ልሣነ አምሐራ ሚዲያ
Open in Telegram
በዚህ ቻናል ፈጣንና ወቅታዊ የአማራ ፋኖ እለታዊ ዘገባዎች እንድሁም ፈጣን ዜናዎች ይቀርባሉ። ለማንኛውም ጥቆማ በ @lisaneamhara ያናግሩን‼️
Show more1 970
Subscribers
No data24 hours
-77 days
-3430 days
Posts Archive
1 970
የቅድመ ጥንቃቄ መረጃ
በሰሜን ጎጃም ሙሉውን በሚባል ደረጃ የሚደረግ የድሮን ቅኝት እንዳለ የባህርዳር ዊክሊክስ ምንጮች ገልፀዋል። በተመሳሳይም በቋሪት ቆላማ ቦታዎች ላይ ትኩረት በማድረግ የሚደረግ ቅኝትም እንደታሰበ ለማወቅ ተችሏል።
1 970
የአደረጃጀት ዜና!
ከአማራ ፋኖ አንድነት በጎንደር፦ ንሥር በለሳ ቅጣው እጅጉ ክ/ጦር የተሰጠ መግለጫ
የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል ትናንት ከነበረበት ደረጃ ገዝፎ፣ የአደረጃጀት አንድነትን ፈጥሮ፣ በመርኅ መተታገልን አጠናክሮ ከሚጓዝበት ደረጃ ላይ ደርሷል። ትግላችን የዐይን ብሌናችን ነው፤ ትግላችን ከነፍሳችን ጋር በአቻነት የምንሳሳለት ነው፤ ትግላችን የሕዝባችንን ኅልውና ማረጋገጫችን ነው። ስለሆነም ይህን ትግል በሁሉም ዘርፍ መጠበቅ፦ የሕዝብን አደራ፣ የወጣንለትን ዓላማ፣ የመዳረሻ ግባችንን መጠበቂያ መልኅቃችን መሆኑን በውል መግለጽ እንወዳለን።
ወደ ጫካ የወጣነው፣ ከተመቻቸ ጎጇችን የወጣነው፣ ከልጆቻችን፣ ከወላጆቻችን በነጻ ፈቃዳችን የተለየነው ግፍንና ገፈኞችን ተቃውመን፣ ኅልውናችን መንግሥት መር በሆነ መንገድ አደጋ ውስጥ ገብቶብን፣ ነጻነት፣ ፍትሕና እኩልነት እንደ ሰማይ ርቀውን በአባቶቻችን በፋኖነትና በአርበኝነት ቁጭት እንጅ የግልና የቡድን ፍላጎት ልናስፈጽም አይደለም። በዚህም የፋኖነት ትግል የወል ጉዳይ የአማራን ሕዝብ ኅልውና ማረጋገጥ መሆኑን ለሕዝባችን ለመላው የትግል ጓዳችን አስረግጠን መግለጽ እንወዳለን።
እኛ በንሥር በላሳ ቅጣው እጅጉ ክፍለ ጦር አደረጃጀት ውስጥ የምንታገል አርበኞች የትግሉን መራርነት ትናንት በጀግንነት ጠላትን እንደቅጠል ጎዝጉዘው በተሰውት አርበኛ ሳላምላክ ነጋሽ፣ አርበኛ ጉልላት ጸጋዬ እና ሌሎችም ጓዶቻችን በዐይናችን ተመልክተናል። የተሰውለትን የትግል ዓላማም በታማኝነትና በጽናት አንድያ ኅያው ነፍሳችንን ሰጥተን ከዳር ለማድረስ በኅያው እግዚአብሔር ስም መሐላ አለብን።
