en
Feedback
HASSEN TAJU

HASSEN TAJU

Open in Telegram

Show more
The country is not specifiedThe category is not specified
3 746
Subscribers
+2024 hours
+1547 days
+56730 days
Posts Archive
አንድ ሀሳብ-3_220602_090915.pdf

السلام عليكم

ኢስራእና ሚዕራጅ የተሰኘውን የታላቁ ነብይ (ሶዐወ) ተአምራዊ ጉዞ በተመለከተ ሐሪማ ቲቪ ባዘጋጀው ፕሮግራም ላይ ያስተላለፍኩት መጠነኛ መልዕክት። ሊንኩን እነሆ፦ https://www.youtube.com/watch?v=RXjjNMnolYo&feature=youtu.be

እድሚያቸው 90ዎቹን የተሻገረው እኒሕ ትልቅ ዋርካ- ሸኽ ሙሐመድ አሚን ካሚል- ዛሬ ጎንደር ላይ ወድቀዋል፤ ኢና ሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጅኡን፤ ሐገሬ ትልቅ ሰው አጥተሻልና መጽናናቱን ይስጥሽ፤ እርሳቸውንም አላሕ ለጀነት ይበላቸው።

photo content

የአፍሪካ ሐገራት አምባሣደሮች

photo content

photo content
+4

photo content

ነ ይደብደብ›› ማለት ደግሞ ቃላት ሊገልጹት የማይችል ዉንብድና ነዉ፡፡ እንኳን አህባሽ አይሁድስ ቢሆኑ? አዛዉንት በጎረምሳ እንዲደበደብ የሚፈቅድ ህሊና እጅግ የላሸቀ ነወ፡፡ ድርጊቱ የማህበረሰብን አጠቃላይ ኪሳራ ያመለክታል፡፡ እነዚህን ጋጠወጥ ወጣቶች ያፈራ የ‹‹ዲን›› ትምህርትና ሰበካ፣ለነርሱ ድርጊት ማብራሪያ ለመስጠት የተጉ ‹ሀይማኖተኞችን› የወለደ አስተሳሰብ መርዝ ነዉና ህጻናት ወደማይደርሱበት ቦታ ርቆ መወርወር አለበት፡፡ እነዚህ ሁሉ ሁኔታዎች ተደራርበዉ ዉጥረቶችን አነገሱ፡፡ ሰለፊ/ዉሀቢና ሌሎች ሙስሊሞች በአንድ መጅሊስ ጥላ ሥር አብረዉ መቀጠል የመቻላቸዉን ነገር እጅግ አጠራጣሪ አደረገዉ፡፡ የአህሉሱናዉ ወገንም ለህልዉናዉ እንዲታገል መግፍኤ ፈጠረለት፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ ተጨማሪ መስጊዶችን በኃይል ለመቆጣጠር የተደረጉ ሙከራዎች እንዲከሽፉ በየአካባቢዉ የሚገኘዉ ህዝበ ሙስሊም ባይረባረብ ኖሮ ሁኔታዎች ከዚህም በላይ ደም አፋሳሽ ይሆኑ ነበር፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የደሴ ከተማን መጅሊስ ለመቆጣጠር ሙከራዎች ተደረጉ፡፡ ማለትም በሀይል ከተነጠቀዉ አረብ ገንዳ መስጊድ ዉስጥ የተወሰኑ ወጣቶች ተሰባስበዉ ተመራረጡና አዲስ መጅሊስ መቋቋሙን አዉጀዉ ህጋዊ መጅሊስ መሆናቸዉንና ከእንግዲህ ግንኙነታቸዉን ከአዲሱ መጅሊስ ጋር እንዲያደርጉ ለመንግስት አካላት ደብዳቤ መጻፋቸዉ፣ በተጨማሪም ነባሩ መጅሊስ በአስቸኳይ ቢሮ እንዲያስረክባቸዉ አጠንክረዉ መጠየቃቸዉ ተሰማ፡፡ ከዚህም አልፈዉ የመጅሊሱን ቢሮ በሀይል ለመቆጣጠር አንድ ጁሙዐ ቀጠሮ ያዙ፡፡ በዚህ ጊዜ የደሴ ሙስሊም ማህበረሰብ ‹‹ቀብር እስኪከለክሉን ድረስ አንጠብቅም›› በማለት ይህን ሥርዓት አልበኝነት ለመዋጋት በቁጣ ተነሳ፡፡ በዚህ መሠረት 18 አባላት ያሉት የሀገር ሽማግሌዎች ኮሚቴ ተቋቁሞ ወደመንግስት አካላት በመሄድ መንግስት ህጋዊ ተቋማትን የመጠበቅ ኃላፊነቱን እየተወጣ እንዳልሆነ በማስረዳት ‹‹ተቋሞቻቸዉን የመከላከሉንና የመጠበቁን ኃላፊነት እኛዉ ራሳችን እንወስዳለን፤ከመንግስት የምንፈልገዉ ጣልቃ እንዳይገባብን ብቻ ነዉ›› ሲልም ቁርጥ አቋሙን አሳወቀ፤ ህጋዊዉን ተቋም ከነጣቂዎች የመከላከሉን ተግባርም ማከናወን ጀመረ፤ነጣቂዎቹ ይህን ኮሚቴ ተራምደዉ ተቋም በመንጠቅ ከሰፊዉ ሙስሊም ማህበረሰብ ጋር ለመጋጨት ድፍረት ስላላገኙ የደሴ መጅሊስ ከነጠቃ ሊድን ቻለ፡፡ ይህ የደሴ የሀገር ሽማግሌዎች ኮሚቴ በኋላ ላይ ከዞኑ እስልምና ጉዳዮች ጋር በመተባበር በደሴ ባህል አንባ አዳራሽ ዉስጥ የግማሽ ቀን ህዝባዊ ኮንፈረንስ አድርጎ ጋብዞን ነበር፡፡ በኮንፈረንሱ ላይ እኔ፣ሸኽ ቃሲም ታጁዲን፣ሸኽ ሙሀመድ አወሎና ኡስታዝ መንሱር ዘይኑ ተገኝተን የአዉራዉን የእስልምና አቅጣጫ ምንነት፣የሀበሻ ዑለሞች፣በተለይም የወሎ መሻኢኾች ይህን የእስልምና አቅጣጫ ለመጠበቅና ለማስፋፋት