cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

ቲሐርቃ ዜና

ያልተሰሙና አዳዲስ ሁሉን አቀፍ መረጃወች ለተጨማሪ ጥቆማ አስተያየቶች @Piyanki2020 ላይ ያናግሩን

Show more
Ethiopia12 141Amharic10 185The category is not specified
Advertising posts
197
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
-330 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

“ለቀጣይ 5 ዓመታት ቱርክን እንድመራ የሀገሪቱ ህዝብ ኃላፊነት ሰጥቶኛል”-ፕሬዝዳንት ኤርዶጋን ረጀብ ጣይብ ኤርዶጋን በድጋሚ የቱርክ ፕሬዚዳንት ሆነው ተመረጡ!! ረጀብ ጣይብ ኤርዶጋን በቱርክ ለሁለተኛ ዙር የተካሄደውን ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ በማሸነፍ በድጋሚ የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት መሆናቸውን አረጋግጠዋል። ከ20 ዓመታት በላይ ቱርክን የመሩት ኤርዶጋን በዛሬው ዕለት በተካሄደው ሁለተኛ ዙር ምርጫ ብርቱ ተፎካካሪያቸው የነበሩትን ከማል ኪሊዳሮግሉን በማሸነፍ ነው ሀገሪቱን ለቀጣይ አምስት ዓመታት መምራታቸውን ያረጋገጡት ሲል አልጀዚራ የሀገሪቱን ሚዲያ ጠቅሶ ዘግቧል።  
Show all...
ናያጄሪያዊዉ ቱጃር አሊኮ ዳንጎቴ በሃገሩ በትልቅነቱ በአለም ተወዳዳሪ የሌለውን የነዳጅ ማጣሪያ ገነባ👏 በ19 ቢሊየን ዶላር የተገነባው የነዳጅ ማጣሪያው በአለም ትልቁ በአፍካም ደግሞ በአይነቱ የመጀመሪያው ነው ተብሏል። የነዳጅ ማጣሪያው ናይጄሪያን ከአፍሪካ ትልቋ የተጣራ ነዳጅ አቅራቢና ላኪ አገር እንደሚያደርጋ ተመልክቷል፡፡ ለአስር ሺዎችም የስራ እድል እንደሚፈጥር ቢቢሲ ጽፏል። ይህ በግዙፍነቱ በአለም ተወዳዳሪ የሌለው የነዳጅ ማጣሪያ በቀን 650 ሺ በርሜል ነዳጅ የሚያጣራ ሲሆን ኩባንያው በሚቀጥለው የፈረንጆቹ አመት በሙሉ አቅሙ ወደ ምርት ሲገባ የአገሪቱን የነዳጅ ፍላጎት ሙሉ በሙሉ በማሟላት ወደ ውጭ እንደሚልክ ታውቋል፡፡ ቲሐርቃ ዜና
Show all...
የማህበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን በኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን በጊዜያዊነት ታገደ። ባለስልጣኑ ፤ ቅዱስ ሲኖዶስ እያደረገ ያለዉን ስብሰባ አስመልክቶ ግንቦት 13 ቀን ሰበር በሚል ባሰራጨው መረጃ መሆኑን ጠቅሷል። ይህም ህዝብን ለግጋጭት የሚያነሳሳ መልዕክት በማሰራጨቱ ነዉ ብሏል።በቀጣይ የባለስልጣኑ ቦርድ ተወያይቶ ዘላቂ ዉሳኔ እስኪሰጥ የጣቢያዉን ፈቃድ አግጃለሁ ብሏል። ቲሐርቃ ዜና
Show all...
