cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking ÂŤAccept allÂť, you agree to the use of cookies.

avatar

# abeni official channal😍😍💖❤👌

in this chanal we sharing funny videos and new musics and also ancient musics and advertisments and also politics.💟😠😠

Show more
The country is not specifiedThe language is not specifiedThe category is not specified
Advertising posts
194
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

ኦሮምያ ክልል አሊደሮ በተባለው አካባቢ በደረሰው የመኪና መቃጠልና በሰዎች ላይ በደረሰ አደጋ ምክንያት ከአማራ ክልል ወደ አ/አበባ የሚደረግ የትራንስፖርት አገልግሎት ተቋርጧል ፡፡ ************************** ***********************  ደጀን ከተማ ኮምዩኒኬሽን ግንቦት 15/2013 ዓ.ም በ14/09/13 ሌሊት ላይ በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን አሊደሮ እየተባለ በሚጠራው ቦታ 1 ኤፍ ኤ ሳር መኪና በመቃጠሉና በውስጡ ባሉ ሰዎች ላይ የመቁሰል አደጋ በመድረሱ ምክንያት ከአማራ ክልል የሚንቀሳቀስ ማንኛውም መኪና እና መንገደኞች ከጠዋቱ 12 ሰዓት ጀምሮ ከደጀን ከተማ እስከ ኪዳንምረት ቤ/ክርስትያን ድርስ ባሉበት ቁመዋል ፡፡  በቦታው በመገኘት መንገደኞችን ፣ሹፌሮችና ረዳቶች ባሉበት ለመቆም ያነሳሳቸውን ምክንያት ሲጠየቁ በየግዜው በክልሉም ሆነ ከክልሉ ውጭ የአማራ ህዝብ እየታረደ፣እተፈናቀለና እየሞተ ሀብትና ንብረቱ እየወደመ የክልሉ መንግስትም ሆነ የፌደራል መንግስት መፍትሄ አልፈለገለትም ፡፡  በቅርቡ ከ1 ወር በፊት እዚሁ አሊደሮ በተባለው ቦታ ላይ ከ 8 ያላነሱ ሹፊሮችና ረዳቶች ሞተውና ሀብትና ንብረት ወድሞ ምንም መፍትሄ ባለመሰጠቱ አሁንም ትላንት ሌሊት መኪና ሲቃጠልና ሰዎች ላይ አደጋ ሲደርስ እያየን መንቀሳቀስ አንችልም ከዚህ ቦታ የምንንቀሳቀሰው መንግስት የህዝባችንን በተለይም የአማራን ህዝብ ሞትና እልቂት ማስቆም ሲችል ነው ፡፡  በተለይ እኛ ሹፊሮች ለሀገራችን ልማት የጀርባ አጥንት ለሆነው የትራንስፖርት አገልግሎት ደፋ ቀና እያልን በምንሰራበት ወቅት የምንታረድ፣የምንሞት፣ ሀብትና ንብረታችንን የምንዘረፍ ከሆነና ለህይወታችንና ለንብረታችን ምንም ዋስታ ከሌለን ባለንበት በመቆም እራሳችንን መከላከል መርጠናል ፡፡ በተጨማሪም በርካታ መንገደኞች እየተፈጠረ ባለው ችግር ላይ በከፍተኛ ስሜት ፣ቁጭትና ምሬት ብሶታቸውን በስፋት ተናግረዋል ፡፡  በደጀን ከተማና ወረዳ የሚገኙ የፖሊስና የፀጥታ ሀይሎች መንገደኞችን በማነጋገር መንገዱ እንዲከፈትና የትራንስፖርት አገልግሎቱ እንዲቀጥል ጥርት ቢደረግም መንገደኞች ፣ሹፌሮችና እርዳቶች ብሶታቸውንና ችግራቸውን በመናገር አሁንም ችግሩ እየቀጠለ ሊሄድ ስለሚችል መንግስት ለህይወታችንና ለንብረታችን ዋስትና ካልሰጠን መንቀሳቀስ አንችልም ብለዋል ፡፡  በመሆኑም ባሁኑ ሰዓት በደጀን ከተማና አካባቢው በርካታ መኪናዎች በመቆማቸውና ወደ አ/አበባ የሚደረግ እንቅሰቀቃሴ በመቆሙ እናቶችና ህፃናት፣አዛውንቶች የጤና ችግር ያለባቸው ሰዎች እየተጉላሉና ለእንግልት እየተዳረጉ ስለሆነ የሚመለከታቸው የመንግስት አካላት መፍትሄ ይፈልጉለት ዘንድ መልዕክታችን ነው ፡፡ © Dejen Ketema Communication Office
Show all...
