንዲት ዘለላ እንባ ቅጣቶቹን እንኳ ለማስቀረት ኃይል አለው!: እግዚአብሔር ምንም ይበላችሁ: #እግዚአብሔር ኤሊን ቁጣውን መቶ ሲነግረወ "እርሱ እግዚአብሔር ነው ደስ ያሰኘውን ያድርግ" አለ። #የእግዚአብሔር ቁጣ የመለሱ የእምነት አርበኞች አሉ ና አለማለት ትችላላችሁ!: እዬዬ እምቢየው ልትሉት እንኳ ትችላላችሁ ፣ በራችሁን ዘግታችሁ ቅስስ ልትሉና ነፍሳችሁን ልታፈሱለት ትችላላችሁ .ጌታም እጅግ የሚምር የሚራራራ ነውና !
እርሱ አሁን ከሰመጣችሁበት ፈተናና መከራ፣ የኃጢአት አዘቀጥም እንኳ ቢሆን ሊያወጣችሁ ይችላል።
ከእናተ ከውስጥ ማንነት ከልብ የሆነ ጩኸት : ከውስጥ ከጥልቅ ስሜት የሆነ ቃላትና እንባ እግዚአብሔር ጆሮ ውስጥ ጣዕም ያለው ዜማ ነው!! እናም ከልባችሁ ፀልዩ!
#ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ
ወደቻናላችን ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለት ጊዜ ብቻ ይንኩ👉@biruk351
#ሼር_ስለሚያደርጉ_እናመሰግናለን🙏
#ቤተሰቦች😍🙏
በእግዚአብሔር ፀጋና በእናንተ እገዛ :1ሺህk ተከታይ ባለው : በቴሌግራም ቻናሌ የተለያዩ ይዘት ያላቸውን ፕሮግራሞች ይዤ ወደ እናንተ መጥቼአለሁ።
#መንፈሳዊ ፣#ማህበራዊ፣#ፖለቲካዊ የሆኑ
➠#መረጃዎች
➠#ትምህርቶች
👉#ኦዲዮ_ስብከቶች_ምስክርነቶች
➠#እንዲሁም_አዝናኝ_የሆኑ_ምስሎች እና ቪዲዮዎች በተለየ ጥራት እና ይዘት ወደ እናንተ እናቀርባለን!
አሁን በዚህ ሳምንት* #ትምህርተ_ፀሎት በሚል ፀሎትንና የፀሎት መርሆችን እናያለን: ደግሞም በሳምንት ለሶስት ሰው ብቻ ምሽት ላይ ቢደወልልኝ የጋራ የእምነት ፀሎት እፀልያለሁ
ይህን ሊንክ አንድ ጊዜ በመንካት ወደ ቴሌግራም ገብተው ✔️#Join_ያድርጉን🙏 👉👉👉👉👉👉👉👉https://t.me/biruk351
#ለማስታወቂያ_Advertisement)
ምርት እና አገልግሎት ለማስተዋወቅም በራችን ክፍት ነው።
ሼር ያድርጉ እናመሰግናለን ጌታ በነገር ሁሉ ይባርኮት 🙏
ይኼንን ወንጌል ተኮር መልዕክት ቢያንስ ለአምስት ሰው ሼር ቢያደርጉና መንፈስ ቅዱስ በቃሉ እንዲወቀስ ብታገለግሉ ምን ይመስላችኋል?: #ኢየሱስም_አለ፦ "በሰው ፊት ለሚመሰክርልኝ ሁሉ እኔም ደግሞ በሰማያት ባለው በአባቴ ፊት እመሰክርለታለሁ (ማቴ 10:32)
⛔️1. #ሰው_ሁሉ_ኃጢአተኛ_ነው
“ሁሉ ኃጢአትን ሠርተዋልና የእግዚአብሔርም ክብር ጎድሎአቸዋል፤” (ሮሜ 3፥23)
⛔️2.#የኃጢአት_ዉጤት_ሞት_ነው
“የኃጢአት ደመወዝ ሞት ነውና፤ የእግዚአብሔር የጸጋ ስጦታ ግን በክርስቶስ ኢየሱስ በጌታችን የዘላለም ሕይወት ነው።” (ሮሜ 6፥23)
🅾️3. #ሰው_ፍርድ_ይጠብቀዋል
“ለሰዎችም አንድ ጊዜ መሞት ከእርሱ በኋላም ፍርድ እንደ ተመደበባቸው፥” (ዕብራውያን 9፥27)
🅾️4. #ሰው_በራሱ_የፅድቅ_ሥራ እራሱን ማዳን አይችልም
"ጸጋው በእምነት አድኖአችኋልና፤ ይህም የእግዚአብሔር ስጦታ ነው እንጂ ከእናንተ አይደለም፤
#ማንም_እንዳይመ_ከሥራ_ አይደለም።" (ኤፌሶን 2÷8-9)
⛔️5. #የሰው_ልጅ_የመዳን_ተስፋው #ኢየሱስ_ክርስቶስ_ነው
“ኃጢአተኞችን ሊያድን ክርስቶስ ኢየሱስ ወደ ዓለም መጣ የሚለው ቃል የታመነና ሁሉ እንዲቀበሉት የተገባ ነው፤ **ከኃጢአተኞችም ዋና እኔ ነኝ*፤”
(1ኛ ጢሞቴዎስ 1፥15)
📢“መዳንም በሌላ በማንም የለም፤ እንድንበት ዘንድ የሚገባን ለሰዎች የተሰጠ ስም ከሰማይ በታች ሌላ የለምና።”🔊 (ሐዋርያት 4፥12)
#ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ
ወደዚህ ቻናል ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለት ጊዜ ብቻ ይንኩ👉@biruk351 🙏
በስውር የሚታገልህን የልማድ ኃጢአት[#Habitual_Sin] ሰብሮ ለመውጣት ሚሊዮን ነፍስ ያላቸው ምክንያቶች አሉ። ዋናውና ሁሌም በፊትህ ሊሳል የሚገባው ምክንያት ግን በእንጨት ላይ ተንጠልጥሎ ያዳነህ ጌታህን፣ ሊቀድስህ በአንተ የሚኖረውን ቅዱሱን መንፈስ እና ሳታውቀው አውቆህ፣ ሳትመርጠው መርጦህ የጠራህን አንዱን አባትህን ማሳዘንህ ነው።
#ፀሎት
ጌታ እግዚአብሔር ሆይ እባክህን አንተን ማሳዘን ምን ማለት እንደሆነ ግለጥልን፤ በዚያም ከብዙ ጥፋት ትሰውረናለህ #አሜን እባክህን አባት ሆይ ካላወቅንህ አሁንም ደግመን ደጋግመን እናሳዝንሃለንና : እራስህን ግለጥልን ያን ካለረክ እንዴት አንተን በድፍረት ከመበደል እንነፃለን?: አሁንም የአንተ ጥገኞችና ተደጋፊዎች መሆናችንን አውቀህ: በልጅ በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል የከፈልክልንን ዋጋ እንዲገለጥልን አርግልን: ምናልባትም የመስቀልህ ነገር ተደጋግሞ ለምዶብን ስለ እኛ የሆንከው በስብከት አውቀን: አንተን ግን ባለማወቅ ውስጥ ተዘፍቀን: ስለ አንተ በማወቅና አንተን በማወቅ መካከል ያለው ልዩነት ተምታቶብን ከሆነም: እባክህ ነፃ አውጣን 🙏
#ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ
ወደዚህ ቻናል ለመቀላቀልና ፀጋን ለመካፈል ይኼንን ሊንክ ሁለት ጊዜ ብቻ ይንኩ👉@biruk351
#ሼር_ስለሚያደርጉ_እናመሰግናለን 🙏
(ወደ ኤፌሶን ሰዎች ምዕ. 2)
----------
5፤ ከወደደን ከትልቅ ፍቅሩ የተነሣ በበደላችን ሙታን እንኳ በሆንን ጊዜ ከክርስቶስ ጋር ሕይወት ሰጠን፥ በጸጋ ድናችኋልና፥.......