በመንግስት በጀት የሚሰራው አባ ቶርቤ እንዲህ ነው የሚያስበው። ይህ ቡድን የኦሮሚያ ክልልና የፌደራል የኦሮም አመራር ያደራጀው ነው። ስሙም "oro abbichu" ነው። ኦርቶዶክስን፣ አማራን እንዲህ ነው የሚያስባቸው። "ምርጥ ስራ እየሰራ ነው።" ተብሎ መወደሱን በመልዕክት መለዋወጫው ተቀምጧል። በዚህ ወቅት ኦርቶዶክስ ላይ እየፈፀመ ያለው ተግባር በዚህ ጥላቻው መሰረት ነው። የኦሮሞ የክልልና የፌደራል ፀጥታና የፓርቲ ሰዎች የተካተቱበት ቡድን ነው።
Show all...
ኃይሉ አዱኛ ይባላል። የኦሮሚያ ክልል ክልል ኮሙኒኬሽን ኃላፊ ነው። "oro abbichuu" የተባለውን ቡድን በመረጃ ይመራል። የተያያዘው ፅሁፍ በውስጥ የተወያዩበት እንደሆነ አንከር ዘግቦታል። አብዛኛው አዲስ አበባ ውስጥ ሱቁን፤ ሻይ ቤቱን ወዘተ እንዴት መቆጣጠር እንዳለባቸው የሚገልፅ ነው። ሌላውን አፈናቅለው ሰላይ ያስገቡበታል። አማራ ክልል ጭምር የሀሰት መረጃ እያቀናበሩ የፌደራል ግብረኃይል ለሚሉት ያደርሳሉ። እነዚህ ሰዎች የፃፉትን ነው እነ ለገሰ ቱሉ ሳይቀር መግለጫ ብለው የሚያወጡት። ረስቸው! አገሩን የሚመራው 100 ፐርሰንት የኦሮሞ መንግስት ነው ይላሉ። እንዴት አይበሉ። መንግስት ቢኖር ይሄ ነበር ኢመደበኛ አደረጃጀት።
Show all...
የአፋኙ ቡድን ሚስጥር! ኢ መደበኛማ ይሄውልህ! ፅንፈኛማ ይሄውልህ! አገር እየተመራ ያለው በዚህ መልክ ነው። እነዚህን ምስሎች ከአንከር ሚዲያ ነው የወሰድኳቸው። የኦሮሚያው አፋኝ ቡድን ነው። ከኦሮሚያ እስከ አዲስ አበባ፣ ሸገር ሲቲ ከሚለው እስከ አማራ ክልል ተደራጅቶ ይሰልላል። አዲስ አበባ ላይ ቤትና ቦታ እንዴት እንደሚነጥቅ ይወያያል። በየመስርያ ቤቱ የራሱን አባላት ይሰገስጋል። በሀሰት እየሰለሉ ያሳፍናሉ። የፌደራል የጋራ ግብረ ኃይል የሚባለውን የሚመሩት እነዚህ ናቸው። ከኦሮሚያ ክልል እስከ ፌደራል ፀጥታና የፓርቲ አባል፣ አክታቪስት ወዘተ ተደራጅተዋል። የኦሮሚያ ክልል ኮሙኒኬሽን ኃላፊ ኃይሉ አዱኛ መረጃውን ለክልል አመራሮች ያደርሳል። የክልል አመራሩ የፌደራል ግብረኃይል ለሚባለው ይሰጣል። የፌደራሉ መግለጫ የሚያወጣው ይህ የኦሮሚያው ማፍያ ቡድን የሚሰራውን ነው። የኦሮሞ ተወላጅ የሆኑ የፌደራል ፀጥታ አባላት፣ አዲስ አበባ የኦሮሚያ ብልፅግና በሙሉ ስራቸው አማራን በጥቆማ ማሳፈን ነው። ይህ ስራቸው በፌደራልም በክልልም የተመሰገነ፣ እየተደገፈ ያለ ሆኗል። ቡድኑ ማን ይባላል? "ORO abbichuu team" ኢመደበኛ አደረጃጀት ማለት ይሄ ነው። በአማራና ኦርቶዶክስ ጥላቻ የናወዘ ቡድን አማራን በሀሰት ፈርጆ የፌደራል ፀጥታ ያስራል። መረጃው ከአንከር ሚዲያ የተወሰደ ነው። ሄዳችሁ ተመልከቱት።
Show all...
ኦሮሚያ ክልል ሸገር ሲቲ በሁለት ቀናት ትናንትና ዛሬ 4 መስጅዶች መፍረሳቸው ተሰምቷል። ① በገላን ጉዳ ኤርቱ ሞጆ የሚገኝ ሐሊማ መስጂድ ② ወለቴ አካባቢ ሐምዛ መስጅድ እና ③በፉሪ ክ/ከተማ በጨፌ ከራቡ ወረዳ ስር የሚገኘው ሐምዛ መስጂድ ዛሬ ረቡዕ የፈረሱ ናቸው ተብሏል። ④ ትናንት ደግሞ አጃምባ ተብሎ በሚጠራ አከባቢ ኑር መስጂድ መፍረሱን  ምዕመናን ተናግረዋል።ከሰሞኑ በአሽዋ ሜዳ፣በ44 ማዞሪያና ለገጣፎ አካባቢ ከ840 በላይ መኖሪያ ቤቶች እንደፈረሱም ተሰምቷል።
Show all...