en
Feedback
Shien ekawuch

Shien ekawuch

Open in Telegram
869
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
-1230 days
Posts Archive
#የኢቲዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ጉባዔ (ኢሰመጉ) የሰጠው ሙሉ መግለጫ!! ETHIOPIAN HUMAN RIGHTS COUNCIL (EHRCO) @አስቸኳይ ጋዜጣዊ መግለጫ በጋምቤላ ክልል ያለው የጎሳ ግጭት በቂ ትኩረትና ዘላቂ መፍትሔ ሊሰጠው ይገባል! ሀምሌ 14/2015 ዓ.ም መግቢያ፡ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባኤ(ኢሰመጉ) ላለፉት 32 አመታት በአገሪቱ ያሉ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶችን በመከታተል እና በመመርመር ያሉ ክፍተቶችን በማሳየት መንግስት የእርምት እርምጃዎችን በመውሰድ የሰዎችን የሰብዓዊ መብቶች የማክበር፣ የማስከበር እና የማሟላት ዋነኛ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ሲወተውት የቆየ አሁንም በመወትወት ላይ የሚገኝ ተቋም ነው፡፡ ኢሰመጉ በተደጋጋሚ ጊዜ በአገሪቱ የሚፈጸሙ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች እንዲቆሙ፣ መንግስት የሰብዓዊ መብቶችን እንዲያከብር እንዲሁም ከመጣስ እንዲቆጠብ እና በሌሎች አካላት የሰዎች የሰብዓዊ መብቶች እንዳይጣሱ እንዲያደርግ በተደጋጋሚ ሲወተውት ቆይቷል፡፡ በኢትዮጵያ የተለያዩ ጎሳዎች እንደሚኖሩ ይታወቃል፡፡ በተለያዩ ጊዜዎች በክልሎች ውስጥ በሚገኙ አጎራባች ጎሳዎች መካከል በሚነሱ የጎሳ ግጭቶች ዘርፈ ብዙ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች ይፈጸማሉ፡፡ በተደጋጋሚ ጊዜ የጎሳ ግጭቶች ከሚስተናገዱባቸው ክልሎች መካከል የጋምቤላ ክልል አንዱ ሲሆን በክልሉ በሚገኙ የአኝዋ እና የኑዌር ጎሳዎች መካከል በሚነሱ ግጭቶች ምክንያት የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች ሲፈጸሙ ቆይተዋል፡፡ ጋምቤላ ክልል፡ በጋምቤላ ክልል ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ እየተባባሰ በመጣው ግጭት ምክንያት በርካታ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች ተፈጽመዋል፡፡ በጋምቤላ ክልል ኢታንግ ልዩ ወረዳ ግንቦት 13 ቀን 2015 ዓ.ም በሁለት ቀበሌዎች ውስጥ ባሉ የአኝዋ እና የንዌር ጎሳዎች መካከል ሲሆን ግጭቱ የጀመረው እና እየተስፋፋ የሄደው በዋናነት ሁለቱ ጎሳዎች በሚገናኙበት ኢታንግ ልዩ ወረዳ ውስጥ ባሉ ቀበሌዎች እና በጋምቤላ ከተማ ነው፡፡ በኑዌር እና በአኝዋ ጎሳዎች መካከል በተደጋጋሚ ጊዜ የጎሳ ግጭቶች የሚነሱ የነበረ ሲሆን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የተወሰኑ መሻሻሎች ታይተው የነበረ ቢሆንም ይህ ግጭት ዳግም ተቀስቅሷል፡፡ ይህ የጎሳ ግጭት በጋምቤላ ክልል በተለይም በኢታንግ ልዩ ወረዳ እና በጋምቤላ ከተማ ብሔር ብሔረሰቦች ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በስፋት የነበረ በመሆኑ ምክንያት በእነዚህ አካባቢዎች በርካታ ቁጥር ያላቸው ሰዎች ላይ ሞት፣ የአካል ጉዳት፣ ንብረት ውድመት እና መፈናቀል የደረሰ ሲሆን በኢታንግ ልዩ ወረዳ ውስጥ በሚገኙ አራት ቀበሌዎች ውስጥ ያሉ ነዋሪዎች መፈናቀላቸውን እና በወረዳው ባሉ የተለያዩ ግጭቱ ከፍተኛ በነበረባቸው ቀበሌዎች ላይ በርካታ ቤቶች መቃጠላቸውን ኢሰመጉ ከአካባቢዎቹ ካሰባሰባቸው መረጃዎች ለመረዳት ችሏል፡፡ በኢታንግ ልዩ ወረዳ ፒኖ ቀበሌ ይህ ሪፖርት እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ በጥቃቱ ምክንያት የተገደሉ ሰዎች አስክሬኖች እንዳልተነሱ፣ በእዚህ የጎሳ ግጭት ላይ የተለያዩ መሳሪያዎችን የታጠቁ ሰዎች እየተሳተፉበት በመሆኑ የጉዳቱን መጠን ከፍተኛ እንዳደረገው፣ በአኝዋ ዞን ጎግ ወረደ ፑኝዶ ወረዳ አሁን ላይ የተሻለ የጸጥታ ሁኔታ ቢኖርም በአካባቢው በተደጋጋሚ ተመሳሳይ የጎሳ ግጨቶች ስለሚነሱ ስጋቶች መኖራቸውን እንዲሁም ይህንን ግጭት ለመቆጣጠር የክልሉ መንግስት በአጠቃላይ ክልሉ ላይ ተፈጻሚ የሚሆን ሰዓት እላፊ ማወጁንና የክልሉ ፖሊስ፣ የፌደራል ፖሊስ እና የመከላከያ ሰራዊት ግጭቱን ለመቆጣጠር ጥረት እያደረጉ መሆኑን።

#የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር "ክልሉን ከጦረነት እንታደግ" ሲሉ ጥሪ አቀረቡ!!! @በአማራ ክልል ባልተለመደ ሁኔታ በላለፉት ሦስት ቀናት በዝግ የተካሄደው የአማራ ክልል ምክር ቤት፤ በክልሉ ወቅታዊ የሰላምና ጸጥታ ጉዳዮች ላይ ከአባላቱ ጠንካራ ጥያቄዎችን ማስተናገዱ ተሰምቷል፡፡ @በምክር ቤቱ ሰብሰባ ላይ ጥያቄ ያነሱት የሕዝብ ተወካዮች፤ "የአማራን ሕዝብ አንገት ለማስደፋት ቀን ከሌሊት የሚሰሩ አካላት አሉ” ሲሉ ተደምጠዋል፡፡ @አባላቱ ክልሉ አሁን ላይ የገጠመውን አለመረጋጋት ለመፍታት መጀመሪያ የክልሉ አስተዳደር መዋቅር ራሱን መፈተሸና ማስተካከል አለበትም ነው ያሉት። @የምክር ቤቱ አባላት አክለውም፤ "ክልሉ ያሉበትን መዋቅራዊ ችግሮች ካላስተካከለና ራሱን አስተካክሎ በግልጽ ካላወጣ፣ የሕዝቡን ጥያቄ መመለስ አይቻልም" ሲሉ ሀሳብ አቅርበዋል፡፡ @በየአካባቢው የሚስተዋሉ ውጊያዎች የክልሉን ሕዝብ እያዳከሙ ነው ያሉት አባላቱ፤ የክልሉ መንግሥት መከላከያ ሠራዊት አስገብቶ ውጊያ እንዲደረግ መፍቀድ አልነበረበትም የሚል ትችትም አንስተዋል። @ከምክር ቤት በአባላቱ ጠንካራ ጥያቄዎች የቀረቡላቸው የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ይልቃል ከፋለ ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች በሰጡትም ምላሽ፤ “ክልሉን እንታደግ” ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ @“ችግራችንን በራሳችን የመፍታት አቅም እንፍጠር” ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ በየዞኑ ከምክር ቤት አባላት አምስት አምስት ሰው ተመርጦ የኃይማኖት አባቶች፣ የአገር ሽማግሌዎች፣ ምሁራንና ተጽዕኖ ፈጣሪ ሰዎች የተሳተፉበት ውይይት ያለምንም ገደብ እንዲደረግም ጥያቄ አቅርበዋል፡፡ @ርዕሰ መስተዳደሩ ያቀረቡት የውይይት ጥሪ በአስር ቀናት ውስጥ እንዲካሄድም ነው የጠየቁት። በውይይቱ የሚነሱ ጉዳዮች በወረዳ፣ በዞንና በክልል በየደረጃው መፍትሔ እንዲሰጣቸው ጥረት እንደሚያደርጉም ጠቁመዋል፡፡ @አስተዳደራቸው ለሰላም አማራጭ ቅድሚያ በመሰጠት፤ በሽዋ፣ በወሎ፣ በጎጃምና በጎንደር ውይይት እንዲደረግ ዕድል መፍጠሩን አስታውሰዋል፡፡ @ርዕሰ መስተዳደሩ “እንታደገው” ያሉትና የሚመሩት ክልል፤ በተለይ የመከላከያ ሠራዊት በተለያዩ የክልሉ አካባቢዎች ከተሰማራ ጊዜ ጀምሮ በውጊያ፣ መንገድ በመዝጋት፣ በሕዝብ ተቃውሞና በመሳሰሉት ሁነቶች ውስጥ እያለፈ ነው፡፡ @የመከላከያ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ከአማራ ክልል የሰላም እጦት ጋር በተያየዘ በቅርቡ በሰጡት አስተያየት፤ “ክልሉ ፓራላይዝድ ሆኗል” ሲሉ መደመጣቸው የሚታወስ ነው፡፡ @ፊልድ ማርሻሉ የአማራ ክልል አስተዳደር ሽባ ሆኗል የሚል ይዘት ያለው አስተያየት ከሰጡ በኋላ፤ የመከላከያ ሠራዊት በተለያዩ የክልሉ አካባቢዎች ከፋኖ ታጣቂዎች ጋር ውጊያ ውስጥ ገብቷል፡፡ @በመንግሥት እና በታጣቂ ቡድኑ መካከል ያለው ግጭት፤ ገና ከጅምሩ በውይይትና በድርድር እንዲፈታ የተለያዩ የፖለቲካ ኃይሎች ጥሪ ሲያቀርቡ ቢቆዩም፣ አሁንም በተለያዩ የክልሉ አካባቢዎች ውጊያዎች እየተካሄዱ ነው፡፡ *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1