In side polotics with abeni please join @dakenbrown
Show all...
የኦነግ ሸኔን ጽንፈኛ ኀይል ለመደምሰስ ከፌዴራልና ከክልል የጸጥታ አካላት ጋር እየተሠራ መሆኑን የሰሜን ሸዋ ዞን አስተዳደር አስታወቀ ቀደም ባሉት ጊዜያት በተለይ የሰሜን ሸዋ ዞን ከኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ጋር በሚዋሰንበት አካባቢ አልፎ አልፎ የግለሰብ ግጭቶች ቢኖሩም በቀላሉ የሚፈቱ እንደነበሩ የሰሜን ሸዋ ዞን አስተዳዳሪ ታደሰ ገብረ ጻዲቅ ተናግረዋል፡፡ በሂደት ግን እነዚህ ግጭቶች መልካቸውን እየቀየሩ በተለይ የሰሜን ሸዋ ዞን ከኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ጋር በሚዋሰንባቸው አካባቢዎች ላይ የተደራጀና ዘመናዊ ጦር መሳሪያ የታጠቀ ጸረ ሰላም ኀይል ጥቃት ሲፈጽም ቆይቷል ብለዋል፡፡ ጥቃቱን በመፈጸምና ባስተባበረው የኦነግ ሸኔ የጥፋት ኀይል አፋጣኝ እርምጃ ባለመወሰዱ ዛሬ ላይ በሰው ህይወትና በንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰ አቶ ታደሰ ተናግረዋል፡፡ በንብረቱ ላይ ጉዳት የደረሰበት የአካባቢው ኅብረተሰብም በተለይ ወደ በርግቢ፣ መሃል ሜዳና ደብረ ብርሃን በመሄድ ተጠልለው ይገኛሉ ነው ያሉት አስተዳዳሪው፡፡ ጽንፈኛውን ኀይል ለመደምሰስ ከፌዴራልና ከክልል የጸጥታ አካላት ጋር እየተሠራ መሆኑን አስተዳዳሪው ተናግረዋል፡፡ @Addis_Merejas
Show all...