8፤ ጸጋው በእምነት አድኖአችኋልና፤ ይህም የእግዚአብሔር ስጦታ ነው እንጂ ከእናንተ አይደለም፤
9፤ ማንም እንዳይመካ ከሥራ አይደለም።
ፍርድ ቤት ውስጥ እንደሆንክ አስብ: ዳኛው እግዚአብሔር ነው: አንተም ፊት ለፊት ቆመሃል: በቅድስናው በኃጢአትህ ምክንያት የማያቋርጥ ጭንቀት ውስጥ ነህ: እግዚአብሔር በነጎድጓዳዊ ድምፅ ጥፋተኛ መሆንህን አውቃለሁ ሲልህ ትሰማለህ: ይሄኔ እየተንቀጠቀጥህ የሞት ፍርድህን ትጠብቃለህ: ምክንያቱም ኃጢአተኛ መሆንህን ታውቃለህ።
" ሁሉ ኃጢአትን ሠርተዋልና የእግዚአብሔርም ክብር ጎድሎአቸዋል፤"
(ወደ ሮሜ ሰዎች 3:23) ስለዚህም ፍርድህን ውስጥህ ራሱ መስክሮልሃል : በትክክል ሞት ይገብሃል ። "የኃጢአት ደመወዝ ሞት ነውና፤ የእግዚአብሔር የጸጋ ስጦታ ግን በክርስቶስ ኢየሱስ በጌታችን የዘላለም ሕይወት ነው።
"(ወደ ሮሜ ሰዎች 6:23) *በዚህ ወቅት ግን አንድ ነገር ወደልብህ መጣ: የዛሬ 2000 አመት በመስቀል ያለ ሀጢአቱ አንድም በደል ሳይገኝበት የተቀጣ የሞተ ና የተነሳ ነበር : ያ ሰው ቅዱሱ የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑንና ስለ አንተ ኃጢአት እንደተሰቀለ አመንክና ሞቴን ወስዶታል ለእኔ የሚገባውን እርሱ ሆኗል ብለህ በልብህ ስታጉተመትም እግዚአብሔር ሰማህ : በደለኛ ነህ ነገር ግን ጻድቅ ነህ ብዬ አውጄአለሁ፣ ቅጣትህ ተሽሯል ይልሃል፤ ይህ መጽደቅ ይባላል እግዚአብሔር በሕግ ፊት አዲስ አቋም ይሰጥሃል የክስ መዝገብህም ነጻ ይሆናል
ኢየሱስ በሠራው ሥራ ምክንያት እግዚአብሔር ጻድቅ ነህ ብሎ አውጇል
እርሱንም እግዚአብሔር በእምነት የሚገኝ በደሙም የሆነ ማስተስሪያ አድርጎ አቆመው፤ ይህም በፊት የተደረገውን ኃጢአት በእግዚአብሔር ችሎታ ስለ መተው ጽድቁን ያሳይ ዘንድ ነው፥
ራሱም ጻድቅ እንዲሆን በኢየሱስም የሚያምነውን እንዲያጸድቅ አሁን በዚህ ዘመን ጽድቁን ያሳይ ዘንድ ነው" (ሮሜ.3:25-26)
#ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ
ወደዚህ ቻናል ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለት ጊዜ ብቻ ይንኩ👉 @biruk351
ሼር ስለሚያደርጉ እናመሰግናለን
ኢየሱስ ብቸኛ አዳኝ ነው
(ወደ ዕብራውያን 12:25)
ለሚናገረው እምቢ እንዳትሉ ተጠንቀቁ፤ እነዚያ በምድር ላስረዳቸው እምቢ ባሉ ጊዜ ካላመለጡ፥ ከሰማይ ከመጣው ፈቀቅ የምንል እኛስ እንዴት እናመልጣለን?
ድሮ አንድ ወንጀለኛ ሰው ተከስሶ ፍ/ቤት ይቀርባል። ዳኛውም የሞት ፍርድ እንደሚገባው በማየቱ: ፍርድ በመስጠት ለመጨረሻ ውሳኔ ወንጀለኛውን ወደ ንጉሱ ይልከዋል። ወንጀለኛውም ፍርዱን ከተቀበለ በኋላ ወደንጉሱ ይቀርባል። ንጉሱም ፍርዱን በማፅናት የሞት ፍርዱ ከተወሰኑ ቀናት ውሰጥ አንዲፈፀም ያዝዛሉ። በዚህ ጊዜ ወንጀለኛው በንጉሱ ፊት እጅግ በመፀፀትና እጅግ በማዘን ንጉሱን እጅ ነስቶ ወደ ወህኒ ቤት ይመለሳል። የወንጀለኛውን ሀዘን ያየው ንጉስም ልቡ እጅግ ይራራል። ልዑል የራሱን ብቸኛ ልጁን በአሰቸኳይ ያስጠራና: ይህንን ደብዳቤ ወደ ወህኒ ቤት ይዘህ ሂድ: የሞት ፍርድ ለፈረድኩበት ሠው እንዲደርሰው : ለወህኒ ቤቱ ሀለፊ ሰተህ ና በማለት ይልከዋል። የልዑሉም ልጅ በብርድና በፀሀይ ወደ ወይኒቤቱ በመገስገስ: የወይኒ ቤቱን ጥበቃ ጠርቶ ልዑል ደብዳቤ ይዞ መጥቶ ይፈልግሀል ብላችሁ ወንጀለኛውን ጥሩልኝ አላቸው። ጥበቃዎችም ወንጀለኛውን ጠርተው ልዑል ይፈልግሁል ይሉታል። ወንጀለኛው ግን ነገ ልሞት ዛሬ ማንንም ማግኘት አልፈልግም ብሎ አሻፈረኝ ይላል።
የልዑሉም ልጅ ወንጀለኛው እኔ እንደምፈልገው መልእክት ባስልክበትም: አለቀበልም ስላለ ደብዳቤውን መልሼ ይዠው መጥቻለሁ በማለት ለንጉሱ ሪፖርት ያደርጋል : በመጨረሻ የሞት ፍርዱ የሚፈፀሞበት ቀን ደረሰና ወንጀለኛው በንጉሱ ፊት ይቀርባል። ንጉሱም አንተ ትቢተኛና አመፀኛ ሰው ልዑል ሊያስፈታህ ደብዳቤ ይዞ መጥቶ ሲያስጠራህ እንዴት አልታዘዝም ትላለህ? ስለዚህ ዛሬ የሞት ፍርዱ ይፈፀማል ይለዋል። አገልጋዮች እንዲገደል አንገቱ ውስጥ ገመድ አሰገብተው ሊገድሉት እየተዘጋጁ እያሉ ንጉሱ ከመሞትህ በፊት የምትለው ነገር አለህ? ብለው ይጠይቁታል። ወንጀለኛውም "ዛሬ የምሞተው በሰራሁት ወንጀል ሳይሆን የልዑሉን ደብዳቤ ባለመቀበሌ ነው" አለ ይባላል። በአዲስ ኪዳን ሰው የዘላላም ሞት የሚፈረድበት ሀጢያተኛ ስለሆነ ሳይሆን ለሀጢያቱ ምትክ ሆኖ የሞተለትን ኢየሱስን ባለመቀበሉና ባለማመኑ ነው"።(የመጀመሪያ ኃጢአት ለኃጢአት የተቀጣልኝን ክርስቶስን አለማመን ነው)
#ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ
ወደዚህ ቻናል ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለት ጊዜ ብቻ ይንኩ👉 @biruk351
ሼር ስለሚያደርጉ እናመሰግናለን 🙏
በእኛ ውስጥ የሚሠራው ኃይል
ኤፌሶን 3፡20
እንግዲህ በእኛ እንደሚሠራው ኃይል ከምንጠይቀው ወይም ከምናስበው ሁሉ በላይ አብዝቶ ሊሠራ ለሚችለው፣
" ለዚህም ነገር ደግሞ፥ በእኔ በኃይል እንደሚሠራ እንደ አሠራሩ እየተጋደልሁ፥ እደክማለሁ።
"(ወደ ቆላስይስ ሰዎች 1:29)
ዳግመኛ በተወለድንበት ቅጽበት መለኮታዊ ተፈጥሮን ተቀበልን እናም መለኮታዊውን ሕይወት ለመኖር በሚያስፈልገን ኃይል ይመጣል። አውቀንም ሆንን ሳናውቀው ይህ ኃይል ሁል ጊዜ በውስጣችን አለ።
"ኃይል" የሚለው ስም (በግሪክ "ዱናሚስ") ማለት "በአንድ ነገር ውስጥ በተፈጥሮው የሚኖር የተፈጥሮ ችሎታ" ማለት ነው። ከላይ ካለው ፍቺ የምንረዳው ይህ ኃይል በክርስቶስ ካለን አዲስ ተፈጥሮ ጋር የተያያዘ መሆኑን ነው። የእግዚአብሔር ተፈጥሯዊ (ተፈጥሯዊ እና ቋሚ) ችሎታ አለን።
ይህ ኃይል ንቁ ነው፦ ለዚህ ነው "የሚሠራው ኃይል" የሚባለው እና በእኛ ውስጥ ንቁ ነው። በዚህ ኃይል መለኮታዊ ተፈጥሮአችንን ለፍጡር መግለጥ እንችላለን።
ይህ ኃይል በእኛ ውስጥ እንዳለን ማወቅ ብቻ በቂ አይደለም፤ እንዴት እንደሚለቀቅ ማወቅ አስፈላጊ ነው።
ከእግዚአብሔር አለም ሀይልን ማስለቀቅ ከፈለክ ለእግዚአብሔር ቃል ምላሽ መስጠት ጀምር!