photo content
+3

#የኢቲዮጵያ መከላከያ ሰራዊት "ራያና ወልቃይትን" ለወያኔ አሳልፎ ለመስጠት መደላድል እየሰራ ነው "አሉ፦ዶ/ር ቴዎድሮስ ኃ/ማሪያም!!! @መከላከያ ሠራዊቱ በአማራ ክልል በህገ ወጥ መንገድ ወረራ ከማካሄድ አልፎ ፣ የክልሉን አስተዳደራዊ መዋቅር በመንጠቅ ወታደራዊ አገዛዝ እንደመሠረተና ራያና ወልቃይትን ለወያኔ አሳልፎ ለመስጠት መደላድል እየሰራ እንደሆነ በግልፅ ሰምተናል ብለዎል። @ሠራዊቱ በዚህ ደረጃ የአንድ ወገን የጥፋት አጀንዳ አራማጅና ጋሻ ጃግሬ መሆኑ ለአማራ ብቻ ሳይሆን ለመላው ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን እጅግ አስነዋሪ ንቀት ነው። ማናቸውም የወታደራዊ አገዛዝ አዝማሚያ በአስቸኳይ መታረም አለበት ሲሉ ተናግረዎል። @ከእንግዲህ መከላከያው በአማራ ክልል የሚያደርገው ህገወጥ እንቅስቃሴ በአማራ ህዝብ ላይ እንደተቃጣ ጠባጫሪነት ይቆጠራል። በመሆኑም ሠራዊቱ ሁለት የሰላምና የጦርነት ምርጫ አለው ያሉ ሲሆን እነሱም። @*አንደኛ በአስቸኳይ ከህገወጥ ስምሪቱ ታቅቦ በክብር ወደ ካምፑ መሰብሰብ ፤ በመደብ ከሚያስፈልገው መጠን የቀረው ሠራዊት ክልሉን በመልቀቅ ወደ ህጋዊ ግዳጁ መሰማራት አለበት። @*ሁለተኛ ሠራዊቱ የሰላም አማራጭን አሻፈረኝ ብሎ የኦህዴድና ወያኔን ሀገር የማፍረስ ሴራ በኃይል አስፈፅማለሁ ካለ በአማራ ህዝብ ላይ ይፋዊ ጦርነት እንዳወጀ ጠላት ይቆጠራል "ብለዎል። *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