… ባለፈው ሳምንት በዕለተ ማክሰኞ ግንቦት 10/2013 ዓም ነበር በቴሌግራም ቻናሌ ላይ የታላቁን ገዳም የዋልድባ አብረንታንት ቤተ ሚናስ ገዳምን ትረዱ እጃችሁንም ትዘረጉላቸው ዘንድ በቴሌግራም ቻናሌ በኩል ቀጠን ብላ ወፈር ያለች… ረዘም ብላ እጥር ያለች እንደ እኔ መራታ ያልሆነች ቀለል ያለች የበረከት ጥሪ ያቀረብኩላችሁ። ያውም ያለፌስቡክ… ያለ ኢቲቪ… ያለ ሲኤንኤን… ያለቢቢሲ። በቴሌግራም በጽሑፍ ብቻ። ልብ በሉ። በቴሌግራም ብቻ። … የመድኃኔዓለም ያለህ… ወዲያውኑ ጎረፈላችኋ… የብር… የዶላር… የፓውንድ… የድርሃም… የዩሮ ብቻ በዓለም ላይ የሚገኙ ሃገራት ገንዘብ ጎረፈላችሁ። በቃ ምንአለፋችሁ ሱናሚ መሰለ… ዋልድባ አብረንታንት ያ የአባቶች ገዳም… ያ ክብሩ ከግብፆቹ ከእነ ገዳመ አስቀጤስ የሚተካከለው ገዳም የፈረንካ ማስቀመጫ ሰንዱቁ በብር ተሞላ። አቤት ደስስ ሲል። … በማግስቱ ለብዙዎቻችሁ ዘመዳችሁ… ለሙጭቅላዎቻችሁ ደግሞ ጠላታችሁ የሆንኩ እኔ ተራየን ወንዝ ማዶ ከአጎት ሃገር ጀርመን… እነ ቀሲስ ሳሙኤል ግዛው… እነ ቀሲስ ልዑልሰገድም በኢትዮ ቤተሰብ የዩቱቲዩብ ቻናል መስኮት በኩሉ ከሚሲሲፒ ወንዝ ማዶ ተአክስት ሃገር አማሪካ ( አማሪካ ግን ተይ እጅሽን አንሺ! ) አንጋፋው የመረጃ ተለብዥኑ ሞተር ጋዜጠኛ ኤልያስ ክፍሌም የመረጃ ሳታላይቱን ከፍቶ… በመላው ኢትዮጵያና በመላዋ ዓለም የገዳማውያኑ የበረከት ጥሪ በአባቶች አንደበት የዐዋጅ ያህል እንዲሰማ… እንዲደመጥም ሆነ። … ከዚያ ወዲህማ ምኑ ይነገራል? ምኑስ ይወራል? አቤት የሥላሴ ሥራ … አቤት የወላዲተ አምላክ የእመአምላክ አማላጅነት… አቤት የቅዱሳኑ ጸሎት… በቃ ምድሪቱ ላይ ያሉ የተዋሕዶ ልጆች ከጥቂቶች በቀር ሁላቸውም በአንድ ተሰለፉላችኋ። ለዋልድባ ያልሆነ ለምን ሊሆን ነው ታዲያ ብለውም ብዙዎች መስጠት ጀመሩ። በላባቸው ያገኙትን ሃብት ለአባቶች የበረከት ጥሪ ምላሽ መስጠትም ጀመሩ። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክም በፈረንካ ተጨናነቀ። … 10 ብር የሰጠ አይቻለሁ። 125 ሺ ብርም የሰጡ አይቻለሁ። 27 ሺ ብር የሰጠ ሙስሊም ወንድምም አይቻለሁ። እስከአሁን ጴንጤ ብቻ ነው ያላየሁት። ብቻ ምንልበላችሁ ጊዜው አስቸጋሪ ገንዘብም እንደልብ የማይገኝበት ዘመነ ኮሮና ቢሆንም ነገር ግን ባለማዕተቦች አጎረፉት። የሚገርመው እስከአሁኗ ሰዓት ድረስ ባንኩ በብር ቁንጣን ተወጥሮ እያቃሰተ ነው የሚገኘው። በግል… በቤተሰብ… በጓደኝነት… በመሥሪያ ቤት ሁላ የሚተዋወቁ ባለማዕተቦች ያላቸውን እያዋጡ ለዋልድባ በደስታ እየላኩ ነው። የእኔን