ምክንያቱም ሁልጊዜ ሀይል ያለው ከቃል በስተጀርባ ነው!
በኢየሱስ ስም የእግዚአብሔር ሀይል በልዩነት ይስራላችሁ✋
ይህ ኃይል የሚለቀቀው በእምነት ቃል ነው። ስለዚህ የእግዚአብሔርን ቃል በእምነት የመናገር አስፈላጊነት።
በመጀመሪያ እግዚአብሔር ሁሉንም ነገር በመናገር ፈጠረ - "እግዚአብሔርም አለ ..., እግዚአብሔርም አለ...". ከፍጥረት ኃይሉ ተፈጥሮ ነገሮችን ወደ መሆን ተናግሯል። እግዚአብሔር የተፈጠረውን ኃይል ፈታ። ይህንን ኃይል በመናገር መልቀቅ አለብን፣ አለበለዚያ በእኛ ወይም በአካባቢያችን ላይ ተጽዕኖ ሳያሳድር በውስጣችን ሊቆይ ይችላል።
እግዚአብሔር በእኛ ውስጥ በሚሠራው ኃይሉ በእኛ በኩል ዕቅዶቹን እና ዓላማውን በምድር ላይ ያደርጋል እና ያጸናል። ለዚህ ዓላማ ኃይል ተሰጥቶናል፣ ስለዚህ በአለማችን ላይ ለውጦችን ማድረግ እንችላለን። ስለዚህ ይህንን ኃይል በእያንዳንዱ ጊዜ ለመልቀቅ ይምረጡ እና የሚፈልጉትን ለውጦች ያድርጉ።
በእኛ ውስጥ የሚሠራው የእግዚአብሔር ኃይል በዓለማችን ላይ ከተፈጥሮ በላይ የሆኑ ለውጦችን የማድረግ ችሎታችን ነው።
#የእምነት_ፀሎት
በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም በውስጣችሁ የገባው መለኮታዊ ሕይወት የተገለጠ ይሁን ፣ በእናንተ የሚሰራውን ያንን ኃይል በውስጥ አይናችሁ ማየትና መጠቀም እንድትችሉ እፀልያለሁ ፣ በዚህ ኃይል ውስጥ የተቀመጠው ክብር ለሌሎች እንድታሳዩና አብን በኢየሱስ በኩል እንድታስከብሩ እፀልያለሁ በኢየሱስ ስም አሚን 🙏
#ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ
ወደዚህ ቻናል ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለት ጊዜ ብቻ ይንኩ👉 @biruk351
ሼር ስለሚያደርጉ እናመሰግናለን 🙏
#መነሳሳት
አንዳንድ ጊዜ በተሰጠን ጸጋ እግዚአብሐርን ለማገልገል እየፈለግን እንዴትና መቼ እንደምንጀምር ግራ ሊገባን ይችላል፤ አንዳንድ ጊዜ እግዚአብሔር በሕይወታችን ላይ ያለውን የከበረ ፈቃድ እያወቅን በዚያ መሄድ ሲታክተን ራሳችንን እናገኛለን ወይም በሕይወታችን ከደረሰብን የተለያየ ፈተና የተነሣ እየጠወለግን የምናመነታ እንሆናለን፤ ወይም በዙሪያችን ባለው ዓለም ከምናየውና ከምንሰማው ነገር የተነሣ ተስፋ መቁረጥና መዳከም ውስጥ ገብተን ልንሠራ የሚገባውን የእግዚአብሔርን ሥራ ቸል እንል ይሆናል፤ አሊያም ከስጋዊ ድካም የተነሳ ፈፅሞ በራሳችን ተስፋ ወደ መቁረጥና ትቶ ወደ መፈርጠጥ እንደርሳለን .....ዛሬ በዚህ ሁኔታ ውስጥ ለምንገኝ አማኞች እግዚአብሔር መንፈሳችንን እንደገና የሚያነሳሳ መልእክትን ይናገራል፡፡
በባቢሎን ምርኮ ለሰባ ዓመታት የኖሩት አይሁድ ሁሉን ነገር ትተው የእግዚአብሔርን ቤት አገልግሎት ሁሉ ረስተው በነበሩበት ሁኔታ ሳሉ: እግዚአብሔር እንደገና ሊያነሳሳቸው ፈለገ፤ በቅድሚያ ለዓላማው ይጠቀምበት ዘንድ እግዚአብሔር የፋርሱን ንጉሥ የቂሮስን መንፈስ አስነሣ (ዕዝ.1፡1)፤ እርሱም በኢየሩሳሌም ያለው የእግዚአብሔር ቤት እንዲሠራ አዋጅ አወጣ፤ በመቀጠልም እግዚአብሔር ከአይሁድ መካከል የአንዳዶችን መንፈስ አነሳሳ፤ “የይሁዳና የብንያም የአባቶች ቤቶች አለቆችም፥ ካህናቱም፥ ሌዋውያኑም፥ በኢየሩሳሌም ያለውን የእግዚአብሔርን ቤት ለመሥራት ይወጡ ዘንድ እግዚአብሔር መንፈሳቸውን ያነሣሣው ሁሉ ተነሡ።” ይላል (ዕዝ.1:5)፡፡
መንፈስ ቅዱስ በዚህ በጸጋው ዘመን እንደ ዘመነ ብሉይ አልፎ አልፎ እየመጣ ሥራ የሚሠራ ብቻ አይደለም፤ የበዓለ ሃምሳ ዕለት እንደወረደ እስከአሁን በአማኞች ዘንድ እና በውስጣችን አለ፤ ስለሆነም በብዙ መጠውለግ ውስጥ ያለነውን አማኞች ለመንፈሳዊ ነገሮች እንደገና ሊያነሳሳን ይፈልጋል፡፡ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በተስፋ መቁረጥ ውስጥ ሆነው እየጠወለጉ ወደ ኤማሁስ ይሄዱ የነበሩትን ሁለት ደቀመዛሙርት ከቅዱሳት መጻሕፍት እየጠቀሰ እንዳበረታቸው (ሉቃ.24፡13-27) ዛሬም በመንፈሱ በኩል ቅዱሳት መጻሕፍትን እየገለጠ ልባችንን እየቀሰቀሰ ይገኛል፤ በሕልም በራዕይ በትንቢታዊ ድምፅ ዛሬም እግዚአብሔር ልጆቹን ያነሳሳል ወይም ደግሞ ደጋግሞ ይቀሰቅሳል ። ሐዋርያው ጳውሎስ በድካም ውስጥ ለነበረው ለጢሞቴዎስ እንደገና ስለመነሳሳት ሲጽፍለት “ስለዚህ ምክንያት፥ እሳት እንደሚያቀጣጥል ሰው፥ እጆቼን በመጫኔ በአንተ ያለውን የእግዚአብሔርን ስጦታ እንድታነሣሣ አሳስብሃለሁ” ብሎታል (2ጢሞ.1:6)፡፡ ስለዚህ ይህን መልእክት ያነበብን ሁላችን ራሳችንን በመፈተሸ ከዛልንበትና ከጠወለግንበት ነቅተን ለመንፈሳዊ ነገሮች በመንፈስ ቅዱስ ኃይል እንደገና ልንነቃቃና ልንነሳሳ ይገባናል፡፡
#የእምነት_ፀሎት
በኢየሱስ ስም ለእግዚአብሔር ሀሳብ በሕይወታችን ላላው ዘለአለማዊ ዕቅድ መነሳት ይሁን ፣ ለከበረው ጥሪ መነሳት ይሁን ፣ ለፈቃድ እውቀት መነሳት ይሁን ፣ ለክርስቲያናዊ ኑሮ መነሳት ይሁን ፣ እንዳንነነሳ የሚታገል ኃይላት በኢየሱስ ስም የወደቁ ይሁኑ አሚን 🙏
#ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ
ደዚህ ቻናል ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለቴ ብቻ ይንኩ👉@biruk351
ሼር ያድርጉ እናመሰግናለን🙏
#ከትላንት_የቀጠለ_የዘላለም_ሕይወት