photo content

#አንጋፋው አትሌት ቀነኒሳ በቀለ ከአርሲ ዩኒቨርሲቲ የክብር ዶክትሬት ተበረከተለት!!! @አንጋፋው አትሌት ፤ በአትሌቲክስ ዘርፍ ባበረከተው ሀገራዊ አስተዋፅኦ ነው የክብር ዶክትሬት የተበረከተለት።ቀነኒሳ ሀገሩን ወክሎ በተካፈለባቸው ውድድሮች የሀገሩን #ኢትዮጵጵያን ስም ከፍ በማድረግ ታሪክ ፅፏል። @ከአትሌቲክሱ በተጨማሪ በሀገር ልማት እና በኢንቨስትመንት ስራዎች ላይ በመሳተፍ ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል በመፍጠር አስተዋጽኦ እያደረገ ይገኛል። @አትሌት ቀነኒሳ በቆጂ ሆቴል፣ በአሰላ ሆቴልና የገበያ ማዕከል፣ በአዲስ አበባ ሆቴል፣ በአዳማ የገበያ ማዕክል በማስገንባት ለአካባቢው እና ለሀገሩ አስተዋፅኦ እያደረገ ይገኛል። @በዚህም ባበረከተውና እያበረከተ ባለው ስራ ከአርሲ ዩኒቨርሲቲ የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ተበርክቶለታል። *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

photo content
+4

#ሼይኽ ሐጅ ኢብራሂም ቱፋ ከአርሲ ዩኒቨርሲቲ የክብር "ዶክትሬት ተበረከተላቸው!!! @የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ሼይኽ ሐጅ ኢብራሂም ቱፋ የክብር ዶክትሬት የተበረከተላቸው በሃይማኖት መቼላል ፣ በእርቅ፣ በሰላም፣ በአንድነት ፣ በበጎ አድራጎት ስራዎች ላይ በባበረከቱት አስተዋፅኦ መሆኑ ተገልጿል። @በኦሮሚያ ክልል መጅሊስ ሲመሰረት ከመስራቾች አንዱ የነበሩ ሲሆን ከሙስሊሞች ሃይማኖታዊ እና ፍትሃዊ ጥያቄ ጋር በተያያዘ በ " ድምፃችን ይሰማ " እንቅስቃሴ ወቅትም የኡላማዎች ሰብሳቢ በመሆን የመብት ተሟጋች ሆነው መስራታቸው ተነግሯል። @በሀገር አቀፍ ደረጃ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች አንድነት ስራዎች የልዩነት አስወጋጅ ኮሚቴ ሰብሳቢ በመሆን ተመርጠውም አገልግለዋል። @በተለያዩ ጉዳዮች ላይም ሽምግልና በመያዝ በርካታ የሰላም ፣ የእርቅ ስራዎችን መስራታቸው ተመላክቷል። @ሼይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ ፤ በሰላም ዙሪያ ከሰሯቸው ስራዎች መካከልም ፤ በአርሲ ዞን በቀድሞ አጠራር አርሲ ክፍለ ሀገር " አርባጉጉ " አውራጃ በ1984 የተከሰተውን የእርስ በእርስ ጦርነትን የአርሲ ዞን ሀገረ ስብከት ኃላፊ ከነበሩት ከአቡነ ናትናኤል ጋር በመሆን በማስቆም ትልቅ አስተዋጽኦ ማበርከታቸው ተገልጿል። @በተጨማሪም በ2003 ዓ/ም በአርሲ ዞን " ሽርካ ወረዳ " ለከፍተኛ ደም መፋሰስ ተቃርቦ የነበረን የእርስ በእርስ ከፍተኛ አለመረጋጋት የመንግስት አካላት እና የፀጥታ ኃይሎች ያልቻሉትን በሽምግልና ይዘው ወደ ሰላም እንዲቀየር ማድረጋቸው ተጠቅሷል። @በሃይማኖት መቻቻል ፣ በትምህርት ዘርፍ፣ ወላጅ የሌላቸው ህፃናት ህክምና፣ ትምህርት አገልግሎት እንዲያገኙ በማድረግ አስተዋጽኦ ማድረጋቸው ተመላክቷል። @ሼይኽ ሐጅ ኢብራሂም ቱፋ የአርሲ ዩኒቨርሲቲ በሚመሰረትበት ወቅት ትልቅ አስተዋፅኦ ማበርከታቸው ተነግሯል። @ባላቸው ስብዕና እንዲሁም በሰሩት ተምሳሌት የሆነ ስራ የክብር ዶክትሬት ዲግሪ እንደተበረከተላቸው ከአርሲ ዩኒቨርሲቲ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። @እሳቸው ውጭ ሀገር ስለሆኑ ተወካያቸው የክብር ዶክትሬቱን ተቀብለዋል። *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

