ልሣነ አምሐራ ሚዲያ
Open in Telegram
በዚህ ቻናል ፈጣንና ወቅታዊ የአማራ ፋኖ እለታዊ ዘገባዎች እንድሁም ፈጣን ዜናዎች ይቀርባሉ። ለማንኛውም ጥቆማ በ @lisaneamhara ያናግሩን‼️
Show more1 970
Subscribers
No data24 hours
-77 days
-3430 days
Posts Archive
1 970
የጉና ክፍለ ጦር የአደረጃጀት(Reform) መረጃ
ግንቦት 4/2017ዓ.ም
የፋኖ ትግል እየጎመራና እየገዘፈ ከሄደበት ጊዜ አንስቶ በአማራ የፋኖ ትግል የመጀመሪያዉ ክ/ጦር የሆነዉ ታላቁና ገናነዉ ጉና ክ/ጦር ሪፎርም አደረገ።
የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ኃይል(አፋብኃ) የሜጀር ጀኔራል ዉባንተ አባተ ኮር(፩ኛ ኮር) አካል የሆነዉ ጉና ክ/ጦር ዋና የትግል ዓላማ ህዝብን አስተባብሮ የተጋረጠብነን የህልውና አደጋ በመቀልበስ የነፃነት፣ የአንድነት ፣ የፍትህ ፣ የእኩልነት ፣የዴሞክራሲ እና የሰብአዊ መብት ጥያቄዎችን ዘለቄታዊ በሆነ መንገድ በመፍታት ሁለንተናዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ እንደሆነ መላው ወገናችን የሚገነዘበው የአደባባይ ሀቅ ነው ።
ክፍለ ጦሩ በዚህ የህልውና ትግል ላይ ማንኛዉንም የትግል እንቅስቃሴና ጉዞ እንዲቀላጠፍ ግንባር ቀደም በመሆን ለፋኖ ትግል የማዕዘን ድንጋይ በመሆን ሁልጊዜ ታሪክ የሚመሰክረው ከተከዜ እስከ ዳዉንት፣ ከዳዉንት እስከ ጭስ አባይ፣ከጭስ አባይ እስከ ጣና ክርስቶስ ሰምራ ድረስ የትግል አድማሱን በማስፋት የጠላትን አከርካሪ እየሠበረዉ ቆይቷል። በኋላም የፋኖ ትግል አድማሡን እያሠፋና የሠዉ ኃይሉ እየገዘፈ ሲመጣ የተለያዩና ሠፊ የሠዉ ኃይል ያላቸዉ ክ/ጦሮች ሲመሠረቱና ሲስፋፉ ጉና ግንባር ቀደም አደራጅ በመሆን ታሪክ የማይረሰዉ አሻራ አሣርፏል። አሁንም ዋና የጠላት ማዘዣ ጣቢያ በሆነዉ ደብረታቦር ዙሪያ በሆነዉ ከክምር ድንጋይ እስከ ስማዳ ዦጋ በረሀ፣ከዦጋ እስከ ጭስ አባይ፣ ከጭስ አባይ እስከ ጣና ክርስቶስ ሰምራና አዲስ ዘመን ድረስ አድማሡን በማስፋት ጣላትን መዉጫ እና መግቢያ አሳጥቶ እየቀጠቀጠዉ ይገኛል።
በአጠቃላይ ጉና ክ/ጦር ባለበት እና በደረሥንበት ቦታ ሁሉ ጠላት ተደምስሷል ፣ ተመትቷል፣ ተዋርዷል እንዲሁም እንደ ጠዋት ጤዛ በየወጣበት ቀጠና ረግፎ ቀርቷል። ይህ የዘወትር ተግባር በዚህ መልኩ እየተከናወነ ያለው የአመራሩና የአባላቱ ጠንካራ መሆን፣ መደማመጥ እና መግባባት መቻሉ ፣ የእርስ በርስ ልምድና ዕውቀት ልውውጦች ማድረጋቸዉ እንዲሁም ድርና-ማግ ሁነዉ በመስራታቸዉ ሲሆን እስካሁን የተጓዘበትን ጠንካራ መንገድ ለማስቀጠል፣ እንደ ወርቅ በሳት መፈተናቸዉን ያለ ድል ላይቆም፣ የህዝባቸዉን አለኝታነት እና መከታነት ላይገቱትና