“መዳን” ከእግዚአብሔር ቁጣና ፍርድ ነጻ መሆን ሲሆን፣ “ሕይወት” ደግሞ ከዚያ በኋላ የዳነው ሰው ከእግዚአብሔር ጋር ባለ ኅብረት የሚኖረው ኑሮ ነው፡፡ ከእግዚአብሔር ቁጣና ፍርድ የዳነ ሰው ከእግዚአብሔር የተገኘው ሕይወት በውስጡ ወዲያውኑ ይገባል፡፡ “መዳን” እና “ሕይወት” ሁለቱም ዘላለማዊ መሆናቸው ተነግሯል፡፡ የመዳንን ዘላለማዊነት ቀደም ሲል የገለጽን ሲሆን አሁን ደግሞ ስለዘላለም ሕይወት ጥቂት እናያለን፡፡
የዘላለም ሕይወት የጊዜ ወሰን በሌለው ሁኔታ ውስጥ ለዘላለም መኖር ብቻ አይደለም፤ ያልዳኑ ሰዎችም ቢሆኑ “በእሳት ባሕር” ውስጥ በሥቃይ የሚኖሩት “ለዘላለም” መሆኑ ተነግሯል፤ “ወደ ዘላለም እሳት ከእኔ ሂዱ” ይባላሉ (ማቴ.25፡)። “በዘላለም ጥፋት ይቀጣሉ” (2ተሰ.1፡10)፣ እንዲሁም “ለዘላለምም እስከ ዘላለም ቀንና ሌሊት ይሣቀያሉ” (ራእ.20፡10) ተብሎ ተጽፏል፡፡ የዘላለም ሕይወት ሲባል ግን በዘመን ሳይገደቡ ለዘላለም መኖር ብቻ ሳይሆን እግዚአብሔርን በማወቅ ከእርሱ ጋር ለዘላለም በኅብረት መኖር ነው፡፡
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመጨረሻው ጸሎቱ ውስጥ የዘላለም ሕይወትን ሲገልጸው “እውነተኛ አምላክ ብቻ የሆንህ አንተን የላክኸውንም ኢየሱስ ክርስቶስን ያውቁ ዘንድ ይህች የዘላለም ሕይወት ናት” ብሏል (ዮሐ.17፡2-3)። እግዚአብሔርን ስናውቅ በእርሱ ዘንድ ያለውን ባሕርይ፣ ፈቃድ እና መሻት በአእምሮአችን ብቻ ሳይሆን በመንፈሳችንም ማለት በውስጣዊ ማንነታችን እናውቀዋለን፤ በተግባርም ይዋሐደናል፡፡ ይህ በመለኮት ዘንድ ያለው የዘላለም ሕይወት በክርስቶስ መምጣት የተገለጠ፣ በሐዋርያትም የተሰበከ ነው፤ ሐዋርያት “ሕይወትም ተገለጠ አይተንማል እንመሰክርማለን፥ ከአብ ዘንድ የነበረውንም ለእኛም የተገለጠውን የዘላለምን ሕይወት እናወራላችኋለን” በማለት ነግረውናል (1ዮሐ.1:2)፡፡ የዚህም ውጤቱ ከአባት ከልጁም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ኅብረት ማድረግ ነው (1ዮሐ.1፡3)፡፡
ይህም የዘላለም ሕይወት የሚገኘው ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን በማመን መሆኑ በተደጋጋሚ ተነግሯል። “በልጁ የሚያምን የዘላለም ሕይወት *አለው ” ተብሎ ተጽፏል (ዮሐ.3፡36)። ራሱም ሲናገር “እውነት እውነት እላችኋለሁ በእኔ የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው ” ብሏል (ዮሐ.6:47)። “#አለው” የሚለው ቃል በክርስቶስ ያመነ ሰው የዘላለም ሕይወት ባለቤት የሚሆነው ባመነ ጊዜ እንደሆነ ያሳያል። ይህም የዘላለም ሕይወት ክርስቶስን አምነን ከተቀበልንው በኋላ ለዘላለም የማይወሰድና በውስጣችን የሚኖር መሆኑን ያረጋግጣል። በዚህ ሕይወትና በሰጪው ተደሰቱ: ፀጋ ከእናንተ ጋር ይሁን!🙏
#ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ
ደዚህ ቻናል ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለቴ ብቻ ይንኩ👉@biruk351
ሼር ያድርጉ እናመሰግናለን🙏
" የዘላለም ሕይወት እንዳላችሁ ታውቁ ዘንድ በእግዚአብሔር ልጅ ስም ለምታምኑ ይህን ጽፌላችኋለሁ።"
(1ኛ የዮሐንስ መልእክት 5:13)
#አሁን_የዘለአለም_ህይወትን የተገናኛችሁት: የዘለአለምን ህይወት አሁን እንድትኖሩት እንጂ ከሞት በኋላ ለዘለአለም የተዘጋጀላችሁ ማረፍያ ቤት እንዳለ እንድታስቡ አልያም ስላለ አይደለም።
#ወደ ኋላ ተመልሳችሁ መመልከት ከቻላችሁ : የካቶሊክ ቤት እምነት ውስጥ ገነትን ትወርሱ ዘንድ የገነትን ትኬት ቁረጡ እያሉ ገንዘብ ሲሰሩ የነበሩ ሰዎችን ታገኛላችሁ።
#በማርቲን ሉተር ይሄ ሀሳብ ተቀባይነት ባለማግኘቱና ሰዎች ገነት በቲኬት ሳይሆን በእምነት የሚገኝ ነው የሚለው ሀሳቡ ሀሳባቸውን Protest (እንዲቃወም) አድርጓል። ቀጥሎም ይሄንን ሀሳብ የሚቃወሙ ከእርሱ ጋር Protest አድርገው Protestant(ሀሳቡን ተቃዋሚዎች) ሆነው ወጥተዋል። እምነትም ልክ እንደ ገንዘብ ሆኖ የዘላለም ህይወትን ይገዛል የሚል አስተሳሰብ ነው። ነገር ግን በማመን ስለሚገኝ የዘለአለም ተስፋ ሳይሆን አሁን በማመን ስለሚገኝ ህይወት ነው።
#አሁንም በእየሱስ እመን ቀጥታ ገነት VIP ይያዝልሀል የሚል የቲኬቱ አይነት አስተሳሰብ አለ። በመጀመርያ እየሱስ ክርስቶ ማነው? ምንድነው? ምን ለመናገር ነው የፈለገው? የሚለውን ሀሳብ መረዳት ግድ ነው።
#ኢየሱስ ክርስቶስ የዘለአለምን ህይወት ወደ እናንተ ይዞ ቢመጣ ለዘለአለም የምትኖሩበትን እውነት ይዞ መምጣቱ ነው። ይህም እውነት ህይወት ሆኖ በውስጣችሁ እንደ ዘር ሊያድግ አልያም ሳያድግ ጨንግፎ ሊቀር ነው፣ይህ ህይወት በመስማት በኩል ህያው በሆነ ቃል ወደ ውስጥ ሰውነታችን የገባ ህያው የሆነ የእግዚአብሔር የራሱ ሕይወት ነው።
#አብ(አባትን) መምሰልን የምትለማመዱበት ይህ ወደ እናንተ የመጣው የልጅነት መንፈስ ወይም የዘለአለሙ ህይወት የልጁ የራሱ ሕይወት ነው።ነገር ግን ልክ ቲኬቱን በገንዘብ ገዝተው ገነትን እንደሚጠባበቁት ሞኞች ብትሆኑ ኢየሱስን አምነናል እና ገነት ሀቃችን ነው የሚል ሞኝ ከመሆን አትድኑም።
#እግዚአብሔርን መምሰል አሁን መለማመዱ ህይወት አሁንም ያለች እውነት እንጂ ገና የምትጠበቅና የምትመጣ አለመሆኗን ማሳያ ነው። በዚህም አሁን ስለተሰጣችሁ ህይወት ትጋደሉ ዘንድ፣(ከውሸት መናፍስቶች ከውሸት አገልጋዮች ከሀይማኖተኞች በመጋደላችሁም የተጋደላችሁለትን አለም ለራሳችሁ ታስገዙ ዘንድ ነው፣ ይህ ከሆነ አሁን በመጋደል ውስጥ የምትገኙ ሆናችሁ ትገኛላችሁ።
ይህ መልካሙ የእምነት ገድል ይባላል። እግዚአብሔር ሕይወቱን ሰቶሃል ይኼ እውነት ነው ብለህ ይኼንን አለምና ስሜትህን ግዛ ።