የተጫወቱትን የላቀ ሚናና የከፈሉትን መስዋእትነት፣እንዲሁም የአሁኑ ትዉልድ የአዉራዉን እስልምና መልእክት ለመታደግ መትጋት እንደሚገባዉ መልእክት አስተላልፈን ተመልሰናል፡፡ አዳራሹ ከወጣት እስከሺማግሌ የተለያየ ዕድሜ ደረጃ ባላቸዉ ታዳሚዎች ከአፍ እስከገደፉ ሞልቶ እንደነበር አስታዉሳለሁ፡፡ ሸኽ አህመድ ሶሂሀይንን ጨምሮ አንቱ የተባሉ አካባቢዉ ዑለሞችም ተሳትፈዉ ነበር፡፡ ይህ ኮንፈረንስ በሌሎች ወገኖች ላይ ከፍተኛ ንዝረት ፈጠረ፡፡ አዉራዎቹ ድንጋጢያቸዉን መደበቅ አልቻሉም፡፡ በማህበራዊ ድረ-ገጽ ስድብና ዛቻ አዘል መልእክቶችን እስከማስተላለፍ ድረስ ሚዛን ሳቱ፡፡ ‹‹የቅጥፈት ማሽነሪዎቻቸዉ›› ኮንፈረንሱን ካለፈዉ መንግስት አካላት ጋር ለማገናኘት አብዝተዉ ለመዋሸት መገደዳቸዉ ማሚቶዉ ሩቅ እንደተሰማ አረጋጋጭ ነበር፡፡ የደሴዉ ኮንፈረንስ በቄራ (ሰላም) መስጊድ በተዘጋጀ ‹‹የአንድነትና የሰላም›› ጉባኤ ላይ ጥላዉን አጥልቶበት ዋለ፡፡ ከዚያ ወዲህ ሌሎች አስደማሚ ህዝባዊ ኮንፈረንሶችም በተለያዩ ሀገሪቱ ክፍሎች ተከናወኑ፡፡ የጥናት ኮሚቴዉ ከተመሠረተ ወዲህ ብቻ እጅግ በርካታ አዛዉንት ኢማሞች በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች ተባረዋል፤ድብደባዎችና ግድያዎች ተከናዉነዋል፤ ንብረቶች ወድመዋል፤ የሀበሻዉን የዒልምና የተርቢያ ማዕከል ዳናን ጨምሮ ሌሎች የኢልም ማዕከላትን ለማፍረስ የዛቱ ወጣቶች ስለነበሩ ከፍተኛ ዉጥረት ነግሷል፤ በወሎ ሶቃ ከተማ ሸኽ ሁሴን የተባሉ ዐሊም አዝመራ ‹‹ኹራፍይ›› ስለሆኑ ተብሎ ተቃጥሏል፤ የዳናዉ ሸኽ ኢማም ቤታቸዉና መስጊዳቸዉ ተቃጥሎ ህይወታቸዉን ለማትረፍ እዚሁ አዲስ አበባ ዉስጥ ከአንድ ወንድም ቤት ተጠግተዋል፤ በጥቅሉ ባለፉት ወራት የዓሊሞች እንባ አብዝቶ ፈሷል፤ሰቆቃቸዉ በርትቷል፡፡ እነዚህ ሁሉ ዕዉነታዎች አንድ መሠረታዊ ጥያቄ ያጭራሉ፤ ‹የግጭትና ሁከት ቋት ከሆነዉ አስተሳሰብ ባለቤቶች ጋር በአንድ ተቋም ዉስጥ አብሮ መቀጠል ይቻላልን? የሰነድ ዝግጅት፣ስምምነት፣ፊርማ ወዘተ ብቻቸዉን ይህን ሰቆቃ ማስቀረት ይሆንላቸዋልን?› ለዚህ ጥያቄ የምንሰጠዉ ልባዊ መልስ ቀጣዩን ሴናሪዮ ይወስነዋል፡፡ ተቋም በባህሪዉ ተመሳሳይ ራዕይ ያላቸዉ ግለሰቦች ራዕያቸዉን በጋራ ለማስፈፀም የሚመሠርቱት አካል ነዉ፡፡ ተፃራሪ ራእይ ያላቸዉን ወገኖች በአንድ ተቋም ስር ‹‹በፖለቲካ ገመድ›› መጠርነፍ ተቋሙን የሥራ ሳይሆን የጦርነት አዉድማ እንደሚያደርገዉ ጥርጥር የለዉም፡፡ ስለዚህ አሁን በተያዘዉ ያልተጠና አቅጣጫ ከተኬደ መጭዉ ዘመን የሁከት እንደማይሆን፣የበለጠ ደሞችን እንደማያፋስስ ምንም ዋስትና የለም፡፡ በእርግጥ ሁከት ‹‹ቢዝነስ›› ለሆነላቸዉ ‹‹የድህነት ልዑላን›› /Lords of poverty/ ይህ ዜና ሰርግና ምላሽ ሊሆን ይችላል፡፡ ለአጠቃላዩ ሙስሊም ግን የመከራ ቸነፈር ነዉ፡፡ ለሀገርም ከፍተኛ ያለመረጋጋት ምንጭ እንዳይሆን ያሰጋል፡፡ ከዚህ አኳያ ቀጣዩ ሂደት በጥንቃቄ መታየት አለበት፡፡ በአሁኑ ሰዓት በሙስሊሙ ህብረተሰብ ዉስጥ ያለዉ ፍልሚያ በአናርኪና በተደራጀ ዕዉቀት፣እንዲሁም በአናርኪና በሥርዓት መካከል መሆኑ መታወቅ አለበት፤ አናርኪስቶች የተደራጀ ዕዉቀትን ከሸሹት ይበልጥና በላይ ህግንና ሥርዓትን የጠበቀ የተቋም ለዉጥን ይሸሻሉ፡፡ ዕዉቀትና ሥርዓት ካሸነፈ የተቋማችንን የዘመናት ድክመት በወጉ አርመን ጠንካራ፣ ቋሚና ዘለቄታዊ የማድረግ ዕድላችን ፍሪያማ ይሆናል፡፡ በተቃራኒዉ አናርኪ ከረታ የዕዉቀትና የአስተዳደር ሥርዓት አልበኝነት ከአሁኑ በከፋ ሁኔታ ይነግሳል፡፡ ስለዚህ በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች የሚገኙ ወጣቶችና ሌሎች የሙስሊሙ ህብረተሰብ ክፍሎች በየአካባቢዉ እተደራጁና እየተቀናጁ አናርኪን ከመገሰጽና ከመቆጣጠር ዉጭ ሌላ ምርጫ የላቸዉም፤ ሀገርን ከብጥብጥ፣ህብረተሰብን ከሰላም እጦት፣ዲኑንም ከጥቃት፣መስጊዶችን ከወረራ፣መሻኢኾችን ከእንግልት መከላከል የሚቻለዉ በዚህ መንገድ ብቻ ነዉ፡፡ የሀገሩን መልካም ገፅታ በመጠበቅ አሁን ያለዉን ሀገራዊ ለዉጥ ማስቀጠል ከሚሻ ሙስሊም ዜጋ ሁሉ ትከሻ ላይ ይህ ኃላፊነት ወድቋል፡፡ (ክፍል 9 ይቀጥላል)

