en
Feedback
ልሣነ አምሐራ ሚዲያ

ልሣነ አምሐራ ሚዲያ

Open in Telegram

በዚህ ቻናል ፈጣንና ወቅታዊ የአማራ ፋኖ እለታዊ ዘገባዎች እንድሁም ፈጣን ዜናዎች ይቀርባሉ። ለማንኛውም ጥቆማ በ @lisaneamhara ያናግሩን‼️

Show more
1 970
Subscribers
No data24 hours
-77 days
-3430 days
Posts Archive
ጀግናው ተሰውቷል:: እኔም የሰማሁት ዘግይቼ ነው!! ለነገሩ እሱ ቢሰዋም የልቡን ሰርቶ ነው:: በአጠቃላይ ሰሞኑን በአማራ ሳይንት ቀጠና በሰፊው የምዕራብ ወሎ ግንባር ነገሮች በፍጥነት ተቀይረዋል:: 2 መከላከያ እና ሚሊሻዎች የአማራ ፋኖ በወሎ ምዕራብ ወሎ ኮር አማራ ሳይንት መቅደላ ክፍለ ጦር አትሮንስ ብርጌድን በመሀል ሳይንት ወረዳ ግንባር ተቀላቅለው ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል የሚል መረጃ አሁን ደርሶኛል:: የአትሮንስ ብርጌድ አዛዥ ፋኖ ጎሹ ታረቀኝ የጠላትን አቅም እያሽመደመደው ነው:: ቁልፍ አዋጊዎችን አምጥቶበታል:: ይህ በእንዲህ እንዳለ በዚሁ በአማራ ሳይንት ቀጠና በለጋምቦ ወረዳ ግንባር ገነቴ አቅራቢያ ሰሞኑን ታሪክ ሲሰራ ሰንብቶ ኖሯል:: ጥር 6 ለ7 ሌሊት በተደረገ ጦርነት የአማራ ፋኖ በወሎ ምዕራብ ወሎ ኮር ቀኝ አዝማች ይታገሱ አረጋው ተወርዋሪ ክፍለ ጦር አደራጅ ኮሚቴ አባል እና የክፍለ ጦሩ ስራ አስፈጻሚ የሆነው ኮማንዶ ተመስገን ሳይንቴው ጀብዱ ፈፅሞ በጀግንነት ተሰውቷል:: የኮሩ ጊዜያዊ ኮሚቴው ተሰባስቦ አዳዲስ ስራ አስፈጻሚዎችን በመሰየም በሰራዊቱ ሊያፀድቅ ከየቦታው ተሰባስቦ ለጋምቦ ወረዳ እና ወግዲ ወረዳ ድንበር አቅራቢያ የምትገኝ ብስቁልል የምትባል መንደር ውስጥ ከኮሩ አዛዥ አርበኛ አደም አሊ ጋር ውይይት ላይ ሳሉ የኮሩ አዛዥ አጃቢ የነበረና ከቀናት በፊት ከድቶ ወደ መንግስት የገባ የየሹም አካባቢ ተወላጅ ባንዳ ከወግዲ ወረዳ በኩል ጠላትን እየመራ መጥቶ ከሌሎች የጎረቤት ወረዳዎችም ተጨማሪ ኃይል በቦታው በመድረስ ሌሊት ከባባ ቢፈፅምም ጀግኖች በታትነውታል:: ሞት አይፈሬው ሳይንቴ ከ4 ወረዳዎች የጥምር ጦሩ ጊዜያዊ ካምፓች ተውጣጥቶ በመጣ ከ400 የማያንስ መከላከያ እና እልቆ የለሽ አ.