en
Feedback
Ethiopian Law//የኢትዮጵያ ህግ ⚖️⚖️🚻🇪🇹

Ethiopian Law//የኢትዮጵያ ህግ ⚖️⚖️🚻🇪🇹

Open in Telegram

📚 Ethiopian Law 🇪🇹 Empowering citizens through legal knowledge & justice access. 📌 Proclamations | Bench Decisions | Journals | Draft Laws 👨‍⚖️ Curated by Surafel Feleke (LL.B) 📞 0915759150 / 0990352428 🗣 Join us via the contacts on our logo

Show more
8 626
Subscribers
+824 hours
+627 days
+23630 days
Posts Archive
በቡርኪናፋሶ የተረጂዎችን ክብር ለመጠበቅ ሲባል ከሚሰጣቸው ዕርዳታ ጋር በፎቶ ማሳየት የሚከለክል አዲስ ህግ ፀደቀ‼️ “ለምን ሰውን ረድተህ ያንን ሰው ከሰጠኸው ምግብ፣ ልብስ ወይም ቁሳቁስ ጎን አቁመህ ለካሜራ ታሳየዋለህ?” ይህ ጥያቄ በቡርኪና ፋሶ አዲስ የመንግሥት አቅጣጫ መሠረት ላይ ተቀምጧል። የኢብራሂም ትራኦሬ መንግሥት በጁላይ 2፣ 2026 በተካሄደው የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰባ የተጋላጭ የእርዳታ ተቀባዮችን ከሚሰጣቸው ዕርዳታ ጋር አብሮ በፎቶ ወይም በምስል ማሳየትን የሚገድብ አዲስ አቅጣጫ አጽድቋል። በተለይ ሕፃናት፣ ተፈናቃዮች፣ የችግር ሰለባዎችና ሌሎች ተጋላጭ ዜጎች ምግብ ወይም ቁሳቁስ ሲቀበሉ ከዕርዳታው ጎን አቁሞ ፎቶ በመነሳት፣ ቪዲዮ በመቅረጽና ምስሉን በማሰራጨት የግለሰቡን የችግር ሁኔታ ለገበያ ወይም ለገንዘብ ማሰባሰቢያ መጠቀም በመሠረቱ እየተቃወመ ያለው ነገር ይህ ነው። አንድ ድርጅት ወይም ግለሰብ እርዳታ ሲሰጥ፣ ተረጂውን ከሰጠው ዕቃ ጎን አቁሞ፣ የፎቶ ወይም የቪዲዮ ምስሉን በማሰራጨት “እኛ እየረዳን ነው” ለማለት የተረጂውን ስቃይ እንደ ማስታወቂያ መጠቀም ነው። እርዳታ መስጠት በራሱ በጎ ተግባር ነው። ግን የሚረዳውን ሰው ክብር ማስከፈል የለበትም። ቡርኪና ፋሶ በራሷ የእርዳታ ሥርዓት ላይም ትልቅ አቅም እያሳየች ነው። ለምሳሌ “Dɛmɛ Sira” በተባለው የአገር ውስጥ የአጋርነት ዘመቻ እስከ መጋቢት 2026 ድረስ ከ1.13 ቢሊዮን CFA ፍራንክ በላይ ማሰባሰቡን መንግሥቱ ገልጿል። በ2025 ደግሞ የቡርኪና ፋሶ መንግሥት ከ22,000 ቶን በላይ ምግብና ከ290 ቶን በላይ መድኃኒት ወደ የጸጥታ ችግር ወዳለባቸው አካባቢዎች መላኩን፣ ወደ 59,000 የሚጠጉ የተፈናቃይ ቤተሰቦችም የቤት ዕቃዎችን ማግኘታቸውን አስታውቋል።