የዉይይቶቹ ተፅእኖ- ክፍል 8 (በ-ሀሰን ታጁ) @ @ @ @ ህዝባችን በተደራጁ ዕዉቀቶችና በሥርዓት ይመራ ዘንድ ያደረግናቸዉ የዑለሞች ዉይይቶች ዜና በአዲስ አበባም ሆነ ከአዲስ አበባ ዉጭ ካሉ ሌሎች ዑለሞች ዘንድ ሲሰማ ከፍተኛ መነቃቃትን ፈጠረ፡፡ በተለይም 4 ለ4 ያደርግነዉ የሀሳብ ሙግት ማሚቶዉ በስፋት ተሰማ፡፡ የአዉራዉን የእስልምና አቅጣጫ ባለቤቶች ከድንዘት ያነቃ፣ተስፋቸዉ እንዲያንሰራራ ያደረገ፣አስተሳሰቡን ከመቃብር ዓለም የቀሰቀሰ ኃይለኛ ድምፅ ነበር፡፡ የዚያን ሰሞን በርካታ ስልኮች ከየአቅጣጫዉ ተደወሉ፡፡ የመሻኢኽ ምርቃቶች ተዥጎደጎዱ፡፡ ዱዐዎች በብዛት ተደረጉ፡፡ ከዚህ በላይ ግን ዑለሞች በየአካባቢዉ እየተሰበሰቡ ለኛ ሀሳብ ያላቸዉን ድጋፍ ይገልጹ ጀመር፡፡ ለምሳሌ 200 ያህል የአማራ ክልል መሻኢኾች ባህርዳር ከተማ ላይ ተሰብስበዉ በመወያየት ሀሳባችንን ደግፈዉ የአቋም መግለጫ አወጡ፡፡ መግለጫዉን በሸኝ ደብዳቤ አስደግፈዉም በአምስት ወኪሎቻቸዉ አማካይነት ወደአዲስ አበባ ላኩት፤ወኪሎቹ ከተቋማዊ ለዉጥ ጥናት ኮሚቴዉ ዘንድ በአካል በመቅረብ ጉዳያቸዉን አስረድተዉ መልእክቱን አስረከቡ፡፡ ከመልዕክት አድራሾች መሀል የጎንደሩ ዐሊም ሸኽ አሊ ጀበል፣የእንፍራንዙ ሙፈሳር ሸኽ ኢብራሂም መሀሊና የሀጅ ራፊእ ደረሳ የሆኑት ሙሀዲስ ሸኽ ሁሴን ዳወቻ ከወሎ ይገኙበታል፡፡ ደሴ፣ ወልደያና ዳና ላይም ተመሳሳይ የድጋፍ ስብሰባዎች ተደረጉ፡፡ የአቋም መግለጫዎች እየወጡና ደብዳቤዎች እየተጻፉ ወደአጥኝዉ ኮሚቴ ቢሮ መላካቸዉን ቀጠሉ፡፡ በተለይም በኦሮሚያ ክልል ያየነዉ ስሜት እጅግ ተስፋ ሰጭ ነበር፡፡ ‹‹መላ ኦሮሚያ ዉሀብያ ሆኗል›› የሚባለዉን ትርክት እጥያቄ ዉስጥ የከተተ ነበር፡፡ በመጀመሪያ በኦሮሚያ ዉስጥ የሚገኙ የ300 ሀሪማ ኸሊፋዎች ተሰባስበዉ በፊርማቸዉ ደገፉን፡፡ ቀጥሎ የኦሮሚያ ዑለሞች ስብሰባና ድጋፍ ተከተለ፡፡ ሁሉም ሀሳባችንን የሚያጸድቅ መግለጫና ደብዳቤ እየያዙ የአጥኝ ኮሚቴዉን ቢሮ አጨናነቁት፡፡ ይህ የስሜት መነቃቃት በወጣቱም ዘንድ መስተዋል ጀመረ፡፡ ‹‹አዉራዉን የእስልምና አቅጣጫ ለመታደግ የኛ ሚና ምን ይሁን?›› የሚል ዓይነት ቃና ያላቸዉ ጥያቄዎች ከየአካባቢዉ ይደርሱኝ ጀመር፡፡ የአዲስ አበባ ወጣቶች -በኑርና በአንዋር መስጊዶች ወጣቶች መሪነትና አስተባባሪነት- ራሳቸዉን አደራጅተዉና ሀሳብ ቀምረዉ የአጥኝዉን ኮሚቴ በር በማንኳኳት ‹‹የቅን አባቶቻችን የእስልምና መስመር፣ የአዉራዉ የዲን ጎዳና ጉዳይ አሳስቦናል›› የሚል አንደምታ ያለዉ ጠንካራ መልእክት አደረሱ፡፡ የአዲስ አበባንና የፌዴራል መጅሊስ ቢሮዎችን አንኳኩተዉም ይንኑ መልዕክት በአፅንኦት አስተላለፉ፡፡ በአዲስ አበባ መጅሊስ ላይ ተፅእኖ በማሳደርም መስጊዶችን ለሌላ ወገን ያለአግባብ በማስረከብ ላይ የነበሩት የቀድሞዉ ፕሬዝዳንት ከስልጣን እንዲባረሩና የአጠቃላይ ሥራ አስፈጻሚዉ ለዉጥ ዕዉን እንዲሆን አደረጉ፡፡ ይበልጥ በተደራጀ መልኩ ለመሥራትም መክረዉና ዘክረዉ የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር በመመሥረት በትጋት ይንቀሳቀሱ ጀመር፡፡ ይህ ማህበር የካቲት 24/2011ና ሚያዝ 13 በአዲስ አበባ ኑርና አንዋር መስጊዶች የተደረጉትን ታላላቅ ህዝባዊ ኮንፈረንሶች ለማደራጀት የበቃና ሌሎችንም ተግባራት በማከናወን ላይ የሚገኝ ተስፋ ሰጭ ማህበር ነዉ፡፡ ከ4 ለ4 የኡለሞች ዉይይት በኋላ የፌስቡኩ ዓለም እየተቀየረ ሄደ፤ አዉራዉን የእስልምና አቅጣጫ ለመታደግ የሚሰሩ አዳዲስ ብዕረኞች መድረኩን መያዝ ጀመሩ፡፡ የግልገል አስተሳሰቦች አቀንቃኞች ሚና እየኮሰመነ ሄደ፤ በፌስቡኩ ዓለም አምቶና ዋሽቶ ማምለጥ ለ‹‹ቅጥፈት ማሺነሪዎች›› አስቸጋሪ እየሆነ መጣ፤ ይህ ትልቅ እመርታ ነዉ፡፡ ከአወሊያዉያን ወገን ‹‹እርቲባክ›› ሊሰኝ የሚችል ሁኔታ ነበር የተፈጠረዉ፡፡ እናም የዉይይቶቹን ማሚቶ ድምፀት ለመቀነስ የተለያዩ ስልቶችን መከተል ጀመሩ፡፡ የሀሰት ዜናዎችና ስም ማጥፋቶች አንደኛዉ መንገድ ነበር፡፡ ከስም ማጥፋት ዘመቻዉ በተጓዳኝ እመሬት ላይ ያለዉን ተጨባጭ ለመቀየር መስጊድ የመንጠቅና የክልልና የአካባቢ መጅሊሶችን የማፈራረስ ንቅናቄዉ ቀጠለ፡፡ በዚህ ረገድ የደሴዉን ሸዋ በር መስጊድ ነጠቃ የመጀመሪያዉ ነበር፡፡ በሌላኛዉ ወገን የተፈጸመ ታሪካዊ ስህተት ነበር፡፡ ከፍተኛ አለመተማመንን ፈጥሮ በዑለሞች ዉይይት ላይ ሳይቀር ጥላ አጥልቷል፡፡ ‹‹የሸዋ በር መስጊድ ወደሙስሊሞች ተመለሰ›› የሚል ዜና በአወሊያዉያን የፌስቡክ ገጾች መለቀቁ የድርጊቱ ፈጻሚዎችና አጋሮቻቸዉ ከነርሱ ዉጭ ያለዉን ሙስሊም ህብረተሰብ እንደሙስሊም እንደማይቀበሉ ያመላከተ ሆነ፡፡ ዕዉነተኛዉ አቋማቸዉ ይህ ሆኖ ስለአንድነት በየመድረኩ የሚያደርጉት ሰበካ የታክቲክ ጉዳይ እንደሆነ ጠቋሚ ነበር፡፡ ድርጊቱ የተፈጸመዉ የሀይል እርምጃ ተወስዶ፣ህጻናት አሰቃቂ ድብደባ ተፈጽሞባቸዉና ሰዉ ተጎድቶ መሆኑ ደግሞ ‹‹ከነዚህ ሰዎች ጋር አብሮ መቀጠል ይቻላልን?›› የሚል ጥያቄ አስነስቷል፡፡ በረዥሙ የኢትዮጵያ እስልምና ታሪክ ዉስጥ በሀይማኖታዊ አስተሳሰብ (መዝሀብ) ልዩነት ሰበብ አንዱ የሌላዉን ደም ሲያፈስ ይህ መጀመሪያዉ ይመስለኛል፡፡ የወደፊቱ ጊዜ እጅግ ፈታኝ ሊሆን እንደሚችል አመላካች ነበር፡፡ ይህ የደሴ በሽታ ወደኮምቦልቻ ተሸጋግሮ እዚያም ህጻናት ተደበደቡ፤የመስጊድ ነጠቃ ሙከራዎች ተደረጉ፤ ህይወት ጠፋ፤ የኮምቦልቻ ሙስሊም ማህበረሰብ በሁኔታዉ ተማሮ ከተማዉን ያንቀጠቀጠ ሰላማዊ ሰልፍ አደረገ፤ግድያዉን ፈጽመዋል ተብለዉ የተጠረጠሩ ግለሰቦች ታሰሩ፡፡ ደሴ ላይ ሌላ አስገራሚ ስህተት ተፈጸመ፤ የሸዋ በርን መስጊድ የነጠቁ ወገኖች አረብ ገንዳንም ደገሙት፡፡ የሚገርመዉ የመስጊድ ነጠቃዉ ተባባሪ በመሆን የመስጊዱ ኢማም የሆኑት የሸኽ ሙሀመድ ሀሚዲን ወንድም የሆኑት ሸኽ ሀሰን ሀሚዲን መሆናቸዉ ስህተቱን በጣም ጎላና የበረታ አደረገዉ፡፡ ነገሮችን ወደነበሩበት ለመመለስ በአወልያዉያንም ሆነ በተቋማዊ ለዉጥ ጥናት ኮሚቴዉ በኩል ሁነኛ ጥረት አለመደረጉ በነዚህ ሁለት አካላት ላይ የበለጠ ተስፋ እንድንቆርጥና ቀጣዩን ሂደት በጥርጣሬ እንድናይ አደረገን፡፡ ይህ ስሜት በመሻኢኾች ዘንድም እንደተጋባ ለመረዳት ችያለሁ፡፡ ይባስ ብሎ በሀረር፣በሶማሌና በአንዳንድ የኦሮሚያ አካባቢዎች መጅሊሶችን አግባብ ባልሆነ መንገድ የመተካት ሂደት ተከናወነ፡፡ ተብሊግ ጀማዐ አባላት በአዲስ አበባ ብቻ በ27 መስጊዶች የተለመደ የዳዕዋ ሥራቸዉን እንዳያከናዉኑ ታገዱ፤ በክልሎችም እንደዚሁ ተመሳሳይ ዜናዎች ይሰሙ ጀመር፡፡ ሻሸመኔ ላይ እጅግ አሳፋሪ ድርጊት ተፈፀመ፤ ይኸዉም ዕድሚያቸዉ ከአሥራዎቹና 20ዎቹ ዉስጥ የሆኑ የሰለፊ/ዉሀቢ ወጣቶች የ70 እና የ80 ዓመታት ሙስሊም አዛዉንቶችን መሬት ላይ ጥለዉ በቡጢ ሲነርቱ በሶሻል ሜዲያ ተለቀቀ፡፡ ሁነቱ እጅግ አሰቃቂም አሳፋሪም ነበር፤ ከዚያ ይበልጥ አሳፋሪዉ አወልያዉያን የልጆቹን ድርጊት ምክንያታዊ ለማድረግ የተጓዙበት ርቀት ነዉ፡፡ ‹‹41 ቀን ስለሆነዉ አታጋንኑ››፤ ‹‹አህባሽ መስለዋቸዉ ነዉ የደበደቧቸዉ›› ወዘተ የሚል ዓይነት ቃና ያላቸዉ ፅሁፎች አከታትለዉ አወጡ፡፡ ክፉ ሥራ 41 ቀን ቀርቶ 41 ሺ ዓመታት ቢኖረዉ እንኳ መነቀፍ አይገባዉምን? ሺዎች ዓመታት የሆናቸዉን የፊርዐዉን፣የአቡጀህል፣የአቡለሀብ ወዘተ ክፉ ሥራዎች እያነሳ የሚያስጠነቅቅን ቁርአን እከተላለሁ ከሚል ወገን እንዲህ ዓይነት አስተያየት መስማት በእጅጉ የሚያሳዝን ነዉ፡፡ ለጊዚያዊ ጥቅም ሲባል ቋሚ መርህን መጨፍለቅ አደጋዉ ትዉልዳዊ ነዉ፡፡ ‹‹ወለቀድ ከረምና በኒ አደመ›› የሚል ቁርአን እያነበቡ ‹‹አህባሽ ስለሆ