ሚ.ፓ. (አጥቦ አይለብሴ ሚሊሻ...አድማ ብተና እና ፓሊስ) ድብልቅ ሰራዊት ጋር በነበረው ትንቅንቅ በርካታ ጠላት ደምስሶ ተሰውቷል:: የአማራ ፋኖ በወሎ ምዕራብ ወሎ ኮር አዛዥ አርበኛ አደም አሊ ጋር ውጊያን በመምራት ላይ ሳለ ነው ኮማንዶ ተመስገን የተሰዋው:: ፊት ለፊት ሲዋጋ ቆይቶ ከበባ ሰብረው እና ጠላትን ከምሽጉ ነቅለው በማስፈርጠጥ ታላቅ ገድል እየፈፀሙ ባሉበት ቅጽበት ነው በድንገት የተመታው:: በዚህ አውደ ውጊያ ከወግዲ በኩል ከመጣው ጥምር ጦር ብቻ 30 በጥይት ቀምሶ 17ቱ ሙት ሲሆን ቀሪው ቆስሏል:: በለጋምቦ በኩልም ከዚህ ያላነሰ ቁጥር ያለው ጠላት ተደምስሶ 20ዎቹ ጊምባ ተቀብረዋል:: ከ5 ቀናት በኋላ ከትናንት በስቲያ አስከሬን ለቀማ ወደ ውጊያው ቀጠና የተጓዘው ጠላት አርሶአደሮችን አፋልጉኝ ብሎ አስገድዶ ሲፈልግ ቆይቶ የ6 ወታደሮችን እግር አግኝቷል:: በብስቁልሉ ኦፕሬሽን በድምሩ ከ60 በላይ ጠላት እንደተመታ ነው መረጃዎች የሚያሳዩት:: የአማራ ፋኖ በወሎ ምዕራብ ወሎ ኮር ቀኝ አዝማች ይታገሱ አረጋው ተወርዋሪ ክፍለ ጦር ኦርዲናንስ ኃላፊን ጨምሮ አንድ የንጉሥ ሚካኤል አሊ ክፍለ ጦር ፋኖ መቁሰሉ የተገለፀ ሲሆን ከኮማንዶ ተመስገን ሳይንቴው ጋር መስዋዕትነት የከፈለም ሳይኖር እንዳልቀረ ነው የሰማሁት:: በጥቂት መስዋዕትነት አስገራሚ የሚባል ጀብዱ ተፈፅሟል ኮማንዶ ተመስገን እንደተሰዋም አንቆጥረውም ሲሉ ነው ጓዶቹ የገለፁት:: ሞት አይፈሬው ጀግና የሳይንቴይቱ ልጅ ከአዲስ አበባ ድረስ ወደ ግንባር ከገባ ሁለት ወር አልሆነውም:: የቀኝ አዝማች ይታገሱን ደም የምንመልሰው ህዝባችን ነጻ ሲወጣ ነው ብሎ የወንድሙን ደም ሊመልስ ገብቶ የልቡን ሰርቶ ተሰውቷል:: ለቃሉ ታምኖ የወንድሙንም አደራ ተሸክሞ እስከ ሞት ድረስ በሀቅ ታግሎ አርፏል:: ይህ ወርቃማ ዕድል ነው:: የዚህ ታሪክ ባለቤት ሆኖ ስም አስሮ መሰዋት መታደል ነው እንጅ ሞት አይባልም!! ለወዳጅ ዘመድ እና ለጓዶቹ በሙሉ መጽናናትን እመኛለሁ!! ነፍስ ይማር!!

