ATTITUDE [ጉልላት አበበ]
Open in Telegram
ትረካ ልቦለድ እና የግጥም ስራዎችን ለማግኘት ተቀላቀሉ join our channel and share ለአስተያየት @EthealBot ይጠቀሙ ለመደወል @Gulilatab +251930756700
Show moreThe country is not specifiedThe category is not specified
3 185
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
3 185
♥የፍቅር ጥግ♥
[ጉልላት አበበ]
ክፍል 9
ወንዶች ዶርም
........
"ተከታትለን እንሹፋቸው እንዴ?"
"አሳይመንቱስ?"
"ናሆሜ ሲመለስ ሰራ ሰራ ያደርገዋላ!"
"ሲያምርህ ይቅር እሺ እሱ ዛሬ ምንም አይሰራም! እኛ ነን የእሱን የምንፅፍለት" አለ ቃል የናሆሜ ሎከር እየከፈተ
" መፃፉንስ ትፅፋለህ፡ ግን መልሱ ከየት ታመጣለህ?"
"እሱም አለ ለካ..."
"ምን እያደረክ ነው ? ሎከሩን ለምንድነው የምትከፍተው?" ናሆሜ
"እኔ ከሆነ ልብስ አልቀይርም"
አስገድደው ልብስ አስቀየሩት አስገድደው ፀጉሩን አስታጠቡት አስገድደው ዶድራንት ነሰነሱበት
የቀጠሮው ሰአት ደረሰ
ይህንን ቦታ ተማሪዎች "ላቭ ሴንተር " ይሉታል ፡ ምናልባት ፍቅረኛሞች የሚገናኙበት ቦታ ስለሆነ ይሆናል
የግቢው ምርጥ ምርጥ ጥንዶች ልክ ከምሽቱ 1 ሰአት ሲሆን ይሽሸጉበታል
የግቢው ሰላም ፎረሞች ( የፍቅር ጠላቶች ይሏቸዋል ጥንዶቹ ) መጥተው እስኪበትኗቸው ፍቅራቸውን ይለዋወጣሉ
ካገኟቸው የሚያበሩባቸው ባህሪ ባውዛ አይጣል ነው
ይህ ቦታ ቀን ቀን የሁሉም ተማሪ ቢሆንም ማታ ማታ ለፍቅረኛሞች ብቻ የተሰጠ ነው
ያወራሉ ፡ ከመተቃቀፍ የዘለለ ይተሻሻሉ ፡ ይሳሳማሉ
ናሆሜ በቀን እዚህ ቦታ የቀጠራት ሌላ የተሻለ ቦታ ያለ ስላልመሰለው ነው
"በሌላ ታስበው ይሆን እንዴ ?" እየጠበቃት ያስባል
"አይ ትክክል ነኝ! እና ላይብረሪ ልቀጥራት ነበር?" በምናቡ ብቻውን ያወራል
(ፍርሀቱ ይሆን?)
ናሆሜ በቀጠሮው ሰአት ቀድሞ ተገኘ
(ይህ የሁልጊዜ ተግባሩ ነው! ለሰአት ከሰው እኩል ክብር ይሰጣል
ጊዜ ጌታ ነው ይላል ደጋግሞ)
ናርዲ ብዙም ሳትቆይ ናሆሜ ባልጠበቀው አቅጣጫ በጀርባው በኩል ከተፍ አለች
"ሰላም ሰላም" (ፈገግታ)
"በስመአብ! " አስደነገጥሺኝ እኮ
"እናቴ ትሙት ! ይቅርታ "
(እናቴ ትሙት የምትለው ከልቧ ስታዝን ነው ! ቃሏ ከእውነቷ በላይ ሲሆን ፡ ማስረዳት ሲያቅታት ፡ ልቧ ሲከፈት ብቻ እናቴ ትሙት ትላለች)
ናሆሜ ተነስቶ አቀፋት
"እውነት በጣም አምሮብሻል " አይኖቿን እያየ
" ታንክዩ" አለቺው ለጥንዶች በተሰራው ወንበር እየተቀመጠች
" 'ገለቶማ ' ብትዪኝ የበለጠ ደስ ይለኝ ነበር እውነትም የናዝሬት አዳማ ልጅ ነሽ " (ተሳሳቁ)
" አየሽ ናርዲ እኛ ከቤታችን ውጪ ነው እየኖርን ያለነው : ባይገርምሽ እየኖርን ያለነውን እንኳን በቅጡ አናውቀውም :
የእውነት እንደዚህ በራስሽ ልብስ ተውበሽ ሳይሽ ደስ ነው ያለኝ ፡
በሌላ አታስቢውና ለአንቺ ያለኝ ክብር ነው የጨመረው፡
( በለቧ "እናቴ ትሙት! አላስበውም" አለች ) አስበሺዋል እኛ ኢትዮጲያዊያን በመምሰል እና በመሆን መሀል ውስጥ እኮ ነን ፡፡ እስኪ በእጃችን ያለው የትኛው ነው? የእኛ ወይስ የነሱ?
የእኛን ጭራሽ አናውቀውም ወይም በጭራሽ አንወደውም ፡ የእነሱን ለመምሰል (መሆን አንችልም ታውቂያለሽ ምክንያቱም እነሱ ሊሆኑ የሚችሉት እነሱ ብቻ ናቸው) እና የእኛ ለመምሰል መላላጥ ምንድነው ትርጉሙ? "
(ናሆሜ ለውይይት ያለው ፍቅር ከምንም በላይ ነው፡ በተለይ ስለ ሀገር ጉዳይ ከሆነ ፡
አሁን እራሱ በስሜት ውስጥ ሆኖ ነው የሚያወራው ፡ ስለ ሀገሩ ማውራት ስለትውልዱ ማሰብ የሁልጊዜ ስራው ነው)
ናርዲ የናሆም ከልብ የመነጨ የአድናቆት ስሜት መላ አካላቷን ሲወራት ይታወቃታል ፡
መደነቋ አስደስቷታል፡
ናሆሜ አለች አይኖቹን እያየች
" ናሆሜ እኔ እንደማስበው ብዙ ችግሮች ያሉብን ይመስለኛል በተለይ ይቅርታ አድርግልኝና የዚህ ዘመን ትውልድ ይህቺን ሀገር አንመጥነውም !
እሱ ብቻ አይደለም ለክፍለዘመኑም ብቁ አይደለንም " አለች
( ግን እኮ እሱም የዚህ ትውልድ አንድ አካል ነው ፡፡ ቅር ይለው ይሆን? ካንተ ውጪ ልበለው እንዴ?)
" ለምን እንደዛ አልሽ?" ጠየቃት
"አየህ ችግሮቻችን ሁሉ የመነጩት ከምንም ሳይሆን ከአይምሮአችን ማነስ ፡ ከአስተሳሰባችንን መድቀቅ የመነጨ ነው፡፡
እስኪ አስበው ወንዶች ሴቶችን የሚያደንቁት ተገላልጠው ሲያገኟቸው ነው፡ ሴቶች ወንዶችን የሚወዷቸው በወሬያቸው መሀል እንግሊዘኛ ሲጨምሩ ነው!
ጭራሽ እኮ ሌሎቹ ገጠሬ ፡ ፋራ ነው ስማቸው!
እሱን ተወው አንዷ የትግራይ ልጅ የትግራይ ባህላዊ ልብስ ለብሳ ወክ ብታደርግ ምን እንደምትባል ታውቃለህ? ስሟ ብሄርተኛ ነው!!
በጣም የሚያስቀኝ ምን እንደሆነ ታውቃለህ?
ጭራሽ ባህላዊ ልብስ ስትለብስ እዛው ተወልደው ያደጉት ልጆች ልክ እንደ ውጪ ሰው ካንተ ጋር ፎቶ ልነሳ የሚሉት ነገር "
ናሆሜ ሳቀ ፡ እረጅም ሳቅ
ሳቁ ግን የቁጭት ነበር፡ ከልቡ እንዳልሆነ፡ ምን ማለት እንዳለበት አላወቀም
" እኔ ምን እንደማስብ ታውቂያለሽ? የሆነ ነገር ተፈጥሮ ከአሜሪካ ወይም ከአንዱ የአውሮፓ ሀገር ባህላችንን፡ አለባበሳችንን ፡ አመጋገብ ስርአታችንን ብንቀያየር፡ ማለቴ የእኛ የእነሱ ሆኖ የእነሱ የእኛ ቢሆን ምን ይፈጠራል ብለሽ ታስቢያለሽ? "
"በእርግጠኝነት አሁንም እኛ የእነሱን እንኮርጅ ነበር "
(ለረጅም ሰአት ተሳሳቁ)
የዘቀጠ ትውልድ!!
"ለማንኛውም ደስ ብሎኛል : ገና እንደመጣሽ በቁምነገር አዛግኩሽ ይቅርታ"
"እናቴ ትሙት ችግር የለውም" (ከልቧ ነው)
"እኔ ለውይይት እና ለክርክር ልዩ ቦታ አለኝ ፡ በጣም ነው የምወደው፡ ባይገርምሽ አንድ ቀን.." ዝም አለ
ናርዲ እጁን ስትይዘው ነበር ያቆመው
"እ ቀጥላ የምን ጀምሮ መቆም ነው"
"እሺ ልንገርሽ ፡ ክላስ ውስጥ እየተማርን ነበረ ፡ እና ከኛ ክላስ ጀርባ በኩል ተማረዎች ገራሚ ክርክር ይዘው ነበረ ፡
የተቀመጥኩት ከኃላ ነበርና ሙሉ ለሙሉ እያዳመጥኳቸው ነበር: እና ከትምህርቱ በላይ ንግግራቸው ሳበኝ "
"ለመሆኑ በምን ነበር የሚከራከሩት?"
"እሱ ነው ቀልቤን የሳበው ፡ እኔ የምፈልገው ርዕስ ነበረ ፡ምን መሰለሽ ክርክራቸው ' የሰው ልጅ በተፅዕኖ ውስጥ ነው ! ምንም ቢያደርግ ልክ ነው ምክንያቱም ድርጊቱ የእሱ ብቻ ሳይሆን የተፅዕኖው ነው የሚል ነበረ"
" ዋው ገራሚ ርዕስ ነው!"
"በጣም! እና ምን ባደርግ አሪፍ ነው ጭራሽ ክላስ ውስጥ እንዳለው እረስቼው ድምፄን ከፍ አድርጌልሽ "ኖ እንደዛ መደምደም አንችልም ተፅዕኖ የሰውን ልጅ ከቨር ሊያደርገው አይችልም!" አላልኩም?
(ሳቅ )
"ወይኔ!( እጇን በአፏ ጭና)
መምህሩ ምን አለህ? በጌታ"
"ምንም አላለኝም አስፈቅጄው ወጣሁ"
"እንደዚህ መወያየት የምትፈልግ ነገር ከሆነ አንድ ጎበዝ ጓደኛ አለቺኝ፡ ታውቃታለህ መሰለኝ ..እ. ህይወት ትባላለች"
አያት
አየቺው
.
.
.
.
ይቀጥላል
Share
share
https://telegram.me/gullea
3 185
♥ኦሪዮን♥
ክፍል ፬ (4)
ከዚህ በፊት ይተዋወቁ ነበር?
ከማን?
ከኦሪዮን
(ፍቅር ሀሳቧ ክላስ ውስጥ የለም)
ከዚህ በፊት ቢተዋወቁ እንኳን ትነግረኝ ነበር ቢያንስ ስልኩ ይኖራት ነበር ፡ ቢያንስ ይደዋወሉ ነበር
ቢተዋወቁስ እኔ ከተዋወቅነው ገጠመኝ ይበልጣል? (ፈገግ)
ፍቅር በሀሳብ ወደ ኃላ ነጎደች
ይህ ታሪኳ ደስም ይላታል ይቆጫታልም
(ሁለት ስሜት ማስተናገድ ይቻላል?)
