en
Feedback
ዳሩል ሀዲስ ኢንስቲትዩት Darul Hadith institute

ዳሩል ሀዲስ ኢንስቲትዩት Darul Hadith institute

Open in Telegram

ዳሩል ሀዲስ የዓረብኛ ቋንቋ እና የሸሪዓዊ ትምህርቶች ኢንስቲትዩት ✔ ኢስላማዊ ቤተ መፃህፍት ✔ የቁርአን ሂፍዝ ፕሮግራም ✔ የአረብኛ ቋንቋ እና ሸሪዓዊ ትምህርቶች معهد دار الحديث لتعليم اللغة العربية والعلوم الشرعية (أديس أبابا – تأسيس 1436 هے) «من يرد الله به خيرا يفقهه في الدين» 👍ዳሩል ሀዲስ

Show more
2 742
Subscribers
No data24 hours
-57 days
-2630 days
Posts Archive
መርከዛችንን የታህፊዝ አስተማሪነት ለረጅም አመታት ስታገለግል የቆየችው ኡስታዛ ነስራ መሀመድ በኢዕቲካፍ ላይ ሳለች ባጋጣሚ ወደ አኼራ ሄዳለች። አላህ መልካም ስራዋን እንዲቀበላት መጨረሻችንንም እንዲያሳምረው እንለምናለን። ለቤተሰብዋ፣ ለጓደኞቿ እና ለመላው የመርከዙ ቤተሰቦች መፅናናትን እንመኛለን። ____ ዳሩል ሀዲስ ኢንስቲትዩት T.me/darulhadis18

🎊 ሴቶች ለሴቶች የሙሀደራ ፕሮግራም የተለመደው ወርሃዊ የሙሀደራ ፕሮግራማችን በአላህ ፈቃድ፦ ▪️እምነታችን እና ▪️ብዙዎች የተዘናጉባቸው ክልከላዎች በሚሉ ወሳኝ ርእሶች ትምህርት አዘጋጅተን እየጠበቅናችሁ ነው። ☑️ ኑ! ተባብረን የተሻለ ማንነት በመፍጠር የሁለት ሀገር ስኬትን እንጎናፀፍ! 🗓 ቅዳሜ ሚያዝያ 8፣2014 🕝 ከጠዋቱ 3:00-6:00 ቀጠሮአችን በኢማሙ አህመድ መስጂድ ይሁን። 🕌 አድራሻ: አለም ባንክ/ አንፎ አል-ጋዚ አደባባይ ⚠️መልእክቱን ለእህቶች በማድረስ የአጅሩ ተቋዳሽ እንሁን! https://t.me/darulhadis18

🎊 እንዳያመልጣችሁ! ሴቶች ለሴቶች የሙሀደራ ፕሮግራም የተለመደው የሙሀደራ ፕሮግራማችን በአላህ ፈቃድ፦ ▪️ ስለተከበረው የእዝነት ወር አቀባበል እና ሌሎች ወሳኝ ርዕሶች ለመተዋወስ 🗓 እሁድ መጋቢት 18፣2014 🕝 ከጠዋቱ 3:00-6:00 ቀጠሮአችን በኢብኑ መስዑድ ይሁን። 🕌 አድራሻ: 18 አደባባይ የሚገኘው መርከዝ ኢብኑ መስዑድ ⚠️መልእክቱን ለእህቶች በማድረስ የአጅሩ ተቋዳሽ እንሁን! https://t.me/darulhadis18

🎊 ሴቶች ለሴቶች የሙሀደራ ፕሮግራም የተለመደው ወርሃዊ የሙሀደራ ፕሮግራማችን በአላህ ፈቃድ፦ የመሰረቶች ሁሉ መሰረት ስለሆነው ▪️አላህን ማወቅ እና ▪️ የተከበረውን የእዝነት ...ወርን እንዴት እንቀበለው? እንዴትስ እንጠቀምበት? በሚሉ ርዕሶች ይሆናል። ☑️ ኑ! ተባብረን የተሻለ ማንነት በመፍጠር የሁለት ሀገር ስኬትን እንጎናፀፍ! 🗓 ቅዳሜ መጋቢት 10፣2014 🕝 ከጠዋቱ 3:00-6:00 ቀጠሮአችን በኢማሙ አህመድ መስጂድ ይሁን። 🕌 አድራሻ: አለም ባንክ/ አንፎ አል-ጋዚ አደባባይ ⚠️መልእክቱን ለእህቶች በማድረስ የአጅሩ ተቋዳሽ እንሁን! https://t.me/darulhadis18