በማፅናት እዉነተኛ አንድነቱን ያደረጃል እንጅ አግላይ ሊሆን አይችልም፡፡ *3. የአካዳሚ ነፃነት* በዲን ትምህርት መስክ አህሉሱና ሰፊ የአካዳሚ ነጻነትን ይፈቅዳል፡፡ አዝሀር ዩኒቨርሲቲ በኦፊሴል አሽዐርያ ቢሆንም ሺዐን ጨምሮ ሌሎች አስተሳሰቦች ይጠናሉ፡፡ የሺዐ የፊቅህ መዝሀብ በትምህርት ማዕዱ ይሰጣል፡፡ በኛ ሀገር የዒልም ማዕዶች የግሪክ ፊሎዞፊና ሎጂክ ሳይቀር ማዕድ ተደርጎ ይሞጠላል፡፡ ከተፍሲር ማዕዶቻችን ላይ ከሚቀርቡ ኪታቦች መሀል የዘመኽሸሪ ‹‹አልከሻፍ›› ይገኝበታል፡፡ ስለዚህ አዉራዉ የእስልምና መንገድ ገዥ ሆኖ በሰነዱ ዉስጥ መካተት የሌሎች ወገኖችን የትምህርት ነጻነት አያቅብም፡፡ እንዲያዉም በእጅጉ ያበረታታል፡፡ በአህሉሱና ዕዉቀት አይታቀብም፤ አሁን ያሉ አንዳንድ ሴክቶች እንደሚያደርጉት ‹‹የእገሌን ኪታብ አታንብቡ፤ እገሌን አትቅረቡ›› እየተባለ መረጃ አይገደብም፤ በሀሳብ በተለየ ወገን ላይ የጥላቻ ዘመቻ ወይም የአስተሳሰብ ሽብርተኝነት አይፈፀምም፡፡ አዉራዉ የእስልምና መንገድ ሲነግስ ዒልም ከእስር ይፈታል፤ የማወቅ ነጻነት በሩ በሰፊዉ ይከፈታል፤ የተለየ ነገር ወይም በተለየ መንገድ ማሰብ የወንድማማችነትንና የፍቅርን ገመድ አይበጥስም፤ አዕምሮ የሚገባዉን ክብርና ደረጃ ያገኛል፡፡ *4. የመጅሊስ ተሀድሶ ነገር* የሀሳብ ፍልሚያዉ መጅሊስ እንዳይታደስ ለመከላከል አድርገዉ የሚያስቡ የዋሆች አሉ፡፡ የመጅሊስ ተሀድሶ ንቅናቄ የተጀመረዉ በ2004 አይደለም፡፡ ከዚያ በፊት ብዙ ጥረቶች ተደርገዋል፣ሸኽ ቃሲም ታጁዲን፣ሀጅ ሙሀመድ ወሌና ሌሎች ሌሎች አባቶች ለእስር ተዳርገዉ ከህይወታቸዉ 3 ዓመታትና ከዚያ በላይ ዋጋ ከፍለዋል፡፡ እንዲያዉም የዚያን ጊዜዉ ንቅናቄ ያነሳቸዉ ጉዳዮች ከመጅሊስም በላይ ከፍ ያሉና ይበልጥ የበሰሉ ነበሩ፡፡ . መጅሊስ መታደስ እንዳለበት የማይስማማ ወገን የለም፤ የተለያዩ ሀሳቦች ሊቀርቡ የሚችሉት እንዴት ይታደስ? በሚለዉ ጥያቄ ዙሪያ ነዉ፡፡ በኛ በኩል ተሀድሶዉ ሶስት ግቦችን ያሳካ ሊሆን እንደሚገባ በፅኑ እናምናለን፡- *ሀ*. የፖለቲካ ጣልቃ ገብነትን እስከመጨረሻዉ ማስቀረት አለበት፡፡ መጅሊስ እስከ 1983 እጅግ የተከበረ፣ መሪዎቹም የታፈሩ፣የስልጣን ሽግግር ሂደቱ የተሳለጠና ሽኩቻ ያልበዛበት በዓሊሞች የሚመራ ተቋም ነበር፡፡ ከ1988 ወዲህ ግን