የጎንደር ፋኖ አንድ ሆነ✊
+3
የጎንደር ፋኖ አንድ ሆነ✊

ጀግናው ተሰውቷል:: እኔም የሰማሁት ዘግይቼ ነው!! ለነገሩ እሱ ቢሰዋም የልቡን ሰርቶ ነው:: በአጠቃላይ ሰሞኑን በአማራ ሳይንት ቀጠና በሰፊው የምዕራብ ወሎ ግንባር ነገሮች በፍጥነት ተቀይረዋል:: 2 መከላከያ እና ሚሊሻዎች የአማራ ፋኖ በወሎ ምዕራብ ወሎ ኮር አማራ ሳይንት መቅደላ ክፍለ ጦር አትሮንስ ብርጌድን በመሀል ሳይንት ወረዳ ግንባር ተቀላቅለው ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል የሚል መረጃ አሁን ደርሶኛል:: የአትሮንስ ብርጌድ አዛዥ ፋኖ ጎሹ ታረቀኝ የጠላትን አቅም እያሽመደመደው ነው:: ቁልፍ አዋጊዎችን አምጥቶበታል:: ይህ በእንዲህ እንዳለ በዚሁ በአማራ ሳይንት ቀጠና በለጋምቦ ወረዳ ግንባር ገነቴ አቅራቢያ ሰሞኑን ታሪክ ሲሰራ ሰንብቶ ኖሯል:: ጥር 6 ለ7 ሌሊት በተደረገ ጦርነት የአማራ ፋኖ በወሎ ምዕራብ ወሎ ኮር ቀኝ አዝማች ይታገሱ አረጋው ተወርዋሪ ክፍለ ጦር አደራጅ ኮሚቴ አባል እና የክፍለ ጦሩ ስራ አስፈጻሚ የሆነው ኮማንዶ ተመስገን ሳይንቴው ጀብዱ ፈፅሞ በጀግንነት ተሰውቷል:: የኮሩ ጊዜያዊ ኮሚቴው ተሰባስቦ አዳዲስ ስራ አስፈጻሚዎችን በመሰየም በሰራዊቱ ሊያፀድቅ ከየቦታው ተሰባስቦ ለጋምቦ ወረዳ እና ወግዲ ወረዳ ድንበር አቅራቢያ የምትገኝ ብስቁልል የምትባል መንደር ውስጥ ከኮሩ አዛዥ አርበኛ አደም አሊ ጋር ውይይት ላይ ሳሉ የኮሩ አዛዥ አጃቢ የነበረና ከቀናት በፊት ከድቶ ወደ መንግስት የገባ የየሹም አካባቢ ተወላጅ ባንዳ ከወግዲ ወረዳ በኩል ጠላትን እየመራ መጥቶ ከሌሎች የጎረቤት ወረዳዎችም ተጨማሪ ኃይል በቦታው በመድረስ ሌሊት ከባባ ቢፈፅምም ጀግኖች በታትነውታል:: ሞት አይፈሬው ሳይንቴ ከ4 ወረዳዎች የጥምር ጦሩ ጊዜያዊ ካምፓች ተውጣጥቶ በመጣ ከ400 የማያንስ መከላከያ እና እልቆ የለሽ አ.ሚ.ፓ. (አጥቦ አይለብሴ ሚሊሻ...አድማ ብተና እና ፓሊስ) ድብልቅ ሰራዊት ጋር በነበረው ትንቅንቅ በርካታ ጠላት ደምስሶ ተሰውቷል:: የአማራ ፋኖ በወሎ ምዕራብ ወሎ ኮር አዛዥ አርበኛ አደም አሊ ጋር ውጊያን በመምራት እሱም ፊት ለፊት ሲዋጋ ከበባ ሰብረው እና ጠላትን ከምሽጉ ነቅለው በማስፈርጠጥ ታላቅ ገድል እየፈፀመሙ ባሉበት ቅጽበት ነው በድንገት የተመታው:: በዚህ አውደ ውጊያ ከወግዲ በኩል ከመጣው ጥምር ጦር ብቻ 30 በጥይት ቀምሶ 17ቱ ሙት ሲሆን ቀሪው ቆስሏል:: በለጋምቦ በኩልም ከዙህ ያላነሰ ቁጥር ያለው ጠላት ተደምስሶ 20ዎቹ ጊምባ ተቀብረዋል:: ከ5 ቀናት በኋላ ከትናንት በስቲያ አስከሬን ለቀማ ወደ ውጊያው ቀጠና የተጓዘው ጠላት አርሶአደሮችን አፋልጉኝ ብሎ አስገድዶ ሲፈልግ ቆይቶ የ6 ወታደሮችን እግር አግኝቷል:: በብስቁልሉ ኦፕሬሽን በድምሩ ከ60 በላይ ጠላት እንደተመታ ነው መረጃዎች የሚያሳዩት:: የአማራ ፋኖ በወሎ ምዕራብ ወሎ ኮር ቀኝ አዝማች ይታገሱ አረጋው ተወርዋሪ ክፍለ ጦር ኦርዲናንስ ኃላፊን ጨምሮ አንድ የንጉሥ ሚካኤል አሊ ክፍለ ጦር ፋኖ መቁሰሉ የተገለፀ ሲሆን ከኮማንዶ ተመስገን ሳይንቴው ጋር መስዋዕትነት የከፈለም ሳይኖር እንዳልቀረ ነው የሰማሁት:: በጥቂት መስዋዕትነት አስገራሚ የሚባል ጀብዱ ተፈፅሟል ኮማንዶ ተመስገን እንደተሰዋም አንቆጥረውም ሲሉ ነው ጓዶቹ የገለፁት:: ሞት አይፈሬው ጀግና የሳይንቴይቱ ከአዲስ አበባ ድረስ ወደ ግንባር ከገባ ሁለት ወር አልሆነውም:: የቀኝ አዝማች ይታገሱን ደም የምንመልሰው ህዝባችን ነጻ ሲወጣ ነው ብሎ የወንድሙን ደም ሊመልስ ገብቶ የልቡን ሰርቶ ተሰውቷል:: ለወዳጅ ዘመድ እና ለጓዶቹ በሙሉ መጽናናትን እመኛለሁ!! ነፍስ ይማር!!