በዚህ መሠረት ንሥር በለሳ ቅጣው እጅጉ ክ/ጦርን በመሠረቱት ብርጌዶች ሙሉ ይሁንታነት የወቅቱን የጠላት አሰላለፍ በወጉ ፈትሾ የሚያታግሉ አርበኞችን ወደፊት አምጥቶ ከ10 ቀናት በላይ ውይይቶችንና ሥልጠናዎችንም ጭምር አድርጎ ሪፎርም ሠርቷል። ይህንን ሪፎርምም ተቋማችን የአማራ ፋኖ አንድነት በጎንደር በላካቸው የተቋሙ ልኡካን አማካይነት እውቅና ተፈጥሯል።
በዚህ መሠረት፦
1. የክ/ጦሩ ዋና አዛዥ.............አርበኛ ሙሉቀን ካሳሁን
2. ም/አዛዥ........አርበኛ አብራራው ፀጋዬ
3. የዘመቻ መምሪያ …አርበኛ አበበ ገብሬ
4. ም/ዘመቻ አዛዥ....አርበኛ መሳፍንት ደጉ
5. የፖለቲካ መምሪያ ኃላፊ............ አርበኛ ጣዕማለው ወልዴ
6. ም/ፖ/መምሪያ ኃላፊ ...........አርበኛ መላክ ደሳለኝ
7. የሕ/ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ........... አርበኛ ሻምበል ኤርሚያስ
8. ልዩ ኦፕሬሽን መምሪያ ኃላፊ...........አርበኛ ሙሉቀን ዮሐንስ
9. ወታደራዊ አሥተዳደር...........አርበኛ አሠፋ በላይ
10."ሎጀስቲክስ መምሪያ ኃላፊ.............አርበኛ ይግዛው ጥጋቡ
11. ሥልጠና መምሪያ ኃላፊ.............አርበኛ ይበልጣል ምላሽ
12. አደረጃጀት መምሪያ ኃላፊ............አርበኛ ማስረሻው አለምነው
13. ፋይናንስ አሥተዳደር..............አርበኛ በላይ መልካም
እና ሌሎችን ኃላፊና ምክትል ኃላፊዎችን ያካተተ ሪፎርም ሠርተናል።
በመጨረሻም የአማራ ፋኖ አንድነት በጎንደር፦ ንሥር በለሳ ቅጣው እጅጉ ክፍለ ጦር ማስተላለፍ የሚፈልገው ጉዳይ ከጎንዮሽ መጓተት ወጥቶ መሬት ላይ ለሕዝባቸው ውድ ሕይወታቸውን የገበሩ የትግል ጓዶቻችንን አደራ ከዳር ማድረስ የሚቻለው በቅንነትና በእውነት ሐቀኛውን የአንድነት መንገድ መከተል ብቻ እንደሆነ ጽኑ እምነታችንን። ከምንም በላይ ክ/ጦራችንን በራሳቸው ፍላጎት ያለሠራዊታችን ይሁንታ የአፋሐድ ሚሊሻ ለማድረግ የፕሮፓጋንዳ ሥራ የምትሠሩ ሚዲያዎች ከድርጊታችሁ እንድትቆጠቡ ማሳሰብ እንወዳለን።
በዚህ መሠረት ንሥር በለሳ ቅጣው እጅጉ ክ/ጦር ትናንት በተበታተነ አደረጃጀት የነበረውን ታጋይ ለመሰብሰብ ጎንደርን በአንድ አታጋይ ተቋም የማታገሉ ሰናይ ተግባር እጅጉን ያስደሰተን መሆኑን እየገለጽን የአንድነት ተቋማችንም "የአማራ ፋኖ አንድነት በጎንደር" በሚሰጠን አቅጣጫ፣ አሠራርና መርኅ ለመታገል ያለንን ቁርጠኝነት ሳንገልጽ ማለፍ አንፈልግም።
ኅልውናችን በተባበረ ክንዳችን!!!