ፖለቲካዉ እጁን በጣም አስገባ፤ ለዚህ የተጠቀመዉ አንዱ መሳሪያ የምርጫ ሂደት ነበር፡፡ ሂደቱ እስካሁን ድረስ ቀጠለ፡፡ ስለዚህ የመንግስትን ጣልቃ ገብነት ልናስቀር የምንችልበት አጋጣሚ አሁን ነዉ፡፡ ‹‹የህወሀት›› የምንለዉን መጅሊስ በግልጽ ወይም በስዉር የፖለቲካ ጉልበት ለማስወገድ መጣር መጭዉን መጅሊስ ‹‹የአብይ›› ተሰኝቶ በከፊሉ ማህበረሰብ ዘንድ እንዲጠላ ከማድረግ ያለፈ ትርፍ አያመጣም፡፡ መጭዉ መንግስትም የተለመደዉን ጣልቃ የመግባት ሂደት ይከዉናል፡፡ መጅሊስን የሚያፈርሰዉ መለስም ይሁን አብይ ዉጤቱ ተመሳሳይ ነዉ፡፡ መንግስት ጣልቃ ገብቶ የመጅሊስ አመራሮችን ያወርድ ዘንድ የሚደረገዉ ዉትወታና ግፊት አደጋዉ እዚህ ላይ ነዉ፡፡ የአንድ ነገር የአፈጻጸም ሂደት (process) ከዉጤቱ እኩል አስፈላጊ ነዉ፡፡ *ለ*. ተሀድሶዉ ህግንና ሥርዓትን በጠበቀ መልኩ መከናወን አለበት፤ ጩኸት ተፈርቶም ህግ አይጣስም፡፡ ካልሆነ ሥርዓት አልበኝነት ይቀጥላል፡፡ እናም በቋሚ ህግ የሚመራ የተረጋጋ ተቋም የመገንባት እድላችንን ያቀጭጨዋል፤ ያዘገየዋል፡፡ በ2008ና 9 በኢህአዴግ አስተዳደር ላይ የተነሳዉን ተቃዉሞ ተከትሎ የተከናወነዉ ለዉጥ የሀገሪቱንም ሆነ የፓርቲዉን ህግና ሥርዓት በጠበቀ ብቻና ብቻ ነዉ የተከናወነዉ፡፡ ሥርዓት ላለመጣስ ሲባል ለስያሜ እንኳ ልዩ ጥንቃቄ ተደርጓል፤ በዚህ መሠረት የትግራይና የሶማሌ ክልሎች መሪዎች ም/ርእሰ መስተዳድር፣ አቶ ታከለ ኦማ ምክትል ከንቲባ ተሰኝተዋል፡፡ መጅሊስም ልክ እንደዚሁ በህግና በሥርዓት ብቻ ይለወጥ ዘንድ መሠራት ይኖርበታል፡፡ . *ሐ*. መልካም አመራሮችን ማስቀመጥ ሕጋዊ ሂደቱን ተከትሎ ያለማንም ጣልቃ ገብነት ሲከናወን ድርብርብ ድል ይሆናል፡፡ ኮንፈረንሱ ከነዚህ ግቦች መካከል አንዱን ከሳተ ለጊዜዉ ስኬት ቢመስልም ዉሎ አድሮ ጉዳት ማስከተሉ አይቀርም፡፡ . እነዚህን ሶስት ግቦች ያለመነጣጠል ከማሳካት ዉጭ ሌላ ምርጫ የለንም፡፡ የኛ ፍላጎት የዉጤት ብቻ ሳይሆን የሂደት ጥራትን ማረጋገጥ ጭምር ነዉ፡፡ ‹‹አልጋየቱ ቱበሪሩል ወሲለህ›› /የትም ፍጭዉ ዱቄቱን አምጭዉ/ ከእስልምና ትምህርትና መርህ ጋር ስለሚጻረር በዚህ ረገድ የሚደረግን የሀሳብ ትግል የመጅሊስን ተሀድሶን ከማስተጓጎል መተርጎም አጓጉል እሳቤ ነዉ፡፡ (ክፍል 8 ይቀጥላል)