የደስታዬን መጠንማ አትጠይቁኝ። ይሄ ነው አይባልም። … አየህ ኦቦሌሶ እግዚአብሔር ፈቃዱ ከሆነ ምንም አይነት ኮሚቴ አይፈልግም… ብዙ እንድትለፈልፍም አይፈልግም… ስብሰባ… ቃለጉባኤ… አጀንዳ እያለ አያዝግህም። የውሎ አበል… ፕሮጀክት ቀረጻ አይልህም… በየሃብታሞቹ ደጅ… ፈረንካ አላቸው በተባሉ ሰዎች ሥፍራ ሁሉ በየጊዜው አያንከራትትህም። ጥላ ዘቅዝቀህ… ወይንና ክትፎ አቅርበህም ድከም… ለምንም አይልህም። የታኪሲ ሳያስወጣ… የማስታወቂያ ሳይስወጣ… የነዳጅ… የውሎ አበል… ኮሚሺን… ፈርቅ ሳያሲዝ… አዳራሽ ፍለጋ… ወንበር ኪራይ… ሞንታርቦ… ምንጥስዮ… ቅብጥርስዬም ብሎ ሳያደክምህ እንዲህ በአንዲት የቴሌግራም ጦማር ልብህንም በርግዶ… ቋጣሪውን እጅህንም ፈትቶ ኪስህንም በርብሮ… ችግርህን አስረስቶ በደስታ መዥረጥ አድርገህ እንድትሰጥ ያደርግሃል። በደስታ፣ በእልልልታ አልኩህ… አስገዳጅ ሳይኖር… የሚገዝት… የሚለማመጥም ሳይኖር በፈቃደኝነት እንዲህ ያሰጥሃል። ፖሊስ አልተላከብህ… አማላጅ አልተላከብህ… በቃ በፈቃድህ እምርር ብለህ ተነሥተህ እየተባረክ ነው የምትሰጠው። … ሦስተኛ ወገን በመሃልህ የለ። ሁለተኛ ወገንም በመሃልህ የለ። ደላላ የለ። ከሰጠህ በኋላ ለኃሜት የሚያመቻች ምልክት የለ። በቀጥታ ከባለጉዳዩ ጋር ተገናኝተህ በሕጋዊ መንገድ ሰጥተህ እንዲህ መባረክ ነው። አንተ በሰጠኸው ገንዘብ ልክ እሱ እንዳደረገ ማስታወቂያ የሚሠራብህ አጭቤ የለ። ምንየለ ምንየለ… በቃ ነገርኩህ ገዳሙና አንተ ትገናኛለህ አበቃ። በእኔ በኩል ላኩ… እኔ ላስገባላችሁ… ወፍ የለም። አከተመ። … አንድ ሱባኤ የሚሞላን ነገ ሰኞ የኪዳነምህረት ዕለት ነው። 7 ቀን የሚሞላን የዚያን ዕለት ነው። እናም በስምንተኛው ቀን ማክሰኞ የቅዱስ እስጢፋኖስ ዕለት አባቶች ከዋልድባ ይመጣሉ። እኔ ከጀርመን መረጃ ቲቪና ኢትዮ ቤተሰብ ከአማሪካ ሆነን እናንተ በየቤታችሁ ሆናችሁ አባቶች የሚሉንን እንሰማለን። የገባውን የብር መጠንም ይፋ እናደርጋለን። እኛም ያልቻልን ቆመን፣ ወይ ተቀምጠን፣ የደከመን ተኝተንም ቢሆን፣ የቻልን ደግሞ ተንበርክከን፣ በግንባራችንም ቢሆን ድፍት ብለን አባቶቻችን የሚሉንን እንሰማለን። የዚያን ዕለት ማታ በዕለተ ማክሰኞ አጠቃላይ ሪፖርቱንም አቀርባለሁ። እስከዚያው ድረስ ላልሰማ አሰሙ። ላላየም አሳዩ። … መልካም ዕለተ ሰንበት  !! ዋልድባ አብረንታንት ገዳም ዘቤተ ሚናስ ማኅበር ጎንደር ዐቢይ ቅርንጫፍ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሂሳብ ቁጥር 1000018796779 SWIFT=CBETETAA
Show all...