የአማራ ፋኖ አንድነት በጎንደር፦ ንሥር በለሳ ቅጣው እጅጉ ክፍለ ጦር
1 970
በዛሬው እለት የስናን አባጅሜ ብርጌድ እና የንጉስ ተክለሃይማኖት ብርጌድ ፋኖዎች በጥምረት ጀብድ ፈፅመዋል‼
የአማራ ፋኖ በጎጃም በቀኝ ጌታ ዮፍታሔ ንጉሴ ክፍለጦር አባል ብርጌዶች የስናኑ ስናን አባጅሜ ብርጌድ እና የደብረ-ማርቆሱ ንጉስ ተክለሃይማኖት ብርጌድ በጋራ በመሆን ከደብረማርቆስ ተነስቶ ወደ ረቡ ገበያ ባለስልጣናቱና ለመሸኘት እና ሬሽን ለማቀበል የተንቀሳቀሰዉን ጠላት አፈር ደቼ አብልተውታል::
በዚህም:
12 ክላሽ
1 ስናይፐር
ከ8 በላይ የወገብ ትጥቅ ከነሙሉ ሎዱ መማረክ የተቻለ ሲሆን 1 ፓትሮል ተቃጥሏል::
በርካታ ቁጥር ያከው የጠላት ሀይል ሲሸኝ የቆሰለውም ብዛት ያለው ነው ሲሉ ምንጮች ገልፀዋል።
1 970
#በአዋጅ_ቀን_ጀብድ‼
ልማደኛው #ዘንገና_ብርጌድና #ግዮን_ሰከላ ብርጌድ መብረቁ ሻለቃ ሁለቱ ተናባቢ ነብሮች ጠላትን ምርኮኛ ሙትና ቁስለኛ በማድረግ ታላቅ ድልን ተቀዳጅተዋል። ቀኑ አንድነት የተበሰረበት የጠላትን ቅስም የሰበርንበት ድማማ ዲክላሬሽን በመባል የሚታወቅና እየተከበረ ያለበት ታሪካዊ እለት ነዉ።
በዚህ ቀን ነዉ እንግዲህ ከሰከላ ወደ ቲሊሊ ተንቀሳቅሶ ሬሽን ለመቀባበል በማሰብ እንደቄጣማ ሲያረግድ ሲጨነቅ ሲጠበብ ቢዉልም በተያዘበት ደፈጣ ሰተት ብሎ ገብቶ ምርኮኛ ሙትና ቁስለኛ ሁኗል።
ከቀኑ 8:00 የጀመረዉ ዉጊያ አድማሱን እያሰፋ ከአሽፋ መገንጠያ እስከ አምቢሲ ዘልቋል።
የኔ ጠላት ያንተ ጠላት ምንለዉ የለንም፤እንደ አማራ ወጠን እንደ አማራ እናሸንፋለን።
በአንድነት ስንሆን እንዲህ ድል በድል ሁነን እንደምቃለን💪
ዝርዝር ምርኮ ከቆጠራ በኋላ የምናደርስ ይሆናል።
ኢትዮ 251 ሚዲያ
1 970
የቀኝ አዝማች ይታገሱ አረጋው ተወርዋሪ ክፍለ ጦር የመጀመሪያ ጉባኤውን ማካሄዱ ተገለፀ::
በዋርካው ምሬ ወዳጆ የሚመራው የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ አምሓራ) ቅርንጫፍ የሆነው ምዕራብ ወሎ ኮር ቀኝ አዝማች ይታገሱ አረጋው ተወርዋሪ ክፍለ ጦር የምዕራብ ወሎ ቀጠና ውስጥ ባሉ 11 ወረዳዎች ውስጥ የሚንቀሳቀስ ሲሆን ከጃማ እስከ ሳይንት እንድሁም ለጋምቦ እና ከላላ ድረስ ሌሎች ወረዳዎችንም አካሎ ከየአቅጣጫው በተውጣጡ ፋኖዎች የተዋቀረ ክፍለ ጦር ነው ተብሏል::
ክፍለ ጦሩ በኮማንዶዎች እንደሚመራም ነው ለማወቅ የቻልነው::
የጀግኖች ስብስብ የሆነውና በንፁሁ ታጋይ ስም የተሰየመው የዚህ ክፍለ ጦር አንዱ ከፍተኛ አመራር ጥር 6 ቀን 2017 ዓ/ም በርካቶችን ጥሎ መስዋዕትነት ሲከፍል ከ4 ወረዳዎች በውጭጩ የመጣው ጠላት ከ60 በላይ ኃይሉ ተደምስሶበታል::
በጥር ስድስቱ ውጊያ የተወርዋሪ ክፍለ ጦሩ ወታደራዊ አዛዥ ኮማንዶ ተመስገን አለምነው መስዋዕትነት የከፈለው ከበባ ሰብሮ እና በርካቶችን በመጣል ጀብዱ ፈጽሞ መሆኑን የምዕራብ ወሎ ኮር ባወጣው የሀዘን መግለጫ ላይ አስታውቋል::
የምዕራብ ወሎ ኮር አዛዥ አርበኛ አደም አሊ በተገኘበት ጉባኤውን ያካሄደው ተወርዋሪ ክፍለ ጦሩ በጎደሉ አመራሮች ቦታ አዳዲሶችን ተክቷል::
ጎርጎራ ቲቪ - ከእውነት ጋር
የጠብመንጃ አንጋቾች ድምጽ
1 970
የደብረ ኤልያስ ቀስተ ደመና ብርጌድ ፋኖዎች በጠላት ላይ ድልን ተቀዳጁ!