" የስምንተኛ ክፍል ሚንስትሪ ውጤታቸውን መቀበል ምክንያት አድርገው ያዘጋጁት ፕሮግራም ላይ መምህራንን ጋብዘዋል ፡ ሁሉም የስምንተኛ ክፍል መምህራን ሲሆኑ በፕሮግራሙ አዘጋጆች አንድ መምህር ከሀይስኩል መርጠው መጋበዝ እንዳለባቸው ወስነው ነበር
ፍቅር ይሄንን አታውቅም ነበር
የፍቅር ውጤት የግቢው ሁለተኛ (ከዮናታን ቀጥሎ) እና ከሴቶች አንደኛ ነበርና ከመምህራኑ ፊት ለፊት ሁለቱ የውጤት ሰቃዮች ተቀምጠዋል
አሁን የቀረው ተጋባዡ መምህር ብቻ ነው ;-ኦሪዮን
ከጥቂት መጠበቅ በኃላ ልክ ኦሪዮን እንደመጣ ፕሮግራሙ ተካሄደ ፡ (ወደፊት አልቀደመም ወደኃላ አልዘገየም)
ኦሪዮን ንግግር እንዲያደርግ በፕሮግራሙ አዘጋጆች ቢለመንም አሻፈረኝ አለ
(ጥሩ ስሜት ላይ አይደለሁም ) ነበረ መልሱ
(ይህ ግን ለፍቅር እና ጓደኞቿ ንቀት ነበረ)
ኦሪዮን ለተማሪዎቹ የተዘጋጀውኝ ሽልማት በፕሮግራም አስተናባሪው ጥሪ ከተደረገለት በኃላ ሰጠ
(ተማሪዎቹ ንግግር ባለመድረጉ ተከፍተዋል በተለይ ፍቅር)
ፍቅር ሽልማቷን ከኦሪዮን እጅ ስትቀበል ፈገግ እንኳን አላለችም
ኦሪዮን ጫጫታ አይወድም ፡ ለፕሮግራሙ አዘጋጆች ክብር ብቻ ብሎ ነበር የተገኘው
ለመቅረት ወስኖም ነበረ
እንደምንም መጥቶ እሱ የሚመለከተውን ካደረገ በኃላ ከፕሮግራሙ ወጥቶ ትምህርት ቤቱን ለብቻው መቃኘት ጀመረ
እጆቹን እራሱ ላይ ያደርጋል ፡ በእግሩ መሬት ይደበድባል፡ ወደ ሰማይ አንጋጦ ይመለከታል
(ፍቅር በአይኗ ትከታተለው ነበረ )
"ምን ሆነሻል?" አጠገቧ የነበረው ተማሪ
"ማን ነኝ ብሎ ነው የሚያስበው? አየኸው ሲጠበርር?"
" አንቺ ምን አገባሽ?"
ፍቅር ተነስታ ተከተለችው
ከጫጫታው እርቆ ነበር (ብቻውን መሆን ፈልጓል)
ተከተለቺው
"ጎበዟ ተማሪ ! እንዴት ነሽ?" ኦሪዮን በፈገግታ ተቀበላት
"ምን ያደርጋል? በአንተ እጅ ሽልማቱን መውሰዴ ቀኔን አበላሸው!"
(ፍቅር ለስድብ ታጥቃ ነው የመጣቺው)
"ምነው ምን አጠፋው?" ኦሪዮን ግራ በተጋባ መንፈስ
"ጉረኛ ነህ በጣም! ላንተ ነው እንዴ ተማሪዎች እንደዚህ ያካበዱት? ኦሪዮን ኦሪዮን የሚሉት አንተን ነው? ቀላል ነህ እሺ! አንተም ብሎ መምህር!"
"ነይ እስኪ ቁጭ በይ" ኦሪዮን አጠገቡ ባለው አግዳሚ ወንበር ተቀመጠ
"ካንተ ጋር ለሰከንድ እንኳን አልቀመጥም እሺ! እያየሁህ እኮ ነው ከመጀመሪያ ጀምሮ ..በመጀመሪያ አረፈድክ ከዛ መጥተህ እንኳን ንግግር አድርግልን ብለው ሲለምኑህ ተጠባረርክ ይህም ሳያንስህ ጭራሽ ፕሮግራማችንን አቋርጠህ እዚህ ትንዘላዘላለህ"
ኦሪዮን ሳቀ " ሳላውቀው አግብቻለሁ እንዴ? አንቺ ለምንድነው ከመጀመሪያው ጀምረሽ የተከታተልሺኝ?" አላት
"ሰው መስለኸኝ !" ፍቅር ፊቷ ቀይ ሆኗል
"እሺ ! ቁጭ በይ ካጠፋሁም ይቅርታ እጠይቃለሁ"
ኦሪዮን ሊያረጋጋት ሞከረ
"ነገርኩህ እኮ ከገባህ! ባዶ ነህ" የበለጠ እየቀረበቺው ጮኸችበት
ኦሪዮን ከተቀመጠበት ተነሳ " አይገርምሽም ጮህሺብኝ እንጂ እስካሁን አልተናገርሺኝም! ምን እንደሆንኩ እንኳን አልጠየቅሺኝም"
ፍቅር ጥላው ሄደች
ኦሪዮን በተፈጠረው ነገር ተናደደ "ዛሬ ምን አይነት ቀን ነው?"
ስልኩን አውጥቶ ፕሮግራም አስተናባሪው ጋር ደወለ
"እባክህ ፕሮግራሙ ከማለቁ በፊት ለ 3 ደቂቃ ንግግር አደርጋለሁ "
ስልኩን ዘጋው
ለፕሮግራሙ ተሳታፊዎች ቡና እና ዳቦ እየታደለ ነበር፡ የፕሮግራሙ መሪ ወደ መድረክ ወጥቶ
"በመጨረሻም ሰርፕራይዝ አለ ! እስኪ እንደማመጥ"
አንፃራዊ ፀጥታ ሰፈነ
"ሁለት ፕሮግራም ቀርተውናል በመጀመሪያ በተማሪ ዮናታን ምርጥ ግጥም ይቀርባል ፡ከዛ ቀጥሎ ተወዳጁ መምህራችን ወደ መድረክ ወጥተው የሚነግሩን ነገር ይኖራል " (ሞቅ ያለ ጭብጨባ)
ፍቅር ጀብደኝነት ተሰማት
"የታባቱ ሰራሁለት! ይንጠባረራል እንዴ?!" ለብቻዋ ፈገገች
ኦሪዮን ግጥሙ እንዳበቃ ወደ ነበረበት ወንበር ተመለስ
ፍቅር ወደ እሱ እያየች ለመሽኮርመም ያደረገችው ጥረት አንዴም አልተሳካም ፡ፍፅሞ ወደ እሷ አልተመለከተም
ኦሪዮን ወደ መድረኩ ተጠራ
" ምናልባት አሁን ላይ ይህንን መናገር አልነበረብኝም ግን በቃ ይቅርታ አድርጉልኝ : እናንተ ገና ወጣቶች ናችሁ ይህ በጣም ደስ ይላል ያላችሁ ተነሳሽነት ፓወር አቅም ይህ ሁሉ ተስፋ ነው! የሚሆን ..የሚሳካ ተስፋ..ግን አለ አይደል አንዳንዴ
ይህ የእናንተ ብቻ ችግር አይደለም ፡ ማለቴ የሰው ልጆች ሁሉ ችግር ነው ፡ እኛ ሁሌም የምናየው ህልማችንን ብቻ ነው ! ማለቴ ጥናቃቄ ይጎለናል
እስኪ አስቡት አንድ ህልም ያለው ተማሪ ህልሙን እያሰበ ብቻ አስፓልት ላይ ቢጓዝ ከዛ መኪና መጥቶ...(አልጨረሰውም)
ስሜቴ ጥሩ አይደለም ፡ ንግግር ያላደረኩት በዚህ ምክንያት ነው ፡ እኔ ወደዚህ ስመጣ ያስተማርኩትን ልጅ በአይኔ እያየሁ በመኪና አደጋ አጣሁት
አልናገርም ብዬ ነበረ ግን አንድም የትም መቼም ቢሆን ጥንቃቄ እንዳይለያችሁ ለማሳሰብ ሲሆን
ሁለት ደግሞ (ወደ ፍቅር እየተመለከተ ) አለመናገሬን በስህተት እንዳትረዱት"
ከመድረኩ ወረዶ ከግቢው ለመውጣት ጉዞ ጀመረ
ፍቅር አንገቷን ደፋች ፡ ፕሮግራሙ በሀዘን ድባብ ተፈፀመ
"አለመናገሩ ልክ ነበረ ፡ ይህ ሁሉ መዐት ይዞ ምጣቱ እንኳን ክብር ያለው ሰው ነው" ፍቅር ለብቻዋ ታወራለች
"ኦሪዮን.. ኦሪዮን .." እየተከተለቺው
ሰምቶ እንዳልሰማ ዝም ብሏት መንገዱን ቀጠለ
.
.
.
.
.
.
.
.
https://telegram.me/gullea
like
Comment
share
አድርጉ
3 185
ኦሪዮንን እና የፍቅር ጥግ የምትከታተሉት ልጆች ብዛታችሁን ማወቅ እፈልጋለሁ
የፍቅር ጥግ የምትከታተሉ 🙏 ተጫኑ
ኦሪዮንን የምትከታተሉ👍
ሁለቱም የምትከታተሉ❤️
3 185
♥የፍቅር ጥግ♥
[ጉልላት አበበ]
ክፍል 8
...ለምሳሌ እነ ቲጂ እነ መክሊት ሆን ብለው ወንድ የሚያጠምዱት ሳያውቁ ነው??
አንድ ሰው ሰውን የሚገድለው ሰው መግደል ሀፂያት መሆኑን ሳያውቅ ነው??
ናርዲ ያስረዳልኛል ያለችውን ምሳሌ በሙሉ ዘረዘረች
ህይወት እያዳመጠቻት ነበር
"አዎ ሳያውቁ ነው!! " ህይወት ተመቻችታ ተቀመጠች
" ምን መሰለሽ ናርዳዬ ሶቅራጠስ ማለት የፈለገው እውቀት እና አንቺ የምትዪው እውቀት በመጀመሪያ...."የናርዲ ስልክ አቋረጣት
"ቀጥዪ በኃላ አነሳዋለሁ " አለች ናርዲ
" እሺ ልቀጥል እውቀት ለሶቅራጦስ ሁለት ትርጉም አለው በእነዚህ ትርጉሞች አንፃር ነገሮችን ስታዪ ምን ያክል እውነት እንደሆነ...." የናርዲ ስልክ በድጋሚ ጠራ
ናርዲ እየተነጫነጨች ወደ ተሰካው ስልኳ አመራች
"ኦ ማይ ጋድ!! ናሆሜ ነው" አለች
ህይወት ከናርዲ በላይ ደነገጠች
"አንሺው ህይወት ካለች የለችም በዪው" አለቻት
እሺ ብላ አነሳቺው
"ሄለው"
"ናርዲ የናዝሬቷ" አላት ድምፅ እንደሰማ
"ናሆሜ የአዲስ አበባው" አለች ፈገግ እያለች
ምንም እንኳን ጥሩ ጓደኝነት ቢኖራቸውም ፡ ምንም እንኳን እሷ በልቧ ደብቃ ብታፈቅረውም ፡ ምንም እንኳን መክሊትና ቲጂ ፕሮጀክታቸው አድርገውት ቢያቅታቸው ፡ ምንም እንኳ ሂዊ እንደ ማንኛውም ወንድ ብትንቀው ናሆሜ ለናርዲ የገነት ቅብ ሲኦል ነው
ከላይ ሲያዩት የሚግባባ ፡ ቀላል ፡ የሚሸነፍ ቢመስልም ግን እሱ ሩቅ ነው የማይደረስበት
ናሆሜን ትወደዋለች ግን ደግሞ በተስፋ መቁረጥ ውስጥ ሆና
"ናርዲ ምነው መደወል አልነበረብኝም እንዴ? ዝም አልሽ" ደነገጠች
"አይ ! እንገናኝ እንዴ ማለቴ አንድ ግቢ ሆነን ካርድ እንዳይቆጥርብህ..ማለቴ መደወልህን ጠልቼ አይደለም .."