ላያቆሙት የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ኀይል/ሜጀር ጀኔራል ዉባንተ አባተ ኮር(፩ኛ ኮር) አመራሮች አርበኛ አመኑ አለም አንተ የኮሩ ሰብሳቢ፣ አርበኛ ቢራራ ደምሤ የኮሩ ዘመቻ መምሪያ፣ አርበኛ በላይነዉ ዳኘዉ የኮሩ ወታደራዊ አዛዥ፣ አርበኛ ሀቅአለዉ ፀጋ የኮሩ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ፣ አርበኛ አበበ ሞገስ የኮሩ ፅ/ቤት ኃላፊ፣ አርበኛ አብተዉ የኮሩ አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ እና አርበኛ ዘመነ እረኛዉ የኮሩ የፖለቲካ ዘርፍ ሀላፊ እና የአማራ ፋኖ አንድነት በጎንደር የማህበራዊና ዕሴቶች ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ አርበኛ መ/ር ፀዳሉ ሙላት እና የአማራ ፋኖ አንድነት በጎንደር ም/የህዝብ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ አርበኛ ድረስ ሞላ በተገኙበት ጉና ክ/ጦር የአመራር ሪፎርም ያደረገ መሆኑን እናሳዉቃለን።
በዚህም መሠረት፦
1.ሰብሳቢ:- አርበኛ ወንዱአንተ አሰፋ
2. ም/ሰብሳቢ፦አርበኛ ይሁኔ አሰፋ
3. ጽ/ቤት ኃላፊ፦ አርበኛ ዮኋንሥ ይርዳዉ
4. ወታደራዊ አዛዥ፦አርበኛ አዛዥ ደሣለኝ
5.ም/ወ/አዛዥ፦ አርበኛ አበራ ንብረቱ
6,ዘመቻ መምሪያ፦ አርበኛ መልሠዉ ደሥተዉ
7.ም/ዘመቻ መምሪያ፦ አርበኛ ጀምበር ገ/መሥቀል
8.ወታደራዊ አስተዳደር፦አርበኛ መ/ር በለጠ አለምነዉ
9.የሰው ኃይል:-አርበኛ ሳሙኤል አባይ
10.ሥልጠና:-አርበኛ ዮሀኒስ የኔአለም
11.ሎጀስቲክ:- አርበኛ ዳንኤል ሙጨየ
12.ፖለቲካ:-አርበኛ አማረ እንደግ
13.ህ/ግንኙነት:- አርበኛ መ/ር አሀዱ በየነ
14,ፋይናንስ እና ንብረት አስተዳደር:-አርበኛ አማረ በላይ
15.አደረጃጀት፦አርበኛ አስረስ መርሻ
16.መረጃና ደህንነት፦ *
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል❗
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን
ሜጀር ጀነራል ውባንተ አባተ ኮር(፩ኛ ኮር)
ጉና ክፍለ ጦር
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ)
ግንቦት 04/09/2017 ዓ.ም
ጎንደር/አምሐራ/ኢትዮጵያ
1 970
«አማራ ፋኖ ብሄራዊ ኃይል»
ለአማራ ህዝብ መብት እና ጥቅም የሚታገል ፤ለአማራ ህዝብ ህልውና ዘብ የሚቆም ፤ የአማራን ህዝብ ጥቅም የሚያስቀድም Amhara First የሆነ ብሄርተኛ ድርጅት መሆኑን ለመግለፅ በድርጅቱ መጠሪያ ስያሜ ላይ “ብሄራዊ” የሚል ቃልን እንዲካተት ተደርጓል።(ኤልሻዳይ የግዮን ልጅ)
#Amhara #Ethiopia