==============================================
ራሱን መከላከያ እያለ የሚጠራው የፋሽስታዊው አብይ አህመድ ወንበር አስጠባቂ የሽብር ቡድን ደብረ ኤልያስ ከተማ ገብቶ በጀግኖቹ የአማራ የቁርጥ ቀን ልጆች መገረፍ ከጀመረ ድፍን ሁለት ወራት አልፈዋል።በእነዚህ ጊዜያት ውስጥ በርካታ የወራሪው ጦር እስከ ወዲያኛው ተሸኝቷል።በርካቶችም ቆስለዋል።
ቀደም ብሎ ካስገባው የጠላት ኃይል በተጨማሪ ከሰሞኑ በርካታ ሰራዊት ማስገባቱ ይታወቃል።ይህም የወረዳውን ገጠራማ አካባቢ ለመቆጣጠርና በዋናነት ግን የብሔረ ብጹዓን አጼ መልክዓ ስላሴ አንድነት ገዳምን በድጋሚ ለማውደም እየተደረገ ያለ እንቅስቃሴ ነው።
ዛሬም ከደብረ ኤልያስ ከተማ ሙሉ ጦሩንና መሳርያዎቹን ጭኖ ወደ ጓይ መገንጠያ በተንቀሳቀሰው የጠላት ኃይል ላይ ጀግኖቹ የቀስተ ደመና ብርጌድ ፋኖዎች ከፍተኛ የሆነ ውጊያን በመክፈት ታላቅ ኪሳራን አድርሰውበታል።በአርበኛ ድረስ አለማየሁና አርበኛ ነጋ መኮንን የተመራው ይህ ውጊያ የጠላትን ቅስም የሰበረ ነበር።ጠላት በዙ-23ና በሞርተር የታገዘ ውጊያ ቢያደርግም ቀስተኞቹ ግን ከምሽጋቸው ፍንክች ሊሉ አልቻሉም።
በዚህ ውጊያ በወገን በኩል ቀላል ቁስለኛ ከሆኑ ጥቂት ፋኖዎቻችን ውጭ የተከፈለ መስዋዕትነት የሌለ ሲሆን በጠላት በኩል ግን 16 አምቡላንስና ፓትሮል በቁጠር ደረጃ ከ112 በላይ ቁስለኛ የተነሳ ሲሆን የሟቹን መጠን ግን በተረጋገጠ መረጃ ማወቅ አልተቻለም።ምክንያቱም በየቦታውና ምሽግ ባደረጉት የሳሰር ቤተ ክርስቲያን ይቀብሩት ስለነበር ነው።ይሁን እንጅ ከቁስለኛው በላይ ሊሆን እንደሚችል ግን የአካባቢው ነዋሪዎች ገልጸውልናል።
ጠላት በአሁኑ ሰዓት በጎፍጭማ ታዳጊ ከተማና የቀጋት ቤተ ክርስቲያን ላይ የሚገኝ ሲሆን የትኩረት አቅጣጫውም የብሔረ ብጹዓን አጼ መልክዓ ሥላሴ አንድነት ገዳምን በድጋሚ ለማውደም እንደሆነ ይታወቃል።
ደብረ ኤልያስ ግን ጠላትን ውጣ ማስቀረቷን ቀጥላለች ትቀጥላለችም።
ድል ለሕዝባችን!
ክብር ለሰማዕቶቻችን!
አዲስ ትውልድ፣አዲስ ተሰፋ፣አዲስ አስተሳሰብ!
ፋኖ ኢ/ር ዘመን ባሳዝነው
የአማራ ፋኖ በጎጃም የቀኝ ጌታ ዮፍታሔ ንጉሴ 6ኛ ክፍለ ጦር
የቀስተደመና ብርጌድ ፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ
ጥር 19/2017 ዓ.ም