ሂዊ ሳቀች (የሂዊ ሳቅ በስልኩ ጆሮዎች ናሆሜ ጋር ደረሰ)
ናርዲ የምታወራው ጠፋባት
እሱ ደውሎ እሷ ላግኝህ ማለቷ ቆጫት (ምናለ ትንሽ ብጠብቅ ?ሊያገኘኝ አይደል እንዴ የደወለው?!)
ናሆም በህይወት ሳቅ ተናዷል
"እሺ ናርዲዬ እኔም ትንሽ ደብሮኛል ፡ ባገኝሽ ደስ ይለኛል"
"እናቴ ትሙት አይደብርህም!"
"እሺ (ሳቀ) ..ከስንት ደቂቃ በኃላ ልምጣ)
"አሁን ! ማለቴ ከ30 ደቂቃ በኃላ"
ናሆሜ ስልኩን ዘጋው
"እንዴ? ምን ሆነሻል አንቺ ! ምን ብሎሽ ነው እንደዚህ?" ሂዊ ጠየቀቻት
ናርዲ ሳትመልስላት ፍራሿ ላይ ተወረወረች፡ ሁለት እጆቿን ዘርግታ በፀጥታ ለሰከንዶች ቆየች
ወንዶች
ተሰብስበው የናሆሜን ስልክ ሲያዳምጡ የነበሩት ጓደኞቹ ልክ ስልኩን እንደዘጋው ዳዊት
" እሺ ናርዲዬ አለ እኮ" (ሁላቸውም ሳቁ)
"ትንሽ ደብሮኛል ..ባገኝሽ ደስ ይለኛል" ቃል እየሳቀ ይናገራል እየተናገረ ይስቃል
ናሆሜ እንደ ማፈር ብሎ ፍራሹ ላይ ተኛ
"ቆይ ምን ያንቀጠቅጥሀል? ከምኔው ከምኔው!" ልኡሌ
ኸረ ዘፈኑን እንበለው
ተሰባስበው " ከምኔው ከምኔው ነውሳ
ልበ ቢስ የሆንኩት በናርዲ የተነሳ
( እያ ጭብጨቡ)
ከምኔው ከምኔው ከምኔው ነው ደግሞ
እንዳልተው ያረገኝ በናርዲ አዳክሞ
(ናሆሜም ተነስቶ ከነሱ ተቀላቀለ)
ምኔው ለምጄ ለምጄ
አረፍኩ ወድጄ
(ሁላቸዌም አንድ ላይ ተሳሳቁ)
ሴቶች ዶርም
"ይህንን ልትለብሺ ባልሆነ? " አለቻት ህይወት በናርዲ አለባበስ ደንግጣ
" አዎ ! ምነው? ማንነቴ እኮ ነው" መለሰችላት
ናርዲ የኦሮሚያ ባህላዊ ልብስ ነበር የለበሰችው
"ልክነሽ ግን ዛሬ የብሔርብሔረሰቦች ቀን ነው እንዴ?"
"አትሳሳች ጓደኛዬ ማንነታችን ውበታችን ነው! በእርግጥ አንቺ ይህንን አትወጂም!"
"ኖ ናርዲዬ እኔ ችግሬ ከልብሱ ጋር እኮ አይደለም ፡ ታውቂያለሽ የኦሮሞ የትግሬ የአማራ የጉራጌ ልብስ ብለን መከፋፈል ልዩነታችንን የበለጠ ያጎላዋል! የኦሮሞ ልብስ መልበስ እኮ እኔ ኦሮሞ ነኝ ማለት አይመስልሽም?!"
"በእርግጥ በእሱ በኩል ከታሰበ አዎ ! ግን እንደዛ ማሰቡ በራሱ ዘረኝነት ነው!
አስበሺዋል አንቺ የመቀሌ ልጅ ሆነሽ ስለ ናዝሬት ስለ ኦሮሚያ ባህል፡ ቅርስ፡ አለባበስ ቁንጅና እኔ ካላሳየሁሽ አንቺ በእኔ ልብስ ካላጌጥሽ እኔ በአንቺ ልብስ ካላጌጥኩ ምኑ ላይ ነው ፍቅራችን?"
ሂዊ ተነስታ የናርዲን ባህላዊ ልብስ አስተካክላ ጉንጯን ሳመቻት
" አምሮብሻል ናርዲዬ! ይቅናሽ እሺ"
ተቃቀፉ
"በቃ ልሂድ ሰአት ደርሷል" አለቻት
ወንዶች ዶርም
"አንተ ተነስተህ አትዘገጃጅም?" ኘለው ቃል በእግሩ እየነካካው
"ምንድነው ምዘገጃጀው ፈተና የምገባ መሰለህ እንዴ?"
(ሁላቸውም ሳቁ)
ልኡሌ እየሳቀ " ከሰላሳ ደቂቃ በኃላ ያለችህ ለምን ይመስልሀል?"
ማንንም ሳይጠብቅ እራሱ ቀጠለ
"አስር ደቂቃው ለልፒስቲክ አስር ደቂቃው ለዶድራንት.."
"ግን ምን የምትለብስ ይመስላቹሀል?" ዴቭ
ተከታትለን እንሹፋቸው እንዴ?
"አሳይመንቱስ?"
"ናሆሜ ሲመለስ ሰራ ሰራ ያደርገዋላ!"
"ሲያምርህ ይቅር እሺ እሱ ዛሬ ምንም አይሰራም! እኛ ነን የእሱን የምንፅፍለት" አለ ቃል የናሆሜ ሎከር እየከፈተ
" መፃፉንስ ትፅፋለህ፡ ግን መልሱ ከየት ታመጣለህ?"
"እሱም አለ ለካ..."
"ምን እያደረክ ነው ? ሎከሩን ለምንድነው የምትከፍተው?" ናሆሜ
"እኔ ከሆነ ልብስ አልቀይርም"
አስገድደው ልብስ አስቀየሩት አስገድደው ፀጉሩን አስታጠቡት አስገድደው ዶድራንት ነሰነሱበት
የቀጠሮው ሰአት ደረሰ
.
.
.
.
ይቀጥላል
ሼር አድርጉ
3 185
♥የፍቅር ጥግ♥
ክፍል 7
[ጉልላት አበበ ]
ባንድ ካፌ እና ሬስቶራንት
ሶስቱም ያዘዙትን ጁስ በእስትሮው ይመጣሉ
" እኔ ግን የነዚህ ልጆች ነገር አሳስቦኛል! ወደው አይደለም ከዶርም የማይወጡት ! ወደው አይደለም ወንድ የማይፈልጉት" አለች ሰላም እንደተጨነቀች ያስታውቅባታል
"እና ምንድነው ልትዪ ነው?" መክሊት ጠየቀች
"ማለቴ ለምን አብረው ይተኛሉ? አንድ አልጋ ላይ?"
"አንቺ ምንድነው የምታወሪው?" መክሊት ተናዳለች
ግን እኮ..ቲጂ ጣልቃ ገባች
"አስባችሁታል የናርዲን ረጅም አንገት ላይ መተኛት..የሂዊን ዳሌ..." መክሊት አቋረጠቻት
"ወሬ የማትቀይሩ ነገር ከሆነ እሄዳለሁ" አለች
" እሺ በቃ የራሳቸው ጉዳይ ተዋቸው"
ሶስቱም አፋቸውን ወደ እስትሮው አስጠጉ
የሴቶች ዶርም
ሂዊ ቀይ ሹራብ እና ጥቁር ቱታ አድርግ በልቧ ተኝታለች
"ትንሽ ተኝቼ እናውራ" አለች
"ማሪያምን አይሆንም! ከተኛሽ ደብሮሽ ታስደብሪኛለሽ..በዚህ ቀን ድብርት.ተነሽ በናትሽ" ናርዲ ወደ ሂዊ እየተጠጋች
"ትንሽ ብቻ እኮ ነው ኽ ናርዲዬ" እየለመነቻት
"ልፍያ ነው የፈለግሺው አይደል?"
"አይደለም አይደለም.."
ናርዲ ወደ ሂዊ አልጋ ወጥታ ከኃላዋ ሆነች
እሺ እነሳለሁ በናትሽ..እንደተማረከ ወታደር ..እንደተሸነፈ እጇን ሰጠቻት
ሂዊ ተስተካክላ ተቀመጠች "እሺ ዛሬ በጣም ካስገረሙኝ ፍልስፍናዎች ስለ 2ቱ ነግሬሸ እንወያይባቸዋለን"
ናርዲ ለመስማት ተዘጋጀች
ወንዶች ዶርም
ዴቭ እና ልኡሌ ፊልም እያዩ ነበር፡ ቃል እና ናሆሜ ለብቻቸው ሀሳብ ውስጥ ገብተዋል
ናሆሜ ይህንን ነገር በቶሎ በድል መጨረስ ይፈልጋል ፡ ለዛም ነው ደጋግሞ የሚያስበው
"አንዳችን የምንደውልበት ሰአት ደርሷል" አለ ናሆሜ
ዴቭ እና ልኡሌ ፊልሙን አቆሙት
"እናንተ አሁን አትሆኑም ምክንያቱም የእናንተ ቺኮች በዚህ ሰአት ከተማ ናቸው"
ፊልም ማየታቸውን ቀጠሉ
"ስለዚህ አሁን ዶርም ውስጥ ናርዲ እና ጉረኛዋ ህይወት ብቻ ናቸው ያሉት ማለት ነው"
ሁላቸውም ወደ ቃል አፈጠጡ
ዴቭ እና ልኡል በጋራ "..ይደወል... ይደወል... ይደወል" እያሉ ጮሁ
ቃል ወደ ናሆሜ እያየ
ናርዲን አስበሀታል ናሆሜ ? አለ አይደል ከሌሎቹ በጣም ትለያለች፡ እርጋታዋ ፡ ለሰው ያላት ክብር ማለቴ እኔ የእነሱ ጓደኛ እንኳን አትመስለኝም እኮ
ብቻ እኔን ከናርዲ ስላደረግከኝ አመሰግናለሁ ፡ ደግሞ እኮ በጣም ቆንጆ ናት አይኖቿ ክብ ጠይም ፊቷ ረጃጅም ፀጉሮቿ
"ቃል!" ናሆሜ አቋረጠው
"ስምምነታችንን አትርሳ እንጂ"
"አልረሳውም እኮ ስለ ውበቷ መናገር ምን ችግር አለው ደግሞ ስትናገር ድምፅ አወጣጧ..."
"እርፍ! ደግሞ የዴቭን ስንል የዚህኛው ይባስ? ወዷታል በቃ! ሰው ቀይር ናሆሜ " አለ ልኡሌ
"ማነው የወደዳት? ሳላገኛት ነው እንዴ የምወዳት?"
ዴቭ ተነስቶ ልኡሌንና ናሆሜን ይዞ ወደ ጓዳ ገባ
" ኸረ ሚስጥር መሆኑ ነው?" ቃል ተናደደ
ዴቭ እጆቹን እያወዛወዘ መናገር ጀመረ
"ናሆሜ አንተ ከናርዲ ጋር ሁን ይሄ ልጅ እቅዳችንን እንዳያበላሸው! ተቀይረሀል ሲባል ምን እንደሚል አይተን በዛውም እንደሚወዳት እና እንደማይወዳት እናያለን፡ እሺ ልቀየር ካለ አይወዳትም አይ አይሆንም ካለ ግን...."
"ዛሬ ገና ተናገርክ : አቦ ይመችሽ!" ልዑሌ አቀፈው
ናሆሜ ወደ ውስጥ ገብቶ " እቅድ ቀይረናል ናርዲን የማገኛት እኔ ሆኛለሁ"
ቃል ሁሉም በአንድ ላይ ሲያፈጡበት አሁን እንዲያገኛት የተቀየረችለትን መክሊትን እያሰብ 'ይሁን' አለ::
ሴቶች ዶርም
ናርዲና ሂዊ ፍልስፍናዊ ክርክራቸው አጣጡፈውታል
ይኸውልሽ ናርዲ አለች ሂዊ ጣቶቿን እየነካካች ሶቅራጠስ ልክ ነው "ማንኛውም ሰው እያወቀ መጥፎ ነገር አያደርግም፡ የመጥፎ ነገር ምንጭ አለማወቅ ወይም ኢግኖራንስ ነው"
ናርዲ "እኔ በዚህ ሀሳብ አልስማማም ፡ ብዙ ሰው እኮ የሚሰራው ነገር ልክ እንዳልሆነ እያወቀ ነው ስህተት የሚሰራው::
ለምሳሌ እነ ቲጂ እነ መክሊት ሆን ብለው ወንድ የሚያጠምዱት ሳያውቁ ነው??
አንድ ሰው ሰውን የሚገድለው ሰው መግደል ሀፂያት መሆኑን ሳያውቅ ነው??
ናርዲ ያስረዳልኛል ያለችውን ምሳሌ በሙሉ ዘረዘረች
ህይወት እያዳመጠቻት ነበር
"አዎ ሳያውቁ ነው!! " ህይወት ተመቻችታ ተቀመጠች
" ምን መሰለሽ ናርዳዬ ሶቅራጠስ ማለት የፈለገው እውቀት እና አንቺ የምትዪው እውቀት በመጀመሪያ...."የናርዲ ስልክ አቋረጣት
"ቀጥዪ በኃላ አነሳዋለሁ " አለች ናርዲ
" እሺ ልቀጥል እውቀት ለሶቅራጦስ ሁለት ትርጉም አለው በእነዚህ ትርጉሞች አንፃር ነገሮችን ስታዪ ምን ያክል እውነት እንደሆነ...." የናርዲ ስልክ በድጋሚ ጠራ
ናርዲ እየተነጫነጨች ወደ ተሰካው ስልኳ አመራች
"ኦ ማይ ጋድ!! ናሆሜ ነው" አለች
ህይወት ከናርዲ በላይ ደነገጠች
"አንሺው ህይወት ካለች የለችም በዪው" አለቻት
እሺ ብላ አነሳቺው
"ሄለው"
.
.
.
.
.
ይቀጥላል
ሼር አድርጉ
https://telegram.me/gullea
3 185
♥የፍቅር ጥግ♥
ክፍል 6
ናሆሜ ሶስት ንፁህ ልሙጥ ወረቀት አዘጋጀ
ከምን እና እንዴት መጀመር እንዳለብን ነው የማሳያችሁ
ከቃል ቀይ እስክሪፕቶ ተቀብሎ እንዲህ ብሎ ፃፈ
ናሆም = መክሊት
ዴቭ = ሰላም
ልዑሌ = ቲጂ
ቃል = ናርዲ
እንዲህ ነው የምናደርገው
በዚህ ካልኩሌሽን በእርግጠኛነት ሁለት ነገር ነው የሚፈጠረው
አላማችን ህይወትን ማጥመድ ነው አይደል?
ሁላቸውም አንገታቸውን አንቀሳቀሱ
ህይወት ተፈላጊ ነኝ ብላ ታስባለች የእኛ ስራ ደግሞ ጓደኞቿ ከእሷ በላይ ተፈላጊ እንደሆኑ ማሳየት ነው
ስለዚህ ሁላችንም ተልዕኮውን በዚህ ህግ ብቻ ነው የምንፈፅመው
"እኔ ጥያቄ አለኝ " ዴቭ እጁን አወጣ ፡ ሁሉም ወደ እሱ ተመለከተ
"በዚህ ካልኩሌሽኝ መሰረት ከሆነ ህይወትን ማንም አይቀጥራትም ፡ እና ልጆቹን የምንቀጥራቸው ህይወት ያለችበት ቦታ ነው? ማለቴ ካላየችን እንዴት ልትቀና ትችላለች?"
ናሆሜ ዶርም ውስጥ መንቀሳቀስ ጀመረ " አያችሁ የእነሱ ግሩፕ ትልቁ ችግር ወረኛ መሆናቸው ነው፡ ብታምኑም ባታምኑም አሁን በዚህ ሰአት ህይወት ለጓደኞቿ ስለ እኔ እያወራችላቸው ነው፡ ላይብረሪ እኔን ፈልጎ መጣ ...ተዋወቀኝ..የወደደኝ ይመስላል..ምናምን ብላ ታወራለች::"
ቃል አቋረጠው
"ስለዚህ እኛ የቀጠርናቸው ልጆች የትም ብናገኛቸው ህይወት መስማቷ አይቀርም ማለት ነው፡"
"በትክክል ቃሌ...ወዲያው ነው እየጨማመሩ የሚነግሯት.. እሱ ብቻ ሳይሆን ሁላቸውም ኢጎ አለባቸው፡ እኛ ይሄንን እንደ አድቫንቴጅ መጠቀም ይኖርብናል" (ናሆሜ በስሜት ነበር የሚያወራው)
"ሌላው መርሳት የሌለብን ነገር ልጆቹን ስናገኛቸው ሁለት ነገር ማድረግ አለብን"
ምንድናቸው? ዴቭ ጠየቀ
"አንደኛ እነሱ ካላነሷት በስተቀረ የህይወትን ስም ፈፅሞ ፈፅሞ አለማንሳት፡፡ ሁለተኛውን እስኪ እናንተ ገምቱ እነሱ ያነሷት ከሆነ ምን ማድረግ ነው ያለብን?"
ዴቭ እጁን አንስቶ " ጤንነቷን መጠየቅ" (ሳቅ ሃሃሃሃ)
ልኡሌ በተራው " ምን ጥያቄ አለው ድብን አድርጎ መስደብ ነዋ "
ቃል ዝምታን መረጠ
ናሆሜ ከላይ ወደ ሚገኘው አልጋው እየወጣ "ማድረግ ያለብን ንግግራችን የጥላቻ እንደሆነ ሳናስታውቅ እንደማትመቸን መናገር ፡ እነሱ ቅመሙን ጨምረው ይነግሯታል ፡፡
ለሁላችንም መልካም ዕድል ሁሉም እየመጣ ውሎውን ሪፖርት ያደርጋል፡
የሴቶች ዶርም
ዘወትር ቅዳሜ እና እሁድ የሴቶቹ ዶርም ኮስሞቲክስ መሸጫ ይመስላል
በዚህ ቀን ዶርም መዋል ለመክሊት ቲጂ እና ሰላም የማይታሰብ ነው
ለዚህ ቦታ የሌላቸው ናርዲ እና ህይወት ብቻ ናቸው
ሁለቱ እነሱን የሚጠሯቸው (ሶስቱ ወንዶች ) እያሉ ነው፡፡
ህይወት ለራሷ የምትሰጠው ከፍተኛ ግምት አንድም የትምህርት ዕውቀቷ አንድም ብዙ መኳኳል የማይፈልገው ድንቅ ውበቷ እና ከመጠን ያለፈ አንባቢነቷ ነው (ይህንን እሷም ታምንበታለች)
"ወንድ ሁሌም ተሸናፊ ነው ፡ የማይሸነፈው አለም ብቻ ነው " ትላለች
ሶስቱ ወንዶች መኳኳላቸውን ጨርሰው ወደ ከተማ ሊወጡ ነው
"ዛሬ ፕሮግራማችን ምንድነው? " ናርዲ ከኩርፊያ ተመልሳ ህይወትን አናገረቻት
"እኔ ምንም የተለየ ፕሮግራም የለኝም፡ ለምን ወደ ካፌ ሄደን በሀሳብ አናወራም?"
ሶስቱ ወንዶች ተለባብሰው ወጡ ቲጂ ፡ መክሊት እና ሰላም
ናርዲ እና ህይወት ሁለት ቀን በፈጀ ክርክራቸው አንድ ነገር ላይ ደርሰዋል
"ሴት ልጅ ከተፈጥሮአዊ ውበቷ በዘለለ ለሰው ሰራሽ ነገር ዋጋ ከሰጠች ውብ ነኝ ብላ አታስብም ፡ ወንዶችን በማንነቷ መሳብ ያቅታታል!
የመሳብ የመፈለግ የመወደድ ታሪኳ አብቅቶ ፈላጊ ትሆናለች ፡፡
መፈለግ ደግሞ የወንድ ባሀሪ ነው ፡ ስለዚህ ቲጂ፡መክሊት እና ሰላም ወንዶች ናቸው፡፡ (ረጅም ሳቅ ሳቁ ሃሃሃሃሃሃሃሃ )
በየተራ ጉንጫቸውን ስመው ለዶርሙ ጥለዋቸው ተከታትለው ወጡ
"ብቻችንን ከሆንን አይቀር ለምን እዚሁ አናወራም?" የህይወት ሀሳብ ነበር
"ደስ ይለኛል ግን በመጀመሪያ ወንዶቹ ያበላሹትን ዶርም ማፅዳት ይጠበቅብናል" ተሳሳቁ
ናርዲ ህይወትን ትወዳታለች ፡ ሁሉ ነገሯ ይመቻታል ፡አሁን አሁን ግን ለወንዶች ያላት ንቀት ያበሳጫት ጀምሯል በተለይ ናሆሜን ስትናገርባት አትወድም
ናርዲ ህልሟ ዝነኛ ደራሲ መሆን ነው ለዛም ነው ከህይወት ጎን የማትለየው፡ ህይወት ታስነብባታለች ፡ታወያያታለች ፡ ብዙ ሀሳብ ትሰጣታለች
ዶርሙን ለማፅዳት አስር ደቂቃ አልፈጀባቸውም
" እሺ ስለምን እናውራ ? አለች ህይወት የለበሰችው ቱታ ከወትሮ በተለየ ወጣጥሯታል
ወደ መስተዋት ተጠግታ እራሷን አየችው.. ዳሌዋን በእጇ እየዳበሰች ፈገግ አለች"
"የምናወራውን አንቺ ምረጪ እንጂ ግን ከፍልስፍና ባይወጣ እመርጣለሁ" አለች ናርዲ የሂዊን ሁኔታ በስርቆት እየተመለከተች
ባንድ ካፌ እና ሬስቶራንት
ሶስቱም ያዘዙትን ጁስ በእስትሮው ይመጣሉ
" እኔ ግን የነዚህ ልጆች ነገር አሳስቦኛል! ወደው አይደለም ከዶርም የማይወጡት ! ወደው አይደለም ወንድ የማይፈልጉት" አለች ሰላም እንደተጨነቀች ያስታውቅባታል
"እና ምንድነው ልትዪ ነው?" መክሊት ጠየቀች
"ማለቴ ለምን አብረው ይተኛሉ? አንድ አልጋ ላይ?"