*የዉይይት ማጠናቀቂያና ቀጣይ ሁነቶች- ክፍል 7* *(በ-ሀሰን ታጁ)* *µ µ µ µµ µ µ µµ µ µ µ* 1. *የመጨረሻ ግንኙነት* . ባለፉት ሁለት ተከታታይ ፅሁፎች የቃኘነዉ የ4 ለ4 ዉይይት በተደረገ በቀናት ዉስጥ የ38ቱ ዑለሞች ስብስብ ሳልስ ተጠራ፤ ዓላማዉ ተንጠልጥለዉ የቀሩ እና ያላግባቡ አጀንዳዎችን ዳግም ፈትሾ እልባት መስጠት ነበር፡፡ እስብሰባዉ መጀመሪያ ላይ የ4 ለ4 ዉይይቱን ዉጤት አስመልክቶ ሪፖርት እንድናቀርብ እኔና ዶ/ር ጀይላን ተጋበዝን፡፡ በመጀመሪያ ዶ/ር ጀይላን ባጭሩ አቀረቡ፡፡ በይዘቱ የአንድነትን አስፈላጊነት የሚያጸናና ሰነዱ በጥቅል አጀንዳዎች ላይ ብቻ ያተኩር ዘንድ የሚጋብዝ ነበር፡፡ በተጨማሪም ለአንድነት ሲባል ብዙ ነገሮች እንደተተዉ (ተናዙል) አተቱ፡፡ በጥቅሉ ‹‹የተደራጁ ዕዉቀቶች›› ያልናቸዉ የዋናዉን እስልምና ወካይ አስተሳሰቦች እሰነዱ ዉስጥ እንዲገቡ ያለመፈለግ አቅጣጫና ዉሳኔ መኖሩን የሚጠቁም ሪፖርት ነበር፡፡ . እኔ በበኩሌ የዉይይቱን አጠቃላይ ሂደትና የኛን ‹አርጊዩመንት› በጥቅሉ ካብራራሁ በኋላ፣በተለይም የተደራጁ የዐቂዳ መዝሀቦች እሰነዱ ዉስጥ በግልጽ ይካተቱ ዘንድ የፈለግንበትን 9 ተጨማሪ ምክንያቶች ዘረዘርኩ፡፡ . ከዚህ በኋላ ሞቅ ያሉ ዉይይቶች ተደረጉ፡፡ አንዳንዶቹ አስተያየቶች ፡- ‹‹ጠብ ያለሽ በዳቦ›› ይመስሉ ነበር፡፡ ለምሳሌ ኢብራሂም የተባለ ደረሳ ‹‹ሱፍዮች ጫት ከመቃም እና ሲጋራ ከማጨስ በስተቀር ሰዎችን ለመከሳብ (ወደናንተ ለመሳብ) ጥረት አታደርጉም›› ሲል ወቀሰ፤ ‹ሰበካ ፈጽሙና ወጣቱን ዉሰዱት› ማለቱ አድርጌ በበጎ ተረዳሁለት፡፡ ቋንቋዉና ሀሳቡን ያቀረበበት መንገድ ግን የአደብ እንጥፍጣፊ የሌለዉ ነበር፡፡ ሌላ ወጣት ደግሞ የፊቅህ መዝሀቦች ብዙ የሚያከፍሩ ሀሳቦች የታጨቁባቸዉ እንደሆኑ በድፍረት ተናገረ፡፡ ታዳሚ ዑለሞች እነዚህን ሁለት አስተያቶች መቋቋም አልቻሉም፡፡ የአደም በዳኔ መስጊድ ኢማም የሆኑት ሸኽ አህመድ አወሎ ከመቀመጫቸዉ ተስፈንጥረዉ በመነሳት መናገር ጀመሩ፡፡ ልጁን ክፉኛ ወቀሱት፤ ‹‹ሰፊናን እንኳ በወጉ አልቀራህም፤ላ ወላ ያለችዉን ቃል መፈሰርም አትችልም›› እያሉ ገሰጹት፡፡ የቀድሞዉ የሸሪዐ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ሸኽ ሲራጅ ማህሙድም እየተንቀጠቀጡና እንባ እየተናነቃቸዉ ይናገሩ ጀመር፡፡ ሀጅ ዑመር ሊያስቆሟቸዉ ቢሞክሩ አልተቀበሉም፡፡ ‹‹ለእንዲህ ዓይነት አደብ ያጣ ስብሰባ ለወደፊቱ እንዳትጠሩኝ›› ማለታቸዉ ብቻ ይታወሰኛል፡፡ ሸኽ ቃሲምም የዚያን ቀን፡- ‹‹ገንዘብ ከፈለጋችሁ ዉሰዱ፤ ስልጣኑንም አንጋራችሁም፤ ዐቂዳችንን ግን እባካችሁ ተዉልን›› በማለት እንባ እየተናነቃቸዉ በምሬት ሲናገሩ ትዝ ይለኛል፡፡ ታላቁን ዐሊም ሸኽ ሙሀመድ ታጁዲንን ‹‹ቄስ›› በማለት የተሳለቁ፣ በርካታ ዑለሞችን ሙሽሪክ ወይም ሙብተዲዕ እያሉ ያነወሩ፣ ሸኽ ሙሀመድ ሳኒ ሀቢብን ካፊር ያሉ፣ ሌሎች አካላዊ ስነ ልቦናዊና ማህበራዊ ግፎችን በዑለሞችና በሌሎች ሙስሊሞች ላይ የፈፀሙ ግለሰቦችን የወለደ ያስተሳሰብ ማዕቀፍ ባለቤቶች ብዙሀን ዑለሞች ለተመሩበት የአቂዳ መስመር ዕዉቅና ለመቸር ሲያቅራቸዉ ማየት ምቾት እንደሚነሳ ሸኽ ቃሲም በአፅንኦት ገለጹ፡፡ . ሀጅ ዑመር ሁሉንም ገስፀዉ ስብሰባዉን ተቆጣጠሩ፡፡ የማጠቃለያ ሀሳቦችን አቅርበዉም መቋጫ አደረጉለት፡፡ የአዲስ አበባ ዑለሞችን ከዚህ በላይ ማወያየት አስፈላጊ አለመሆኑንና ከገጠር የሚመጡ መሻኢኾችን ጋብዘዉ እንደሚያወያዩ ገልፀዉ አሰናበቱን፡፡ ግና የተባለዉ የገጠር ዑለሞች ዉይይት አንድ ጊዜ ለታህሳስ 19፣ ሌላ ጊዜ ደግሞ ለታህሳስ 29 ቀጠሮ ተይዞለት እያለ -ዑለሞቹ አዲስ አበባ ከደረሱ በኋላ- ሁለት ጊዜ ተሰረዘ፡፡ ለስረዛዉ የቀረቡ ምክንያቶች ዉሀ የማይቋጥሩ ናቸዉ፡፡ በተለይም ‹‹ዶክተር አብይ አህመድ እንዲራዘም አዘዋል›› የሚለዉ የታህሳስ 29/2011 ስብሰባ ለመሰረዝ የቀረበዉ ሰበብ ፍፁም የማይመስል ነዉ፡፡ የመጋቢት 21ዱ ስብሰባም የታቀደበት መንገድ የተዝረከረከ ስለሆነ ተጨናገፈ፡፡ . ዉይይቱን ሲከታተል የቆየ አንድ የአወልያዉያን ወገን የሆነ የአጥኝዉ ኮሚቴ አባል፡- ‹‹ታንቄ እሞታታለሁ እንጅ እኔ በህይወት እያለሁ እነዚህ የዐቂዳ መዝሀቦች (ጥልቅና ሰፊ ዉይይት የተደረገባቸዉን ሀሳቦች ማለቱ ነዉ፤) ከሰነዱ ዉስጥ አይካተቱም›› በማለት መዛቱን ሰማን፡፡ ነገሩ በዒልምና በኪታብ ብቻ እንጅ በአንድ ሰዉ መታነቅ ወይም አለመታነቅ የሚወሰን እንዳልሆነ ስለምናዉቅ ብዙም ትኩረት አልሰጠነዉም፡፡ እነዚህ ጽንሰ ሀሳቦች ከተካተቱ ዉይይቱን ጥለዉ እንደሚወጡ የዛቱም ነበሩ፡፡ ዛቻና ማስፈራሪያ ከዒልምና ከመረጃ ፊት ዋጋ እንደሌላቸዉ ሲገነዘቡ በመጨረሻዋ ሰዓት ለመቀበል ተገደዱ፡፡ የተቀበሉበት ሁኔታና ፅንሰ-ሀሳቦቹ እሰነዱ ዉስጥ የሚገቡበት አወቃቀር በዑለሞች መታየት የነበረበት ቢሆንም ተዘሏል፡፡ ምናልባትም በየሀሪማዉ የሚያቀሩ ሊቃዉንት ተጋብዘዉ ይመረምሩት ዘንድ ተስፋ ተደርጎ ነበር፤ ሆኖም ዑለሞች ቀድመዉ ባልደረሷቸዉ ሰነዶችና ከእነርሱ ይልቅ በባለሞያ ሊተሀየሱ በሚገባቸዉ የመዋቅርና የህግ ጉዳዮች ላይ ‹‹ለመወያት›› ለሚያዝያ 23 በሻራተን አዲስ ቀጠሮ ተይዞላቸዋል፡፡ ለ9ኝ ወራት የተሰናዱ ሶስት ባለብዙ ገጽ ሰነዶችን በሁለት ቀናት ጉባኤ መመርመር እንደማይቻል እሙን ነዉና ለዑለሞቻችን በቂ ጊዜ ካልተሰጠ ጉዳዩ በ‹‹ድርጅታዊ አሠራር›› የመዝለል ሂደት ይሆንና አሉታዊ ዉጤትን ያስከትላል፡፡ በቂ የሰነድ ዉይይት ሳይኖር ወደሌሎች እርምጃዎች መሄድ ደግሞ ጉዳዩን የበለጠ ያወሳስበዋል፡፡ . *2. የአካታችነት ጉዳይ* አህሉሱና ወል ጀማዐን እንደ ሴክት (ፊርቃ) የመቁጠር ስሁት ግንዛቤ በመንገሱ የተነሳ የአቂዳ፣ የፊቅህና የሱሉክ መዝሀቦች ከሰነዱ ዉስጥ መካተታቸዉ ሌላዉን አካል ማግለል መስሎ ያለአግባብ ተስሏል፡፡ ይህ ስህተት አህሉሱና አዉራዉና አቃፈዉ የእስልምና መስመር መሆኑን፣ እንዲሁም በሴክትና በመዝሀብ መካከል ያለዉን ልዩነት በወጉ ካለመረዳት የሚመነጭ ነዉ፡፡ አንድነት ለአህሉሱና ለጊዚያዊ የፖለቲካ ትርፍ የሚሰበክ ሳይሆን የዐቂዳዉ መሠረታዊ አካል ነዉ፡፡ ‹‹ላኑከፊሩ አህለል ቂብላ›› (ወደቂብላ ዞሮ የሚሰግድን ማንኛዉም ግለሰብ አናከፍርም) የዚህ የአቂዳ መዋቅር አብይ አካል ነዉ፡፡ የአህሉሱና ዐቂዳ የሶስተኛዉ ክ/ዘመን አዉራ ኢማም አቡልሀሰነል አሽዐሪ በእስልምና ታሪክ የተነሱ የሺዐ፣ የኸዋሪጅና ሌሎች አስተሳሰቦችን ታሪክ ለጻፉበት አንድ ኪታብ የሰጡት ስያሜ የመዝሀቡን ከሰማይ ከምድር የሰፋ ልቦናና አካታችነት በጉልህ ያሳያል፤ ‹‹መቃላቱል ኢስላሚይን፤ወኽቲላፉል ሙሶሊን›› ይላል የኪታቡ ስም፡፡ ይህ ማለት ‹‹በዚያ ኪታብ ዉስጥ የተዘረዘሩ አፈንጋጭ አስተሳሰቦች ባለቤቶች በሙሉ ሙስሊሞች ናቸዉ፤ ልዩነቶችም ወደአንድ አቅጣጫ ዞረዉ በሚሰግዱ የዕምነት ወንድማማቾች መካከል የተፈጠረ ነዉ›› ማለት ነዉ፡፡ ከዚህ በላይ አቃፊነት ያለ አይመስለኝም፡፡ ኢማም አቡሀሚድ አልገዛሊ የጻፉትን ‹‹ፈይሶሉ ተፍሪቃ…›› ኪታብ የቀራ በአህሉሱና አካታችነትና ስፋት ይደመማል፡፡ የራያዉ የዒልም ንጉስ ጀማሉዲን አልአኒ ‹‹አንድን ሙስሊም በስህተት ካፊር ከማለት አንድ ሺ ካፊሮችን በስህተት ሙስሊም ማለት የተሻለ ነዉ›› ሲሉ ከፈታዋቸዉ ዉስጥ ማስፈራቸዉ የአህሉሱናን ሆደሰፊነትና የበዛ ጥንቃቄ በወጉ ያሳያል፡፡ ስለዚህ የተደራጁ ዕዉቀቶች በሰነዱ ዉስጥ ተካተዉ የመጅሊስ መመሪያ መሆናቸዉ ሙስሊሙን ወደታወቁ የዕዉቀት ቋቶች በመሰብሰብና አሁን ሜዳ ላይ የሚታየዉን ሽኩቻ በማለዘብ፣እንዲሁም ያስተሳሰብ ብዝሀነትን