ቀጥታ ከቁንዝላ:- የአቸፈሩ አስደማሚ ትንቅንቅ! የቢትወደድ አያሌው ልጆች ጀግንነት! https://youtube.com/watch?v=BFK0hIx41eQ&si=uqvE6qwQFLj4Jewn

ምዕራብ ጎጃም ከቡሬ ከተማ ወጣ ብሎ ደረቋ ላይ ሀይለኛ ጦርነት በመካሄድ ላይ ሲሆን ከቡሬ ከተማ ታንክ እዬሄደ ይገኛል አስፈላጊው ጥንቃቄ እንዲደረግ መረጃው በአስቸኳይ ይዛመት።

የጣናው መብረቅ ብርጌድ ከባህር ዳር አፍጫ ስር በምትገኘው መሸንቲ ከተማ ውስጥ ትናትን 8 ሰአት ላይ የተሰካ ኦፕሬሽን ሰርቷል::

🔥🔥የዞዝ አምባ ንጉስ ክ/ጦር አስደናቂ የደፈጣ ኦፕሬሽን🔥🔥 👉የአማራ ፋኖ በጎንደር፦ የዞዝ አምባ ንጉሥ ክ/ጦር ትንታጎች ጥር 01/2017 ዓ.ም በሁለት ግንባሮች በተጠና ደፈጣ ወራሪ ሠራዊቱ ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሷል። 👉 የመጀመሪያ ግንባር ከእብናት በአራት ኦራል ተጭኖ ቋሊሳን ለመያዝ የተንቀሳቀሰን ወራሪ ሠራዊት ልዩ ቦታው ገላ ማጠቢያ የተባለ ቦታ ላይ ደፈጣ የጣሉት የዞዝ አምባ ንጉሥ ክ/ጦር፣ ተከዜ ግንባር ናደው ብርጌድ ባለ ልዩ ተልዕኮ መብረቆች አማካይነት በተወሰደ መብረቃዊ ጥቃት በርካታ ሙትና ቁስለኛውን እያዝረከረከ ፈርጥጦ ወደ እብናት ገብቷል። 👉 ሁለተኛው  ግንባር በተመሳሳይ ከእብናት በአራት ኦራል ተጭኖ ቆላ መልዛ ኒቋራ ከተማን ለመያዝ የተንቀሳቀሰን ወራሪ ሠራዊት በሌላኛዋ አግኝቸው ቢተዋ ብርጌድ በተጣለ ደፈጣ ከ20 በላይና በርካታ ቁስለኛውን እያዝረከረከ ፈርጥጦ እንደለመደው እብናት ከተማ ገብቷል።      ኅልውናችን በተባበረ ክንዳችን!!! የአማራ ፋኖ በጎንደር የሚዲያና ሕ/ግንኙነት መምሪያ