"አንቺ ምንድነው የምታወሪው?" መክሊት ተናዳለች
ግን እኮ..ቲጂ ጣልቃ ገባች
"አስባችሁታል የናርዲን ረጅም አንገት ላይ መተኛት..የሂዊን ዳሌ..." መክሊት አቋረጠቻት
"ወሬ የማትቀይሩ ነገር ከሆነ እሄዳለሁ" አለች
" እሺ በቃ የራሳቸው ጉዳይ ተዋቸው"
ሶስቱም አፋቸውን ወደ እስትሮው አስጠጉ
የሴቶች ዶርም
.
.
.
ይቀጥላል
3 185
እንዴት አደራችሁ
በባለፈው የፍቅር ጥግ ክፍል 5 ላይ ነበረ ያቆምነው ላላነበባችሁት አሁን እለቅላቹሀለው
ዛሬ ግን ክፍል 6 ይቀርባል
ወደ ማታ ደግሞ ኦሪዮን ክፍል 4
ይቀርባል
3 185
የፍቅር ጥግ የሚለውን ከአንድ መጀመሬ ሊያሰለቻችሁ ይችላል
ከዚህ በኃላ ግን አላቋርጥባችሁም !! ሁሉንም ታሪክ በየቀኑ አቀርብላቹሀለው!!
ኦሪዮን
የመጀመሪያው ቅዳሜ
ሌዲዋ ምዕራፍ ሁለት
አላደረኩትም ምዕራፍ ሁለት
በተከታታይ የሚቀርቡ ናቸው♥ ከእናንተ የሚጠበቀው ሼር ብቻ ነው!!
መልካም ምሽት♥
3 185
ባቂ በድብቅ ወንዱን እያየቺው
ናሆሜ ፈገግ ብሎ ወደ ውስጥ ገባ
በመጀመሪያው ማንበቢያ ክፍል ውስጥ ማንም የለም፡ ከላይ ወደ ታች መፅሀፍት ተደርድረዋል
"ተማሪው የት ሄደ? "
ወደ ሁለተኛው ክፍል አመራ ፡ ከአንድ ሴት በቀር ማንም የለም
ናሆሜ ሰአቱን ተመለከተ 7:45 በዚህ ሰአት እንዴት ተማሪ ያነባል? ሙቀቱ ሀያል ነው ተማሪውም አይፈረድበትም
ናሆሜ ወደ ብቸኛዋ ተማሪ ተመለከተ
ነጭ ቲሸርት ያደረገች አንድ ሴት ፊቷን ወደ ግድግዳው መልሳ ታነባለች፡ በእርግጠኝነት ህይወት ናት
ላይብረሪ ውስጥ ማንም አለመኖሩ ተመችቶታል፡ እንደፈለገ ማውራት ይችላል
ከተደረደሩት መፃህፍት በመጠኑ ቀለል ያለውን በማንሳት ወደ ተመለከታት ሴት አመራ
አጠገቧ ተቀመጠ አላየችውም፡ ሰላም አላት አልመለሰችለትም
"ኢንሳይክሎፒዲያ ለምንድነው የምታነቢው የሚመለከትሽን ነገር አታነቢም?"
ዝም
"ምነው አትመልሺልኝም?"
"ተናገርክ እንጂ እኮ አልጠየከኝም፡ ወይም ጥያቄ የመሰለህ ጥያቄ ስላልሆነ ነው ዝም ያልኩት"
"ጥያቄን ጥያቄ የሚያደርገው ምኑ ነው?"
"አየህ አሁን ገና ጠየቅክ..እ..እና ስመልስልህ እንደ እኔ ጥያቄን ጥያቄ የሚያደርገው ጥያቄ ምልክቱ ነው ..ክክክክ ረጅም ሳቅ.."
"እንዴ! ላይብረሪ ነን እኮ!"
"ለምን እንደሳቅኩ ታውቃለህ? " ተመለከተቺው
"እንዴ ናሆም! እዚህ ምን ትሰራለህ?" በድንጋጤ
"ታውቂኛለሽ እንዴ? አየሽ ታዋቂ ነኝ፡ እኔ እኮ አላውቅም እንደምታወቅ" ፈገግ አለ
"እየቀለድኩ አይደለም የሰው ላይብረሪ ምን ትሰራለህ?"
"እና የሰይጣን ላይብረሪ እንድገባ ነበር፡ ቆይ አንቺ ግማሽ ወሬ ካወራን በኃላ ለምን አየሺኝ፡ ሰው እንደመጣ ማንነቱን ማጣራት የለብሽም? ወይስ ከሌሎቹ ለመለየት ብለሽ?"
"አንተ ከሌሎቹ ለመለየት ብለህ ነዋ እዚህ የመጣሀው ወይስ እኔን ለማግኘት?"
አየቺው ፡ አላያትም
"ሁለቱም አይደለም ፡ ለፕሮጀክቴ የሚያግዘኝ ነገር ለመፈለግ ነው አመጣጤ! አንቺን ሳይሽ ግን ሀሳቤን ቀየርኩ፡ ጎበዝ ተማሪ እንደሆንሽ አውቃለሁ እና እኔ ገና የእናንተን አንብቤ ለመረዳት ሰአት ከምገድል አንቺ ብታስረጂኝ ሰአቴን እቀንሳለሁ"
"የቻልኩትን እሞክራለሁ፡ አሁን ግን እስቴዲየም መሄድ ይኖርብኛል"
"ካልደበረሽ አብረን መሄድ እንችላለን"
"አብረን መሄድ እንችላለን እዛ ግን ብቻዬን መሆን ነው የምፈልገው አድርሰኸኝ ከተመለስክ እሺ!"
"እውነትም ነገሩ ከባድ ነው" አለ ናሆም
ህይወት የደረሰችበትን የመፅሀፉን ገፅ በማስታወሻዋ ላይ ፃፈች
ወደ ናሆሜ ተመለከተች " ዶርም 24 ሰአት የሚያወሩት ለዚህ ልጅ ነው? ምኑ ስቧቸው ነው? ፊቱ ውስጥ ሞኝነት ብቻ ነው የሚነበበው! ቆይ መክሊት ሳየው እንባዬ ይመጣል ያለቺው በምኑ ነው?፡ ቲጂ የሚያስደነግጣት የቱ ጋር ነው?" አለች በሀሳቧ
"እየሳልሺኝ ነው እንዴ? ኸረ በቃሽ!" ህይወት በሀሳብ ውስጥ ሆና አልታወቃትም እንጂ አተኩራ እያየቺው ነበር
" በጣም ይገርማል! የዶርም ጓደኞቼ ግን ሲያሳዝኑ ፡ በጋራ አንድ ወንድ አፍቅረው፡ በተለይ አንደኛዋ" አለች ህይወት
" የእኔም ጓደኞች እንደዛው! በተለይ አንዱ ሊሞት ነው! እኔም እኮ አመጣጤ ለዛ ነበር"
"ለምኑ"
"እ..ለፕሮጀክቱ ነዋ"
"ምን ትቀባጥራለህ ቀባጣሪ.."
ከላይብረሪ ወጡ፡ ወንዱ ዘበኛ አልነበረም ፡ ሴቷ ብቻዋ ህይወትን ካሳለፈቻት በኃላ ናሆሜን አስቆመቺው
"መታወቂያህን ታመጣለህ?"
"አይ አላመጣም"
"እሺ እንዳታመጣ! በጣም ይቅርታ እሺ ስላስከፋሁህ"
"መች አስከፋሺኝ? ችግር የለውም"
"ከዚህ በኃላ እንደፈለክ ትገባለህ?"
"እሺ"
"ዛሬ ትመጣለህ"
"አልመጣም"
"ነገስ?"
"ናሆም ሄጃለሁ.." አለች ሂዊ
ጠባቂዋን ሳይመልስላት ህይወትን ተከተላት
"ተፈላጊ ነኝ ለማለት ነው?" አለቺው እንደደረሰ፡
"ምን አገናኘው?" አላት
"(ፈገግታ) ስቀልድ ነው..ደግሞ እኮ ተፈላጊ ነህ..እኔ ግን ይቅርታ አድርግልኝና ምንህ እንደሚስባቸው አይገባኝም?"
ቆመ ፡ ሄደች፡ ደግሞ ተከተላት
.........
ክፍል 3
3 185
እነሆ የፍቅር ጥግ 1
♥የፍቅር ጥግ♥
[ጉልላት አበበ]
1
በቅጡ ያልተዘጋውን የዶርም በር በርግዶት ገባ፡ከናሆሜ በስተቀር አምስቱ የዶርሜ ጓደኞሞች ስለ ሀገራቸው ቀደምትነት እየተወያዩ ነበር ፡ ሁሉም ፀጥ አለ፡ ዴቭ ነበር ቀልባችንን የገፈፈው
ዴቭ እንዲህ ዶርም ሊመታ ቀርቶ ሲያንኳኳም አስፈቅዶ ነው፡ ዛሬ ምን ነካው?
"ስምሽ እንዳልጠራ
ያውቁብኛል ብዬ
ፅጌሬዳ አልኩሽ በአበባ
አስመስዬ
ውብ ፀአዳሽ እርካታዬ
ፅጌሬዳ አበባዬ
ውብ ቀለምሽ ቢስበኝም
እሾክህሽ ግን አልበጀኝም..."
እየዘፈነ ተመለከተን፡ አይኖቹ ሊያለቅሱ የእርሱን ፍቃድ ይጠባበቃሉ
ሲያሳዝን!
" ዘፈኑ መልዕክት ይኖረው ይሆናል፡ ምናልባት በዘፈኑ ተነስተን ዴቭ ምን እንደሆነ መገመት እንችላለን" አለ ናሆሜ
ማንም የሰማው የለም
ዴቭ ሲያዝን አይኖቹ ይተልቃሉ፡ ፊቱ የህፃን ልጅ ይሆናል፡ በአዝናኝነቱ የሚታወቀው ዴቭ ለምን እንዳዘነ ለማወቅ ጓጉተናል
ዴቭ መዝጊያው ስር ተለጥፎ ቆሟል፡ቀጭን ሆና ቦርጫም እሱን ብቻ ነው ያየሁት :ከላይ ወደታች ላየው ሌክሲ እስክሪፕቶ ይመስላል ፡ሆዱ ለብቻው ተለይቶ ተወጥሯል ያደረገው ነጠላ ጫማ እና ቀይ የቁንጣ መለያ ብቻ ነው፡
"አቦ ተናገራ !ምን ሆነሀል?" አለው ' ቃል' ወደ ጀመሩት ወሬ ለመመለስ እየጓጓ
ዴቭ አይኖቹ እንባ አቀረሩ
ነገሩ ከባድ ሚዛን ነው መሰለኝ
ናሆሜ ከነበረበት አልጋ ወረደና ዴቭን እጁን ይዞ አስቀመጠው
"የተፈጠረ ነገር አለ?"
"የለም"
"እና ምን ሆነሀል እያለቀስክ እኮ ነው"
አለው ናሆሜ ላፕቶፑን እየዘጋ
"ሂዊ" አለ ድምፁን ዝቅ አድርጎ፡
እኛ እንዳንሰማው ተጠንቅቆ ቢናገርም እያየነው ስለነበር "ሂዊ" ማለቱን በአፉ እንቅስቃሴ ተረዳን
"እሷ በእርግጥ ፅጌሬዳ ናት ግን እሾህ አላት ያውም በጣም ብዙ" አለ እያለቀሰ
ልዑል ሳቁን መቆጣጠር አልቻለም
( ክክክ...ረጅም ሳቅ)
የሚጀምርልን አጥተን እንጂ እኛም መሳቅ ፈልገን ነበር፡ እድሜ ለልኡሌ እኛም ሳቅን
"አያስቅም!" አለ ናሆሜ በቁጣ
"አሾህ በዝቶባት ሳይሆን እሾህ አብዝታ ነው!"
