ዝገት ከjo ጋ
★ሰውን በማዝናናት የብቃት ማረጋገጫ ያለው ብቸኛው ቻናል ሁሌም Telegram ላይ በጥበብ ደምቀን እናሸበርቃለን https://t.me/zeget_kjoga »የተመረጡ እና ማንም ያላያቸው የአማሪኛ ቀልዶች እንዲሁም የሚያስደንቁ ስዕሎችንና ቪዲዮ ያገኛሉ።
Show moreThe country is not specifiedThe language is not specifiedThe category is not specified
221Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
- Subscribers
- Post coverage
- ER - engagement ratio
Data loading in progress...
Subscriber growth rate
Data loading in progress...
አንድ ጊዜ አባት ከቢሮ ድክም ብሎት ቤት ሲገባ ልጁ ሁለት ፖም🍏 ይዞ ሶፋ ላይ ቁጭ ብሏል፡፡ አባት ፈገግ አለና ልጁን አንዱን ፖም እንዲሰጠዉ ጠየቀዉ፡፡ ይህን የሰማዉ ልጅ ሁለቱንም ፖሞች አንድ አንዴ ገመጥ ገመጥ አደረጋቸዉ፡፡
#በዚህ_ጊዜ አባት ተቆጣ... “አንተ ሆዳም! እንደዚህ ይደረጋል! አንዱ አይበቃህምና ነዉ ሁለቱንም ለመብላት የምትጣደፈዉ...!” እያለ የንዴት መትረየሱን አርከፈከፈዉ፡፡
ልጅ አዝኖ እንዲህ አለ “አባዬ እኔኮ ሁለቱንም የገመጥኩት ከሁለቱ የትኛዉ በጣም እንደሚጣፍጥ ለማወቅ ነዉ ... ይሄ በጣም ይጣፍጣል... ስለዚህ እንካ ላንተ! እኔ የቀረዉን ልብላ' ብሎት ለአባቱ የሚጣፍጠዉን ፖም ሰጠዉ:: አባት እንባዉን መቆጣጠር አልቻለም፡፡
#አንዳንዴ_ነገሮች ምንም ሳይገቡን መጮህ፣ መናደድና መቆጣት እንፈልጋለን፡፡ አንድን ነገር ዉጤቱን ገምተን ከምንጀምር ቀረብ ብለን ከመሰረቱ ብንረዳ የበለጠ መልካም ነዉ፡፡
✰ ❍✰ ❍
••━━ •••◉ jo ኒ ◉●••• ━ •••
ትክክለኛ ዋጋህ ትክክለኛ ቦታ ነው የሚገኘው። አንድ አባት ከሞት አፋፍ ላይ ሆኖ ልጁን እንዲህ ሲል ተናገረው..
"ይህ የእጅ ሰዓት አባቴ በውርስ የሰጠኝ ነው፤ ከ200 ዓመታት በላይ የቆየ ነው አባቴም ከአባቱ የትሰጠው ነው። ነገር ግን እኔ ላንተ ከመስጠቴ በፊት ሂድ እና ሰዓት ቤቶች ስንት ሊገዙህ እንደሚችሉ ጠይቀህ ብቻ ና።" አለው።
#ልጁም በመጀመሪያ የሄደው የተበላሸ ሰዓት የሚሰሩ ባለሙያዎች ጋር ጠይቆ መጣ እና በንዴት በብስጭት "አሮጌ ስለሆነ 5 ብር እንገዛሃለን" እንዳሉት ነገረው።
#አባቱም_ድጋሚ ሸቀጣሸቀጥ መሸጫ ሱቆች ጋር ሄዶ እንዲጠይቅ ይነግረዋል። ልጁም ጠይቆ ይመጣ እና አሁንም ከ50 ብር በላይ እንደማይገዙት ይነግረዋል።
#የመጨረሻ_ልላክህ ብሎ "ሙዚየም ሄደህ ጠይቅ" ይለዋል አባቱ። ልጁም ጠይቆ ከመጣ በኋላ ደስታ የበዛበት ድንጋጤ ውጦት ትንፋሹ እየተቆራረጠ "አባቴ አንድ ሚሊዮን ብር እንደሚገዙኝ ነገሩኝ እኮ" አለው።
#አባቱም መልሶ "ልጄ እንድታውቅ የፈለኩት የአንተንም ትክክለኛ ዋጋ (ቦታ) የሚሰጥህ ትክክለኛ ቦታ ላይ እንድትገኝ እንጂ የተሳሳተ ቦታ ላይ ሄደህ ሳይሳካልህ ሲቀር እንድትናደድ እንድትበሳጭ አይደለም። ምንጊዜም ያንተን ዋጋ የሚያውቁ ብቻ ናቸው ዋጋ፣ ክብርና አድናቆት የሚሰጡህ ስለዚህ የተሳሳተ ቦታ ላይ አትገኝ!!