… ዝርዝር ቀደዳዬ ከታች ተጥፏል … 👇👇👇 አንብቡት። አፌን ስለሚበላኝ እንጂ እኔም እንደ ማነው ስሙ? አፌ ላይ እኮ ነው። ኡፋ ማነው ጥሩልኝማ… ኢቶጴያኖች ጎፈንድሚ ኪፈቱልኝ። ሚስቴ አባረራቺኝ ያለው? እንደሱ ዝም ብልስ? ክፉ ልማድ ይዞኝ ያስለፈልፈኛል።
Show all...
… ሥልጣን ላይ ያለው ኦህዴድ ነው። ኦህዴድ ደግሞ ኦሮሞ ነው። የኦሮሞ ልጆች ናቸው አሁን ሃገሪቷን የሚመሩት። ይሄ እውነት ነው። … ሰሞኑን ዐቢቹ " የውጭ ኃይሎች ጣልቃገብነትን አንቀበልም " እያለ አፋር ክልል ላይ ሲፈፎክር ታየ። ከዚያ የዲሲ ግብረ ኃይልና ኢዜማዎች በአንደዜ ግልብጥ ብለው "አማሪካ እጅሽን ከኢትዮጵያ ላይ አንሺ" አንሺ ተናግረናል… ወዮልሽ ንስሐም ግቢ እንዳትቀሰፊ እያሉ ሲያስነኩት ሳይ ተደነቅኩ። ድንስር ብዬ ቀጥ ብዬም ነው የቀረሁት። አማሪካ ምንብላን ይሆን እንደዚህ የሚጮሁባት ብዬ ነበር መደነቄ። በእውነት አልገባኝም ነበር። ሩቅ ሃገር ያለ ሰው እኮ አይሰማም። አትፍረዱብኝ። … ቆይቶ እንግሊዛዊው ኦቦ አንዳርጋቸው ጽጌም የለንደን መሄጃ የሮጲላ ትኬታቸውን በግራ ኪሳቸው ክትት አድርግተው…ወይም አድርገው… በጦቢያ ተለቭዥን ቀርበው በቀኝ እጃቸው እየፈከሩ " የአማሪካንን ባንዲራ አቃጥላለሁ !" ሲሉ ባይ ኧረ እኚህ እንግሊዛዊ ምን ሁነው ነው ብዬ መደንገጤን አልደብቃችሁም። ኧረ አታቀሳስሩን ብዬ መጨሆም ፈልጌ ነበር " ሀሞተ… ቢስ… ፈሪ ወኔ የሌለህ እባላለሁ ብዬ ፈርቼም ነው ዝም ያልኩት። ቆይቶ እሳቸውም ፈሩ መሰለኝ አፈገፈጉ። ካድሬውም ክፍያ አነሰው መሰለኝ ሰልፍም የሚወጣም ጠፍቶ 26 የኦህዴድ ካድሬዎች ሃምሌ 19 መናፈሻ ጋር" በአማርኛና በኦሮሚኛ" አሜሪካንን በኃይለኛው ተቆጥተው ለኢሳት በኦሮሚኛ መግለጫ ሰጥተው ተበተኑ። ባንዲራም ወረቀትም አላቃጠሉም ነበረ። ምድረ ቦቅባቃ ሁላ ልላቸው ፈልጌ ልሴ ተንቦቁቡቄ ፈርቼ ጮጋ ያልኩበትን የሰው ሰው ካድሬ ምን ክፉ አናገረኝ ብዬ ሂሴን ውጬ ዝም አልኩ። … ሰሞኑን የኦህዴድ ሰዎች የሌለ አደባባይ ወጥተው "እኛ እኮ በዓድዋ፣ በማይጨው ስንት ተጋድሎ የፈጸምን ኢትዮጵያውያን ነን ሲሉ ስሰማ ከመደንገጤ የተነሣ ደግሞ ማን ሊሞት ይሆን ብዬ ክፉ ክፉ ወደማሰብ ሁላ ሄጄ ነበር። ይቅር ይበለኝ። ሽመልስ አብዲሳ፣ ታዬ ደንደአ ሳይቀሩ " እኛ ኢትዮጵያውያን" ሲሉ ስሰማ ክው ብዬ ነበር የቀረሁት። … ፒፒሌ "አማሪካ እጅሽን አንሺ !" ሲል ዐቢይ ነፍሴ  ከአማሪካ ጋር የተጣላ መስሎ ከኋላ ሥራውን