photo content
+3

#ቀዳማዊት እመቤት "ዝናሽ ታያቸው የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ተበረከተላቸው!!! @የአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እያካሄደ ባለው የምረቃ ስነስርዓት ላይ ለቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው የክብ
+3
#ቀዳማዊት እመቤት "ዝናሽ ታያቸው የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ተበረከተላቸው!!! @የአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እያካሄደ ባለው የምረቃ ስነስርዓት ላይ ለቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው የክብር ዶክትሬት አበርክቷል። @ቀዳማዊት እመቤት ለሀገር ባበረከቱት አስተዋፅኦ ነው የክብር ዶክትሬቱ የተበረከተላቸው። *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

#በጠለምትና አካባቢው በትግርኛ ቋንቋ የሚጠሩ ወረዳዎችና ቀበሌዎች ስያሜ ወደ አማርኛ ሊቀየር መሆኑ ተነገረ!!! @በአማራ እና ትግራይ ክልል አዋሳኝ አካባቢዎች የሚገኙና "በትግርኛ ቋንቋ የሚጠሩ ወረዳዎች እና ቀበሌዎች ስያሜ ወደ "አማርኛ ቋንቋ ሊቀየር መሆኑን የጠለምት አማራ ማንነትና ወሰን አስመላሽ ኮሚቴ አስታውቋል። @ኮሚቴው በጠለምትና አካባቢው የሚገኙና በትግርኛ ቋንቋ ስያሜ ያላቸው ኹሉም ወረዳዎች፤ ቀበሌዎችና ጎጦችን የአማርኛ ስያሜ ሊሰጣቸው መሆኑን አመላክቷል። @በወቅቱ ክልሎች ሲመሰረቱ አካባቢው ወደ ትግራይ ክልል እንዲካለል በመደረጉ በአማርኛ ቋንቋ ይታወቅ የነበረው ስያሜያቸው ወደ ትግርኛ ቋንቋ እንዲቀየር ተደርጎ ቆይቷል ነው የተባለው። @ይህን ተከትሎም በአሁኑ ወቅት በጠለምትና አካባቢው የሚገኙ ወረዳዎችን፣ ቀበሌዎችንና ጎጦችን ስያሜ ለመቀየር እንቀስቃሴ መጀመሩን መረዳት ተችሏል። @ለአብነትም አራተኛ መደበኛ ጉባኤውን ሐምሌ 01/2015 ያካሄደው የአዲርቃይ ወረዳ ምክር ቤት፤ “ሰላም በር” እና “ሰገነት” የተሰኙ ኹለት አማራጭ ስያሜዎችን ተቀብሎ በሕዝብ ምርጫ እንዲጸድቅ ወስኗል ነው የተባለው። @በተጨማሪም በወረዳው ሥር የሚገኙ ቀበሌዎች ስያሜ ለውጥ እንዲደረግ የተለያዩ ስያሜዎች ለምክር ቤቱ ቀርበው እንዲጸድቁም መወሰኑ ተጠቅሷል። @በማይጠብሪ ወረዳም ተመሳሳይ እንቅስቃሴ መኖሩ የተገለጸ ሲሆን፤ በጠለምት አካባቢ የሚገኙት እንደ ማይትክሊት፣ አዲወሰኔ፣ ጻዳቀርኒ የተባሉ ቀበሌዎች እንዲሁም አዶፋሪ፣ አዲናቴ፣ አዲሐሮሶን፣ ማይ ዳጉሳ፣ ማይ ቃጫ፣ ማይ ሎሚን የተባሉ ጎጦች የአማርኛ ቋንቋ ስያሜ ሊሰጣቸው መሆኑ ተጠቁሟል። @የሥም ለውጥ የሚደረግባቸው ኹሉም ቦታዎች ሥም ዕቅድ ተዘጋጅቶ በጠለምት ሥር ለሚገኙ ወረዳዎች ምክር ቤት መሰራጨቱ እንዲሁም፤ ጉዳዩ በክልልና በዞን ደረጃም ተቀባይነት ማግኘቱ ነው የተገለጸው። @የቦታዎች ስያሜ ሲቀየር፤ የየመስሪያ ቤት ማህተሞችን ጨምሮ በተለያዩ ተቋማት ላይ የስያሜ ለውጥ መደረጉም አይቀሬ ነው ተብሏል። @በእነዚህ አካባቢዎች ኹለቱም ክልሎች የይገባኛል ጥያቄ የሚያነሱ ሲሆን፣ ቦታዎቹ በአማራ እና በትግራይ ክልል ሕዝብ ዘንድ በተለያዬ ስያሜ ሲጠሩ ይስተዋላል። አዲስ ማለዳ *👉ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