" መልካሙን የእምነት ገድል ተጋደል፥ የተጠራህለትንም በብዙም ምስክሮች ፊት በመልካም መታመን የታመንህለትን የዘላለምን ሕይወት ያዝ።"
(1ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 6:12)
#ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ
ወደዚህ ቻናል ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለቴ ብቻ ይንኩ👉@biruk351
ሼር ያድርጉ እናመሰግናለን 🙏
#ቀኖናዊ_እምነት እና #ተግባራዊ_እምነት
Doctrinal faith Vs Practical faith
==========================
ተግባራዊ እምነት ማለት ለውድቀት አጋልጠውን የነበሩ ነገሮችና ከዚህ ዓለም የመጣብን ነቀፋ በሙሉ በክርስቶስ ተሽሮአል ብሎ ማመን ነው። ኢየሱስ ክርስቶስ አልአዛር ሞቶ እያለ: ማርታን "ወንድምሽ ይነሳል" ሲላት "አዎ በትንሳኤ ቀን እንዲነሳ አውቃለሁ" አለችው (ዮሐ. 11: 23-24) ይህ ደግሞ ቀኖናዊ እምነት ይባላል። ማርታ በወቅቱ ያልተረዳችው በትንሳኤ ቀን ለሚሆነው ነገር የእምነት መኖር አስፈላጊ አለመሆኑን ነው። እያንዳንዱ በራሱ ተራ ስለሚሆን (ዮሐ. 5: 28-29 / 1ቆሮ. 15:23) እኛ አመንም አላመንም በትንሳኤ ቀን የሚሆነው ይሆናል። ኢየሱስ ቀጠለና "ሕያው የሆነም የሚያምንብኝም ሁሉ ለዘላለም አይሞትም ይኼን ታምኛለሽ?" ሲላት በአሳቧ ወደዚህ እምነት ወደማይጠይቀው ቀን በመጓዝ "አዎን ጌታ ሆይ፤ አንተ ወደ ዓለም የሚመጣው ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆንህ እኔ አምናለሁ አለችው።"
(ቁ. 27) አለችው። ይሄ ድርጊቷ ማርታ ቀኖናዊ እምነት ውስጥ እንደ ነበረች ያሳያል። ኢየሱስ ግን ወዲያውና አሁን ስለሚሆነው ተግባራዊ እምነት የሚፈልገውን የወንድሟን መነሳት ነበር እየነገራት ያለው።
ብዙ ጊዜ የነገ አመለካከት ያላቸው ሰዎች ወደፊት ይሆናል ብለው ስለሚያስቡት እንጂ አሁን ስለሚሆነው ነገር አያስቡም። ማንኛውንም የእግዚአብሔር መንፈስ አሰራር (ስለ መዳን፣ ስለ በረከት በሉት ስለ ፈውስ) ስናምንና ስንቀበል ከወደፊት ጋር አያይዘን ሳይሆን አሁንና ወድያው እንደሚሆን አርገን ከሆነ አልአዛር ያኔውኑ ከሞት እንደ ተነሳ እኛም እምነታችን ወድያውኑ ውጤታማና ተግባራዊ ሲሆን እናየዋለን። ችግሩ የቀኖና እምነት ሰዎች አሁን አዲስ ፍጥረት ነኝ፣ አሁን ድኛለሁ፣ አሁን ተባርኪያለሁ፣ አሁን ገዢ ነኝ፣ አሁን ጸድቂያለሁ፣ አሁን ቅዱስ ነኝ፣ አሁን ነውር አልባ ነኝ፣ አሁን ጤነኛ ነኝ ወዘተ እንዲሉ አያደርግም። ከተግባራዊ እምነት ይልቅ በቀኖናዊ እምነት ላይ እንድንደገፍ የሚያደርገን ነገር በሙሉ አሮጌ ስርዓት ነው። እግዚአብሔር የአሮጌው ስርዓት ወግና መገለጫ የሆኑት ነገሮች በእናንተ ዘንድ የሉም ሲለን አቤቱ አሜን የሉም ብለን በእምነት ከተቀበልን ሕይወት፣ ብልፅግና፣ ሰላም፣ ጥበብ፣ ብርታትና ኃይል ይሆንልናል።
በየትኛው ላይ ነን?
ሼር ያድርጉ እናመሰግናለን የተቋረጠው ጀምረዋል
#ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ
ወደቻናላችን ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለቴ ብቻ ይንኩ @biruk351 የ
#ለፀሎት_ያዘጋጀናል
በመጽሃፍ ቅዱሳችን ውስጥ እንደ ሰቆቃወ ኤምርያስ ልብን የሚያስቆዝም መጽሃፍ ያለ አይመስለኝም፡ ከጅምሩ እስከፍጻሜው ድረስ ክፍተኛ የሆነን ምሬት የሚያሳይና በተስፋ መቁረጥ ጭጋግ የተሞላ መጽሃፍ ነው፡ የኤርምያስን ያህል አይናችን እንባን ባያዥጎደጉድም በውስጣችን ግን ሳናለቅስ ማንበብ አንችልም።
ኤርምያስ ኢየሩሳሌምን ወክሎ ወይም ለብሶ ( as the embodiment of Jerusalem ) ነበር የነፍሱን ብሶት በኃይለኛ ሰቆቃ ውስጥ ከኃጢአታቸው የተነሳ ወደ ቀጣቸው ያህዌህ በሰለለ ድምጽ የሚያፈሰው፡
በ 721ኛው ዓመተ አለም ነበር የሰሜኑን መንግስት ( አስሩን ነገዶች ) አሦራውያን ምርኮ አድርገው የወሰዱአቸው፡ ከዛም በተደጋጋሚ በተለያዩ ነብያት የተቀረውን የደቡቡን መንግስት ያህዌህ ከክፉ ስራቸው እንዲመለሱ፣ በተለይ ጣኦት አምልኮን እርግፍ አድርገው እንዲተው ሲወተውታቸው ነበር፡ ነገር ግን ይሁዳ እንዳለ አሻፈረኝ በማለት ሕጉን በመተላለፍና የቃል ኪዳኑን አምላክ ገሸሽ በማድረግ ኤርምያስ በትንቢቱ እንደሚነግረን ሁለቱን ክፉ ነገሮች አደረጉ፦
“ሕዝቤ ሁለቱን ክፉ ነገሮች አድርገዋልና፤ እኔን የሕያውን ውኃ ምንጭ ትተውኛል፥ የተቀደዱትንም ጉድጓዶች፥ ውኃውን ይይዙ ዘንድ የማይችሉትን ጉድጓዶች፥ ለራሳቸው ቆፍረዋል” ( 2 ፡ 13 )
ከዚህም እምቢተኛነታቸው የተነሳ ያህዌህ በብርቱ ቃል እያስጠነቀቀ ሲናገራቸው የነበረውን ፍርድ አመጣባቸው፡ ይህ ፍርድ ደግሞ ከዚህ በፊት አይተውትና አስበውት የማያውቁት አይነት ነበር፡ ያህዌህ ሲመለክበት የነበረው ቤተመቅደስ በ 586 ዓመተ አለም አይናቸው እያየ በባቢሎን መንግስት በእሳት ተቃጠለ፡ ንዋየ-ቅዱሳቱም ወደባቢሎን ተወሰዱ፣ እንዲሁም ካህናትና ሹማምንት ሁሉ ተገደሉ የተረፉትም ወደ ግዞት ተከተቱ፡፡
ይህንን ሰቀቀን ኤርምያስ እጅግ በሚያምና ስእላዊ በሆነ መልኩ - ልክ አንባቢው ፊልም የሚያይ እስከሚመስለው ድረስ - ይስለዋል፡ ገና መጽሃፉን ሲጀምር እንዲህ ይላል፦
“ሕዝብ ሞልቶባት የነበረች ከተማ ብቻዋን እንዴት ተቀመጠች! በአሕዛብ መካከል ታላቅ የነበረች እንደ መበለት ሆናለች፤ በአውራጆች መካከል ልዕልት የነበረች ተገዢ ሆናለች”
ሕዝብ #ሞልቶባት የነበረች ከተማ እንዴት ብቸኛ ሆነች?