በሱዳን ፍርድ ቤት ላይ በተፈጸመ የድሮን ጥቃት የ10 ሰዎችን ህይወት ቀጠፈ በሱዳን ሰሜን ኮርዶፋን ግዛት በምትገኘው ኡም ራዋባ ከተማ በአንድ ፍርድ ቤት ላይ በተፈጸመ የድሮን ጥቃት 10 ሰዎች መገደላቸው ተገለጸ። የሱዳን የሰብዓዊ መብቶች ቡድን እንዳስታወቀው፣ ጥቃቱ በተፈጸመበት ወቅት በፍርድ ቤቱ የነበሩ ሰዎች ላይ ጉዳት እንደደረሱ ገልጾ በርካቶችም ቆስለዋል ብሏል።  ቡድኑ በጥቃቱ የሞቱት ሰዎች ቁጥር በቅድሚያ 10 መድረሱን ገልጾ፣ የሟቾችና የተጎዱት ቁጥር ሊጨምር እንደሚችል አመልክቷል። በተጨማሪም ቡድኑ፤ በሲቪሎችና በሲቪል ተቋማት ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶች እየበዙ መምጣጥተዋል ያለ ሲሆን ይህም በሱዳን ያለውን የሰብዓዊ ሁኔታ እያባባሰው መሆኑን ጠቁሟል። በተለይም የፍርድ ቤት ተቋማትና ሠራተኞች በጥቃት ዒላማ መሆናቸው በሕግ ሥርዓቱና በሲቪሎች ደህንነት ላይ ከፍተኛ ስጋት እንደፈጠረ አስጠንቅቋል። አክሎም  በሲቪሎች፣ በሲቪል ተቋማትና በዳኝነት ተቋማት ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶች በአፋጣኝ እንዲቆሙ የጠየቀ ሲሆን በተጨማሪም የጥቃቱን አጠቃላይ ሁኔታ ለማጣራት ገለልተኛና ግልጽ ምርመራ እንዲካሄድ ጥሪ አቅርቧል። በጥቃቱ ዙሪያ የፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ (አር.ኤስ.ኤፍ.) እስካሁን የሰጠው ይፋዊ ምላሽ እንደሌለ ተገልጿል ። የተባበሩት መንግስታት መረጃ እንደሚያሳየው ከሆነ በዚህ ዓመት ከጥር ወር እስከ ሰኔ ባለው ጊዜ ብቻ በሱዳን በተፈጸሙ የድሮን ጥቃቶች 1,100 ሲቪሎች መገደላቸውን አናዶሉ ዘግቧል። ይህ የድሮን ጥቃት በጦርነቱ ውስጥ በሲቪሎች ላይ የሚያስከትሉት አደጋ እየጨመረ መምጣቱን ያሳያል ተብሏል። ሰሜን፣ምዕራብና ደቡብ ኮርዶፋንን ያካተተው የኮርዶፋን ክልል በቅርብ ወራት በሱዳን ጦርና በአር.ኤስ.ኤፍ መካከል የተጠናከሩ ውጊያዎችን እያስተናገደ ይገኛል። በሁለቱ ኃይሎች መካከል እ.አ.አ ከሚያዝያ 2023 ጀምሮ በቀጠለው ጦርነት በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ሲገደሉ፣ ወደ 13 ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎች ደግሞ ከመኖሪያቸው ተፈናቅለዋል።(አዲስ ማለዳ)

የታክስ አለመግባባትን በመስማማት ስለመፍታት በተሻሻለው የፌዴራል ታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1434/2018 አንቀጽ 61 የታክሱ ባለስልጣን የታክስ አለመግባባትን በመስማማት ለመፍታት ያለውን ስልጣ
የታክስ አለመግባባትን በመስማማት ስለመፍታት በተሻሻለው የፌዴራል ታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1434/2018 አንቀጽ 61 የታክሱ ባለስልጣን የታክስ አለመግባባትን በመስማማት ለመፍታት ያለውን ስልጣን በተመለከተ የሚከተለውን ይላል፡- 👉 የታክሱ ባልስልጣን የታክስ አለመግባባቶችን በመስማማት የመፍታት ስልጣን ተሰጥቶታል። 👉 ማናቸውም በስምምነት የሚፈታ የታክስ ያለመግባባት በጽሁፍ የሚደረግ እና የተስማሚ ወገኖች ፊርማ ያረፈበት ሊሆን ይገባል። 👉 የታክስ አለመግባባቶችን በመስማማት የመፍታት ስልጣን የሰጠው ድንጋጌ ቢኖርም የሚከተሉት ሁኔታዎች ሲኖሩ ጉዳዩ በማስማማት ሊታይ አይችልም፦ 1. የታክስ ማጭበርበር ወይም ሆን ተብሎ የተደረገ ታክስን የመሰወር ድርጊት መኖሩ ወይም ሌላ ከታክስ ጋር የተገናኘ ወንጀል መኖሩ ሲጠረጠር፤ 2. በማስማማት የሚደረግ ስምምነት ከኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ-መንግሥት እና ከሚመለከታቸው የታክስ ሕጎች ጋር የሚጋጭ ሲሆን፤ 3. ከሁለቱ ወገኖች አንዱ በሽምግልና ሂደት ውስጥ ለመሳተፍ ፈቃደኛ ካልሆነ። 👉 ሚኒስቴሩ የአስማሚውን የትምህርት እና ሙያ ደረጃን ጨምሮ የመስማማት ሂደት የሚመራበትን ሥርዓት የሚወስን ዝርዝር የአፈፃፀም መመሪያ ያወጣል፡፡