አለ ጠረጴዛውን እየመታ
"ንግግሩን አከበድከው ጀለስ! ከእሾህ ወደ ኦሾ ሆነ እኮ" ቃል ነበረ
ናሆም" ..ዝም በል አንተ
ሌሎቹን ሴቶች እንዴት ነው የምታሳምኑት? ታዲያ እሷን ምነው ከበዳችሁ? ወይስ ለእሱ ስለሆነ ነው? ጓደኛችሁ እኮ ነው.." አለ
ልኡሌ ጉሮሮውን ጠራረገ
ምን መሰለህ?
" ናሆሜ አንተ ያለገባህ ነገር አለ ልጅቷ እንደሌሎቹ አይደለችም
ወግ አጥባቂ ነገር ናት፡
ብዙ ጊዜ ሞከርን እሺ ልትለን አልቻለችም ምናልባት እሱን ወዳው ላይሆን ይችላል ብለን አስበን ለራሳችን አምስታችንም ጠይቀናት ነበር ለሁላችንም የሰጠችን መልስ ተመሳሳይ ነበር
"ምን አለቻችሁ?" አለ ናሆሜ
ልዑል ጠረጴዛውን እየመታ በጣም ነው የገረመችን መልሷ ያልጠበቅነው ነገር ነበር፡ ቆይ ግን የእውነት ፍቅር ቢዘን ምን ታረገን ነበር
" እባክህ ልዑል ምን እንዳለቻችሁ ብቻ ንገረኝ" አለ ናሆም
ቃል የጀመሩትን ርዕስ ለመቋጨት እየጓጓ ነበር ዳዊት በሩን በርግዶት የገባው
ሁሉንም በንቀት ተመልክቶ
"ስለ ምን ፍቅር ..ህይወት ..ነው የምታወሩት? አቦ እሷን ተዋት! ይልቅ ከአፄ ቴዎድሮስ በፊት ስለነበረው የሀገራችንን ታሪክ ብናወራው ምን ይመስላቹሀል?"
"አንተ ምን ሆነሀል? ታሪክ ታሪክ እያልክ ልትሞት ነው እንዴ?"
ልዑሌ በድጋሚ ጉሮሮውን ጠራረገ
ለአምስታችንም
ምን እንዳለችን ታውቃለህ?
{እኔ የማንም ሰው ንብረት መሆን አልፈልግም!}
ናሆም " እስኪ እናያለን በዚህ አቋሟ ከቀጠለች" አለ ላፕቶፑን ወደ ሎከሩ እያስገባ
ዴቭ "ምን ልታደርግ ነው?" አለው
ልኡል" አንተም ልትጀናጀን ባልሆነ ፡ እንዴ ችከላውስ? ኸረ እኔ አላምንም! ግን ጠብ እንደምታደርጋት አልጠራጠርም"
ቃል" እኔ ግን የሚከብደው ይመስለኛል ምክንያቱም ይሄ ትምህርት አይደለም መካኒክስ ወይ አፕላይድ አይደለም 'ፍቅር' ነው፡፡ እሱም እንደኛ ' የማንም ሰው ንብረት መሆን አልፈልግም' ተብሎ ይመጣል
ናሆሜ " ይልቅ ስለ ልጅቷ አንዳንድ ነገሮች ማወቅ እፈልጋለሁ" አለ
"አብሽር ሁሉም አለ ሙሉ መረጃ አለን፡ ምን እንደምትወድ ፡ ምን እንደምትሰራ ፡ የት እንደምትውል ሁሉን እናውቃለን"
ቃል ነበረ ከብርሀን ፍጥነት እኩል የሚያወራው
"ተናገር" አለ ናሆሜ
"ሂዊ የሶስተኛ አመት የሲቪል ኢንጂነሪንግ ተማሪ ናት አብዛኛውን ግዚ የምታሳልፈው ግቢ ውስጥ ባሉ ክበባቶች በተለይም የኪነ ጥበብ ክበብ ውስጥ ሲሆን 8 ሰአት ሁሌም ላይብረሪ እየገባች ኢንሳይክሎፒዲያን ታነባለች
እዚህ ከሌለች ደግሞ እስቴዲየም ሄዳ በጠራራ ፀሀይ ብቻዋን ትቀመጣለች
እንደሌላው ተማሪ አትተኛም
"ይበቃል ሌላውን ለኔ ተውልኝ " አለ ናሆሜ
ስለ ሴት አውርቶ የማያውቅ ልጅ፡ ከትምህርት ሌላ አስቦ የማያውቅ ልጅ አሁን ከግቢያችን ደረቅ ተማሪ ጋር ሊፋለም ነው
ሁላችንም ጓጉተናል ፡ ምን ይፈጠር ይሆን?
ይሄ ለመገመት በጣም ከባድ ነው
ምክንያቱም ሂዊ የራሷ ህይወት የራሷ አቋም ያላት ልጅ ናት እስካሁን ከወንድ ጋር ሆና አታውቅም ፡ በሌላ በኩል ደግሞ ናሆሜ ማንም ሴት ለፍቅር የሚመኘው አይነት ልጅ ነው፡ አፈቀርኩህ ያሉት ልጆች ብዛት እኛ ሁላችንም ከጀነጀናቸው ከተሳኩልንም ካልተሳኩልንም ሴቶች ቁጥር ይበልጣል
አሁንስ ምን ይፈጠር ይሆን? ናሆሜ ልቧን ያሸንፈዋል ወይስ እንደኛ ይመለሳል?
ናሆም 7:30 ሲሆን ከዶርም ለመውጣት ተነሳ ከሎከሩ ልብሶቹን አውጥቶ ይለባብስ ጀመር
"ይቅናህ" አለው ቃል
ናሆሜ ምንም ሳይል ከደረጃው በፍጥነት እየወረደ መጓዝ ጀመረ
ጉዞ ወደ ሲቪል ምህንድስና ላይብረሪ ህይወትን ፍለጋ
......
ክፍል 2 ነገ ይቀጥላል
የፍቅር ጥግ
ክፍል 2
....ናሆሜ ምንም ሳይል ከደረጃው በፍጥነት እየወረደ መጓዝ ጀመረ
ጉዞ ወደ ሲቪል ምህንድስና ላይብረሪ ህይወትን ፍለጋ
ናሆሜ ወደ ላይብረሪ ሲደርስ አንድ ነገር አለማሰቡ ታወሰው፡
በመጀመሪያ የእሱ ፊልድ ሌላ ነው፡ የአርክቴክቶች እስቱዲዮ ሲቪል መሀንዲሶች አይገቡም በተቃራኒው አርክቴክቶች ወደ ሲቪሎች አይገቡም
"የግድ መግባት አለብኝ " አለ ናሆሜ ወደ ላይብረሪው በር እያየ
የሚገባውን ከሚወጣው የሚለዩት ሁለት ወንድ እና ሴት ፊት ለፊት አሉ
"ወንዱ ቢፈቅድልኝ እንኳን ሴቷ ታካብዳለች! ምን ማለት ነው አሁን ወንድ እና ሴት ዘበኛ ማድረግ?"
ሄኖክ ብዙ ጊዜ በሴቶች በደል ይደርስበታል፡ በረባ ባልረባ ነገር ቢሮ ከምታመላልሰው የዲዛይን መምህራቸው ጀምሮ፡ ምግብ ቤት ገብቶ ከከፈለ በኃላ ለመልስ የሚያስጠብቁት ሴቶች፡ በሆነ ባልሆነ ወሬ የሚጠምዱት የክላሱ ሴት ተማሪዎች ፡ ትዝ አሉት
በተለይ የሚያናድደው ምክንያታቸው ነው "ደስ ስለምትለን እኮ ነው" ይሉታል
ወደ ላይብረሪው በድጋሚ ተመለከተ : ሁለቱም አሉ
አያት፡ አየቺው፡ ፈገግ አለች፡ ተቆጣ
የእድሉን መሞከር ጀመረ
ቀጥ ብሎ በኩራት ወደ ውስጥ "ሰላም " ብሏቸው ሲያልፍ
"መታወቂያ አሳይ ወንድም" የሚል ድምፅ ከጉዞው ገታው
ሴቷ ናት፡ ወንዱ ምንም አላለም
የጠበቀው ነገር ስለነበር አልደነገጠም
"ኦው በጣም ይቅርታ
መታወቂያ አልያዝኩም ስምንት ሰአት ደግሞ ፈተና አለኝ፡ የተረሳኝ ነገር ለማስታወስ ብቻ ነው አልቆይም፡ ፍቀዱልኝ" አላቸው ፊቱን አሳዛኝ ለማድረግ እየሞከረ
ናሆሜ ትወና ይችላል፡ ሀይስኩል እያለ ዘበኛ ፡ ሀኪም፡ ፖሊስ ፡ ነጋዴ ፡ ገበሬ፡ ሆኖ ተውኗል
"እሺ ግባ " አለው ወንዱ ጠባቂ
"ና ! ትሰማለህ? ከፈተናው በኃላ መታወቂያህን ይዘህ እኔ ጋር ትመጣለህ" አለችው ሴቷ ጠ
3 185
♥ ኦሪዮን ♥
[ ጉልላት አበበ]
፫
"እንዴት አደራችሁ ተማሪዎች ? ( እግዚአብሄር ይመስገን ብለን ቁጭ) ዛሬ ደስ ብሎኛል ፡፡ ለብዙ ጊዜ እዚህ ግቢ ስከራከርበት የነበረው አንድ ጉዳይ ዛሬ እልባት አግኝቷል ፡፡ ትምህርት ቤቱ ልክ እንደሌላው ትምህርት ሁሉ አንድ የሳይኮሎጂ መምህር ቀጥሮ ስራ እንድትጀምር ሆኗል!:: ( ለረጅም ጊዜ አጨበጨብን)
ኦሪዮን ቀጠለ " መምህሯ መጀመሪያ ማግኘት ያለባት የእኔን የተለዩ ተማሪዎች ነው ብዬ ይዣት መጥቻለሁ " (በድጋሚ ጭብጨባ)
ከኦሪዮን ንግግር የሳይኮሎጂ መምህራችን ሴት ናት ፡፡ ( ይህ ለፍቅር ብዙም ደስ አላላትም፡ ሴት መምህራን ከኦሪዮን የሚያጣብቃቸው ነገር አለ ፡ ምን አለ ጓደኞቻቸውን ቢፈልጉ ትላለች ፡ እነሱን እንዳለፈባቸው በማሰብ )
ኦሪዮን ወደ ውጭ ወጥቶ መምህራችንን ይዟት መጣ መምህርት ቤቲ ..የፍቅር እህት....
"ሰላም እንዴት ናችሁ ቤተልሄም እባላላለሁ የሳይኮሎጂ አማካሪ መምህራችሁ ነኝ ፡ ከአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ በ 2010 ነው የተመረቅኩት ፡ የዚህ የገዳም ሰፈር ሁለተኛ ደረጃ በሙሉ የሳይኮሎጂ መምህራችሁ ነኝ (ፍቅር እጇን አፏ ላይ ጭና አንዴ እህቷን አንዴ ኦርዮንን ትመለከታለች )
ቤቲ ቀጠለች ...