#ታላቅ የነበረች ከተማ እንዴት መበለት ሆነች?
#ልዕልት የነበረች ከተማ እንዴት ተገዢ ሆነች?
ሽማግሌዎችና ህጻናት በጎዳና ወደቁ፣ እናቶች የልጆቻቸውን ስጋ በሉ፣ ቤተመቅደሱ ስለፈረሰ ለአመት በአል ወደኢየሩሳሌም የሚወጣ ስለሌለ ጎዳናዎች አለቀሱ፣ ጠላት በተቀደሰው ነገር ሁሉ ላይ እጁን ዘረጋ፣ ከተማዋ ለሦስት ዓመት ከመከበብዋ የተነሳ ሰዎች በርሃብና በጥም እንደ ቅጠል ረገፉ፣ ከውሃ ጥም የተነሳ የህጻናት ምላስ ከትናጋቸው ጋር ተጣበቀ፣ ውሃቸውንና ምግባቸውን በብራቸው ጠጡ በሉ፣ እናቶች በአንድ ቀን ልጅ አልባና መበለቶች ሆኑ፣ መከራን እንደውሃ ጠጡ።
በዚህ ሁሉ ሰቀቀን ውስጥ ጭል ጭል የምትል የተስፋ ብርሃን ግን አሁንም ቢሆን ከኤርምያስ አልጠፋችም ነበር፡ በዚህ ሁሉ ውርደትና ውድመት ውስጥ ኤርምያስ አሁንም ቢሆን ከክር በቀጠነች ድምጹ ያህዌህ ተስፋቸው እንደሆነና ከስራቸው ሙሉ በሙሉ ነቅሎ እንዳልጣላቸው እንዲህ በማለት ይናገራል፦
“ያልጠፋነው ከእግዚአብሔር ምሕረት የተነሣ ነው፤ ርኅራኄው አያልቅምና ፤ ማለዳ ማለዳ አዲስ ነው፤ ታማኝነትህ ብዙ ነው”
ውድመታቸውና ውርደታቸው የቱንም ያህል ስር የሰደደ ቢሆንም አሁንም ያህዌህ የተስፋ አምላክ ነው፡ ለዚህም ነው አሁንም ኤርምያስ በእንደዚህ አይነት በእንባ የመታጠብ ታሪክ ውስጥ ሆኖ ያህዌህን የሚለማመጠው፣ እንዲህ በማለት፦
“አቤቱ፥ አንተ ለዘላለም ትኖራለህ፤ ዙፋንህ ከትውልድ እስከ ትውልድ ነው ፤ ስለ ምን ለዘላለም ትረሳናለህ? ስለ ምንስ ለረጅም ዘመን ትተወናለህ? አቤቱ፥ ወደ አንተ መልሰን እኛም እንመለሳለን፤ ዘመናችንን እንደ ቀድሞ አድስ ፤ ነገር ግን ፈጽመህ ጥለኸናል፤ እጅግ ተቈጥተኸናል”
ቤተመቅደሱ ከመፍረሱ በፊት የነበረውን መልካም ዘመን እያሰበ ኤርምያስ ያህዌህን እባክህ እንደቀድሞ ዘመን ዘመናችንን አድስልን ይለዋል።
በመሰረቱ ከእንደዚህ አይነት ማጥ ውስጥ ከያህዌህ ሌላ ማን ሊያወጣ ይችላል?
አንዳንዴ በግሌ ሳስብ እኛ ወይም ቤተክርስትያን ያለንበት ዘመን እንደዚህ አይነት የምርኮ ወቅት ይመስለኛል፡ ብዙዎቻችን በትዝታ የምንኖርና የእግዚአብሔርን ጉብኝት ደግሞ በናፍቆትና በመንጠራራት “ካሁን ካሁን ይመጣ ይሆን” እያልን የምንጠብቅበት ዘመን እንደሆነ አስባለሁ፡ ብዙ ነገራችን ተወስዶብንና ፀጉራችን ከጭንቅላታችን ተወግዶ ( ምንም እንኳን እንዳልተወሰደብን ለመሆን ብንሞክርም ) ባዶ እጃችንን ቀርተን እንደገና ያህዌህ እንዲያስበንና ቀና እንዲያደርገን በርሃብ የምንጮህ “ምርኮኞች” ነን፡፡ አዎ ቤተክርስትያን ልክ እንደ ኤርምያስ ሕዝብ በምርኮ ያለች አይነት ስሜት በግሌ ይሰማኛል፡ በመሰረቱ የእኔ ብቻ ሳይሆን አንዳንድ ወገኖችም እንዲህ እንደሚሰማቸው ማወቅ ብቻ ሳይሆን በተለያየ አጋጣሚ የተጫወትነውና የጸለይንበትም እውነት ነው።
የምንክደው ሳይሆን አምነን ተቀብለን እንደገና የያህዌህን ፊት በመፈለግ “እባክህ እንደቀድሞው ዘመን አስበን” በማለት የምንጮህበት ወቅት ይመስለኛል።
የሆነው ሆኖ፣ እኛም ከኤርምያስ ጋር ተደምረን፦
ዘመናችንን እንደ ቀድሞ አድስ ብለን እንጮሃለን። ቸር አምላክ በቸርነቱ ሁላችንንም ያበርታን 🙏
**ወደቻናላችን ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለት ጊዜ ብቻ ይንኩ👉 @biruk351
#ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ
#ሼር_ስለሚያደርጉ_እናመሰግናለን ❤🙏
ከወዴት እንደ ወደቅህ አስብ ?