photo content

#1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ሰዎችን ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ለመስጠት መመዝገቡን የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም አስታውቀ!!! @በዚህ አመት መገባደጃ ላይ ደግሞ 3 ሚሊዮን ሰዎችን ለመመዘገብ ዕቅድ አውጥቶ በመንቀሳቀስ ላይ እንደሚገኝ በብሄራዊ መታወቂያ ፕሮግራም የኮሙኒኬሽን ዩኒት ዳይሬክተር አቶ አቤኔዘር ፈለቀ በተለይ ለኢቢሲ ሳይበር ገልፀዋል። @የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ምዝግባ በተለያዩ የምዝገባ ጣቢያዎች፤ በአንድነት ፓርክ እንዲሁም በባንኮች በተመረጡ ቅርንጫፎች ላይ እየተከናወነ ነው፡፡ @በ id.et ዌብ ሳይት እንዲሁም በማህበራዊ ሚዲያ ቻናሎች በየዕለቱ የግንዝቤ ማስጨበጫ ስራዎች በስፋት እየተሰራ እንደሚገኝም አቶ አቤኔዘር ተናግረዋል ። @የብሔራዊ የዲጂታል መታወቂያ ፕሮግራም ስትራቴጂ ዋና አላማ ዜጎች የዲጂታል መታወቂያ ተጠቅመው የተለያዩ የማህበራዊ አገልግሎቶችን እንዲያገኝ ማስቻል እንደሆነም ነው ዳይሬክተሩ የገለፁት ። @ከባንኮች ጋር የዲጂታል መታወቂያን ማቀናጀት ተጀምሯል፤ እስካሁንም በ8 በተመረጡ የባንኮች ቅርንጫፎች ላይ የማቀናጀት ስራን እየተሰራ መሆኑንንም ገልፀዋል፡፡ @ወደ ፊት ዲጂታል መታወቂያን ከፋይናንስ ሴክተር ጋር በማቀናጀት አንድ ሰው መታወቂያውን ተጠቅሞ ፋይናንስ አገልግሎቶችን በቀላሉ ማግኘት እንዲችል እየሰራን ነው ብለዋል። *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook grESAT TV955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

photo content

#በዛሬው ዕለት የተለያዩ የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎቻቸውን እያስመረቁ ይገኛሉ። - ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ - ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ - ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ - አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨ
+4
#በዛሬው ዕለት የተለያዩ የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎቻቸውን እያስመረቁ ይገኛሉ። - ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ - ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ - ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ - አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ - ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ - መቅደላ አምባ ዩኒቨርሲቲ - አሶሳ ዩኒቨርሲቲ - የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ - አርሲ ዩኒቨርሲቲ በየተለያዩ የትምህርት መስኮችና መርሀ ግብሮች ያስተማሯቸውን ተማሪዎች እያስመረቁ ነው። *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