የሰው ልጅ በየዕለቱ በጣም ብዙ ውስጣዊ እና ውጫዊ ችግሮች ተጋላጭ ነው ነገር ግን ማህበረሰባችን ለውጫዊው እንጂ ለውስጣዊ ችግሮች መፍትሄን ሲፈልግ አናየውም ፡፡ (ኸረ ኮንፊደንስ! )
የሰው ልጅ ሁሌ ሞቲቬት ከተደረገ ፡ ውስጡን ገልጠው ካሳዩት ሀዘንን አያውቀውም :: (ተማሪዎቹ ከልባቸው ነበር የሚያደምጧት)
ፍቅር በቤቲ ንግግር ፈገግ ትላለች (አሁን ይሄ ንግግር ምኑ ያስፈግጋል? እህቴ እኮ ናት ብላ መናገር ነው የቀራት ወዲህ ወዲያ ትወራጫለች)
ፍቅር ትንፋሿን ወደ ውስጥ ስባ 'ተመስገን' አለች
ቤቲ በጣም ቆንጆ ናት ፡ ስራ አጥታ ቤት እናቷን እየረዳች ነበር ፡፡ የቤቲ ስራ ማጣት ከእሷ በላይ ፍቅርን ነው የጎዳት፡ እህቷ ቤት እንድትቀመጥ አትፈልግም ፡ የምትጨነቅ ይመስላታል፡ የምትጎዳ ይመስላታል፡ ከእራሷ በላይ ትወዳታለች ፡ ቤቲን ብለው ቤት የማይመጡ የሉም ..ውበቷ ስቧቸው ( እሺ አሁን ቤቲ ከፍቅር ወጣች ነው ፍቅር ከቤቲ ወጣች የሚባለው)
ቤቲ ሁሉንም እያየች ታወራለች
በማህበረሰባችን አንድ ሰው ታመመ የሚባለው ሲተኛ ብቻ ነው ( ተማሪው ፈገግ አለ )
ነገር ግን ሁላችንም መገንዘብ ያለብን ውስጣዊ ሰላማችንን ነው ፡ ፡
ሁሌም የሚረብሹን ፡ ሁሌም የሚያሳስቡን ፡ ከአዕምሯችን አልጠፋ ያለንን ማንኛውም ነገር ካለ እኔን ግቢ ውስጥም ሆነ ከግቢ ውጪ ማናገር ትችላላችሁ ፡፡
በተጨማሪም በኦሪዮን በኩል እኔን ኮንታክት ማድረግ ትችላላችሁ
( ፍቅር ትንሿን ጣቷን አፏ ውስጥ አድርጋ እያሰበች ነው ..በኦሪዮን በኩል ምን ማለት ነው? ለምን በእህቴ በኩል አላለችም?)
ሰአታችሁን ተሻማው መሰለኝ ( ኦሪዮን ፈገግ አለላት )
ኦሪዮን ወደ መሀል ወጥቶ
"እናመሰግናለን ቤቲ ! መምህራችሁን ወደዳችኃት? "
(ተማሪዎች አጨበጨቡ ..ከሁሉም የፍቅር ጭብጨባ ጎልቶ ይታይ ነበር)
ወንዴ ወጥቶ ቾክ ቦርዱን እያፀዳ ነበር
ኦሪዮን እና ቤቲ ተያይዘው ከክላስ ወጡ ( ሸኝቷት ሊመለስ)
ምን እያወሩ ይሆን? ፍቅር ወደ ቤት ገብታ እህቷን ስለተፈጠረው ነገር ለመጠየቅ ጓግታለች
"ምናባትሽ ነው ያልነገረሽኝ ? ምናባትሽ ነው እህቴ ናት ያላልሺው? ምናባትሽ ነው ስታወሪ አይን አይኔን ያላየሺኝ? በትራስ ደብድቤ ደብድቤ ...በመሀል ፈገግ ትላለች
ግን ለምን በዘፈን አላደርግላትም? ማለት ልክ እንደዚህ
አስችሎሽ ይሆን አስችሎሺ
በኔ ላይ ሌላ ሰው የሆንሺው ( ሁለት ጊዜ)
እኔ እንጃ እኔንጃ
እኔ እንጃልኚ (2×)
ፍቅርሽ በአይኔ ላይ ዞረብኚ
እኔ እንጃ እኔ እንጃ እኔ እንጃልኚ
.
.
.
ከዚህ በፊት ይተዋወቁ ነበር?
ከማን?
ከኦሪዮን
(ፍቅር ሀሳቧ ክላስ ውስጥ የለም)
ከዚህ በፊት ቢተዋወቁ እንኳን ትነግረኝ ነበር ቢያንስ ስልኩ ይኖራት ነበር ፡ ቢያንስ ይደዋወሉ ነበር
ቢተዋወቁስ እኔ ከተዋወቅነው ገጠመኝ ይበልጣል? (ፈገግ)
ፍቅር በሀሳብ ወደ ኃላ ነጎደች
" የስምንተኛ ክፍል ሚንስትሪ ውጤታቸውን መቀበል ምክንያት አድርገው ያዘጋጁት ፕሮግራም ላይ መምህራንን ጋብዘዋል ፡ ሁሉም የስምንተኛ ክፍል መምህራን ሲሆኑ በፕሮግራሙ አዘጋጆች አንድ መምህር ከሀይስኩል መርጠው መጋበዝ እንዳለባቸው ወስነው ነበር
ፍቅር ይሄንን አታውቅም ነበር
የፍቅር ውጤት የግቢው ሁለተኛ (ከዮናታን ቀጥሎ) እና ከሴቶች አንደኛ ነበርና ከመምህራኑ ፊት ለፊት ሁለቱ የውጤት ሰቃዮች ተቀምጠዋል
አሁን የቀረው ተጋባዡ መምህር ብቻ ነው ;-ኦሪዮን
.
.
.
.
(በየቀኑ የሚቀርብ ነው)
ቴሌግራም ለሚመቻችሁ
https://telegram.me/gullea
like
Comment
share
አድርጉ
3 185
♥ ኦሪዮን♥
፪
[ጉልላት አበበ]
.....ቤቲ ስትስመኝ ሰውነቴ መሞቅ እንደሚጀምር አይገባትም፡፡ ( ለእሷ ገና ልጅ ነኝ )
ለመሆኑ ማታ ማታ ትራሴን ታቅፌ ኦሪዮንን እንደማስብ ያውቃሉ?
ትምህርት ቤት ደረሰች
ትምህርት ቤቱ ኦሪዮን ይመስላታል ፡፡ ኦሪዮን ኦሪዮን ኦሪዮን ትላለች
በአይን መጫወት ትወዳለች (ይህንን ጫወታ ያስለመደቻት እህቷ ናት )
ፍቅር ወደ ወደ ገዳም ሰፈር ሁለተኛ ትምህርት ቤት ከገባች ጊዜ ጀምሮ እስካሁን የእኔ የምትለው ጓደኛ አላፈራችም፡፡ ጓደኞቿ እህቷ እና እናቷ ብቻ ናቸው
የሴት ጓደኛ ያስፈልጓታል
እየተሰማት ያለውን በሙሉ ሳትደብቅ የምትነግራት፡ እንደልጅ የማትቆጥራት፡ ድርጊቷን የምትደግፍላት፡ ውብ እንደሆነች የምትነግራት (እቺን እንኳ እህቷም ታደርገዋለች)
ፍቅር ጠይም መካከለኛ ቁመት ያላት ሲሆን የፀጉሯ ውበት እና ርዝመት ፡ ስትስቅ ብቻ የሚታየው ስርጉደቷ የእሷ ብቻ የሆኑ ውበቶች ናቸው፡፡ ሁሉም ይመኟታል፡ (እሷስ የምትፈልገው ይህን አይደል?)
ወንዶች ትኩር ብለው ካዩዋት ማየታቸውን እስኪያቆሙ ፍጥጥ ብላ ታያቸዋለች ከዛም አፍረው አይናቸውን ይሰብራሉ ፈገግ ብላ "ፈሪ" ትላለች ( ይህንን እሷ የአይን ጫወታ ትለዋለች ከእህቷ ነው የተማረችው ፡ እህቷን ግን በዚህ አሸንፋት አታውቅም፡ ፍጥጥ ብሎ መተያየት ማን ቀድሞ ፊቱን ያዞራል? የፈጣጣነት ጫወታ እንበለው? እህቷ በዚህ ደረቅ ናት ምናልባት የሳይኮሎጂ ምሩቅ ስለሆነች ይሆን?)
ፍቅር
"ወንዶች ፈሪ ናቸው " ትላለች
"እየፈለጉ እንዳልፈለጉ እየወደዱ እንዳልወደዱ ይሆናሉ ፡ በልባቸው ብዙ ያስባሉ በቃላቸው ምንም አይሉም ፡ ቆንጆ ሴት ሲያዩ ቀድመው ይደነግጣሉ::" ትላለች
ወደ ትምህርት ቤቱ ገባች
ዛሬ ዘበኛው ጋሽ ዘውዱ በር ላይ የሉም ፡ አላመነችም ፡ ጭቅጨቃቸው ሁሌም ደስ ይላታል ፡ የዘወትር ምክራቸውስ ቢሆን "ልጄ እራስሽን ከወንድ ጠብቂ ፡ ወንዶችን አትመኚ (እርሳቸው ሴት ናቸው እንዴ? ወይስ በወንድ የደረሰባቸው ነገር አለ?)
ጋሽ ዘውዱ ወንድ የተባለ ነገር አይወዱም ( ለመሆኑ እራሳቸውንስ ይወዳሉ?)
የሚያከብሩት አንድ ወንድ ቢኖር ኦሪዮንን ብቻ ነው (እኔ የምወዳቸው ለዛ ይሆን ኦሪዮንን ስለወደዱልኝ)
ለሰከንዶች ግራ ቀኝ አየች ፡ የሉም፡፡
ወደ ውስጥ ዘለቀች
ገዳም ሰፈር የሚገኘው ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከተመሰረተ ረጅም አመታትን አስቆጥሯል
ለብዙዎቹ የፍቅር ጅማሬያቸው እዚህ ነው ፡፡ እዚህ ትምህርት ብቻ አይሰጥም የተባለ ይመስል ጥንድ ጥንድ ሆነው ከዚህ ይወጣሉ
የሰፈራችን መፅሔት እና ጋዜጣ አዟሪዎች ገዳም ሰፈርን የፍቅር ገዳም ብለዋታል
****
የክላሷ ተማሪዎች ግማሾቹ በር ላይ በቡድን በቡድን ሆነው ያወራሉ
ግማሾቹ ክላስ ውስጥ የመምህራቸውን መምጣት ይጠብቃሉ::
በእጃቸው ማውለብለብ እስከ ደረቅ ፈገግታ ተቀብላ ወደ ክላስ ገባች
የልብ ጓደኛ የላትም ነገር ግን ይህ ብዙም አያሳስባትም፡
ክላስ ውስጥም ልክ እንደ ውጪው በቡድን በቡድን ሆነው ያወራሉ
ምህረት ከተሰበሰቡት ለብቻዋ ተነጥላ ከኃላ ተቀምጣለች
( እንደ ፍቅር የሴት ጓደኛ የላትም፡ ምናልባት እሷም ቆንጆ ስለሆነች ይሆን?)
ፍቅር በዝግታ ወደ ምህረት አመራች
"ሞነው ለብቻሽ ? ለብቻ መሆን ትንሽ አይከብድም ? " እራሷን አረጋግታ እንደተቀመጠች
" በእርግጥ ይከብዳል ግን የማይለመድ ምን አለ? በዛ ላይ እኮ እስከ ስድስት ሰአት ብቻ ነው ለብቻዬ የምሆነው ከዚህ ከወጣው ብዙ ጓደኞች አሉኝ "
ዝምታ ሰፈነ
ምህረት ቀጠለች " ግን እኮ አንቺም ጓደኛ የለሽም ፡ ልክ እንደኔ " አለቻት
ፍቅር ትንሽ አስባ " ጓደኞች እንዲኖሩኝ ስላልፈለግኩ ብቻ እንጂ ቡዙዎቹ ከእኔ ጋር ጓደኛሞች መሆን ይፈልጋሉ"
(ይህንን ኮንፊደንሷ ትወደዋለች እሷ ተወዳጅ ቆንጆ እና ከማንም እንደማታንስ ነው የሚሰማት)
ውጪ የነበሩት ተማሪዎች ግር ብለው ወደ ክላስ ገቡ (እንዲህ ሲሆን መምህር መጥቷል ማለት ነው፡፡)
ተማሪዎች ፊታቸው ውስጥ ደስታ ይነበባል (ይህ ማለት የመጣው መምህር ኦሪዮን ነው ማለት ነው) ከሌላው ጊዜ በተለየ ግን ሁሉም ያንሾካሽካሉ
"ምናልባት ኦሪዮን አዲሱን መምህራችን አመጣልን እንዴ? " ፍቅር ሁሉንም ለማየት ጓጓች
ኦሪዮን ወደ ክላስ ገባ
ሁሉም ቆመው ተቀበሉት ( ይህ ለእሱ ብቻ ነው!)