አሁን አሁን ከመቼውም ጊዜ በበለጠ መልኩ እኛ በፕሮቴስታንቲዝም ውስጥ ክርስትና ብለን የምናስበውና በአዲስ ኪዳናችን፣ በተለይ በተለይ ደግሞ በሐዋርያው ጳውሎስና በሐዋርያው ዮሃንስ በኩል የሚተረክልን ክርስትና ልዩነቱ ሰፊ ሆኖ ይታየኛል:: በእርግጠኝነት የቱ ጋር እንደሳትን ታሪካዊ ሰሌዳ ላይ ጊዜ ማስቀመጥ ቢቸግርም፣ እንደሳትን ወይም ክርስትናን በተንጋደደ መልኩ እንደተረዳነው ወይም ተንከባሎ ተንከባሎ እኛ ጋር የደረሰው ክርስትና ሃዲድ ሳት ማድረጉን መጠቆም ግን የሚያዳግት አይመስለኝም: ሃዲድ ለመሳታችን ወይም መጀመሪያ የተነገረው ቃል ላይ ተጨምሮ ወይም ተቀንሶ በእኛ ጆሮ ቅጭል ብሎ መደመጡን የሚመሰክሩ በርካታ ማስረጃዎችን መጥቀስ ቢቻልም በክርስትና ስም ዘመን ተሻግረው እዚህ የደረሱ የክርስትና varieties or versions መኖራቸው ግን አንዱና ዋንኛው ይመስለኛል።
ሐዋርያው ጳውሎስና ሐዋርያው ዮሃንስ አሁን ከእኛ ጋር ቢሆኑና በየአምልኮ ፕሮግራማችን ታድመው በርካታ ስብከቶቻችንንና ትምህርቶቻችንን እንዲሁም ፀሎቶቻችንን ጨምሮ ቢያደምጡ "ይሄ የትኛው ሃይማኖት ነው?" ብለው ሊጠይቁ ሁሉ የሚችሉ ይመስለኛል: ከዚህ በፊት እንደጠቀስኩት እውቁ የአዲስ ኪዳን መምህር Craig Evans ያሉትን እዚህም ጋር መጥቀሱ ተገቢ እንደሆነ አስባለሁ፤ በአጭሩ እንዲህ ነበር ያሉት፦
“የመጀመሪያው ዘመን ክርስትና ከእኛ ዘመን ክርስትና የተለየ ነው”
እንግዲህ በወንጌላውያን አማኞች ውስጥ ያሉና በ conservatism ነታቸው የሚታወቁ አንድ የአዲስ ኪዳን መምህር እንዲህ ሲሉ መስማት ጉዳዩ ርካሽ አለመሆኑን የሚያሳይ ይመስለኛል።
በግሌ አለመስማማት አልችልም፡፡
በእኛና በመፅሃፉ መካከል ቀድመው የገቡ ሰዎች በጣም ስለሚጮሁ መፅሃፉ የሚናገረውን መስማት ተቸገረን::
ብዙ ሰዎች በክርስትና ተስፋ እየቆረጡና ትንሽ ቆይተው ጥለውን እየሄዱ ያሉት ለምን ይመስልሃል ?
ለምን ይመስላችኋል ክርስትና፣ በተለይ ፕሮቴስታንቲዝም፣ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየቀጨጨና መዐዛው እየተቀየረ የሚሄደው?
ለምን ይመስላችኋል በብዙ ስብከትና ትምህርቶቻችን ሰዎች ለአንድ ሰአት ብቻ ከነቁ በኋላ ወደየቤታቸው ሲመለሱ ሁሉን ነገር ከነመፈጠሩ የሚረሱት?
#ለምን_ይመስላችኋል_ብዙ "#አገልጋዮች" የስነ መለኮት ምሁራንንም ጨምሮ ስለአዲሱ ሰው ሲሰብኩና ሲያስተምሩ ሰንብተው ሁኔታውና ጊዜው ሲመቻቸው የተደበቀው የዘረኝነት ጉንፋን የሚያስላቸው?
ለምን ይመስላችኋል ከማንምና ከምንም የሚበልጥ እውነት እኛ ቤት ነው ያለው እያልን ነገር ግን እንኳን ሰዎች ወደዚህ እውነት ሊመጡ አይደለም ከእኛም ጋር የነበሩት ራሳቸው ጥለውን የሚነጉዱት?
ለምን ይመስላችኋል ወቀጥነውም ፈለጥነውም የሚደቅ ወይም የሚሰነጠቅ ነገር የማናየው?
#ለምን_ይመስላችኋል “እጅ ለእጃችን ተያይዘን ኢየሩሳሌም እንገባለን” ብለን ዘምረን አንድ ሜትር እንኳን ርቀን መሄድ ያልቻልነው?
ለምን ይመስላችኋል “#በቤተክርስትያን” ብዛትና በስነ መለኮት ትምህርት ቤቶች ተከበን ነገራችን ሁሉ ባለህበት እርገጥ የሆነው?
ለምን ይመስላችኋል አገልጋይ የሆንን ብዙዎቻችን በሁለት በኩል የሚለበስ “#ጃኬት” ያለንና እንደ ጆከር ሁሉም ጋር የመግባት ክህሎት የተጠናወተን?
ለምን ይመስላችኋል በአንድ ሺህ አንድ ስብከትና ትምህርታችን እንኳን ሌላውን አይደለም ራሳችንን መለወጥ ያቃተን?
ለምን ይመስላችኋል ባለንበት ማህበረሰብ ውስጥ ከአምናው ዘንድሮ ትርጉም እያጣንና ተጽዕኖ መፍጠር እያቃተን የመጣው?
ለምን ይመስላችኋል ከሁሉም እንሻላለን ብለን በያዝነው ሃይማኖት የሁሉም ጅራት ለመሆን እየተንደረደርን ያለነው?
ለምን ይመስላችኋል አንድ ወቅት ላይ እንደትንታግ የነበሩና ማን ያቆማቸዋል ሲባሉ የነበሩ አገልጋዮች በመሰላቸትና ተስፋ በመቁረጥ ስሜት ተውጠው ዱካቸውን ያጠፉት?
ለምን ይመስላችኋል ጨውም ብርሃንም ልንሆንበት በሚገባ የላሸቀ የኑሮ ዘይቤ ባለው ዓለም ውስጥ እኛው ራሳችን ጨውና ብርሃን የሚያስፈልገን?
ለምን ይመስላችኋል ከመከፋፈልና እርስ በርስ ከመናቆር ሌላ ያን ያህልም ሌሎችን ሊስብ የሚችል አንድነትና ሕብረት የሌለን?
ለእነዚህ መሰረታዊ ጥያቄዎች የተለያዩ መልሶችን መዘርዘር ብንችልም በዋነኛነት ግን ከላይ የጠቀስኩት የተሃድሶ ( ለዛውም ስር ነቀል ) አሳብ ዓይነ-ግቡ ይመስለኛል::
አዎ ከዚህ በፊት እንዳልነው ብዙ ጊዜ ተዘርቶበት አላበቅል ያለን መሬት በሬውን ወይም ገበሬውን በመቀየር ምንም ለውጥ አናመጣበትም፡ ለውጡ መሬቱን መቀየር እንኳን የሚጠይቀን ከሆነ ወደ ኋላ ማለት የለብንም፡ ድሮም ቢሆን Change is only for the courageous
እግዚአብሔር ፋና ወጊ የሚሆኑ ሰዎችን ይስጠን::
እኛ እየተለወጥን ሌሎችን ለመለወጥ ካልሰራን የትም አንደርስም: ክርስትና ስር-ነቀል ለውጥ ያሻል፤ አለበለዚያ ይሄ አሁን የምንመጻደቅበት የፕሮቴስታንቱ ክርስትና የጊዜ ጉዳይ ነው እንጂ RIP እንደሚጻፍበት ምንም ጥርጥር የለኝም - በትንሹ ያለፈውን የ 30 ዓመት ታሪክ ማጥናት በቂ ነው: ልባም ሰው ከ 30 ዓመት ሳይሆን ከአንድ ቀን ብዙ ይማራል፡፡
#አቤቱ_መልሰን_እኛም_እንመለሳለን
ወደ ቻናላችን ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለቴ ብቻ ይንኩ👉@biruk351
#ፀጋና_እውነት_ቤተክርስቲያን_ጅማ
#ሼር_ስለሚያደርጉ_እናመሰግናለን ❤🙏
ክብር ከሕዝቡ ሲለቅቅ!