#ዛሬ የምናገረውን ነገ ሊገድሉኝ ይችላሉ። የጊዜ ጉዳይ ነው እንጅ ሁላችሁም አይቀርላችሁም።" - አቶ ዮሐንስ ቧያለው!!! @አለመታደል ሆኖ የአማራን ችግር እንዳንመክር፣ በአማራ ምክር ቤት አፈጉባኤ
#ዛሬ የምናገረውን ነገ ሊገድሉኝ ይችላሉ። የጊዜ ጉዳይ ነው እንጅ ሁላችሁም አይቀርላችሁም።" - አቶ ዮሐንስ ቧያለው!!! @አለመታደል ሆኖ የአማራን ችግር እንዳንመክር፣ በአማራ ምክር ቤት አፈጉባኤ ተከልክለናል። ወይ አፈጉባኤዋ ጭራሽኑ ከአድዋ፣ ወይ ከበሻሻ በሆነች። @ከእኛ ባልሆነች የጊዜ ጉዳይ ካልሆነ ሁላችንንም ይገድሉናል ለስልጣናችን፣ ለህልውናችን የተዋደቀውን ልዩ ሀይል አፈረሳችሁት። @ኢትዮጵያን እናፈርሳታለን፣ አማራን እናዋርዳለን ያሉት ጀነራሎች በነፃነት በሚንፈላሰሱባት ሀገር፣ እያነከሰ ያዋጋው ጀነራል ህክምና ተከለከለ ለአማራ የቆሙ አመራሮች ተገደሉ፣ ተባረሩ። ምን ቀረን? @ጠላቶቻችን በአንድነት ዘምተውብናል። ክልሉን ልክ እናስገባዋለን በማለት ተነስተዋል መከላከያ ያለ ክልሉ ፍቃድ፣ አማራን እያተራመሰ ነው። እኛስ? @አሁኑኑ መፍትሔ እናስቀምጥ በዚህ ምክር ቤት በአማራ ክልል የተፈጠረውን ችግር እና መፍትሔ የሚያጠና ቡድን ይዋቀር። *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

#የሩሲያው ፕሬዝዳንት ፑቲን በቀለኛ ሰው መሆናቸውን "አሜሪካ ገለጸች!!! @የአሜሪካ የስለላ ተቋም ሲአይኤ ሀላፊ ዊሊያም በርንስ በጉዳዩ ዙሪያ እንዳሉት "ፕሬዝዳንት ፑቲን በቀለኛ ሰው ናቸው" ሲሉ
#የሩሲያው ፕሬዝዳንት ፑቲን በቀለኛ ሰው መሆናቸውን "አሜሪካ ገለጸች!!! @የአሜሪካ የስለላ ተቋም ሲአይኤ ሀላፊ ዊሊያም በርንስ በጉዳዩ ዙሪያ እንዳሉት "ፕሬዝዳንት ፑቲን በቀለኛ ሰው ናቸው" ሲሉ መናገራቸውን ቢቢሲ ዘግቧል። @በርንስ አክለውም ፕሬዝዳንት ፑቲን ትክክለኛውን ጊዜ እየጠበቁ እንጂ የዋግነሩ አዛዥ ፕሪጎዥን ለፈጸመው ስህተት መቀጣቱ አይቀሬ እንደሆነም ተናግረዋል። @የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ከሰሞኑ "የዋግነሩ አለቃ ተመርዘው ሊገደሉ ይችላሉ" ሲሉ መናገራቸው ይታወሳል። *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

#በአሜሪካ የሚገኘው ኢስላሚክ ዩንቨርስቲ ለኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሸይህ ሐጅ "ኢብራሂም ቱፋ የክብረ ዶክትሬት አበረከተ!!! @በአሜሪካን ሀገር ሚኖሳታ የሚገኘው "
+3
#በአሜሪካ የሚገኘው ኢስላሚክ ዩንቨርስቲ ለኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሸይህ ሐጅ "ኢብራሂም ቱፋ የክብረ ዶክትሬት አበረከተ!!! @በአሜሪካን ሀገር ሚኖሳታ የሚገኘው " ኢስላሚክ ዩንቨርስቲ " ለኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዜዳንት ሸይህ "ሐጅ ኢብራሂም ቱፋ እና ለአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሸይህ ሱልጧን ሐጅ አማን የክብር ዶክትሬት አበረክቶላቸዋል። @የክብር ዶክትሬት ዲግሪውን ያጎናጸፉት የኢስላሚክ ዩንቨርስቲ ፕሬዝዳንት የሆኑት ፕሮፌሰር ወሊድ እድሪስ መሆናቸውን ከኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የደረሰን መረጃ ያሳያል። @በሌላ በኩል ፤ የአርሲ ዩኒቨርሲቲ ሴኔት በወሰነው ውሳኔ ዛሬ ለሁለት ኢትዮጵያውያን የክብር ዶክትሬት ያበረክታል። @የክብር ዶክትሬት የሚበረከትላቸው የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ሸይህ ሐጅ ኢብራሂም ቱፋ እንዲሁም አንጋፋው አትሌት ቀነኒሳ በቀለ መሆኑን ከተቋሙ የተገኘው መረጃ ያሳያል። *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