#jo
👆👆👆👆👆
👉👉https://t.me/meme_zone2
አኔ ተቀልቅዬሀለሁ ከሱስ ነፃ ትውልድ እንፍጠር ለወዳጅ ዘመዶ በማጋራት ዘመቻውን ይቀላቀሉ
#ፀረ_ሱስ
#ፀረ_ሲጋራ
ሲጋራ_የማጨስ_ሶስቱ_ዋናዋና_ጥቅሞች
1 የሚያጨሱ ሰዎች አያረጁም
2 የሚያጨሱ ሰዎች በውሻ አይነከሱም
3 የሚያጨሱ ሰዎች ለሊት በተኙበት ቤታቸው በሌባ የመዘረፍ እድሉ አነስተኛ
ነው
~~~~
# ለምን ?????
1 የሚያጨሱ ሰዎች አያረጁም:: ምክንያቱም:- በሳንባቸው ላይ በሚደርሰው
ከፍተኛ ጉዳት እና ተያያዥ ችግሮች ምክንያት በወጣትነታቸው ሰለሚሞቱ
* * * *
2 የሚያጨሱ ሰዎች በውሻ አይነከሱም ምክንያቱም :- በሳንባቸው ላይ
በሚደርሰው ከፍተኛ ጉዳት ምክንያት ቀጥ ብለው መሄድ አየከበዳቸው
ሰለሚመጣ ምረኩዝ ዱላ መጠቀም ይጀምራሉ፡፡ ውሻ ደሞ ዱላ የያዘ ሰው
ደፍሮ አይነክስም
* * * *
3የሚያጨሱ ሰዎች ለሊት በተኙበት ቤታቸው በሌባ የመዘረፍ እድሉ አነስተኛ
ነው ምክንያቱም :- ለሊቱን በሙሉ ከፍተኛ ደረቅ ሳል እንቅልፍ ነስቶ እያሳላቸው
ስለሚያድሩ ሌባ ደፍሮ ቤታቸው አይገባም፡፡
* * * **
ከሱስ የፀዳ ትውልድ ለምድራችን!!!!!
* * * * *
እኔ የዘመኔ ትውልድ ህይወት ይገደኛል!!!!
*
ዘመቻዬን በይፋ ጀመርኩ
ከሱስ ነፃ ትውልድ ለምድራችን!!!!!
◉ በህይወቴ ከተማርኩት ነገር ውስጥ አንደኛው ለሰዎች መልካም ነገር ብታደርግ ለመልካምነትህ ከሰዎች ዘንድ ምላሽ መጠበቅ ሊጎዳ እንደሚችል ነው።
••●◉••
● አንዳንዱ መልካም ስታደርግ ሞኝ እንደሆንክ ሊቆጥርህ ይችላል።
••●◉••
◉ አንዳንዱ ደግሞ ከእሱ የሆነ ነገር ፈልገህ የምታደርግለት ይመስለዋል።
••●◉••
● ሌላኛው ደግሞ ከምስጋና ይልቅ ጠላትህ ሊሆን ይችላል።
••●◉••
◉ እናም እልሀለሁ ለመልካምነትህ ከሰዎች ምላሽን አትጠብቅ!
••●◉••
● ባገኘኸው አጋጣሚ ሁሉ ምላሹ ምንም ይሁን ምን መልካምነት አብሮህ ይሁን! ፈጣሪህ ይከፍልሀልና! ••
••◉••
መልካም ቀን
ፎቶዬን ልፖስት እልና "ለምን ሴት ልጅ በኔ ምክንያት ከፍቅረኛዋ ጋር ትጣላለች ብዬ ተወዋለው...
:
#እያለ_ያበጥረኛል ይ ሄ ቱ ሪ ና ፋ