ወሎ ቤተ አምራ ውስጥ አስደናቂ ድል ተመዘገበ:- በደቡብ ወሎ ዞን መቅደላ ወረዳ የአማራ ፋኖ በወሎ ምዕራብ ወሎ ኮር አማራ ሳይት መቅደላ ክፍለ ጦር ሼህ ሁሴን ጅብሪል ብርጌድ ታሪካዊ ድል አስመዝግቧ
+1
ወሎ ቤተ አምራ ውስጥ አስደናቂ ድል ተመዘገበ:- በደቡብ ወሎ ዞን መቅደላ ወረዳ የአማራ ፋኖ በወሎ ምዕራብ ወሎ ኮር አማራ ሳይት መቅደላ ክፍለ ጦር ሼህ ሁሴን ጅብሪል ብርጌድ ታሪካዊ ድል አስመዝግቧል:: - ትናንት ታህሳስ 30 ቀን 2017 ዓመተ ምህረት ከወረዳው መቀመጫ ማሻ ከተማ ወደ ኮሬብ በሲኖትራክ ሲንቀሳቀስ የነበረ አድማ ብተና ላይ በተፈፀመ ድንገተኛ ጥቃት ሲኖትራኩ ላይ ያሉት አድማ ብተናዎችን እሳት በልቷቸዋል:: - ደምወዝ ተቀብለው ሲገሰግሱ ድስም የምትባል ቦታ ላይ ነው ጭዳ የተደረጉት:: የአማራ ሳይት መቅደላ ክፍለ ጦር ምክትል አዛዥ ፋኖ ሙሀመድ አሊ (ጭንቅየለሽ) እና የሼህ ሁሴን ጅብሪል ብርጌድ ዋና አዛዥ ፋኖ በለጠ ምትክ (ድሮን) በመሩት በዚህ ኦፕሬሽን አስደናቂ ድል ሊመዘገብ መቻሉን የአማራ ፋኖ በወሎ ምዕራብ ወሎ ኮር አማራ ሳይት መቅደላ ክፍለ ጦር ህዝብ ግንኙነት ሀላፊ ፋኖ ቃለአብ ወርቅዬ አስታውቋል:: - በዚሁ በመቅደላ ወረዳ ውስጥ ታህሳስ 28 ቀን አቶ ኢብራሂም የተባለ ግለሰብ ከኮሬብ ወደ ማሻ ከተማ የቤተሰቡን እና የጎረቤቹን የሴፍቲኔት ገንዘብ ለመቀበል እንደመጣ መነሀሪያ ፊት ለፊት ህይወቱን በግፍ ተነጥቋል:: ይህ ግለሰብ ከፋኖ ጋር ምንም አይነት ግንኙነት የሌለው ሲሆን ከዚህ ቀደምም አንድ የባጃጅ ሾፌርን ሙዚቃ ለምን ከፈትክ ብለው ህይወቱን ተነጥቋል ተብሏል:: ጥምር ጦሩ በንፁሀን ላይ አሰቃቂ ግፍ መፈፀሙን ቀጥሏል ያለው ፋኖ ቃለአብ ይህን ግፍ የሚፈፅም ጠላት ጋር ንግግር ስለሌለን በምክክር ኮሚሽን ስም ደሴ ተሰባስቦ የሚመክር አካል ወደ እኛ ቢመጣ ቅጣታችን የከበደ እና እስከ ሞት የሚደርስ ነው ብሏል::

ፋኖ ጋዜጠኛ ወግደረስ ጤናው የአማራ ፋኖ በጎጃም የህዝብ ግንኙነት ክፍል ስራ አስፈፃሚ አባል በመሆን የቴሌቪዥን ፕሮግራም አዘጋጅና ሀላፊ በመሆን ተሹሟል!
ፋኖ ጋዜጠኛ ወግደረስ ጤናው የአማራ ፋኖ በጎጃም የህዝብ ግንኙነት ክፍል ስራ አስፈፃሚ አባል በመሆን የቴሌቪዥን ፕሮግራም አዘጋጅና ሀላፊ በመሆን ተሹሟል!