ይሠራል። ወዳጄ የበሻሻው አራዳ ምኑ ሞኝ ነው። አቢቹ ሆዬ ገብሴን በባዶ ሆዷ አማሪካንን በአማርኛ እያሰደበ፣ እያስረገመም እሱ ሆዬ በጓሮ በር በጎን ቴሌን ለአማሪካ ካምፓኒ ሽጦት አረፈው አሉ ዶክተር ዳዊት። https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=1157642084716648&id=100014126017674 … ለውድድር የቀረቡት የቻይናና የአሜሪካ ካምፓኒዎች ነበሩ አሉ። አቢቹ ግን ምርጫው አማሪካ ሆናለች። ምስኪን ቻይና ስታሳዝን። ባለፈው በተባበሩት መንግሥታት ስብሰባ ላይ አማሪካ እጇን ልትጭንብን ስትል ቻይናና ሩሲያ ነበሩ የተቃወሙልን። ቻይናን አቢቹ ደህና አድርጎ ነው የቀጣት። ኤትአባቷንስና። ይበላት የእጇን ነው ያገኘችው። እሷን ብሎ የእኛ ጠበቃ። … ፒፕሉ አሁንም " አማሪካ ሆይ እጅሽን አንሺ " እያለ ነው። ከምናቸው ላይ እንደምታነሳ ብቻ ነው ያልገባኝ። አሁን ደግመው አማሪካ ሆይ እጅሽን አንሺ ካሉ ወይ አየር መንገዱ፣ ወይ የህዳሴ ግድቡ እንደተሸጠ ቁጠሩት። በተለይ ባህርዳር ነገ ሰልፍ እንዲወጣ ህዝቡ በቀበሌ ነው የታዘዘው። "አማሪካ ሆይ እጅሽን አንሺ እያሉ ጣና ዳር እስክስታ ሲያስወርዱት ሊውሉ ነው የሚል መረጃም ደርሶኛል። …ደግሞ እኮ ደጋግሞ ኢትዮጵያ አትፈርስም ይልልሃል። ምን አስቦ ነው ግን መሪዬ? … በሉ አንድ ጊዜ ሰብሰብ ብለን እንፈክርማ !!  ተቀበሉኝ። “ I Can't Breathe ” አለ ጆርጅ ፍሎይድ። • አማሪካ እጅሽን ከኢትዮጵያ ላይ አንሺ ! አንሺ!   • ኤርትራም እጅሽንም እግርሽንም ከኢትዮጵያ ላይ አንሺ !! • ሱዳንም እጅሽንም፣ እግርሽንም፣ ዳሌሽንም፣ ዱላሽንም ከኢትዮጵያ ላይ አንሺ !! ልል ፈለግኩና " ሆሆይ ደግሞ "ባንዳ" ብባልስ… በቅዳሜ ምሽት በኢዜማና በብልጽግና ሰዎች ለምን እሰደባለሁ ያጎፍታኮ ብዬ ሱዳንና ኤሪ ይቀመቀጡ ብዬ ጭጭ። ኢጂሊሲ ሱዲዬ… ኩፍ በይ ኤሪዬ… አዎ ኩፍ በሉ። • አማሪካና አውሮጳ ግን ብታርፉ ይሻላችኋል !!
Show all...
Log in to Facebook

Log in to Facebook to start sharing and connecting with your friends, family and people you know.

Choose a Different Plan

Your current plan allows analytics for only 5 channels. To get more, please choose a different plan.