جدول_حفظ_القرآن_في_سنة_بدون_تاريخ.pdf2.98 MB

ሂዳያ በነሲሓ የታዳጊዎች የረመዳን ኮርስ || NesihaTv አስደሳች ዜና ለታዳጊዎች 👉🏼 ኢስላማዊ ዕውቀት መገብየት ትሻላችሁ? 👉🏼 ረመዳንን እንዴት በአግባቡ ልጠቀምበት ብላችሁ ተጨንቃችኋል? 👉🏼 ራሳችሁን መለወጥ ትፈልጋላችሁ? እንግዲያውስ የብስራት ዜና እነሆ! ሂዳያ በነሲሓ የረመዳን የታዳጊዎች ኮርስ ለናንተ በሚመጥን! ወደችሁ እንድትከታተሉት ሳቢና ማራኪ በሆነ አቀራረብ! የተዘጋጀ "የረመዳን ጉዞዬ" የተሰኘ አዲስ መጽሐፍ በኮርስ መልኩ ቀርቦላችኋል! መጽሐፉ እናንተን ታሳቢ ተደርጎ የተዘጋጀ ሲሆን። በውስጡ 👉🏼 ሐዲሦች 👉🏼 ጥያቄዎች 👉🏼 የእቅድ መጻፊያዎች 👉🏼 ራስን መገምገሚያ መጠይቆች እና መመዘኛ ጥያቄዎችን እንዲሁም የምስክር ወረቀት አካቶ ይዟል። የመጽሐፉ ማብራሪያ ፕሮግራም በነሲሓ ቴሌቪዥን በረመዳን 1433 ይቀርባል። መጽሐፉን በማንበብ ኮርሱን በመከታተል በረመዳን አዲስ የለውጥ ጎዞ ጀምሩ… መጽሐፉን ለማግኘት 👉🏼 በአልዐፊያ ትምህርት ቤቶች ሁሉም ቅርንጫፎች 👉🏼 በኢብኑ መስዑድ ኢስላሚክ ሴንተር ቅርንጫፍ ጣቢያዎች አስራ ስምንት 👉🏼 ቤተል ነሲሓ ቲቪ ቢሮ 👉🏼 አባ ጂፋር (የቀድሞ መርየም) መድረሳ 👉🏼 ቤተል ተቅዋ መስጂድ አካባቢ ባለው መድረሳ 👉🏼ቃሊቲ ኢሕሳን መድረሳ 👉🏼ፊሊ ዶሮ አካባቢ ኡማ መድረሳ 👉🏼አቃቂ ቢላል መስጂድ በተጨማሪም 👉🏼 ግራር ነሲሓ መድረሳ 👉🏼 አንፎ ኢማሙ ነወዊይ ሒፍዝ ማዕከል 👉🏼ሎሚ ሜዳ ዐሊ መድረሳ 👉🏼 ስልጤ ሰፈር ሰላም መስጂድ 👉🏼 አብነት 26 ዑመር ኢብኑል ኸጣብ መስጂድ እና አልፋሩቅ መድረሳ 👉🏼 ኮካ ቢላል መስጂድ 👉🏼አንፎ ኢማሙ አሕመድ መስጂድ 👉🏼 ወይራ ሰልማን አላፋሪስ መስጂድ በክልል ከተሞች 👉🏼 ወሊሶ 👉🏼 ደሴ 👉🏼 ባህርዳር 👉🏼 አዳማ እና 👉🏼 ጉብሬ 👉🏼 እንዲሁም በተለያዩ ኢስላማዊ ማዕከላት ማግኘት ይችላሉ! ለበለጠ መረጃ ስልክ፦ 0930484284 ሂዳያ ተርቢያ ከነሲሓ ቲቪ ጋር በመተባበር፡፡ @nesihatv

ሂዳያ በነሲሓ የታዳጊዎች የረመዳን ኮርስ || NesihaTv ለበለጠ መረጃ ስልክ፦ 0930484284 ሂዳያ ተርቢያ ከነሲሓ ቲቪ ጋር በመተባበር @nesihatv