#ፍትህ "ያለ ይላሉ ቤተሰቦች!!! @ትላንት ከ አዲስ አበባ ቡታጅራ በዶልፊን ህዝብ ጭኖ ሲመጣ ተሬ በሚባል ከተማ ጥሰኸናል ብለው በሌላ ፓትሮል ተከታትለው የፀጥታ አካላት ደርሰው በጥይት ገደሉት። @
#ፍትህ "ያለ ይላሉ ቤተሰቦች!!! @ትላንት ከ አዲስ አበባ ቡታጅራ በዶልፊን ህዝብ ጭኖ ሲመጣ ተሬ በሚባል ከተማ ጥሰኸናል ብለው በሌላ ፓትሮል ተከታትለው የፀጥታ አካላት ደርሰው በጥይት ገደሉት። @ሳሚ መረተ ምስኪን ቢያጆ በያዘው መኪና ከ ሁለት ልጆቹ ለዩት የጥሰት ክስ በጥይት ቀየሩት አንድ አሽከርካሪ ከጣሰም በመጣሱ የሚቀጣ ባለበት ሂደት ህይወት ማጥፋት ማናለብኝነት እና ትልቅ ወንጀል ነው። *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb

#ትግራይ ክልልም እንደ ማንኛውም ክልል መደበኛ ፖሊስ እና ሚሊሻ ብቻ ነው የሚኖረው "አሉ ፦ጄነራል አበባው ታደሰ!!! @የጦር ኃይሎች ምክትል ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጄኔራል አበባው ታደሰ መከታ ከተባ
#ትግራይ ክልልም እንደ ማንኛውም ክልል መደበኛ ፖሊስ እና ሚሊሻ ብቻ ነው የሚኖረው "አሉ ፦ጄነራል አበባው ታደሰ!!! @የጦር ኃይሎች ምክትል ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጄኔራል አበባው ታደሰ መከታ ከተባለ የመከላከያ ሰራዊት መጽሄት ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ከልዩ ኃይሎችና ሌሎች ኢ መደበኛ ኃይሎች መልሶ ማደራጀት ዙሪጣ አስተያየት ሰጥተዋል። @በዚህም የትግራይ ኃይልን በተመለከተ ከትግራይ ጋር ተያይዞ ያለውም እንደ ማንኛውም ክልል እሱም የሚኖረው መደበኛ ፖሊስ እና ሚሊሻ ብቻ ፤ በተቀመጠለት ስታንዳርድ ብቻ ነው የሚሄደው ሲሉም ምክትል እታማዦር ሹሙ ተግናረዋል። @ጄኔራል አበባው ታደሰ ከልዩ ኃይል ጋር በተያያዘም አሁን ላይ “ምንም በልዩ ሃይል የሚታዘዝ አደረጃጀትና የኮማንድ ስርዓት ያለው አሁን የለም፤ እንደ ሃይል ወይ መከላከያ ሆኗል ወደ መደበኛ ፖሊስ ሆኗል ወይም ደግሞ ፌዴራል ፖሊስ ሆኗል ብለዋል። *ፈጣን ወቅታዊ መረጃወች ለማግኘት👇👇 *👉ቴሌግራም፦https://t.me/Esattvnews *👉facebook group፦https://facebook.com/groups/156058869715955/ *👉youtube፦https://www.youtube.com/@EsatTv-number1 *👉facebook፦https://www.facebook.com/profile.php?id=100066809890548 *👉Esat tv ቴሌግራም group፦https://t.me/fetagroupb