"የፊንሐስ ሚስት አርግዛ ልትወልድ ተቃርባ ነበር የእግዚአብሔርም ታቦት እንደ ተማረከች፥ አማትዋና ባልዋም እንደ ሞቱ በሰማች ጊዜ ምጥ ደርሶባት ነበርና ተንበርክካ ወለደች። ወደሞትም በቀረበች ጊዜ በዙሪያዋ ያሉት ሴቶች። ወንድ ልጅ ወልደሻልና አትፍሪ አሉአት። እርስዋ ግን አልመለሰችላቸውም፥ በልብዋም አላኖረችውም። እርስዋም የእግዚአብሔር ታቦት ስለ ተማረከች ስለአማትዋና ስለ ባልዋም። ክብር ከእስራኤል ለቀቀ ስትል የሕፃኑን ስም። ኢካቦድ ብላ ጠራችው። (1ሳሙ 4፡19-21)፡፡
እህል ውሃቸው ካልጎደለ፣ እንቅልፍ መኝታቸው ከተደላደለ ለሌላው ነገር የማይጨነቁ ብዙ ሰዎች አሉ፡፡ ከምግብ ያለፈ ራዕይ፣ ከትዳር ያለፈ ጉዳይ፣ ከምድር ያለፈ ሰማይ የሌላቸው ብዙ ሰዎች አሉ፡፡ የሕይወት ዓላማቸው፣ የመኖር ሕልማቸው በምድራዊ ነገር ላይ የተንጠላጠለ ብዙ ሰዎች አሉ፡፡
በቤተክርስቲያን ውስጥም ብዙዎቹ ለአባልነቱ እንጂ፣ ለአስራት መባቸው እንጂ፣ እሁዱን ጠብቀው ለመመላለሳቸው እንጂ ለሌላው ነገር ደንታ የሌላቸው ሰዎች አሉ፡፡ እንደ አሕዛብ ሁሉ ምኞታቸው መማር ሥራ መያዝ፣ ማግባትና መውለድ፣ መክበድና መክበር የሆነ ብዙ የቤተክርስቲያን ሰዎች አሉ፡፡
ታውቃላችሁ፣ እግዚአብሔር በቤቱ ተመቸው አልተመቸው፣ ደላው አልደላው፣ ደስ አለው አላላው ፣ ከሰረም አተረፈ ደንታ የማይሰጣቸው ብዙ ሰዎች አሉ፡፡ የእግዚአብሔር ሕዝብ አደገም አላደገ፣ ተነሳም ወደቀ፣ ግድ የማይላቸው ሰዎች አሉ፡፡
ወገኖች ሆይ፣ የፊንሐስን ሚስት እናስብ! ዙሪያዋን የሞሉ አጽናኞች ቢኖሩም፣ ወንድ ልጅ ብትወልድም፣ ታቦት ተማርኳልና፣ የእግዚአብሔር ክብር ከሕዝቡ ለቅቋልና መጽናናት አልቻለችም፡፡ ከወሊድ የምጥ ስቃይ፣ ከባሏ ሞት በላይ፣ ከአማቷም ሞት በላይ ነፍሷን ያስጨነቀው የእግዚአብሔር ክብር ነው፡፡
ታውቃላችሁ፣ ክብሩ ከለቀቀ መጽናናት አይኖርም፡፡ ክብሩ የሌለበት ልጆች ቢወለዱም፣ አጃቢዎች ቢኖሩም፣ አባላት ቢበዙም መጽናናት ግን የለም፡፡ ክብሩ የሌለበት ፕሮግራም ቢበዛ፣ አምልኮ ቢንዛዛ መጽናናት አይመጣም፡፡ ክብሩ የሌለበት ሰባኪ–ዘማሪ፣ ወንጌል–አስተማሪ፣ እረኛ–መጋቢ፣ ወይንም ማናቸውም አገልጋይ ቢበዛ፣ ጎመን ቢጠነዛ እንጂ መጽናናት አይመጣም!
ታውቃላችሁ፣ ክብሩ በሌለበት የሚቀርብ እልልታ፣ የጨረባ ሰርግ፣ የጨረባ ተስካር ነው! ክብሩ በሌለበት የሚደረግ ሽብሸባ ባዶ ዝማሜና ማዶና ማዶ ነው! የእግዚአብሔር ክብር ከእግዚአብሔር ሕዝብ ሲለቅ ዝማሬው እሮሮ፣ እልልታው መርዶ ነው!
በኢየሱስ ስም እውነተኛ ንቃት ይሁን 🙏
ወደ ቻናላችን ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለት ጊዜ ብቻ ይንኩ👉@biruk351
ክብር ከሕዝቡ ሲለቅቅ!
"የፊንሐስ ሚስት አርግዛ ልትወልድ ተቃርባ ነበር የእግዚአብሔርም ታቦት እንደ ተማረከች፥ አማትዋና ባልዋም እንደ ሞቱ በሰማች ጊዜ ምጥ ደርሶባት ነበርና ተንበርክካ ወለደች። ወደሞትም በቀረበች ጊዜ በዙሪያዋ ያሉት ሴቶች። ወንድ ልጅ ወልደሻልና አትፍሪ አሉአት። እርስዋ ግን አልመለሰችላቸውም፥ በልብዋም አላኖረችውም። እርስዋም የእግዚአብሔር ታቦት ስለ ተማረከች ስለአማትዋና ስለ ባልዋም። ክብር ከእስራኤል ለቀቀ ስትል የሕፃኑን ስም። ኢካቦድ ብላ ጠራችው። (1ሳሙ 4፡19-21)፡፡
እህል ውሃቸው ካልጎደለ፣ እንቅልፍ መኝታቸው ከተደላደለ ለሌላው ነገር የማይጨነቁ ብዙ ሰዎች አሉ፡፡ ከምግብ ያለፈ ራዕይ፣ ከትዳር ያለፈ ጉዳይ፣ ከምድር ያለፈ ሰማይ የሌላቸው ብዙ ሰዎች አሉ፡፡ የሕይወት ዓላማቸው፣ የመኖር ሕልማቸው በምድራዊ ነገር ላይ የተንጠላጠለ ብዙ ሰዎች አሉ፡፡
በቤተክርስቲያን ውስጥም ብዙዎቹ ለአባልነቱ እንጂ፣ ለአስራት መባቸው እንጂ፣ እሁዱን ጠብቀው ለመመላለሳቸው እንጂ ለሌላው ነገር ደንታ የሌላቸው ሰዎች አሉ፡፡ እንደ አሕዛብ ሁሉ ምኞታቸው መማር ሥራ መያዝ፣ ማግባትና መውለድ፣ መክበድና መክበር የሆነ ብዙ የቤተክርስቲያን ሰዎች አሉ፡፡
ታውቃላችሁ፣ እግዚአብሔር በቤቱ ተመቸው አልተመቸው፣ ደላው አልደላው፣ ደስ አለው አላላው ፣ ከሰረም አተረፈ ደንታ የማይሰጣቸው ብዙ ሰዎች አሉ፡፡ የእግዚአብሔር ሕዝብ አደገም አላደገ፣ ተነሳም ወደቀ፣ ግድ የማይላቸው ሰዎች አሉ፡፡
ወገኖች ሆይ፣ የፊንሐስን ሚስት እናስብ! ዙሪያዋን የሞሉ አጽናኞች ቢኖሩም፣ ወንድ ልጅ ብትወልድም፣ ታቦት ተማርኳልና፣ የእግዚአብሔር ክብር ከሕዝቡ ለቅቋልና መጽናናት አልቻለችም፡፡ ከወሊድ የምጥ ስቃይ፣ ከባሏ ሞት በላይ፣ ከአማቷም ሞት በላይ ነፍሷን ያስጨነቀው የእግዚአብሔር ክብር ነው፡፡
ታውቃላችሁ፣ ክብሩ ከለቀቀ መጽናናት አይኖርም፡፡ ክብሩ የሌለበት ልጆች ቢወለዱም፣ አጃቢዎች ቢኖሩም፣ አባላት ቢበዙም መጽናናት ግን የለም፡፡ ክብሩ የሌለበት ፕሮግራም ቢበዛ፣ አምልኮ ቢንዛዛ መጽናናት አይመጣም፡፡ ክብሩ የሌለበት ሰባኪ–ዘማሪ፣ ወንጌል–አስተማሪ፣ እረኛ–መጋቢ፣ ወይንም ማናቸውም አገልጋይ ቢበዛ፣ ጎመን ቢጠነዛ እንጂ መጽናናት አይመጣም!
ታውቃላችሁ፣ ክብሩ በሌለበት የሚቀርብ እልልታ፣ የጨረባ ሰርግ፣ የጨረባ ተስካር ነው! ክብሩ በሌለበት የሚደረግ ሽብሸባ ባዶ ዝማሜና ማዶና ማዶ ነው! የእግዚአብሔር ክብር ከእግዚአብሔር ሕዝብ ሲለቅ ዝማሬው እሮሮ፣ እልልታው መርዶ ነው!
በኢየሱስ ስም እውነተኛ ንቃት ይሁን 🙏
ወደ ቻናላችን ለመቀላቀል ይኼንን ሊንክ ሁለት ጊዜ ብቻ ይንኩ👉@biruk351