📣 የፕሮግራምና የቦታ ለውጥ ወርሃዊ የሴቶች ለሴቶች ፕሮግራም ለነገ እሁድ የካቲት 27 መቀጠሩ ይታወሳል ሆኖም በዚሁ እለት በመርከዙ አቅራቢያ ባለው አባጅፋር መስጂድ የተዘጋጀ ሙሃደራ ስላለ ሴቶች ይህን ፕሮግራም እንዲታደሙ እየጋበዝን ለተፈጠረው የፕሮግራም መዛባት ይቅርታ እንጠይቃለን። ✔️መልእክቱን በማዳረስ የተለመደው ትብብራችሁ አይለየን። https://t.me/darulhadis18

👆ለነገ እንዳያመልጥዎ!
👆ለነገ እንዳያመልጥዎ!

⚠️የፕሮግራም ለውጥ አንዳንድ የግል እንዲሁም የመንግስት ትምህርት ቤቶች የሴሚስተር እረፍት ጊዜ ቀድሞ ከያዝነው ፕርግራም ጋ ባለመገጣጠሙ የታዳጊዎች ኮርስ መስጫ ጊዜው (የሁሉም ጣቢያ)ወደ ቀጣዩ ሳምንት ማለትም የካቲት 21 መሸጋገሩን ከአክብሮት ጋ እናሳውቃለን። መልእክቱን አስተላልፉት❗️ ኢብኑ መስዑድ ኢስላሚክ ሴንተር @darulhadis18

📣ቤተልና አካባቢዋ ለሚገኙ ሴት ታዳጊዎች አማራጭ የኮርስ ጣቢያ 🏢ቤተል 30 ሜትር ላይ የሚገኘው አልአፊያ ት/ቤት ለበለጠ መረጃ +251911062499 ይደውሉ @darulhadis18

🌼ሴቶች ለሴቶች ወርሃዊ የሙሃደራ ፕሮግራም🌼 ኑ! ስለራሳችንና ሰለዲናችን በጋራ በመመካከር የተሻለ ማንነት እንፍጠር! በአላህ ፈቃድ ስራዎቻችን አላህ ዘንድ ተቀባይነት ይኖረው ዘንድ ማሟላት ያለብን 2 መስፈርቶች 🌴ኢኽላስ (ኒያን ማጥራት)እና 🌴ሙታበአቱ ረሱል (መልእክተኛውን አለይሂ ሶላቱ ወሰላም መከተል) የሚሉ ርእሶች የሚዳሰሱበት ድንቅ ፕሮግራም አዘጋጅተን የእናንተን ውድ እህቶቻችንን መምጣት በናፍቆት እየጠበቅን ነው! 🗓 ቅዳሜ የካቲት 12፣2014 ⏱ከጠዋቱ 3:00-6:30 🕌 አድራሻ አለም ባንክ የሚገኘው ኢማሙ አህመድ (አንፎ ሜዳ) መስጂድ መልእክቱን ሼር እናድርገው። @darulhadis18

ታዳጊዎች የመጪው ጊዜ የኢስላም ተረካቢዎች! ውድ ለሆኑት ትውልዶች! ለታዳጊ ተማሪዎች የተዘጋጀ ለ 5 ቀናት የሚቆይ ድንቅ ኮርስ! በአላህ ፈቃድ፦ ▪️ከዕውቀቶች ሁሉ ታላቅ ስለሆነው ዕውቀት የሚማሩበት
ታዳጊዎች የመጪው ጊዜ የኢስላም ተረካቢዎች! ውድ ለሆኑት ትውልዶች! ለታዳጊ ተማሪዎች የተዘጋጀ ለ 5 ቀናት የሚቆይ ድንቅ ኮርስ! በአላህ ፈቃድ፦ ▪️ከዕውቀቶች ሁሉ ታላቅ ስለሆነው ዕውቀት የሚማሩበት! ▪️መልካም ስነ ምግባር የሚላበሱበትን ቁልፍ የሚያገኙበት! ▪️የኢስላምን ውበት ተረድተው በእምነታቸው የሚኮሩበት! ▪️አላህን በማውሳት ልዕልና ከፍ የሚሉበት! ⚠️ኮርሱ የሚሰጠው ለሁለቱም ጾታዎች በሁለት ደረጃዎች ተከፍሎ ሲሆን፦ ደረጃ 1፡ ዕድሜያቸው ከ12-14 ደረጃ 2፡ ዕድሜያቸው ከ15-18 🗓ቀን ከየካቲት 14 - 18፣2014 🕘ጠዋት ከ3:00-6:30 🕌 አድራሻ ለሴቶች፦18 ማዞሪያ አካባቢ ከቀድሞ አልአፊያ ት/ቤት አጠገብ ለወንዶች፦ቤተል 40ሜትር የሚገኘው አልአፊያ ት/ቤት ለመመዝገብ፦ ለሴቶች 0967671891 ወይም 0904366666 ለወንዶች 093 048 4284 ይደውሉ ወላጆች ልጆቻችሁን በመላክ ኃላፊነታችሁን ተወጡ! እኛም መልዕክቱን በማስተላለፍ ሀላፊነታችንን እንወጣ! https://t.me/darulhadis18