"እንዴት አደራችሁ ተማሪዎች ? ( እግዚአብሄር ይመስገን ብለን ቁጭ) ዛሬ ደስ ብሎኛል ፡፡ ለብዙ ጊዜ እዚህ ግቢ ስከራከርበት የነበረው አንድ ጉዳይ ዛሬ እልባት አግኝቷል ፡፡ ትምህርት ቤቱ ልክ እንደሌላው ትምህርት ሁሉ አንድ የሳይኮሎጂ መምህር ቀጥሮ ስራ እንድትጀምር ሆኗል!:: ( ለረጅም ጊዜ አጨበጨብን)
ኦሪዮን ቀጠለ " መምህሯ መጀመሪያ ማግኘት ያለባት የእኔን የተለዩ ተማሪዎች ነው ብዬ ይዣት መጥቻለሁ " (በድጋሚ ጭብጨባ)
ከኦሪዮን ንግግር የሳይኮሎጂ መምህራችን ሴት ናት ፡፡ ( ይህ ለፍቅር ብዙም ደስ አላላትም፡ ሴት መምህራን ከኦሪዮን የሚያጣብቃቸው ነገር አለ ፡ ምን አለ ጓደኞቻቸውን ቢፈልጉ ትላለች ፡ እነሱን እንዳለፈባቸው በማሰብ )
ኦሪዮን ወደ ውጭ ወጥቶ መምህራችንን ይዟት መጣ መምህርት ቤቲ ..የፍቅር እህት....
.
.
.
.
(በየቀኑ የሚቀርብ ነው)
ቴሌግራም ለሚመቻችሁ
https://telegram.me/gullea
like
Comment
share
አድርጉ
3 185
♥ ኦርዮን ♥
የፍቅር ታሪክ
[ ጉልላት አበበ]
፩
የሞላችው አላርም እና እህቷ እኩል ደረሱ ፡ (ዕድለ ቢስ አላርም ነው ማንም ላይሰማው የሚጮኽ)
ቤቲ ላትሰማው ነገር ሁሌም አላርሟን ትሞላለች (ወጉ እንዳይቀር ብላ)
ኳ ኳ ኳ..ቤቲ...ቤቲ ተነሽ እረፍዷል (በሩን እየደበደበች )
እህቷን እንደ መቀስቀስ ደስ የሚላት ነገር የለም፡ ሁሌም መጀመሪያ የምታያት እሷ ናት
አንቺ ቤቲ ( ኳ ኳ ኳ...)
(በጠዋቱ ተነስቼ :ፊቴን ተጣጥቤ : እህቴን ቀስቅሼ...) የፍቅር [ የዘወትር ፀሎት] የዘወትር ተግባር ነው
አንቺ ቤቲ ....
በሩ ተከፈተ
ቤቲ ፍቅርን አቅፋ ወደ አልጋዋ ወረወረቻት ከላይዋ ወጥታ ትነካካታለች እየደባበሰች ታስቃታለች
በእናትሽ ፀጉሬን የማስተካክልበት ሰአት የለኝም ሃሃሃሃ... ሳቅ
(ስትለምናት ፀጉሯን ማሸቷን የበለጠ ታደርገዋለች )
ማሚ..ማሚ ነይ-ልኝ ሃሃሃሃ መናገር አቅቷት ትስቃለች
ቢቲ እናቷ እስካልመጣች ፍቅርን እየነካካች ማሳቋን አታቆምም
(ፍቅር ይሄ ናፍቋት ይሆን በጥዋቱ የምትመጣው?)
"እናንተ ልጆች! ይህ ዝላያቹ አይሰለቻችሁም? " እናቷ ቤቲ ክላስ እየገቡ
ቤቲ ፍቅርን ላይ ተቀምጣ ጉንጯን ..ግንባሯን..አንገቷን ትስማታለች
ተነሽ አንቺ ( ባቷን ቷ አደረገቻት ) ለፍቅር አግዛ
"በዪልኝ እናቴ "
ለሁለት ቤቲን ከስር አድርገው ይስሟታል (የመሳሳም በቀል- አሁን የመጀመሪያ ልጃቸው ወንድ ቢሆን ..)
ቤቲም አላርሟን የምትሞላው ፍቅርም ወደ ቤቲ ክላስ የምትሄደው ከሚነቁበት 20 ደቂቃ ቀድመው ነው (ለልፊያ የተመደበ ሰአት)
ቤቲ ከእናቷ ጋር ሆነው ለትምህርት ቤት የሚያስፈልጓትን በሙሉ ያዘገጃጃሉ ..5 ደቂቃ አይጨርስባቸውም)
ፍቅር ለሁለት ተበጃጅታ ከቤት ትወጣለች ይህ ፍቅር ሁሌም አብሯት አለ
ቤት የመሆን ፍላጎቷ ከፍ የሚያደርገው ይህ ከአድማስ የሰፋ ሀዘንን የሚያርቅ ቤተሰባዊ ፍቅር ነው
የአስረኛ ክፍል ተማሪ ናት ፡ የምትወዳት እህቷ ተመርቃ ስራ ስላጣች ( ሁለት አመት ሆናት ) ትምህርት ላይ ቡዙም አታተኩርም
ትምህርት ቤቱ ከቤታቸው ብዙም አይርቅም
እየሄደች ታስባለች ፡ እያሰበች ትሄዳለች
"ቤተሰቦቼ እኔን አያውቁኝም" ትላለች
ሁሌም ልጅ ነው የምመስላቸው
"የሰው ልጅ በእህቱ እና እናቱ እንክብካቤ ብቻ አይኖርም በወንድ ትንፋሽ እንጂ" ልበላቸው እንዴ? ፈገግ ትላለች
የአስፓልቱ ጥግ ይዛ ትራመዳለች
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የእህቷ እና የእናቷ የልብስ መረጣ ስላልተመቻት እሷ መምረጥ ጀምራለች
(ልብስ ትኩረትን ካልሳበ ምን ያደርጋል?) ትላለች
ወንዶች ካዩዋት ደስ ይላታል
"ቤተሰቦቼ አያውቁኝም" ትላለች
"ቢያንስ የስውነቴ ቅርፅ እንደተቀየረ አይገባቸውም? " እራሷን ትዳብሳለች
ቤቲ ስትስመኝ ሰውነቴ መሞቅ እንደሚጀምር አይገባትም፡፡ ( ለእሷ ገና ልጅ ነኝ )
ለመሆኑ ማታ ማታ ትራሴን ታቅፌ ኦሪዮንን እንደማስብ ያውቃሉ?
ትምህርት ቤት ደረሰች
ትምህርት ቤቱ ኦሪዮን ይመስላታል ፡፡ ኦሪዮን ኦሪዮን ኦሪዮን ትላለች
.
.
.
(በየቀኑ የሚቀርብ ነው)
https://telegram.me/gullea
like
Comment
share
አድርጉ
3 185
ይህቺን ምርጥ የፍቅር ተከታታይ ታሪክ ተጋበዙልኝማ በእርግጠኝነት ትወዱታላችሁ
♥የሁለት እህትማማቾች አንድ ልጅ ማፍቀር♥
መልካም ንባብ
3 185
ሰላም እንዴት ናችሁ?
እስካሁን በትዕግስት የጠበቃችሁኝ እውነተኛ የፅሁፌ ተከታታይ መሆናችሁን አውቄያለሁ
♥ ከዛራ ጀምሮ በእጥፍ እክሳችኃለሁ♥
3 185
ከሳይኮሎጂ ገፅ
ራስን ከራስ ጋር ማስታረቅ
ራስን ከራስ ጋር ማስታረቅ ማለት በእውነተኛ ማንነታችንና እንዲህ ነኝ ብለን
በምናስበው መካከል ያለውን ልዩነት ማስታረቅ ማለት ነው፡፡ አንድ ሰው
እንዲህ ነኝ ብሎ የሚያስበው በራሱ ላይ ያለው ግምት ከእውነተኛ ማንነቱ
ሲለያይ ራሱን ያታልላል፡፡
ይህ አይነቱ ራስን ማታለል የሚመነጨው ያልሆንነውን እንደሆንንና የሌለንን
ነገር እንዳለን አድርገን ለሰዎች ለማሳየት ከመሞከር ነው፡፡ አንዳንድ ሰዎች
የተታለለ ሕይወት ነው የሚኖሩት፡፡
እውነተኛ ማንነታቸውንም ሆነ ትክክለኛ ሁኔታቸውን ለማወቅ አይኖቻቸውን
መክፈት አይፈልጉም፡፡ ለታይታ በሚያሳዩት ሁኔታ ሸፋፍነውት በመኖር
ለእድገት የሚሆንን መፍትሄ ሳያገኙ ይኖራሉ፡፡
በዚህ ሳምንት ማንነቴንና አስተሳሰቤን ለማስተካከል የምወስዳቸው
እርማጀዎች፡-
1. ራስን የማታለል ሃሳቦች አቆማለሁ
መለወጥ የሚጀምረው አስተሳሰቤን ስለውጥ ነው፡፡ የማሰላስላቸውን
የማስመሰል ሃሳቦች ሳላቆም ማስመሰልን ማቆም አልችልም፡፡ ስለዚህ፣
ያልሆንኩትን መስሎ የመታየትንና የሌለኝን እንዳለኝ የማስመሰልን ሃሳብ
አቆማለሁ፡፡
2. የታይታ ተግባሮቼን አቆማለሁ
ማቆም ያለብኝ ሃሳቤን ብቻ አይደለም፡፡ ከሃሳቤ አልፎ በመሄድ ወደ ተግባር
የተለወጠውን ሁኔታ ሁሉ አቆማለሁ፡፡ በሰው ፊት ያልሆንኩትን መስዬና
የሌለኝን እንዳለኝ አድርጌ የምቀርባቸውን የአቀራረብ ሁኔታዎች ሁሉ
አቆማለሁ፡፡
3. አዲስ እርምጃ እጀምራለሁ
መሆን ወደሚገባኝ ማንነትና ማድረግ ወደምፈልገው ታላቅ ነገር የመድረስን
ጎዳና እጀምራለሁ፡፡ መሆን የምፈልገውን ነገር የምሆነው በማስመሰል
ሳይሆን ወደ መሆን የማደግ ጎዳናን በመጀመር ነው፡፡ አላስመስልም፣ ወደ
መሆን አድጋለሁ፡፡
== በቅንነት ሼር ያድርጉ Please LIKE and SHARE
https://telegram.me/gullea
3 185
♥ይፍቱን ስንል♥
በክፋት ብርቱ ሀረግ
ሳለን ተተብትበን ፡፡
አንቺን ሚያህል ጋኔን
እኔን ሚያህል ሰይጣን ፡፡
የነፍስ አባት ቀርቶ
እግዜር እንዴት ይፍታን❓
ምሬ
እንዴት ናችሁሁ😍😍 ተመልሻለሁ
https://telegram.me/gullea