🎊 ሴቶች ለሴቶች የሙሀደራ ፕሮግራም የተለመደው ወርሃዊ የሙሀደራ ፕሮግራማችን በአላህ ፈቃድ፦ የመሰረቶች ሁሉ መሰረት የሆነውን ▪️አላህን ስለማወቅ እና ▪️አሁን ላይ ብዙዎቻችን ዝንጉ የሆንበትና ሴት እህቶቻችን ለጉዳት የተዳረጉበት የሆነውን ጉዳይ የምንመካከርበት መድረክ ይሆናል። ☑️ተባብረን የተሻለ ማንነት በመፍጠር ትውልዱን እንታደገው። 🗓 እሁድ ጥር 29፣2014 ⏱ከጠዋቱ 3:00-6:30 ቀጠሮአችን በዳሩል ሀዲስ ይሁን። ⚠️(የቦታ ለውጡን አስተውሉ) 🕌 አድራሻ፦ 18 ማዞሪያ አካባቢ ከቀድሞ አልአፊያ ት/ቤት አጠገብ 👆መልእክቱን ለእህቶች በማድረስ የበኩላችንን ሀላፊነት እንወጣ! https://t.me/darulhadis18

★ታላቅ የሙሐደራ መርሓ ግብር★ 🎙ሸይኽ ኢልያስ አሕመድ ☞"የአምልኮ መከታ እውነታና ብዥታ" ⇨እሁድ ጥር 29/2014 ከጠዋት 3:30 ጀምሮ ⇨አብነት በሚገኘው ዑመር ኢብኑል ኸጥ'ጣብ መስጂድ (26 መስጂድ)

🌼ሴቶች ለሴቶች ወርሃዊ የሙሃደራ ፕሮግራም🌼 ኑ! ስለራሳችንና ስለልጆቻችን በጋራ በመመካከር የተሻለ ማንነት እንፍጠር! በአላህ ፈቃድ ▪️ሙራቀበቱላህ እና ▪️መልካም የልጆች አስተዳደግ(ክፍል 2) የተመለከቱ ወሳኝ ርዕሶች የሚዳሰሱበት ድንቅ ፕሮግራም አዘጋጅተን የእናንተን ውድ እህቶቻችንን መምጣት በናፍቆት እየጠበቅን ነው! 🗓 ቅዳሜ ጥር 14፣2014 ⏱ከጠዋቱ 3:00-6:30 🕌 አድራሻ ኢማሙ አህመድ መስጂድ (አለም ባንክ) መልእክቱን ሼር እናድርገው። @darulhadis18

Coming Soon... #_ነሲሓ_ቲቪ_1000

🎊 ሴቶች ለሴቶች የሙሀደራ ፕሮግራምሙራቀበቱላህ! የአላህ ፍራቻ "ተቅዋ" ን ለመላበስ እና ኢማንን ለማበልፀግ ከሚያግዙ ነገሮች አንዱ ሲሆን እሱም አላህ እንደሚቆጣጠረንና የምንሰራውን ስራ ሁሉ እንደሚመለከት ማሰብ ነው። በዚህና በሌሎች ርእሶች ዙሪያ ለመተዋወስና በአላህ ፈቃድ የተሻለ ማንነት ለመፍጠር 🗓 እሁድ ጥር 1፣2014 ⏱ከጠዋቱ 3:00-6:30 ቀጠሮአችን በዳሩል ሀዲስ ይሁን። 🕌 አድራሻ፦ አባጂፋር መስጂድ አጠገብ የቀድሞ መርየም መድረሳ። 👆መልእክቱን ለእህቶች በማድረስ የበኩላችንን ሀላፊነት እንወጣ! https://t.me/darulhadis18